የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚስዮን እና ቲኦሎጂ መምሪያ ከፒ-ኤል-አይ ኢንተርናሽናል(PLI International) ጋር በትብብር የሚሰጠው የመጋቢነት አመራር ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚስዩን እና ቲኦሎጂ መምሪያ ከፒ-ኤል-አይ ኢንተርናሽናል(PLI International) ጋር በትብብር የሚሰጠው የመጋቢነት አመራር ሥልጠና የደቡብ ክላስተር፤ ዛሬ በደቡብ ሲኖዶስ አዘጋጅነት በዲላ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።
ሥልጠናውም ላለፉት ሶስት ዓመታት የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በተለያዩ አርዕስት ሲያሰለጥን የቆየ ሲሆን የማጠቃለያ ዓመት በሆነው የአራተኛው ዓመት ስልጠና "ደቀመዛሙርትን፣ ደቀመዛሙርት አድራጊዎችን እና መሪዎችን ማባዛት" በሚል ዋና ዐርስት ላይ መሠረት በማድረግ በመላው ኢትዮጵያ በተለያዩ ክላስተሮች ሥልጠናው በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በዚህም የክላስተር ሥልጠና በደቡብ ኢትዮጵያ ከሚገኙ 14 ሲኖዶሶች የመጡ በሲኖዶስ፣ በሰበካ እና በማህበረ ምዕመናን የሚያገለግሉ መሪዎች እና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በመካፈል ላይ ይገኛሉ።
የቤተ ክርስቲያኒቱም የሚስዩንና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል፣ የአዲስ አበባ ሲኖዶስ ኘሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ጽጌ በረሃ እና የቤተክርስቲያኒቱ የካምፓስ አገልግሎትና ከተማ ወንጌል ማዳረስ የሥራ ክፍል አስተባባሪ የሆኑት ቄስ ወርቁ ኤባ ሥልጠናውን በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አገኘነው
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚስዩን እና ቲኦሎጂ መምሪያ ከፒ-ኤል-አይ ኢንተርናሽናል(PLI International) ጋር በትብብር የሚሰጠው የመጋቢነት አመራር ሥልጠና የደቡብ ክላስተር፤ ዛሬ በደቡብ ሲኖዶስ አዘጋጅነት በዲላ ከተማ መሰጠት ተጀምሯል።
ሥልጠናውም ላለፉት ሶስት ዓመታት የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በተለያዩ አርዕስት ሲያሰለጥን የቆየ ሲሆን የማጠቃለያ ዓመት በሆነው የአራተኛው ዓመት ስልጠና "ደቀመዛሙርትን፣ ደቀመዛሙርት አድራጊዎችን እና መሪዎችን ማባዛት" በሚል ዋና ዐርስት ላይ መሠረት በማድረግ በመላው ኢትዮጵያ በተለያዩ ክላስተሮች ሥልጠናው በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በዚህም የክላስተር ሥልጠና በደቡብ ኢትዮጵያ ከሚገኙ 14 ሲኖዶሶች የመጡ በሲኖዶስ፣ በሰበካ እና በማህበረ ምዕመናን የሚያገለግሉ መሪዎች እና አገልጋዮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር በመካፈል ላይ ይገኛሉ።
የቤተ ክርስቲያኒቱም የሚስዩንና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል፣ የአዲስ አበባ ሲኖዶስ ኘሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ጽጌ በረሃ እና የቤተክርስቲያኒቱ የካምፓስ አገልግሎትና ከተማ ወንጌል ማዳረስ የሥራ ክፍል አስተባባሪ የሆኑት ቄስ ወርቁ ኤባ ሥልጠናውን በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አገኘነው
ቤተልሔም ደረጄ ፡ ኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን