YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ኢትዮጵያ የራሷን ሰነድ ለድርድር ልታቀርብ ነው #itsmydam

የኢትዮጵያ መንግሥት የታላቁ ህዳሴ ግድብ የውኃ አሞላልና አለቃቀቅን የተመለከተ ሰነድ አዘጋጅቶ ለድርድር እንደሚያቀርብ ተሰማ። አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የሪፖርተር ምንጭ እንደገለጹት፣ በአሜሪካና በዓለም ባንክ አመቻችነት የግድቡን የውኃ አሞላልና አለቃቀቅን በተመለከተ ሲደረግ የቆየው ድርድር ውጤት የኢትዮጵያን ጥቅም የሚጎዳ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን የአገሪቱን ሉዓላዊነትና ጥቅም የሚያስከብር የድርድር ሰነድ እንዲያዘጋጅ በመንግሥት ታዞ ሰነዱን በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ከተደራዳሪ ቡድኑ በተጨማሪ የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የዓለም አቀፍ ሕግ ስምምነት ባለሙያዎች፣ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሙያዎች፣ ከተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ ዩኒቨርስቲዎች የተወጣጡ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ሰነዱን በማዘጋጀት ሒደት ላይ ሌት ተቀን እየሠሩ እንደሚገኙ ማረጋገጥ ተችሏል።

ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ጠንካራ ትስስር ያላት አገር በመሆኗ በድርድሩ መሳተፍ ትክክል ቢሆንም፣ አሜሪካ ያዘጋጀችው የመጨረሻው ሰነድ ውስጥ ያልተፈቱ ጉዳዮች መኖራቸውን ምንጩ ጠቁመዋል፡፡ ታዛቢዎቹ በድርድሮች ወቅት በኢትዮጵያ ላይ ግፊት እያደረጉ እንደነበር ተሰምቷል። ይህ የአገሪቱን ጥቅም የሚፃረር ስለሆነ በቀጣዩ ድርድር ላይ ላለመሳተፍ የተሰጠው ውሳኔ ትክክለኛ መሆኑን አክለዋል።

የታዛቢነት ሚና የተሰጣቸው አሜሪካና ዓለም ባንክ ድርድሩን ወደ ሽምግልና መቀየራቸውና በመጨረሻም ራሳቸው አዘጋጅተው ለስምምነት ያቀረቡት ረቂቅ ሰነድ፣ ኢትዮጵያ እንደማትደራደርባቸው የገለጸቻቸውን በርካታ ነጥቦች ያላካተተና ለታችኞቹ የተፋሰሱ አገሮችም ጥቅም በእጅጉ ያደላ በመሆኑ፣ በኢትዮጵያ ተቀባይነት እንደማይኖረው አቋም መያዙን እኚሁ ምንጭ አስታውቀዋል።

የቀረበው ረቂቅ የስምምነት ሰነድ ከላይ ከተገለጸው በተጨማሪ ከህዳሴ ግድብ አልፎ የዓባይ ውኃ ክፍፍልን የሚመለከቱ አንቀጾች የተካተቱበት በመሆኑ፣ ከድርድር አጀንዳው ያፈነገጠ እንደሆነ ተለይቷል ሲሉ ምንጩ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የግድቡ ባለቤትና በግዛቷ ውስጥ የሚገኝ እንደ መሆኑ መጠን፣ እንዴት መሞላት አለበት የሚለውን ጉዳይ በዓለም አቀፍ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች አጠቃቀም መርሆን መሠረት በማድረግ ለታችኞቹ አገሮች ማሳወቅ፣ አገሮቹ ሊያነሱ የሚችሉት ሥጋትም በዓለም አቀፍ መርሆች ውስጥ የሚወድቅ ከሆነ ለማካተት ድርድር እንደሚደረግበት ያሳወቁት እኚሁ ምንጭ፣ በዚህ አግባብ ሰነዱን የማዘጋጀት ሥራ በመፋጠን ላይ መሆኑን አስረድተዋል። የሰነዱ ዝግጅት ሲጠናቀቅ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለግብፅና ለሱዳን እንደሚላክ ገልጸዋል።

በአሜሪካና ዓለም ባንክ አመቻችነት በሦስቱ አገሮች መካከል ሲደረግ የነበረው ድርድር ባለፈው ሳምንት ይፈረማል ተብሎ ዕቅድ ወጥቶለት የነበረ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ባወጣው መግለጫ ለስምምነት ዝግጁ እንዳልሆነና ልዑካኑንም ወደ አሜሪካ እንደማይልክ በይፋ አስታውቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሳምንት በፊት ለግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ በላኩት መልዕክት፣ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርድሩን አስመልክቶ የተረቀቀውን ሰነድ ለማጤን ኢትዮጵያ በቂ ጊዜ እንደምትፈልግ ማስታወቃቸው ይታወሳል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድን መልዕክት ለግብፅ ፕሬዚዳንት ያደረሰው በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የተመራ ልዑክ መሆኑም እንዲሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በላኩት በዚህ መልዕክት ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ድርድርን በተመለከተ ጊዜ ወስዳ ማጤን እንደምትፈልግ፣ የምትደርሰበትን አቋም እንደምታሳውቅ የሚያስረዳ እንደሆነ መዘገባችን አይዘነጋም። መንግሥት ይህንን አቋሙን ባለፈው ሳምንት ለሕዝብ ይፋ ካደረገ በኋላ፣ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የተወሰደውን አቋም በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲደግፉ ተስተውለዋል።

ምንጭ:- Reporter
@YeneTube @Fikerassefa
መልካም ቀን ይሁንሎት
#ግድቡየኔነው
#itsmydam
ጎሮ አከባቢ ድምፃችን ለግድባችን በማለት ድምፃቸውን እያሰሙ ይገኛሉ።
#ግድቡ_የኔ_ነው
#itsmydam

Via:- ኦዚል የኔቲዩብ
@Yenetube @Fikerassefa
ድምፃችን ለግድባችን ጀሞ አንድ ኮንዶሚንየም
#ግድቡ_የኔ_ነው
#ItsMyDam
Via:- ሶል/የኔቲዩብ
@Yenetube @Fikerassefa1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ድምፃችን ለግድባችን!

ገላን ኮንዶምኒዬም አካባቢ የነበረው ድባብ

#ግድቡ_የኔ_ነው
#itsmydam

Via Jo/YeneTube
@YeneTube @FikerAssefa1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ድምፃችን ለግድባችን!

አዲስ ከተማ፣ ሰባተኛ አካባቢ የነበረው ድባብ

#ግድቡ_የኔ_ነው
#itsmydam

Via King/YeneTube
@YeneTube @FikerAssefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በተመሳሳይ ቃሊቲ 40/60 ኮንዶሚንየም ድምፃቸውን አሰምተዋል።

#ግድቡየኔነው💪
#Itsmydam💪🏻
Via:- Beza (Yenetube)
@Yenetube @Fikerassefa1
ድምፃችን ለግድባችን!

በተመሳሳይ ቦሌ አራብሳ አካባቢ የነበረው ድባብ በፎቶ

#ግድቡየኔነው
#Itsmydam

Via Bezawit[YeneTube]
@YeneTube @FikerAssefa
ድምፃችን ለግድባችን!

ሐምሌ19 አካባቢ የነበረው ድባብ በፎቶ

#ግድቡየኔነው
#Itsmydam

Via SAM[YeneTube]
@YeneTube @FikerAssefa