ሕይወት ይቀጥላል !
ለሀገራችን ይበጃል ብለን በመረጥነው መንገድ እኔ እና ባልደረቦቼ በምንችለው ሁሉ ምርጫውን ለማሸነፍ ሌት ተቀን ደክመን ሠርተናል።
ለምርጫ የተመዘገበው ሕዝብ በካርዱ ያልተመዘገበው ደግሞ በዝምታው ምርጫውን አሳውቋል። ኢዜማ እንደ ፓርቲ ስለምርጫው ሂደት እና ውጤት ዝርዝር ማብራሪያ እንደሚሰጥ እና አቋም እንደሚይዝ ይጠበቃል።
መጪው ጊዜ የሕዝብን ምርጫ እና ውሳኔ በጸጋ ተቀብሎ ከአሸናፊው ጋር እንደ አገር ልጅ ተደጋግፎ የምንጓዝበት እንዲሆን እመኛለሁ። እስከዛሬ የሀሳብ ክርክር እና የምርጫ ፉክክር ስናደርግ ነበር። ከአሁን በኋላ ግን የተመረጠው እቅዱን ለማሳካት ያልተመረጥነው ደግሞ ለመጪው ጊዜ ለመዘጋጀት ዕድል አግኝተናል።
በምርጫ ስንወዳደር በሀገር ቤትም ሆነ ከሀገር ውጪም በሚያስፈልገን ሁሉ ለደገፋችሁን ምሥጋናችን ብዙ ነው። አሸናፊ ባያደርገንም ሃሳቦቻችንን ደግፋችሁ ድምጻችሁን የሰጣችሁን ኢትዮጵያውያንን ከልብ እናመሠግናለን። ሕይወት ግን እንደወትሮው ይቀጥላል።
#ኢትዮጵያ_እናመሰግናለን
#አዲስ_አበባ_እናመሰግናለን
አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን
@Yenetube @Fikerassefa
ለሀገራችን ይበጃል ብለን በመረጥነው መንገድ እኔ እና ባልደረቦቼ በምንችለው ሁሉ ምርጫውን ለማሸነፍ ሌት ተቀን ደክመን ሠርተናል።
ለምርጫ የተመዘገበው ሕዝብ በካርዱ ያልተመዘገበው ደግሞ በዝምታው ምርጫውን አሳውቋል። ኢዜማ እንደ ፓርቲ ስለምርጫው ሂደት እና ውጤት ዝርዝር ማብራሪያ እንደሚሰጥ እና አቋም እንደሚይዝ ይጠበቃል።
መጪው ጊዜ የሕዝብን ምርጫ እና ውሳኔ በጸጋ ተቀብሎ ከአሸናፊው ጋር እንደ አገር ልጅ ተደጋግፎ የምንጓዝበት እንዲሆን እመኛለሁ። እስከዛሬ የሀሳብ ክርክር እና የምርጫ ፉክክር ስናደርግ ነበር። ከአሁን በኋላ ግን የተመረጠው እቅዱን ለማሳካት ያልተመረጥነው ደግሞ ለመጪው ጊዜ ለመዘጋጀት ዕድል አግኝተናል።
በምርጫ ስንወዳደር በሀገር ቤትም ሆነ ከሀገር ውጪም በሚያስፈልገን ሁሉ ለደገፋችሁን ምሥጋናችን ብዙ ነው። አሸናፊ ባያደርገንም ሃሳቦቻችንን ደግፋችሁ ድምጻችሁን የሰጣችሁን ኢትዮጵያውያንን ከልብ እናመሠግናለን። ሕይወት ግን እንደወትሮው ይቀጥላል።
#ኢትዮጵያ_እናመሰግናለን
#አዲስ_አበባ_እናመሰግናለን
አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን
@Yenetube @Fikerassefa