Dn Abel Kassahun Mekuria
15.3K subscribers
538 photos
49 videos
1 file
846 links
ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው።

ይወዳጁን

ለፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL

ለyoutube
https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_

ለInstagram
https://www.instagram.com/abelkassahunm?igsh=OW
Download Telegram
"በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል። እግዚአብሔርን፡— አንተ መታመኛዬ ነህ፡ እለዋለሁ፤ አምላኬና መሸሸጊያዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ። እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ያድንሃልና። በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም በታች ትተማመናለህ፤ እውነት እንደ ጋሻ ይከብብሃል። ከሌሊት ግርማ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ፥ በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን አትፈራም። በአጠገብህ ሺህ በቀኝህም አሥር ሺህ ይወድቃሉ፤ ወደ አንተ ግን አይቀርብም። በዓይኖችህ ብቻ ትመለከታለህ፥ የኃጥኣንንም ብድራት ታያለህ። አቤቱ፥ አንተ ተስፋዬ ነህና፤ ልዑልን መጠጊያህ አደረግህ። ክፉ ነገር ወደ አንተ አይቀርብም፥ መቅሠፍትም ወደ ቤትህ አይገባም።
በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ። ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውማለሁ። ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ።"

                መዝሙር 91

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
12👍6
የቀደሙት ሰዎች በሰናዖር ከምድር እስከ ሰማይ፣ እስከ አምላክ ማደሪያ የሚደርስ ግንብ ሊሠሩና ስማቸውን ሊያስጠሩ ተነሡ። ነገር ግን በትዕቢታቸው ጠፉ። እነዚህ የባቢሎን ሰዎች ምንኛ ችኩሎች ሆኑ?! ጥቂት ዘመን ቢታገሱ ኖሮ ራሱ አምላክ ከእነርሱ እንደ አንዱ ሰው ሆኖ በግርግም ተኝቶ ያገኙት አልነበር?!

እነዚህ የሰናዖር ሰዎች ትንሽ ቢታገሱ ኖሮ ከምድር ወደ ሰማይ መሻገሪያ የምትሆን በእግዚአብሔር እጅ የታነጸች ታላቋን የብርሃን ድልድይ ድንግል ማርያምን ያገኙዋት ነበር። በዚህችም የብርሃን ድልድይ (መሰላል) እነርሱ ብቻ ሳይሆኑ የሰው ልጆች ሁሉ ስም እንደ ተጠራ አይተው ደስ ይሰኙ ነበር።

====

አቤቱ ጾም፣ ጸሎት፣ መንፈሳዊ ትሩፋቶቻችን የአንተ ረድኤት የሌለባቸው በትዕቢት ያቆምናቸው የሰናዖር ግንቦች አይሁኑብን። እንዲህም ከሆኑ፣ በሥራዬ እያለ ልባችን እንዳይኮራ፣ ዓይናችንም ወደታች እያየ ወዳጆቹን እንዳይንቅ ወደ አንተ የማያደርሱንን እነዚህን የሐሰት ግንቦች አፍርስልን። በእነርሱም ፈንታ በትሕትና እና በፍቅር ያጌጡ ውብ ግንቦችን እናንጽ ዘንድ ረድኤትህን ላክልን።

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://tttttt.me/Dnabel
https://youtube.com/channel/UCRvatZyeFOJtXnAjZSOdrZg
5👍1
ሰው አያከብርህም?

ሰው ሲሰድብህ ትናደዳለህ? የሚያዋርድ እና አንገት የሚያስደፋ ነገር ቢያደርግብህስ በቁጣ ትገነፍላለህ? ግን አንድ ጊዜ ቆም ብለህ እስኪ ራስህን ጠይቅ? ከአንተ በላይ አንተን የሰደበ፣ ከአንተ በላይ አንተን ያዋረደ እና አንገት የሚያስደፋ ነገር ያደረገብህ አለ? ከአንተ በላይ አንተነትህን ዋጋ ቢስ ያደረገ ማን ነው? አንተ አይደለህ?

አንተው መልስ!

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚለው ለሰው ጠላቱ ማንም አይደለም፤ ራሱ ነው። የሕይወትን ዛፍ ቸል ብሎ ወደ እጸ በለስ የሚሮጠው፣ የብርሃኑን ልብሱን ጥሎ ቅጠል ማገልደም የሚያምረው፣ ከወንድሙ ጋር በሰላም ከመኖር ይልቅ ደሙን አፍስሶ ዚቅበዘበዝ መኖር የሚመርጠው ሰው ራሱ ነው።

ሌላውን ከመውቀስህ በፊት መጀመሪያ አንተ ራስህን ታከብራለህ? በአንተ ዘንድ የአንተነትህ ዋጋው ስንት ነው? ከልብስ ይልቅ ሰውነትህን ከመብልስ በፊት ነፍስህን ታስቀድማለህ? አንተ ራስህን በክፋት እና በበደል እንዲህ እያጎሳቆልክ “ማንም አያከብረኝም” እንዴት ትላለህ?

ዲያቆን አቤል ካሣሁን
abelzebahiran@gmail.com
👍135
ሰሞኑን በሎሳንጀለስ ከተነሣው ሰደድ እሳት ጋር ተያይዞ በየማኅበራዊ ድረ ገጹ ሲዘዋወር የቆየ አንድ ፎቶ ነበር። ለነገሩ ቤቱ ነው እንጂ አንድ ፎቶዎቹ ግን ሦስት ዓይነት ነበሩ። ከፎቶዎቹም ጋር ተያይዞ “ይህ ቤት በሎሳንጀለስ የሚኖር የክርስቲያን ቤት ሲሆን የእሳት ወላፈን ሳይነካው በእግዚአብሔር ጥበቃ የተረፈ ነው”የሚሉ ያልተረጋገጡ ዘገባዎች በስፋት ሲዘገቡ ሰንብተዋል።

ነገር ግን ከሦስቱ የቤት ፎቶዎች ሁለቱ በ2023 ዓ.ም. አውስትራሊያ ላይ ተፈጥሮ ከነበረው ሰደድ እሳት የተረፈ የአንድ ቤት ምስል ሲሆኑ፣ ሦስተኛው (የተቃጠሉ ቤቶች መካከል ያለው) ደግሞ በAI ቴክኖሎጂ አማካኝነት የተፈበረከ ፎቶ ነው።

እግዚአብሔር ከሚነድ እሳት ሊያድን እንደሚችል መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ባያድንም ግን እግዚአብሔርነቱ ጥርጥር ውስጥ የሚገባ አይደለም። የውሸት ፎቶ እየፈበረኩ እንዲህ ዓይነት ዜና መንዛት ግን ሃይማኖት እና ሃይማኖተኝነትን ያዋርድ እንደ ሆነ እንጂ አያስከብርም።

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

https://www.snopes.com/news/2025/01/14/la-fires-home-god-saved/
👍81
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መቼ ላግባ?

እንኳን ለቃና ዘገሊላ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
👍9
🌸🐝 የንብ ዓይን ይኑርህ🌸🐝

አንዳንድ ሰዎች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ብዙ የተሳሳቱ ነገሮች እንደሚያዩ እና ያም እንደሚያሳዝናቸው ይነግሩኛል። እኔም ለእነዚህ ሰዎች ይህን እላቸዋለሁ:-

ዝምብን አግኝታችሁ “እዚህ አካባቢ አበባ አይተሻል?” ብትሏት፡- “ስለ አበቦቹ እንኳን የማውቀው ነገር የለም። ባይሆን እዚያ ጋር የምታየው ክምር ላይ የፈለግኸውን ቁሻሻ ልታገኝ ትችላለህ” ብላ ልትመልስልህ እና ንጹሕ ያልሆኑ ብዙ የቆሻሻ ዓይነቶችን ልትዘረዝርልህ ትችላለች።

