የፊታችን እሁድ ሊካሄድ የነበረው ፍቅር ያሸንፋል የኢትዮጲያ ሩጫ እና ፌስቲቫል ተራዘመ፡፡
ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ በሚል መሪ ሀሳብ የፊታች እሁድ የካቲት 15 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል ተብሎ ቀጠሮ የተያዘለት ፍቅር ያሸንፋል የኢትዮጲያ ሩጫ እና ፌስቲቫል መራዘሙን ሰምተናል፡፡
የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች እና የመንግስት ሀላፊዎች ያስጀምሩታል ተብሎ ይጠበቅ የነበረው ፌስቲቫል እና ሩጫው ወደ ሌላ ጊዜ የተላለፈበት ምክንያት የካቲት 14 ምሽት ላይ ከሚካሄደው #የድምፃዊ_ቴድሮስ_ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ኮንሰርት ጋር የመርሀግብር መቀራረብ በመከሰቱ መሆኑን አዘጋጆቹ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
ውድድሩ መራዘሙን እንጂ ትክክለኛ የሚካሄድበትን የውድድር ቀን ገና አልወሰንም ምክንያቱም የአትሌቲክስ ፌዴሪሽን ፕሮግራሞችን ማጣራት ስለሚኖርብንም ብለዋል አዘጋጆቹ፡፡
ከከንቲባ ጽህፈት ቤት እና ከፀጥታ ሀይሎች ጋርም ተነጋግረነን የፕሮግራም ሂደቱን ማመቻት ስለሚያፈልግ ቲሸርቶች የገዙ ተሳታፊዎች ትክክለኛውን ቀን ይፋ እስከምናደርግ በትዕግስት ጠብቁን ብለዋል፡፡በተቀያሪው የጊዜ ሰሌዳ አይመቸንም የምትሉ ታሳታፉዎች ካላችሁ ቲሸርቶቹን በመመለስ ገንዘባቹን ማግኘት ትችላላቹ ተብላቹሀል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ በሚል መሪ ሀሳብ የፊታች እሁድ የካቲት 15 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል ተብሎ ቀጠሮ የተያዘለት ፍቅር ያሸንፋል የኢትዮጲያ ሩጫ እና ፌስቲቫል መራዘሙን ሰምተናል፡፡
የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች እና የመንግስት ሀላፊዎች ያስጀምሩታል ተብሎ ይጠበቅ የነበረው ፌስቲቫል እና ሩጫው ወደ ሌላ ጊዜ የተላለፈበት ምክንያት የካቲት 14 ምሽት ላይ ከሚካሄደው #የድምፃዊ_ቴድሮስ_ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ኮንሰርት ጋር የመርሀግብር መቀራረብ በመከሰቱ መሆኑን አዘጋጆቹ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡
ውድድሩ መራዘሙን እንጂ ትክክለኛ የሚካሄድበትን የውድድር ቀን ገና አልወሰንም ምክንያቱም የአትሌቲክስ ፌዴሪሽን ፕሮግራሞችን ማጣራት ስለሚኖርብንም ብለዋል አዘጋጆቹ፡፡
ከከንቲባ ጽህፈት ቤት እና ከፀጥታ ሀይሎች ጋርም ተነጋግረነን የፕሮግራም ሂደቱን ማመቻት ስለሚያፈልግ ቲሸርቶች የገዙ ተሳታፊዎች ትክክለኛውን ቀን ይፋ እስከምናደርግ በትዕግስት ጠብቁን ብለዋል፡፡በተቀያሪው የጊዜ ሰሌዳ አይመቸንም የምትሉ ታሳታፉዎች ካላችሁ ቲሸርቶቹን በመመለስ ገንዘባቹን ማግኘት ትችላላቹ ተብላቹሀል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa