YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የአፍሪቃ ህብረት ቢሮ አባል ሃገራት መሪዎች ኢትዮጵያና ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴ ግድብ ሰበብ የገጠሙትን ዉዝግብ ለማስወገድ የጀመሩትን ጥረት ዛሬ ቀጥለዉ ዉለዋል።

የቢሮዉ አባል ሃገራት መሪዎች የሦስቱ ሃገራት ባለስልጣናት ከአንድ ሳምንት በፊት በደረሱበት የዉይይት ዉጤት ላይ ዛሬ ሲነጋገሩ ነዉ የዋሉት።

የአፍሪቃ ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበር የደቡብ አፍሪቃዉ ፕሬዚደንት ሲሪል ራማፎዛ የሚመሩት ዉይይት በርቀት በቪዲዮ አማካኝነት ነዉ የተካሄደዉ።
የዉይይቱ ሂደትም ለጋዜጠኞች ለመገናኛ ዘዴዎች ዝግ ነዉ።

የአፍሪቃ ህብረት ቢሮ አባላት መሪዎች ከዚህ ቀደምም በአወዛጋቢዉ የህዳሴ ግድብ ላይ ለተከታታይ ቀናት ተወያይተዉ ነበር።

#DWAmharic

@YeneTube @FikerAssefa1