ንብን አግኝተህ ደግሞ “እዚህ አካባቢ የተጣሉ ቆሻሾች አይተሽ ይሆን?” ብለህ ብትጠይቃት፣ “ቆሻሻ ነገሮች? ኸረ እኔ ምንም አላየሁም። ይህ ቦታ እኮ ልዩ ልዩ መዓዛ ባላቸው አበቦች የተሞላ ነው” ስትል ልትመልስልህ እና በአትክልቱ ስፍራ ያሉትን አበቦች አንድ በአንድ ልታስቆጥርህ ትችላለች።

አየህ! ዝምብ የቆሸሹ ነገሮች የት ሊገኙ እንደሚችሉ ብቻ ስታውቅ፣ ንብ ግን ውብ የሆኑ አበቦች መኖሪያ ወዴት እንደሆነ ታውቃለች።

አሁን ላይ እንደ ተረዳሁት ከሆነ አንዳንድ ሰዎች ንብን ሲመስሉ ሌሎች ደግሞ ዝንብን ይመስላሉ። ዝንብን የሚመስሉት በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ክፉን ነገር ብቻ እያሻተቱ የሚፈልጉ እና ሐሳባቸውም በዚያ የሚዋጥባቸው ናቸው። እነዚህ ሰዎች የትም ቦታ ቢሆን ጥሩ ነገር አይታያቸውም።

ንቧን የሚመስሉት ግን በሚያዩዋቸው ነገሮች ሁሉ ውስጥ ጥሩን ነገር ያስተውላሉ።

ትርጉም፡ ዲያቆን አቤል ካሣሁን
ምንጭ፡ St. Paisios of Mt. Athos, "Good and Evil Thoughts”
19👍10
እንደ እመቤታችን ይህ ዓለም ያልተገባው ማን ነው? የእርሷ ስደት የሚጀምረው ገና በእናቷ ማኅጸን ሳለች ነው። ከተወለደችም በኋላ ሰይጣን ዕረፍት አልሰጣትም። ክፉ መንፈስ ባደረባቸው አይሁድ ምክንያት ብዙ መከራ ተቀብላለች። ከወለደችው የበኩር ልጇ የተነሣ እንደ ሰይፍ የሚወጉ ብዙ የልብ ኃዘኖች ደርሰውባታል። ልጇ የተሰደባቸው ስድቦች በላይዋ ወድቀዋል። በጅራፍ መገረፉ፣ በዘንግ መመታቱ፣ በጦር መወጋቱ የእናትነት አንጀቷን እንደ እሳት አቃጥለዉታል። የማዳን ሥራውን ፈጽሞ ከዐረገ በኋላም የትንሣኤው ጠላት የነበሩት አይሁድ የትንሣኤን እናት ድንግልን አሳድደዋታል። ይህች ዓለም ለአንዲት ደቂቃ እንኳን ለእመቤታችን ተገብታት አታውቅም ነበር።

ስለዚህ ከምድራዊቷ ወደ ሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም ሊያሸጋግራት፣ ከክፉው ወደ መልካሙ ዓለም ሊጠራት ልጇ በታላቅ ልዕልና ወደ እርሷ ወረደ። ጌታ ወደ ማኅጸኗ እቅፍ በገባ ጊዜ "ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች። መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች። የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና" ስትል እንዳመሰገነችው፣ ዳግመኛም እናቲቱ ወደ ልጇ እቅፍ በገባች ጊዜ በዚህ ቃል መልሳ አመስግናዋለች።

እንኳን ለእመቤታችን በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሰን!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://tttttt.me/Dnabel
👍2111
“በአንተ ታምናለችና በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ። ጌታ እግዚአብሔር የዘላለም አምባ ነውና ለዘላለም በእግዚአብሔር ታመኑ”

