በአዲስ አበባ ንግድ ቤቶች እና ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች ከዛሬ ጀምሮ እስከ ምሽት ሶስት ተኩል እና አራት ሰዓት አገልግሎት መስጠት አለባቸው ተባለ፡፡
በከተማዋ የኮሪደር ልማት በተሰራባቸው አካባቢዎች ሱቆች እና ሌላም የንግድ አገልግሎት ሰጭዎች እስከ ምሽት በራቸውን እንዳይዘጉ ወይም በራቸው ዝግ ከሆነ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት በራቸው ላይ እንዲያኖሩ የሚያስገድደው ደንብ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ ገብቷል ተብሏል፡፡
ይህን ያለው የከተማዋ ንግድ ቢሮ ነው፡፡
በመንገድ ዳር ያሉ #ንግድ_ቤቶች ፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እስከ ሶስት ሰዓት ተኩል የህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ ደግሞ እስከ 4 ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ ደንቡ ያስገድዳል፡፡
ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎችም እስከ ምሽት 4 ሰዓት ሲቆዩ ከተፈቀደው ታሪፍ በላይ ማስከፈል እንደማይችሉ በደንቡ ተደንግጓል፡፡
ይህም ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
በከተማዋ የኮሪደር ልማት በተሰራባቸው አካባቢዎች ሱቆች እና ሌላም የንግድ አገልግሎት ሰጭዎች እስከ ምሽት በራቸውን እንዳይዘጉ ወይም በራቸው ዝግ ከሆነ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት በራቸው ላይ እንዲያኖሩ የሚያስገድደው ደንብ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ ገብቷል ተብሏል፡፡
ይህን ያለው የከተማዋ ንግድ ቢሮ ነው፡፡
በመንገድ ዳር ያሉ #ንግድ_ቤቶች ፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እስከ ሶስት ሰዓት ተኩል የህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ ደግሞ እስከ 4 ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ ደንቡ ያስገድዳል፡፡
ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎችም እስከ ምሽት 4 ሰዓት ሲቆዩ ከተፈቀደው ታሪፍ በላይ ማስከፈል እንደማይችሉ በደንቡ ተደንግጓል፡፡
ይህም ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
👍56👎20😁10❤3