YeneTube
117K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.88K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
#የ8ኛ_ክፍል_ፈተና_ውጤት_ይፋ ተደረገ


ክልል አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ተደረገ

የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ትምህርት ቢሮ የ2011 ዓ.ም 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ አደረገ፡፡

በክልሉ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠረው አለመረጋጋት ለፈተና ከተመዘገቡ ተማሪዎች መካከል በርካታ ተማሪዎች ያቋረጡ ቢኖርም በአሁን ጊዜ በመደበኛ፣ በማታና በግል በአጠቃላይ 340 ሺህ 85 ከተመዘገበው 331 ሺህ በፈተና የተቀመጡ ሲሆን ከተመቀመጡት ውስጥ 70 በመቶ ማለፋቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃለፊ አቶ ተሰማ ዲማ ገልፀዋል፡፡

የማለፊያ መቁረጫ ነጥብ በጥሬ ማርክ ለወንዶች 45 ለሴቶች 43 እና ለዓይነ ስውራን 40 እንዲሆን በተደረገው ውሳኔ በክልሉ በመደበኛ፣ በማታ እና በግል በአጠቃላይ ፈተና ላይ ከተቀመጡት 331 ሺህ ተማሪዎች ወስጥ 230 ሺህ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ወደሚቀጥለው 9ኛ ክፍል ማለፋቸውንም ገልፀዋል፡፡

ምንጭ፡ የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
@YeneTube @FikerAssefa