YeneTube
116K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.92K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
2😁1
ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ!

ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው ብሏል፡፡ 

በዚህም ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት መወሰኑን አስታውቋል፡፡በማሻሻያው ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4 ሺህ 760 ወደ ብር 6 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ነው ያለው።

ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21 ሺህ 492 ወደ ብር 39 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ብሏል።የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6 ሺህ 940 ወደ ብር 11 ሺህ 500 የሚሻሻል መሆኑን ገልጿል።

ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ እንደሚደረግበት አስታውቋል።ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል ያለው ኮሚሽኑ፤ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል ብሏል።

@YeneTube @FikerAssefa
👍3938😁10😭2
ንግድ ባንክ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ብቻ ከአንድ ሺ በላይ ለሚሆኑ ደንበኞቹ 541 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጪ ምንዛሪ ክፍያ ፈጽሚያለሁ አለ!

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ብቻ አንድ ሺ 140 ለሚሆኑ ደንበኞቹ 541 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጪ ምንዛሪ ክፍያ ፈጽሚያለሁ ሲል ገለጸ።

ከሐምሌ 22 እስከ ነሃሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም ባሉት ቀናት በአጠቃላይ ለባንኩ አንድ ሺ 140 ደንበኞች 541 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ተመጣጣኝ የውጭ ምንዛሪ ፈቅጃለሁ ሲል በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ባጋራው መረጃ አስታውቋል።

በአንድ ቀን ብቻ ማለትም ነሐሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም ለባንኩ የቀረቡ የውጭ ምንዛሪ የደንበኞች ማመልከቻዎችን ሁሉንም ማጽደቁን የጠቆመው ባንኩ በዚህም የ420 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸውን የተለያዩ የውጭ ምንዛሪ ዓይነቶች ለተለያዩ ፍላጎቶች መፍቀዱን አመላክቷል።

ባንኩ ከሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለገቢ ንግድና ለአገልግሎት ክፍያዎች በአጠቃላይ ከአንድ ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ክፍያ መፈጸሙንም አስታውቋል።

ይህም የተሰጠው የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ ከነዳጅ፣ ማዳበሪያ እና ሌሎች የአገልግሎት ክፍያዎች ጋር በተያያዘ በየቀኑ ከሚሰጠው መደበኛ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት በተጨማሪ የተሰጠ መሆኑን ጠቁሟል።

Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
26😁14
ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ መሐመድ እና ዮናስ አማረ ያሉበትን ሁኔታ መንግስት በግልፅ እንዲያሳውቅ ኢዜማ እና የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር ጠየቁ!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር፤ ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ መሐመድ እና ጋዜጠኛ ዮናስ አማረ “ከሕግ አግባብ ውጪ መሰወራቸውን” በመግለጽ ያሉበትን ሁኔታ መንግስት በግልፅ እንዲያሳውቅ በተናጥል ባወጡት መግለጫ ጠየቁ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበርም በበኩሉ ትናንት ባወጣው መግለጫ "ጋዜጠኞቹ በወንጀል ተጠርጥረው ቢሆን እንኳን በሕግ አግባብ ተይዘው በ48 ሰዓት ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው፣ ያሉበት አለመታወቁ በእጅገ ያሳስበናል" ብሏል።

ኢዜማ በበኩሉ፤ "በመንግሥት በኩልም በተደጋጋሚ ያለአግባብ ያሠርኩት ጋዜጠኛም ሆነ ዜጋ የለም የሚል ምላሽ ሲሰጥም ተመልክተናል" ሲል ጠቅሶ፣ “መንግሥት ድርጊቱን እየፈፀመ እየደበቀው ወይም ከመንግሥት እውቅና ውጪ በሌሎች የተደራጁ አካላት እየተፈፀመ መሆኑን የሚያሳይ ነው” ብሏል።

@YeneTube @FikerAssefa
31👀4👍3
በምዕራብ ትግራይ ወደ ቀያቸው በተመለሱ ተፈናቃዮች ላይ የመንግስት ወታደሮች ተሳታፊ የሆኑበት ግድያ እና አፈና እየተበራከተ ይገኛል ሰል ህወሓት አስታወቀ!

