YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
483 videos
79 files
3.85K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመረጃ ሳጥን (black box) #ሙሉ_መረጃው ሊያስገኝ በሚችል ደረጃ ላይ መሆኑን ምርመራውን ያከናወነው የፈረንሳዩ ቢ.ኢ.ኤ የአውሮፕላን አደጋ ምርመራ ኤጀንሲ ማስታወቁን የትራንስፖርት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት መረጃዎቹን መረከቡን የትራንስፖርት ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡

ዝርዝር ትንተናው በቅርቡ በአንድ ወር ውስጥ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም ተገልጿል፡፡ ከመረጃ ሳጥኑ የሚገኙ መረጃዎች በቅርቡ ለ157 ሰዎች ህይወት ማጣት ምክንያት ለሆነው የቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን መከስከስ ምክንያት ፍንጭ እንደሚጠቁም የሮይተርስ ዘገባ ያስረዳል፡፡

ምንጭ:- ETV
@YeneTube @FikerAssefa