#update ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተጎዱ ዜጎችን መልሶ #ለማቋቋም የሀብት ማሰባሰብ ስራ ጀመረ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተከስቶ በነበረዉ ሁከትና ብጥብጥ የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳትና መልሶ ለማቋቋም የሀብት ማሰባሰብ ስራ መጀመሩን የክልሉ መንግስት አስታወቀ፡፡
የክልሉ መንግስት የብት ማሰባሰቢያ የባንክ ሂሳብ ቁጥርም ይፋ አደርጓል፡፡
የክልሉ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ #ዘላለም ጃለታ ለኢቢሲ እንደተናገሩት በክልሉ ባሳለፍነዉ የመስከረም ወር ተከስቶ በነበረዉ ሁከትና ብጥብጥ ቁጥራቸው ከ57 ሽህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች በከፋ ችግር ውስጥ ይገኛሉ፡፡
ይህን ችግር ለመቅረፍም የክልሉ መንግስት #ከ5 ሚሊየን ብር በላይ መድቦ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታና መልሶ ማቋቋም ስራ እንዲሰራ በክልሉ ካቢኔ መመሪያ ወጥቶ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሀብት የማሰባሰብ ስራ መጀመሩንም አቶ ዘላለም ገልፀዋል፡፡
የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ አመራሮችና ሰራተኞች በችግሩ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ከጥቅምት ወር ደመወዛቸው የሚቆረጥ የደመወዛቸውን 10 በመቶ ድጋፍ አድርገዋል፡፡
በተመሳሳይም የክልሉ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ ሰራኞችም ከጥቅምት ወር ደመወዛቸዉ 4 በመቶ ድጋፍ አድርገዋል።
ይሁን እንጂ እየተደረገ ያለዉ ድጋፍ በቂ ባለመሆኑ መላዉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እና ለጋሽ አካላት የቻሉትን ድጋፍ ያደርጉ ዘንድ የሀብት ማሰባሰቢያ #የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000261313301 መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታዉቋል፡፡
ምንጭ ፦EBC
@yenetube @mycase27
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተጎዱ ዜጎችን መልሶ #ለማቋቋም የሀብት ማሰባሰብ ስራ ጀመረ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተከስቶ በነበረዉ ሁከትና ብጥብጥ የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳትና መልሶ ለማቋቋም የሀብት ማሰባሰብ ስራ መጀመሩን የክልሉ መንግስት አስታወቀ፡፡
የክልሉ መንግስት የብት ማሰባሰቢያ የባንክ ሂሳብ ቁጥርም ይፋ አደርጓል፡፡
የክልሉ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ #ዘላለም ጃለታ ለኢቢሲ እንደተናገሩት በክልሉ ባሳለፍነዉ የመስከረም ወር ተከስቶ በነበረዉ ሁከትና ብጥብጥ ቁጥራቸው ከ57 ሽህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች በከፋ ችግር ውስጥ ይገኛሉ፡፡
ይህን ችግር ለመቅረፍም የክልሉ መንግስት #ከ5 ሚሊየን ብር በላይ መድቦ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታና መልሶ ማቋቋም ስራ እንዲሰራ በክልሉ ካቢኔ መመሪያ ወጥቶ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሀብት የማሰባሰብ ስራ መጀመሩንም አቶ ዘላለም ገልፀዋል፡፡
የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ አመራሮችና ሰራተኞች በችግሩ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ከጥቅምት ወር ደመወዛቸው የሚቆረጥ የደመወዛቸውን 10 በመቶ ድጋፍ አድርገዋል፡፡
በተመሳሳይም የክልሉ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ ሰራኞችም ከጥቅምት ወር ደመወዛቸዉ 4 በመቶ ድጋፍ አድርገዋል።
ይሁን እንጂ እየተደረገ ያለዉ ድጋፍ በቂ ባለመሆኑ መላዉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እና ለጋሽ አካላት የቻሉትን ድጋፍ ያደርጉ ዘንድ የሀብት ማሰባሰቢያ #የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000261313301 መሆኑን የክልሉ መንግስት አስታዉቋል፡፡
ምንጭ ፦EBC
@yenetube @mycase27