ወደ ቀያቸው በተመለሱ የምዕራብ ትግራይ ጸለምት ወረዳ ተፈናቃዮች ላይ “የኢትዮጵያ መንግስት ሰራዊት ተሳታፊ የሆነበት ግድያ እና እገታ እየተበራከተ ነው” ሲል ህወሓት ከሰሰ።

በምርጫ ቦርድ ምንም አይነት ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ እግድ የተላለፈበት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ነሃሴ 9 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው ሳምንታዊ መግለጫው፤ "የኢትዮጵያ መንግስት ከለላ እሰጣችኋለሁ ብሎ እንዲመለሱ ባደረጋቸው የጸለምት ነዋሪዎችን ሊከላከልላቸው አልቻለም" ሲል ተችቷል፤ “ከሌሎች ታጣቂዎች ሊከላከልላቸው ይቅር እና እራሱ ተሳታፊ ሆኗል” ሲል ገልጿል።

“በኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮች ባሳለፍነው ሳምንት በማይጸብሪ የተፈጸመው ግድያ የቅርብ ማሳያ ነው” ሲል በመግለጫው አመላክቷል።

@YeneTube @FikerAssefa
22😭9👎5👀2👍1😁1
Forwarded from Nati Getnet
ናቲ  ስፒች ላንጉጅ ቴራፒ ኪሊኒክ
Nati Speech language therapy clinic

ከእርስዎ ወይም ከቤተሰብዎ ከንግግር ጋር በተያያዘ ችግር ያለበት ሰው ያውቃሉ?

እንግዲያውስ ናቲ የንግግር የቋንቋ ሕክምና እና ማማከር ክሊኒክ ለእርስዎ የሚሆን መፍትሔ ይዞልዎት መጥቷል ከንግግር ከቋንቋ እንዲሁም ከተግባቦት ጋር በተያያዘ ህክምና ወይም ስልጠና ከፈለጉ ወደ ናቲ የንግግርና የቋንቋ ሕክምና እና ማማከር ክሊኒክ ይምጡ ወይንም ይደውሉ እፎይ የሚሉበትን ምላሽ ያገኛሉ

“አለመናገር ጨዋነት አይደለም እክል እንጂ”

👉አድራሻ፡ መገናኛ ሾላ አባይ ባንክ የካ ሚካኤል ቅርንጫፍ ያለበት ህንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 205
ከመምጣትዎ በፊት ደውለው ቀጠሮ ያስይዙ

☎️ስልክ፡- 09- 08- 78- 26 -52  


  👉በተጨማሪም በነዚህ አማራጮች ያገኙናል
👉የቴሌግራም ገጽ ፡- https://tttttt.me/Nslt19

 👉የቲክቶክ ገጽ፡-https://vm.tiktok.com/ZM69FtgrR/
👉  የፌስቡክ ገጽ፡-https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
👉በ YouTube ገፅ:-https://youtube.com/@natigetnet1989?si=_81wKG_5Ev45AZvY

👂👂በነፃ

የከንፈር እና የላንቃ መሰንጠቅ ህክምና  በየትኛውም ክልል ለሚኖሩ በነፃ
7
በአዲስ አበባ ቢንጎ ማጫወቻ ቤቶች እየታሸጉ መሆኑ ተነገረ

በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የቢንጎ ማጫወቻ ቤቶች፣ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ እየታሸጉ መሆኑ ተገልጿል። በተለይም በወጣቶች ዘንድ ተወዳጅ የሆኑ እነዚህ ቤቶች ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ፣ በስፋት እየተስተዋለ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።

ይህ መታሸግ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች እየተስተዋለ ቢሆንም፣ በተለይም በአቃቂ ቃሊቲ አካባቢ የሚገኙ በርካታ የቢንጎ ቤቶች በዛሬው ዕለት መታሸጋቸው ካፒታል ተመልክቷል።

አንዳንድ የጨዋታ ቤቶቹ ባለቤቶች እንደተናገሩት፣ መታሸጉ የተፈጸመው “አዋኪ ድርጊት” ፈጽመዋል በሚል ምክንያት ነው። በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እነዚህ አጫዋቾች፣ እርምጃው ቀጣይነት እንደሚኖረው እንደተነገራቸው ገልጸዋል።

ምንም እንኳ እነዚህ ቤቶች ዋነኛ ተግባራቸው የቢንጎ ጨዋታ ማቅረብ ቢሆንም፣ ከጨዋታው በተጨማሪ የጫት መጠቀሚያ እና ለህገወጥ ወንጀሎች መነሻ ቦታዎች እንደሆኑ እና ይህንንም መንግስት ለማስቆም በሚል እርምጃውን እየወሰደ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።

በተለይ በአዲስ አበባ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በስፖርት ውድድር ላይ የሚደረጉ የውርርድ (ቤቲንግ) ጨዋታዎችን ከማሸግ ጀምሮ የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ እንዲገኝ የሚታወቅ ሲሆን አሁን የቢንጎ ቤቶች መታሸግ ከዚህ ጋር ግንኙነት ያለው ስለመሆኑ ግን እስካሁን በይፋ የተረጋገጠ ነገር የለም።
44👍13👎3
ሀገራችን ኢትዮጵያ የራሷን ጦርነት ሳትቋጭ የፕሮክሲ ጦርነት ላይ እየተሳተፈች ትገኛለች።

የሱዳን እርስ በእርስ ጦርነት ስንት ሀገሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ ?

https://youtu.be/rs3JTbs89vg
13😁12👍1
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
3
YeneTube
Photo
ለዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች እየቀረበ ያለዉ ሀይል ተፅዕኖ እያሳደረበት እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልገሎት ገለፀ

ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልገሎት  ወደ ሶስት ያህል ለሆኑ የዳታ ሴንተሮች ሀይል እያቀረበ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢ/ር ጌቱ ገረመዉ ተናግረዋል።

አገልግሎቱ ለእነዚህ የዳታ ሴንተሮች ከ 10 እስከ 20 ሜጋ ዋት ሀይል እየወሰዱ እንደሚገኝ ተቋሙ የተጠናቀቀው በጀት አመት የስራ አፈፃፀም እና የ2018 አመት እቅዶቹ ዙሪያ ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ስራ አስፈፃሚዉ ይህንን የገለፁት።
የዳታ ማይኒንግ ዘርፍ ላይ ለሚገኙ ድርጅቶች ከፍተኛዉን ሀይል እያቀረበ የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል መሆኑን የገለፁት ኢ/ር ጌቱ ገረመዉ  ለድርጅቶቹ የሚቀርበዉ ሀይል ከፍተኛ መሆን በአገልግሎቱ ፍላጎት ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል ብለዋል።

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሪፖርት እንደተገለፀዉ ከሆነ በተጠናቀቀው በጀት አመት አገልግሎቱ 16 ሺህ 2 መቶ 43 ጌጋ ዋት ሀይል ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በጅምላ መግዛቱን ያሳያል።

ይህ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም የሀይል ፍላጎቱ 18.2 በመቶ ከፍ ማለቱን ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ሰምተናል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢ/ር ጌቱ ገረመዉ መንግስት በዳታ ማይኒግ ዘርፍ ለሚሰማሩ ድርጅቶች በቀጣይ የሚሰጠዉ ፍቃድ አለመኖሩን አስታዉሰዉ።
ሆኖም በአገልግሎቱ ላይ ለድርጅቶቹ እየቀረበ የሚገኘዉ ሀይል ተፅዕኖ መኖር በግልፅ የሚታይ ነዉ ሲሉ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በበኩሉ በበጀት አመቱ ከዚህ ዘርፍ የመጣው ገንዘብ በተቋሙ አጠቃላይ ገቢ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የያዘ መሆኑን ይገልፃል።

ለመደበኛ ተጠቃሚዎች የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸጥ ከተገኘው ገቢም የሚበልጥ መሆኑን ገልፆል።

ነገር ግን  ከአሁን በኋላ ለአዲስ የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ፈቃድ እንደማይሰጥ እና ያሉትም  በሂደት እንዲወጡ የመግፋት ፍላጎት እንዳለው ይፋ አድርጓል።

@Yenetube @FikerAssefa
13😁8👍7👎1👀1
የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ እንዲቀጥል ተወስኗል - የገንዘብ ሚኒስቴር

የገንዘብ ሚኒስቴር በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ማሻሻያ መሰረት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ እንዲቀጥል ተወስኗል አለ፡፡

ነባሩ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ከምጣኔ ውጭ ሌሎች ማሻሻያዎችን በማካተት ከ3 አስርት ዓመታት በኋላ ተሻሽሎ በ2017 በጀት አመት ስራ ላይ መዋሉን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡

የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ከነበረው ከ12 በመቶ በላይ ድርሻ በየዓመቱ በተከታታይ እየቀነሰ ከ7 በመቶ በታች መድረሱን ጠቅሶ፥ ከዚህ ጠቅላላ ቅናሽ 44 በመቶው የተጨማሪ እሴት ታክስ ድርሻ እንደሆነ አመልክቷል፡፡

የተጨማሪ እሴት ታክስ ህጉን አሁን ካለው የኢኮኖሚ ሁኔታ የቀጣይ ዓመታት ለውጦች ጋር እንዲጣጣም በማድረግ በመካከለኛ ዘመን የገቢ ስትራቴጂው መሰረት ተሻሽሎ በ2017 በጀት ዓመት ስራ ላይ እንዲውል ተደርጓል ብሏል፡፡

በማሻሻያው መሰረት በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ማሻሻያ መሰረት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ እንዲቀጥል መወሰኑን ነው የገንዘብ ሚኒስቴር ያስታወቀው፡፡

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
18👍9😁2
4 ቢሊየን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል ሲል የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን አስታወቀ!

ኮሚሽኑ በተቋሙ ታሪክ ትልቁ ቁጥር ያለው የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን ገልጿል፡፡ኮሚሸኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ በ2017 በጀት አመት 4 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል ይህም ካለፈው አመት ጋርሲነጻጸር የ2.2 በመቶ እድገት አሳይቷል።

በበጀት አመቱ ለ 525 አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች ፈቃዶች እና 19 የማስፋፊያ ፈቃዶች መሰጠቱን ጠቁሞ አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከወሰዱት ውስጥ የውጭ ባለሃብቶች 308፣ 109 ለጣምራ ኢንቨስትመንት እና ከ98 በላይ ደግሞ ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ሊሰጥ ችሏል። ይህም በተቋሙ ታሪክ ትልቁ ቁጥር ሆኖ መመዝገቡን አስታውቋል።

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ ባሉ ኢንቨስትመንቶች 123 ሚሊዮን ዶላር ከወጪ ንግድ ገቢ ያስገኙ ሲሆን ከዞኖቹ ውጪ ባሉ ኢንቨስትመንቶች 543.11 ሚሊዮን ዶላር ተገኝቷል።ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው በ2017 በጀት አመት ከ1 ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያወጡ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ በሚመረቱ ምርቶች በመተካት ስኬት እንዳስመዘገበ ገልጿል።

@YeneTube @FikerAssefa
16😁12🔥2👎1
YeneTube
Photo
ወደ ሶማሊያ ሲጓዝ በፑንትላንድ ሀይሎች ተይዞ የነበረውና የተለቀቀው የጦር መሳሪያ የጫነ መርከብ አቅጣጫውን ወደ ጅቡቲ ቀይሮ መጓዙ ተነገረ!

“ሲ ወርልድ” የተሰኘው መርከብ በቅርቡ የጦር መሳሪያ ጭኖ ከቱርክ፥ ኢዝሚር ግዛት ወደ ሶማሊያ ሲጓዝ፥ በሶማሊያ ሰሜናዊ ግዛት በፑንትላንድ ሀይሎች ተይዞ ከተለቀቀ በኋላ፥ አቅጣጫውን በመቀየር ወደ ጅቡቲ መጓዙን ከስፍራው የወጡ ዘገባዎች አመላከቱ። የመጀመሪያ መድረሻው ሞቃዲሾ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን በአቅራቢያው ወደምትገኘው ጅቡቲ አቅጣጫውን ቀይሯል።

የጭነት መርከቡ በፑንትላንድ የባህር ኃይል ፖሊስ (PMPF) ተይዞ መክረሙ ከሰሞኑ ሲዘገብ ቆይቷል። መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ መርከቡ የጦር መሳሪያ እገዳ ከጥቂት አመታት በፊት የተነሳላት የሶማሊያን ዋና ከተማ ሞቃዲሾ አቅጣጫ አድርጎ እየተጓዘ ነበር።

በወቅቱ የወጡ ተጨማሪ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት፣ የጦር መሳሪያው በሶማሊያ “TURKSOM” በመባል በሚታወቀው ወታደራዊ ካምፕ የሚውል ነው። “TURKSOM” የሶማሊያና ቱርክ ጥምር ወታደራዊ ማሰልጠኛ በአል-ሻባብ ላይ በሚደረገው ውጊያ ለሚሰለጠኑት የ “ጎርጎር” ወታደሮች ማሰልጠኛ ስፍራ እንደሆነ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ፣ በርካታ በሱማሊያ የሚሰራጬ ዘገባዎች፣ መርከቡ በወቅቱ ግልፅ ባልሆነ ምክንያት ሞቃዲሾን ትቶ አቅጣጫውን ወደ ጅቡቲ መቀየሩን ጠቁመዋል።
ሞቃዲሾም ሆነ አንካራ እስካሁን ባለው ሁኔታ ላይ ምንም አይነት መግለጫ አልሰጡም።

ከሶስት ሳምንታት በፊት የፑንትላንድ የባህር ኃይል ፖሊስ በኮሞሮስ ባንዲራ ስር ይጓዝ የነበረውን ይህን  “ሲ ወርልድ” የተባለ የጭነት መርከብ ከቱርክ የተላከ ወታደራዊ መሳሪያ ጭኖ ለሶማሊያ ጦር (SNA) ለማድረስ በሚል ሲጓዝ በቦሳሶ ወደብ ነበር የተያዘው ።

በፑንትላንድ ባለስልጣናት መግለጫ መሰረት፣ የቱርክ አምባሳደር ወደ ሶማሊያ ባደረጉት ጉብኝት፣ በመርከቡ ላይ ያለው የጦር መሳሪያ፣ የቱርክ መንግስት ንብረት መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ካቀረቡ በኋላ የፑንትላንድ ባለስልጣናት መርከቡን ለመልቀቅ ወስነዋል።ነገር ግን፥ ትላንት የወጣው የጋሮዌ ዘገባ መርከቡ ለምን ወደ ጅቡቲ እንዳቀና አልገለጸም።

Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
25👍1
ሂልተንን ጨምሮ አራት ሆቴሎች 564 ሚሊዮን ብር ትርፍ አስመዘገቡ!

