የአፍሪቃ ህብረት ቢሮ አባል ሃገራት መሪዎች ኢትዮጵያና ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴ ግድብ ሰበብ የገጠሙትን ዉዝግብ ለማስወገድ የጀመሩትን ጥረት ዛሬ ቀጥለዉ ዉለዋል።
የቢሮዉ አባል ሃገራት መሪዎች የሦስቱ ሃገራት ባለስልጣናት ከአንድ ሳምንት በፊት በደረሱበት የዉይይት ዉጤት ላይ ዛሬ ሲነጋገሩ ነዉ የዋሉት።
የአፍሪቃ ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበር የደቡብ አፍሪቃዉ ፕሬዚደንት ሲሪል ራማፎዛ የሚመሩት ዉይይት በርቀት በቪዲዮ አማካኝነት ነዉ የተካሄደዉ።
የዉይይቱ ሂደትም ለጋዜጠኞች ለመገናኛ ዘዴዎች ዝግ ነዉ።
የአፍሪቃ ህብረት ቢሮ አባላት መሪዎች ከዚህ ቀደምም በአወዛጋቢዉ የህዳሴ ግድብ ላይ ለተከታታይ ቀናት ተወያይተዉ ነበር።
#DWAmharic
@YeneTube @FikerAssefa1
የቢሮዉ አባል ሃገራት መሪዎች የሦስቱ ሃገራት ባለስልጣናት ከአንድ ሳምንት በፊት በደረሱበት የዉይይት ዉጤት ላይ ዛሬ ሲነጋገሩ ነዉ የዋሉት።
የአፍሪቃ ህብረት የወቅቱ ሊቀመንበር የደቡብ አፍሪቃዉ ፕሬዚደንት ሲሪል ራማፎዛ የሚመሩት ዉይይት በርቀት በቪዲዮ አማካኝነት ነዉ የተካሄደዉ።
የዉይይቱ ሂደትም ለጋዜጠኞች ለመገናኛ ዘዴዎች ዝግ ነዉ።
የአፍሪቃ ህብረት ቢሮ አባላት መሪዎች ከዚህ ቀደምም በአወዛጋቢዉ የህዳሴ ግድብ ላይ ለተከታታይ ቀናት ተወያይተዉ ነበር።
#DWAmharic
@YeneTube @FikerAssefa1