#FakeLetterAlert
የገቢዎች ሚኒስቴር እንደማንኛዉም ባለበጀት መስሪያ ቤት በጀት ተመድቦለት በበጀት የሚንቀሳቀስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ነዉ፡፡
ስለዚህ የበጀት ፍሰቱ ቁጥጥር የሚደረግበትና በስርዓት የሚመራ ነዉ፡፡ ከአሰራርና መመሪያ ዉጪ ከተመደበለት በጀት ዉጪ እንደፈለገዉ ለሚዲያም ሆነ ሌሎች አካላት ድጋፍ ማድረግ አይችልም፡፡ በማህበራዊ ሚዲያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለግል ሚዲያ(ኦኤም ኤን)ድጋፍ አድርጓል ተብሎ የሚናፈሰዉ ወሬ አሉባልታና ሆን ተብሎ ለማደናገሪያነት የተሰራጨ ስለሆነ የፌስ ቡካችን ተከታታዮች በጠየቃችሁን መሰት ወሬዉ ዉሸት መሆኑን እንድታዉቁ እናስታዉቃለን፡፡
በተለይ በዘንድሮዉ ሩብ አመት ያስመዘገብነዉ ዉጤት ሰራተኛና አመራሩን ለተሻለ ዉጤት የሚያነሳሳ እንጂ ለአሉባልታ ቦታ ሰቶ ወደ ኋላ የሚመልስ ስላልሆነ ስኬታማ እንቅስቃሴችንን ለማደናቀፍ የምትጥሩ አካላት ከዚሁ ድርጊታችሁ እንድትታቀቡ እናሳስባለን፡፡ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ ወሬ ተሰራጭቶ ዉሸት መሆኑን ምላሽ የሰጠንበት ሲሆን አሁንም እየተሰራ ያለዉን ስራ ለማጠልሸት ሆን ተብሎ የተሰራጨ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡
-የገቢዎች ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
የገቢዎች ሚኒስቴር እንደማንኛዉም ባለበጀት መስሪያ ቤት በጀት ተመድቦለት በበጀት የሚንቀሳቀስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ነዉ፡፡
ስለዚህ የበጀት ፍሰቱ ቁጥጥር የሚደረግበትና በስርዓት የሚመራ ነዉ፡፡ ከአሰራርና መመሪያ ዉጪ ከተመደበለት በጀት ዉጪ እንደፈለገዉ ለሚዲያም ሆነ ሌሎች አካላት ድጋፍ ማድረግ አይችልም፡፡ በማህበራዊ ሚዲያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለግል ሚዲያ(ኦኤም ኤን)ድጋፍ አድርጓል ተብሎ የሚናፈሰዉ ወሬ አሉባልታና ሆን ተብሎ ለማደናገሪያነት የተሰራጨ ስለሆነ የፌስ ቡካችን ተከታታዮች በጠየቃችሁን መሰት ወሬዉ ዉሸት መሆኑን እንድታዉቁ እናስታዉቃለን፡፡
በተለይ በዘንድሮዉ ሩብ አመት ያስመዘገብነዉ ዉጤት ሰራተኛና አመራሩን ለተሻለ ዉጤት የሚያነሳሳ እንጂ ለአሉባልታ ቦታ ሰቶ ወደ ኋላ የሚመልስ ስላልሆነ ስኬታማ እንቅስቃሴችንን ለማደናቀፍ የምትጥሩ አካላት ከዚሁ ድርጊታችሁ እንድትታቀቡ እናሳስባለን፡፡ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ ወሬ ተሰራጭቶ ዉሸት መሆኑን ምላሽ የሰጠንበት ሲሆን አሁንም እየተሰራ ያለዉን ስራ ለማጠልሸት ሆን ተብሎ የተሰራጨ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡
-የገቢዎች ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa