የኢትዮጵያ መድን ድርጅት አገልግሎቱን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በእጅ #በሞባይል የታገዘ የተለያዩ የኢንሹራንስ አገልግሎቶችን ለመስጠት ማቀዱን አስታወቀ።
የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ነጻነት ለሜሳ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት ድርጅቱ አገልግሎቶቹን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በአነስተኛና በጥቃቅን ሙያዎች ለተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች በሞባይል በመታገዝ የኢንሹራንስ አገልግሎቶችን ሊሰጥ ነው። እንደ መደበኛው የኢንሹራንስ አገልግሎት ቅርጫፍ እየከፈቱ አረቦን በአካል እየመጡ እንዲከፍሉ ማድረግ አዋጪና ቀልጣፋ ባለመሆኑ አገልግሎቶቹ በሞባይል በመታገዝ የሚሰጡ ይሆናል።
በሞባይል የታገዘ የኢንሹራንስ አገልግሎት ህብረተሰቡ ባለበት ቦታና አካባቢ ሆኖ አገልግሎቱን እንዲያገኝ የሚያስችለው መሆኑን አመልክተው አገልግሎቱን ለመጀመር የድርጅቱን የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማትና ሶፍት ዌር የማሻሻል ስራ እንደሚሰራና ለዚህም 450 ሚሊዮን ብር በጀት መያዙን ተናግረዋል።
@YeneTube @Fikerassefa
የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ነጻነት ለሜሳ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት ድርጅቱ አገልግሎቶቹን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በአነስተኛና በጥቃቅን ሙያዎች ለተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች በሞባይል በመታገዝ የኢንሹራንስ አገልግሎቶችን ሊሰጥ ነው። እንደ መደበኛው የኢንሹራንስ አገልግሎት ቅርጫፍ እየከፈቱ አረቦን በአካል እየመጡ እንዲከፍሉ ማድረግ አዋጪና ቀልጣፋ ባለመሆኑ አገልግሎቶቹ በሞባይል በመታገዝ የሚሰጡ ይሆናል።
በሞባይል የታገዘ የኢንሹራንስ አገልግሎት ህብረተሰቡ ባለበት ቦታና አካባቢ ሆኖ አገልግሎቱን እንዲያገኝ የሚያስችለው መሆኑን አመልክተው አገልግሎቱን ለመጀመር የድርጅቱን የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማትና ሶፍት ዌር የማሻሻል ስራ እንደሚሰራና ለዚህም 450 ሚሊዮን ብር በጀት መያዙን ተናግረዋል።
@YeneTube @Fikerassefa