በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል ተቋረጠ!
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው በተፈፀመ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት በኢንደስትሪ መንደሩና በአካባቢው ኃይል ተቋርጧል።132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በዘራፊዎች ተፈቶና ተቆርጦ በመውደቁ በሌላ ምሰሶ ላይ ተጨማሪ ጉዳት በማድረስ ነው ኃይል የተቋረጠው።በዚህም የኢንደስትሪ መንደሩን ጨምሮ በሰሚት ኮንዶሚኒየም፣ በቦሌ አራብሳ፣ በአየር መንገድ ማህበር፣ በጎሮ፣ በአይሲቲ ፓርክ፣ በገርጂ ወረገኑና በገርጂ ካሳንቺስ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጣል።
ችግሩ እንደተከሰተ የተቋማችን የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የጥገና ባለሙያዎች ችግሩን ለመቅረፍ እንቅስቃሴ ቢጀምሩም ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ምሰሶውን መልሶ በማቆም መስመሩን ማገናኘት አልተቻለም።
የተሰረቁትን የምሰሶ አካላት በሌላ ተክቶ መልሶ ለማቆም መለዋወጫና በርካታ ቀናት የሚፈልግ ቢሆንም ሌላ ተለዋጭ የእንጨት ምሰሶ በመትከል መስመሩን ለማገናኘት ጥረት ተጀምሯል።በመሆኑም በኢንደስትሪ መንደሩም ሆነ ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል መልሰን እስከምናገናኝ ድረስ ህብረሰተቡ በትዕግስት እንዲጠብቀንና ሌሎች የኃይል አማራጮችን እንዲጠቀም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሳስባል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ከቦሌ ለሚ መስመር ጋር የተገናኘው የቃሊቲ አካባቢ መስመር ተጠግኖ ኃይል መስጠት ጀምሯል።
#EEPCO
@YeneTube @FikerAssefa
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው በተፈፀመ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት በኢንደስትሪ መንደሩና በአካባቢው ኃይል ተቋርጧል።132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በዘራፊዎች ተፈቶና ተቆርጦ በመውደቁ በሌላ ምሰሶ ላይ ተጨማሪ ጉዳት በማድረስ ነው ኃይል የተቋረጠው።በዚህም የኢንደስትሪ መንደሩን ጨምሮ በሰሚት ኮንዶሚኒየም፣ በቦሌ አራብሳ፣ በአየር መንገድ ማህበር፣ በጎሮ፣ በአይሲቲ ፓርክ፣ በገርጂ ወረገኑና በገርጂ ካሳንቺስ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጣል።
ችግሩ እንደተከሰተ የተቋማችን የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የጥገና ባለሙያዎች ችግሩን ለመቅረፍ እንቅስቃሴ ቢጀምሩም ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ምሰሶውን መልሶ በማቆም መስመሩን ማገናኘት አልተቻለም።
የተሰረቁትን የምሰሶ አካላት በሌላ ተክቶ መልሶ ለማቆም መለዋወጫና በርካታ ቀናት የሚፈልግ ቢሆንም ሌላ ተለዋጭ የእንጨት ምሰሶ በመትከል መስመሩን ለማገናኘት ጥረት ተጀምሯል።በመሆኑም በኢንደስትሪ መንደሩም ሆነ ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል መልሰን እስከምናገናኝ ድረስ ህብረሰተቡ በትዕግስት እንዲጠብቀንና ሌሎች የኃይል አማራጮችን እንዲጠቀም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሳስባል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ከቦሌ ለሚ መስመር ጋር የተገናኘው የቃሊቲ አካባቢ መስመር ተጠግኖ ኃይል መስጠት ጀምሯል።
#EEPCO
@YeneTube @FikerAssefa