⚠️WARNING ⚠️ *GRAPHIC*
26 ሰዎችን የገደለው አንድ የታይላንድ ወታደር በፖሊስ ተገደለ ፡፡ ቢያንስ 42 የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ጥቃት አድራሹ ግድያውን የጀመረው በሀገሪቱ የሰዓት አቆጣጠር ትናንት ከሰዓት በኋላ ነበር። የ32 ዓመቱ ግለሰብ በመጀመሪያ ኮራት በመባል የሚታወቅ ቦታ የሚገኝ ወታደራዊ ሰፈር ውስጥ አለቃውን እና ሌሎች ሁለት ሰዎች ገድሎ ሸሽቷል።
ከዛም ጠመንጃ እና ጥይቶች ሰርቆ በወታደራዊ መኪና ያመለጠው ይሄው ግለሰብ በዘፈቀደ ሰዎች ላይ እየተኮሰ መግደሉን እና ይህንን ድርጊቱንም በቪዲዮ እየቀረፀ ኢንተርኔት ላይ ይለቅ እንደነበር ተገልጿል።
በመጨረሻም ወደ ገበያ አዳራሽ በመግባት ሰዎች ላይ ሊተኩስ እና በአስራዎቹ የሚቆጠሩ ሰዎችንም ማገቱን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ግለሰቡም ከ 17 ሰዓታት በኋላ በልዩ ኃይል ፖሊስ ሊገደል ችሏል። የድርጊቱ ምክንያት በውል አልታወቀም።
Via:- DW #Photo social media
@YeneTube @Fikerassefa
26 ሰዎችን የገደለው አንድ የታይላንድ ወታደር በፖሊስ ተገደለ ፡፡ ቢያንስ 42 የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ጥቃት አድራሹ ግድያውን የጀመረው በሀገሪቱ የሰዓት አቆጣጠር ትናንት ከሰዓት በኋላ ነበር። የ32 ዓመቱ ግለሰብ በመጀመሪያ ኮራት በመባል የሚታወቅ ቦታ የሚገኝ ወታደራዊ ሰፈር ውስጥ አለቃውን እና ሌሎች ሁለት ሰዎች ገድሎ ሸሽቷል።
ከዛም ጠመንጃ እና ጥይቶች ሰርቆ በወታደራዊ መኪና ያመለጠው ይሄው ግለሰብ በዘፈቀደ ሰዎች ላይ እየተኮሰ መግደሉን እና ይህንን ድርጊቱንም በቪዲዮ እየቀረፀ ኢንተርኔት ላይ ይለቅ እንደነበር ተገልጿል።
በመጨረሻም ወደ ገበያ አዳራሽ በመግባት ሰዎች ላይ ሊተኩስ እና በአስራዎቹ የሚቆጠሩ ሰዎችንም ማገቱን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ግለሰቡም ከ 17 ሰዓታት በኋላ በልዩ ኃይል ፖሊስ ሊገደል ችሏል። የድርጊቱ ምክንያት በውል አልታወቀም።
Via:- DW #Photo social media
@YeneTube @Fikerassefa