ኢሳ 26:3-4
51👍10🙏3
ዝምታ ራሳችንን የምናይበት ጥሩ መጽሔት(መስታወት) ነው። አብዛኛውን ሰዓት በወሬ ተጠምዶ የሚውል ሰው ራሱን የሚመለከትበት እድል አይኖረውም። በሌሎች ኃጢአት ሲፈርድ፣ ሲተችና ሲያማ ስለሚውል የራሱን ስህተትና ውድቀት ለማወቅ ይቸገራል። ቀኑን ሙሉ እንዲሁ ሲያወራ የሚውል ሰው የሚያሳዝነው ዝም አለማለቱ ብቻ ሳይሆን የሚጠቅም ነገር የማይናገር መሆኑም ጭምር ነው። ነገር ግን ማር ይስሐቅ እንደሚለው "አንድ ሰው ከሰዎች ጋር ብዙ ማውራት ባቆመ ጊዜ ወደ ራሱ ይመለሳል። በእግዚአብሔርም ፊት ምግባሩን ማቅናት ይጀምራል"

የሥጋ አንደበታችንን መቆጣጠርና ዝም ማስባል ስንችል የነፍስ ጆሮአችን ንቁህ መሆን ይጀምራል። ስለዚህም ነፍሳችን ሳይሰለች ከልባችን ደጅ ቆሞ የሚያንኳኳውን የመልካሙን እረኛ ድምጽ ትሰማለች። ደጇንም ከፍታ ታስገባዋለች። ከእርሱም ጋር ለእራት ትሰየማለች።(ራእይ 3፥20) በእውነት ይህ እንደ ምን ያለ መታደል ነው? ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር "የዝምተኛ ሰው ጆሮ የእግዚአብሔርን ድንቆች ትሰማለች" ያለው ለዚህ ይሆን?!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
262👍36❤‍🔥16🔥4👏2🥰1
ብዙ ሰው "ያሰብኹት ሁሉ ምንም ሊሳካልኝ አልቻለም" እያለ ያጉረመርማል፤ "እግዚአብሔርማ እኔን ሳይተወኝ አልቀረም!" እያለ ፈጣሪውን ያማርራል። "ይሰጠኛል" ሳይሆን "አገኘዋለሁ" ብሎ ይጀምርና ሳይሆን ሲቀር በእጁ የነበረውን የነጠቀው ያህል አምላኩ ላይ ያለቅሳል። ስታቅድ ያላስታወስከውን አምላክ ያቀድከው ሲፈርስ ስሙን እየጠራህ ስለምን ትወቅሰዋለህ? በሕይወትህ መቼ ቦታ ሰጠኸው? እንደ ፈቃዴ ካልሆነ አልህ እንጂ መቼ "እንደ ፈቃድህ ይሁን" ብለህ ጸለይህ? ባላማከርከው ለምን ተከሳሽ ታደርገዋለህ?

ልሥራ ብለህ በተነሣህበትም ቀን እንዲሁ በግዴለሽነት ስሙን ጠርተህ እንደ ሆነም ራስህን መርምር? በትክክል ጸልየህና በመንገድህ ሁሉ ይመራህ ዘንድ ፈቅደህ ከጀመርህ ግን ግድ የለም እረኛህን እመነው። አንተ እንደ ሎጥ ከመረጥኸው እና ለጊዜው የገነት አምሳል ሆኖ ከሚታይህ ነገር ግን እግዚአብሔር ከማይከብርበት ከለምለሙ ሰዶምና ገሞራ ይልቅ፣ አሁን ብዙም ለአይን የማይስበው በኋላ ግን ወተትና ማር የሚያፈሰው ለልጅ ልጆችህም ርስት የሚሆነው እግዚአብሔር የሚሰጥህ ከነአን ይሻልሃል።

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
179🥰42🙏34👍21
ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል።

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
https://tttttt.me/Dnabel
228👍21🙏16🥰8👏3
+++ ልሸፈንላችሁ? +++

