YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
#ጀዋር መሀመድ እና #ታማኝ በየነ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ #ለኢቢሲ የሰጡት ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች
@yenetube @mycase27
እስክንድር ነጋ Vs ጀዋር መሐመድ ( # DW)

የአዲስ አበባ የባለቤትነት ዉዝግብ

«እኛ የምንለዉ ሕጉ የሚለዉን ነዉ።የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ሕግ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ዋና ከተማ ነች ይላል።የፌደራሉ ሕገ መንግሥትም ኦሮሚያ (ከአዲስ አበባ) ልዩ ጥቅም እንዳለዉ ያስቀምጣል------»
የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ሥራ አስኪያጅና የመብት አቀንቃኝ ጀዋር መሐመድ
«የአዲስ አበባ ጉዳይ የዜግነት ጥያቄ ነዉ-----ሕገ መንግስቱ ከየት መጣ? ማን አወጣዉ? ምንስ አላማ ነበረዉ?------» ጋዜጠኛና የመብት አቀንቃኝ #እስክንድር_ነጋ

«እንዴ!! ምነዉ እባክሕ? እስክንድር ነጋ እኮ የመብት ታጋይ ነዉ----ልንቃወመዉ፣ ልንተቸዉ እንችላለን፣ ከዚያ ባለፈ ግን ዛሬ እስክንድርን ያስፈራሩ ነገ ጀዋርን ያስፈራራሉ-----እስክንድር ብቻዉን ሳይሆን ሁላችንም አብረነዉ ተሰልፈን እንታገላለን----» ጀዋር መሐመድ
ጀዋር ያለዉን «የምጠራጠርበት ምንም ምንም ምክንያት የለኝም።አመሰግነዋለሁ።-------» #እስክንድር_ነጋ

«በግሌ ከጠይቀከኝ ከእስክንዳር ጋር አይደለም ከማንም ጋር በማንኛዉም ሰዓት በዚሕ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ብቻ ሳይሆን በሌላም ጉዳይ ላይ ለመወያየት ዝግጁ ነን----» #ጀዋር_መሐመድ

«ለመወያየት መቶ በመቶ ዝግጁ ነኝ። የምንፈታዉም በድርድርና ዉይይት ነዉ።----ብስለቱም አለን» እስክንድር ነጋ።
@YeneTube @FikerAssefa
ከኢፌዴሪ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት

''12፣12፣12 ''ተብሎ የተፈጠረው ስልፍ ህገወጥ በመሆኑ ህብረተሰብ የጥሪው ዓላማ ህገወጥና ፀረ-ሰላም መሆኑን በመገንዘብ ለዚህ ስልፍ ተባባሪ እንዳይሆን ። በሌላ በኩል አቶ #ጀዋር_ሙሀመድ ተሟል ችግር ደርሶበታል ተብሎ በተለያዩ የሚዲያ አውታሮች የሚወራው ሐሰተኛ መረጃ መሆኑንና ግለሰቡ በተሟላ ጤንነት ላይ የሚገኝ መሆኑን እየገለጽን በዚህ በዚህ ሰበብ ሰውን እያወናበዱ በሀሰተኛ ወሬ የፍርድ ሂደቱን ለማዛባት የሚደረገው ጥረት በማንኛውም ሁኔታ ተቀባይነት የሌለው ተግባር መሆኑን ህበረተሰብ ተገንዝቦ ለህገወጥ ጥሪዎችና ቅስቀሳዎች ተባባሪ እንዳይሆንና ሰላምና ፀጥታ በማስከበር ተግባር ላይ ከተሰማሩ የፀጥታ ሀይሎች ጎን ተሰልፎ ሰላሙን እንዲጠብቅና እንዲያረጋግጥ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪውን ያስተላልፋል ።
ነሐሴ 11 ቀን 2012 ዓ.ም
@Yenetube @FikerAssefa