አሜሪካ ለዓለም ጤና ድርጅት የማዋጣውን ገንዘብ አቋርጫለሁ አለች
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኮሮናቫይረስ የሰጠው ምላሽ ቀርፋፋ ነው፤ በአካሄዱም ቻይናን ማዕከል አድርጓል ላሉት የዓለም ጤና ድርጅት አገራቸው የምታበረክተውን የገንዘብ መዋጮ እዲቋረጥ አዘዙ።
ይህም ማለት አሜሪካ ለድርጅቱ በየዓመቱ ለድርጅቱ ትሰጥ የነበረው ገንዘብ እንዲቆም የሚያደርግ ነው ተብሏል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የትራምፕን ውሳኔ "ጊዜውን ያላገናዘበ እርምጃ" ሲሉ ተችተውታል።
ዶናልድ ትራምፕ ከሳምንታት በፊት ዶ/ር ቴድሮስ አድኃኖም የሚመሩትን መሥሪያ ቤት ክፉኛ ሲወቅሱ ነበር። በየዓመቱ የሚሰጡትን መዋጮ ለማጤን እንደሚገደዱም መጠቆማቸው ይታወሳል።
ትራምፕ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ "ለደረሰው ጥፋት ድርጅቱ ተጠያቂ መሆን አለበት" እስከ ማለት ደርሰዋል።
አሜሪካ ለዓለም ጤና ድርጅት የምትሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ለድርጅቱ ወሳኝና የጠቅላላውን 15 በመቶ የሚይዝ ሲሆን፤ ቻይና በአንጻሩ በፈረንጆቹ 2018/19 ለድርጅቱ ያዋጣቸው ገንዘብ 76 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው፤ የአሜሪካ የባለፈው ዓመት መዋጮ 400 ሚሊዮን ዶላር ይደርሳል።
"ድርጅቱ ቫይረሱ ከዉሃን የተነሳ ሰሞን ፈጥኖ እርምጃ ቢወስድ ኖሮ ይህ ሁሉ ቀውስ ባልተፈጠረ ነበር። ከዚያ ይልቅ ቻይና እየወሰደችው የነበረውን እርምጃ ሲያንቆለጳጵስ ነበር" ሲሉ ዶ/ር ቴድሮስ የሚመሩትን ድርጅት ወቅሰዋል፤ ፕሬዝዳንት ትራምፕ።
የአሜሪካንን እርምጃ በተመለከተ የዓለም ጤና ድርጅት መሪ ዶ/ር ቴድሮስ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Via: #BBCAmharic
@Yenetube @Fikerassefa
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኮሮናቫይረስ የሰጠው ምላሽ ቀርፋፋ ነው፤ በአካሄዱም ቻይናን ማዕከል አድርጓል ላሉት የዓለም ጤና ድርጅት አገራቸው የምታበረክተውን የገንዘብ መዋጮ እዲቋረጥ አዘዙ።
ይህም ማለት አሜሪካ ለድርጅቱ በየዓመቱ ለድርጅቱ ትሰጥ የነበረው ገንዘብ እንዲቆም የሚያደርግ ነው ተብሏል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የትራምፕን ውሳኔ "ጊዜውን ያላገናዘበ እርምጃ" ሲሉ ተችተውታል።
ዶናልድ ትራምፕ ከሳምንታት በፊት ዶ/ር ቴድሮስ አድኃኖም የሚመሩትን መሥሪያ ቤት ክፉኛ ሲወቅሱ ነበር። በየዓመቱ የሚሰጡትን መዋጮ ለማጤን እንደሚገደዱም መጠቆማቸው ይታወሳል።
ትራምፕ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ "ለደረሰው ጥፋት ድርጅቱ ተጠያቂ መሆን አለበት" እስከ ማለት ደርሰዋል።
አሜሪካ ለዓለም ጤና ድርጅት የምትሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ለድርጅቱ ወሳኝና የጠቅላላውን 15 በመቶ የሚይዝ ሲሆን፤ ቻይና በአንጻሩ በፈረንጆቹ 2018/19 ለድርጅቱ ያዋጣቸው ገንዘብ 76 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው፤ የአሜሪካ የባለፈው ዓመት መዋጮ 400 ሚሊዮን ዶላር ይደርሳል።
"ድርጅቱ ቫይረሱ ከዉሃን የተነሳ ሰሞን ፈጥኖ እርምጃ ቢወስድ ኖሮ ይህ ሁሉ ቀውስ ባልተፈጠረ ነበር። ከዚያ ይልቅ ቻይና እየወሰደችው የነበረውን እርምጃ ሲያንቆለጳጵስ ነበር" ሲሉ ዶ/ር ቴድሮስ የሚመሩትን ድርጅት ወቅሰዋል፤ ፕሬዝዳንት ትራምፕ።
የአሜሪካንን እርምጃ በተመለከተ የዓለም ጤና ድርጅት መሪ ዶ/ር ቴድሮስ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Via: #BBCAmharic
@Yenetube @Fikerassefa