ሙሴ ከሲና ተራራ ወርዶ ከሕዝቡ ጋር ሲገናኝ የፊቱን ማንጸባረቅ አይተው "ተሸፈንልን" ያሉት ሕዝቡ ናቸው። እርሱ "ከእግዚአብሔር ጋር ስነጋገር ቆይቼ እኮ አሁን መውረዴ ነው? ምነው የፊቴ ብርሃን አስቸገራችሁ? ልሸፈንላችሁ እንዴ?" አላለም። እንዲያውም ቅዱስ መጽሐፍ "ሙሴም ከተራራው በወረደ ጊዜ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለ ተነጋገረ የፊቱ ቁርበት እንዳንጸባረቀ አላወቀም ነበር" ነው የሚለው።(ዘጸ 34፥29) ለቅዱሳን እግዚአብሔር በፊታቸው የሚሥለው የክብር ብርሃን እነርሱን ለሚመለከታቸው እንጂ ለራሳቸው አይታወቃቸውም። እውነተኞቹ ቅዱሳን "ተሸፈኑልን" የሚባሉ እንጂ "ልሸፈንላችሁ" የሚሉ አይደሉም።

ጥቂት በጎ ሥራ ሠርተህ ጻድቅነትህን በግድ ለማሳየት አትሞክር። ሌሎች ተሸፈንልን ይበሉህ እንጂ፣ አንተ ራስህ "ልሸፈንላችሁ" እያልህ የዋሐንን አታስጨንቅ።

በአገራችን የሚታወቅ ተረት አለ። አንድ ጊዜ ትንኝ በሬ ቀንድ ላይ ቆመችና "ከብጄህ እንደ ሆነ ንገረኝና ልነሣልህ" አለችው። በሬውም "እንኳን ልትከብጅኝ መኖርሽንም አላወቅሁም" አላት።

"ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው" ሉቃስ 18፥9

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
አዲስ አበባ
199👍28🙏10🥰8
ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊው እንደሚነግረን ጌታችን የተፈተነው በአርባኛው ቀን ብቻ ሳይሆን አርባውን ቀን በሰይጣን እየተፈተነ ነው የሰነበተው፡፡(ማር 1:13) መጻሕፍት በአርባኛው ቀን የተፈተናቸውን ፈተናዎች ብቻ ይዘው መገኘታቸው በሚበልጠው ለመናገር ነው እንጂ እነዚህን ብቻ ነው የተፈተነው ማለታቸው አይደለም፡፡ በፈተና የሚያልፉ ክርስቲያኖች በደል ሳይገኝበት ‹በነገር ሁሉ የተፈተነ› እና በድካማቸው የሚራራላቸው አምላክ እንዳላቸው አውቀው ይጽናኑ ዘንድ እርሱ በበጎ ለሚፈተኑ ሁሉ በኩር ሆነ፡፡ (ዕብ 4:15)

ጌታ የተፈተነው ከተጠመቀ በኋላ ነበር፡፡ ይህ ለእኛ ምን ያስተምረናል? ምዕመናን ሁል ጊዜ የእግዚአብሔርን ኃይል ፣ልጅነትን በጥምቀት ከተቀበሉ በኋላ የሚያስተናግዱት የፈተና ሕይወት እንዳለ ነው፡፡ ሰይጣን ደስ የሚሰኝበት ምንም ዓይነት የጽድቅ ሥራ ባለመኖሩ ፣የፈተና ወጥመዱን የሚዘረጋው ፈቃዱን ለሚፈጽሙ ደካሞች ሳይሆን በጥምቀት የእግዚአብሔርን ልጅነት ላገኙ እና የዲያቢሎስን ክፋት በመልካም ተጋድሎ ለሚቃወሙት ጽኑዓን ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ‹ኃይልን የምንታጠቀው እኮ ለመዋጋት ነው እንጂ ለመቀመጥ አይደለም› ይለናል! እውነት ነው!፡፡ እግዚአብሔር በጥምቀት መንፈሳዊውን ኃይል የሚያስታጥቀን ከጠላት ዘንድ ፋታ የሌለው ውጊያ ስላለብን አይደለምን? ታዲያ ለምን ለፈተና ሁል ጊዜ እንግዶች እንሆናለን?

