ከግርግሙ ማን ይቀራል?
የምድር ነገሥታት ሰማያዊውን ንጉሥ ለማምለክ ሊመጡ ይገባል። ወታደሮችም ሠራዊትን ሁሉ በአፉ እስትንፋስ ያጸናውን ጌታ ለማገልገል ሊቀርቡ ያስፈልጋል። ሴቶችም ኀዘናቸውን ወደ ደስታ ይለውጥ ዘንድ ከሴት የተወለደውን ያዩ ዘንድ ሊመጡ ይገባል። ሕፃናትም ከሚጠቡ እና ከሕፃናት አፍ ምስጋናን ያዘጋጅ ዘንድ ሕፃን የሆነውን ይመለከቱ ዘንድ ሊመጡ ያስፈልጋል። እረኞችም ነፍሱን ስለ በጎቹ የሚያኖር መልካሙን እረኛ ለማየት ይመጡ ዘንድ ይገባል። ባሮችም የባርነት ቀንበራቸውን ሰብሮ በነጻነት ያከብራቸው ዘንድ የባሪያውን መልክ የነሣውን ሕፃን ያዩ ዘንድ መምጣት ይገባቸዋል። ዓሣ አጥማጆቹም የቃሉን መረብ አስይዞ ሰው አጥማጅ የሚያደርጋቸውን ወንድ ልጅ ለማየት ይቀርቡ ዘንድ ይገባቸዋል። ቀረጥ ሰብሳቢዎችም ከቀራጮች መካከል ወንጌላዊ አድርጎ የሚመርጠውን ጌታ ለማየት ሊመጡ ይገባቸዋል። ዘማውያን ቅዱሳት እግሮቹን በዘማውያን እንባ እንዲታጠብ የሚሰጠውን የፍቅር አምላክ ለማየት ይቀርቡ ዘንድ ይገባል። ኃጥአን ሁሉ የዓለምን ኃጢአት የሚሸከመውን የእግዚአብሔር በግ ለማየት ሊመጡ ይገባል።
#ዛሬ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት በአእላፋት ዝማሬ እንገናኝ!
https://tttttt.me/Dnabel
የምድር ነገሥታት ሰማያዊውን ንጉሥ ለማምለክ ሊመጡ ይገባል። ወታደሮችም ሠራዊትን ሁሉ በአፉ እስትንፋስ ያጸናውን ጌታ ለማገልገል ሊቀርቡ ያስፈልጋል። ሴቶችም ኀዘናቸውን ወደ ደስታ ይለውጥ ዘንድ ከሴት የተወለደውን ያዩ ዘንድ ሊመጡ ይገባል። ሕፃናትም ከሚጠቡ እና ከሕፃናት አፍ ምስጋናን ያዘጋጅ ዘንድ ሕፃን የሆነውን ይመለከቱ ዘንድ ሊመጡ ያስፈልጋል። እረኞችም ነፍሱን ስለ በጎቹ የሚያኖር መልካሙን እረኛ ለማየት ይመጡ ዘንድ ይገባል። ባሮችም የባርነት ቀንበራቸውን ሰብሮ በነጻነት ያከብራቸው ዘንድ የባሪያውን መልክ የነሣውን ሕፃን ያዩ ዘንድ መምጣት ይገባቸዋል። ዓሣ አጥማጆቹም የቃሉን መረብ አስይዞ ሰው አጥማጅ የሚያደርጋቸውን ወንድ ልጅ ለማየት ይቀርቡ ዘንድ ይገባቸዋል። ቀረጥ ሰብሳቢዎችም ከቀራጮች መካከል ወንጌላዊ አድርጎ የሚመርጠውን ጌታ ለማየት ሊመጡ ይገባቸዋል። ዘማውያን ቅዱሳት እግሮቹን በዘማውያን እንባ እንዲታጠብ የሚሰጠውን የፍቅር አምላክ ለማየት ይቀርቡ ዘንድ ይገባል። ኃጥአን ሁሉ የዓለምን ኃጢአት የሚሸከመውን የእግዚአብሔር በግ ለማየት ሊመጡ ይገባል።
#ዛሬ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት በአእላፋት ዝማሬ እንገናኝ!
https://tttttt.me/Dnabel
❤140👍18👏2