የኦሞ ወንዝ ባስከተለው የውሃ መጥለቅለቅ 15 ሺህ ሰዎች ተፈናቀሉ
በደቡብ ክልል የሚገኘው የዳሰነች ወረዳ በኦሞ ወንዝ ውሃ በመጥለቀለቁ፤ 15 ሺህ ገደማ ሰዎች መፈናቀላቸውን የደቡብ ኦሞ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዩች መምሪያ አስታወቀ። ወንዙ ባስከተለው ጎርፍ 15 ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በሌሎች ተቋማት ላይ ጉዳት መድረሱንም ገልጿል።
የዞኑ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዩች መምሪያ ኃላፊ አቶ መላኩ ለማ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት የኦሞ ወንዝ ላስከተለው የውሃ መጥለቅለቅ መንስኤው #የግልገል_ጊቤ ሶስት የኃይል ማመንጫ ግድብ ከመጠን በላይ በመሙላቱ የተለቀቀ ውሃ ነው። በዚህም ምክንያት በዳሰነች ወረዳ ከሚገኙ 40 ቀበሌዎች ውስጥ ሃያ ስምንቱ በዚህ ሳምንት በወንዙ መጥለቅለቃቸውን አስረድተዋል።
Via:- ethiopiainsider
@Yenetube @Fikerassefa
በደቡብ ክልል የሚገኘው የዳሰነች ወረዳ በኦሞ ወንዝ ውሃ በመጥለቀለቁ፤ 15 ሺህ ገደማ ሰዎች መፈናቀላቸውን የደቡብ ኦሞ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዩች መምሪያ አስታወቀ። ወንዙ ባስከተለው ጎርፍ 15 ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በሌሎች ተቋማት ላይ ጉዳት መድረሱንም ገልጿል።
የዞኑ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዩች መምሪያ ኃላፊ አቶ መላኩ ለማ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት የኦሞ ወንዝ ላስከተለው የውሃ መጥለቅለቅ መንስኤው #የግልገል_ጊቤ ሶስት የኃይል ማመንጫ ግድብ ከመጠን በላይ በመሙላቱ የተለቀቀ ውሃ ነው። በዚህም ምክንያት በዳሰነች ወረዳ ከሚገኙ 40 ቀበሌዎች ውስጥ ሃያ ስምንቱ በዚህ ሳምንት በወንዙ መጥለቅለቃቸውን አስረድተዋል።
Via:- ethiopiainsider
@Yenetube @Fikerassefa