አምላካችን በወንጌል በምሳሌ እንዳስተማረው ኢየሩሳሌም ከተባለች ልዕልና ኢያሪኮ ወደ ተሰኘች ትሕትና አንድ ሰው የተባለ አዳም ሲወርድ በመንገድ አጋንንት አግኝተው ፈትነው ፣ልጅነቱን ቀምተው ፣በኃጢአት ቁስል አቁስለው በሞትና በሕይወት መካከል ጥለውት እንደሄዱ ፤ የአዳምና የሔዋንን እዳ ለመክፈል ሰው የሆነ ክርስቶስም ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ሲወርዱ በሚያገኙት የቆሮንቶስ በረሃ አዳምን ያቆሰሉትን አጋንንት ድል ነስቶለታል፡፡ (ሉቃ 10)

መልካም ጾም ይሁንልን!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
124👍22🙏17
በንጽሕና ለመኖር እየታገለ የሚወድቅን እግዚአብሔር አያዝንበትም። ድካሙን እና ያልተቋረጠ ጥረቱን አይቶ ድል የሚነሣበትን መንፈሳዊ ጸጋ ይሰጠዋል እንጂ። እንድትኖር በታዘዝከው ልክ ለመኖር ሞክረህ ስላልሆነልህ በራስህ ተስፋ አትቁረጥ። መሆንህን ብቻ ሳይሆን ፈልገህ መሞከርህን እግዚአብሔር ይቆጥርልሃል። ሰይጣን አቁስሎህ ስለሻረው ጠባሳህ አትቆጭ። ብዙ ጠባሳ እኮ ለሚዋደቅ ጀግና ወታደር የክብር ምልክቱ ነው። አፈ ወርቅ ዮሐንስ እንደሚለው የማይቆስለው የማይዋጋ ብቻ ነው።

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
305🙏25👍15🔥5🥰5
+++ ጸልየህ ልታደርገው ትችላለህ? +++

ማልዶ ቤተ ክርስቲያን ተሳልሞ ወደ ሥራ የሚሄድ አንድ መንፈሳዊ ሰው በጉዞው ከሌላ መንገደኛ ሰው ጋር ይገናኛል። ጥቂት እንደ ተጨዋወቱ ይህ በመንገድ ያገኘው ሰው ከደረት ኪሱ የሲጋራ ፓኮ በማውጣት አንዱን መዝዞ እንዲወስድ ይጋብዘዋል። ያም መንፈሳዊ ሰው "አይ ይቅርብኝ" ሲል እምቢታውን ገለጸ። ባለ ሲጋራውም "ኃጢአት ነው ብለህ ስላሰብህ ነው እምቢ ያልከኝ? ማጨስ እኮ ከአስጨናቂዋ ሕይወት ፋታ ለመውሰድና ራስን ዘና ለማድረግ ይረዳል። ግድ የለህም አንዱን ሞክር" እያለ ሊያግባባው ጣረ። በመጨረሻም መንፈሳዊው ሰው "ግድ የለም ለእኔ ይቅርብኝ። ባይሆን አንተ ይጠቅመኛል ካልህ በቃ ሲጋራውን ከመለኮስህ በፊት አንድ "አባታችን ሆይ" ጸልይና ጀምር" አለው። በዚህ ጊዜ ያ መንገደኛ ደንግጦ እንዲህ ሲል መለሰ "ጸሎት ጸልዬማ እንዴት እንዲህ አደርጋለሁ?!"

በጸሎት ልትጀምር የማትችላቸው ማናቸውም ነገሮች ለአንተ መልካም አይደሉም። በልብህ ኃጢአት እንድታደርግ የሚገፉፉህ ክፉ ሐሳብ ሲመጣ "ይህን ጸልዬ ማድረግ እችላለሁ?" ብለህ ራስህን ጠይቅ። ከጸሎት ጋር የማይጣጣም ከመሰለህ እርሱ ኃጢአት ነውና ተወው። ጸልዮ የሚዘሙት፣ ጸልዮ የሚሰርቅ፣ ጸልዮ ባልንጀራውን የሚሳደብ፣ ጸልዮ በወንድሙ ላይ ክፉ የሚያደርግ ማን ነው?

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
abelzebahiran@gmail.com
አዲስ አበባ
296👍45🙏16❤‍🔥9🥰7