ሂልተን ሆቴልን ጨምሮ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስር የሚተዳደሩ አራት የቱሪዝም ዘርፍ ድርጅቶች፣ በ2017 የበጀት ዓመት ከታክስ በፊት 564.2 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘታቸው ተገለጸ። ይህ ውጤት ከታቀደው የትርፍ ግብ በ37 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ባደረገዉ የስራ አፈጻጸም ግምገማ ፣ የስፓ አገልግሎት ኢንተርፕራይዝ (ፍል ዉሃ)፣ የጊዮን ሆቴሎች ኢንተርፕራይዝ፣ ሂልተን ሆቴል እና የገነት ሆቴልን ያካተተውን የሆቴል ዘርፍ አፈጻጸም ላይ ትኩረት አድርጓል።

ድርጅቶቹ በድምሩ 2.1 ቢሊዮን ብር ገቢ በማሰባሰብ ከታለመው 114 በመቶ ማሳካት ችለዋል የተባለ ሲሆን አሁን ላይ እያደገ የመጣውን የገበያ ፍላጎት እና የቱሪስቶች ፍሰት በመጠቀም ንግዳቸውን እንዲያሰፉ አሳስቧል።

ለዘላቂ እድገት ሲባልም የደንበኞችን እርካታ ማሻሻል፣ ዘመናዊ የግብይት ስልቶችን መጠቀም፣ እንዲሁም ዲጂታል አገልግሎትና የቦታ ማስያዣ ስርዓቶችን ማዘመን እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ተሰጥቷል።

Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
14😁5👍3👎3🔥1
ብሔራዊ ቲያትር የቲኬት ዋጋን ወደ 200 ብር አሳደገ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር የመግቢያ ትኬት ዋጋን ከ ስምንት ዓመት በፊት ከነበረበት 80 ብር ወደ 200 ብር ማሳደጉን አስታውቋል። ቲያትሩ ከ1948 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ ኪነጥበብ ከፍ ማለት እና መከበር አለበት በሚል ዋጋዉን ለማሻሻል ጥናት ሲደረግ መቆየቱ ተገልጿል።

ይህ ውሳኔ የኪነጥበብን ደረጃ ከፍ ለማድረግ እና የቲያትር ቤቱን አገልግሎት ለማሻሻል ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።የቲያትር ቤቱ ኃላፊዎች፣ የቲኬት ዋጋው ከዚህ ቀደም በጣም ዝቅተኛ ስለነበር፣ አሁን የተደረገው ጭማሪ ሳይሆን 'ማሻሻያ' ነው ሲሉ አብራርተዋል። የዋጋ ማሻሻያው "ማንንም የማይጎዳ መልኩ" መሆኑን በማስረገጥ፣ የቲኬት ዋጋው ለሁሉም ትያትሮች በ200 ብር መወሰኑን ገልጸዋል።

ኦንላይን ትኬት ሽያጭ እና ሌሎች ለውጦች
ከተመሠረተ 70 ዓመታትን ያስቆጠረው ብሔራዊ ቲያትር፣ አዳዲስ ለውጦችን በማምጣት ተመልካቹን ለማርካት መዘጋጀቱን አስታውቋል።ከለውጦቹ መካከል ተመልካቾች ከየቤታቸው ሆነው ትኬት መግዛት የሚያስችላቸውን 'ኦንላይን' የቲኬት ሽያጭ ሥርዓት ማመቻቸቱ ተገልጿል።

በተጨማሪም፣ የቲያትር ቤቱ ኃላፊዎች በቀጣይ ሁሉም ክልሎች የሚሳተፉበት ሥልጠና በብሔራዊ ቲያትር እንደሚሰጥ አስታውቀዋል። ይህ የዋጋ ማሻሻያ እና ሌሎች ተያያዥ ለውጦች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማምጣት እና ዘመናዊ አገልግሎቶችን ለመስጠት እንደሚያግዝ ይጠበቃል።

@YeneTube @FikerAssefa
40👎9😁3👍1