አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት ሀገራት የሰብዓዊ ዕርዳታ እና ልማት አመራሮች በቀጣዩ ሳምንት በትግራዩ ጦርነት ላይ ሊመክሩ እንደሆነ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ የስብሰባው ዐላማ በትግራይ ባለው የሰብዓዊ ቀውስ እና ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዙሪያ የጋራ መግባባት ለመፍጠር እና በተመድ ማዕቀፍ ውስጥ በአስቸኳይ ሰብዓዊ ዕርዳታ ላይ ወሳኝ ርምጃዎች እንዲወሰዱ ለማድረግ ነው፡፡ የቡድን-7 ሀገሮችም በሰኔ ወር የመጀመሪያ ቀናት በኢትዮጵያው ቀውስ ላይ እንደሚመክሩ ተሰምቷል፡፡
አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት የልማት አጋሮች ዛሬ በአዲስ አበባ ባደረጉት ስብሰባ ለትግራይ ክልል ተረጅዎች 500 #ሚሊዮን_ዶላር እንደሚለግሱ አውሮፓ ኅብረት በትዊተር ገጹ አስታውቋል፡፡ በትግራይ ክልል ሁሉም ወገኖች ግጭት እንዲያቆሙ፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ ሥርጭትን እንዳያሰናክሉ እና ጋዜጠኞች በክልሉ ተንቀሳቅሰው እንዲዘግቡ እንዲፈቅዱ ሀገራቱ በስብሰባቸው በጋራ ጠይቀዋል፡፡ በክልሉ አስከፊ ርሃብ እንዳይከሰት መንግሥት አስቸኳይ ርምጃዎችን እንዲወስድም አሳስበዋል፡፡
[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት የልማት አጋሮች ዛሬ በአዲስ አበባ ባደረጉት ስብሰባ ለትግራይ ክልል ተረጅዎች 500 #ሚሊዮን_ዶላር እንደሚለግሱ አውሮፓ ኅብረት በትዊተር ገጹ አስታውቋል፡፡ በትግራይ ክልል ሁሉም ወገኖች ግጭት እንዲያቆሙ፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ ሥርጭትን እንዳያሰናክሉ እና ጋዜጠኞች በክልሉ ተንቀሳቅሰው እንዲዘግቡ እንዲፈቅዱ ሀገራቱ በስብሰባቸው በጋራ ጠይቀዋል፡፡ በክልሉ አስከፊ ርሃብ እንዳይከሰት መንግሥት አስቸኳይ ርምጃዎችን እንዲወስድም አሳስበዋል፡፡
[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa