Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
❤2
Forwarded from YeneTube
በ 25% ዲስካውንት ለገበያ አቅርበናል!
📌 ፒያሳ ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት
👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
✅ መገልገያዎች
👉 ሦስት ሊፍት
👉 ባለ 3 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ ቦታ
👉 ቴራስ
👉 ያልተገደበ የውሃ አቅርቦት
👉 የመጠባበቂያ ጀነሬተር
📌 የካሬ አማራጮች
👉ባለ 1መኝታ - 63 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 86 እስከ 103 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 132 እስከ 146 ካሬ
👉1 መኝታ 63ካሬ=
10% ቅድመ ክፍያ 693,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
👉2መኝታ 86 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 946,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 9,460,000 ብር
👉3መኝታ 114 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 1,219,800 ብር
ሙሉ ክፍያ 12,198,000 ብር
ለበለጠ መረጃ
☎️ +251976195835
Telegram username
@Ruthtemersales
What's app
https://wa.me/251976195835
TEMER PROPERTIES
Create | Construct | Deliver
#TemerProperties #Temerrealestate
📌 ፒያሳ ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት
👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
✅ መገልገያዎች
👉 ሦስት ሊፍት
👉 ባለ 3 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ ቦታ
👉 ቴራስ
👉 ያልተገደበ የውሃ አቅርቦት
👉 የመጠባበቂያ ጀነሬተር
📌 የካሬ አማራጮች
👉ባለ 1መኝታ - 63 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 86 እስከ 103 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 132 እስከ 146 ካሬ
👉1 መኝታ 63ካሬ=
10% ቅድመ ክፍያ 693,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
👉2መኝታ 86 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 946,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 9,460,000 ብር
👉3መኝታ 114 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 1,219,800 ብር
ሙሉ ክፍያ 12,198,000 ብር
ለበለጠ መረጃ
☎️ +251976195835
Telegram username
@Ruthtemersales
What's app
https://wa.me/251976195835
TEMER PROPERTIES
Create | Construct | Deliver
#TemerProperties #Temerrealestate
❤1
Forwarded from ALX Ethiopia
🚀 Want to become a Virtual Assistant? Join our live Telegram session to learn about the programme, how to apply, and get your questions answered!
Don’t miss it - happening this Saturday, 3 ነሐሴ 2017 (August 9, 2025) starting at 11፡00 (5:00 PM) in our Telegram group
👉🏾 t.me/virtualassistantapplicationguide
#ALXEthiopia #ALXAfrica #ALXTribe #AIwithALX #VirtualAssistant
Don’t miss it - happening this Saturday, 3 ነሐሴ 2017 (August 9, 2025) starting at 11፡00 (5:00 PM) in our Telegram group
👉🏾 t.me/virtualassistantapplicationguide
#ALXEthiopia #ALXAfrica #ALXTribe #AIwithALX #VirtualAssistant
YeneTube
ከናይሮቢ አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ! ከኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ በአውቶብስ ተጓዦችን ማመላለስ መጀመሩን 'አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች' የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት አስታወቀ።ድርጅቱ ባለፈው ሳምንት እሁድ በይፋ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን 'አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች' ዳይሬክተር ሚካኤል ጄምስ ማቺዮ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በአንድ ጉዞ 7 ሺህ…
"ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እውቅና ውጪ ነው"
ቢቢሲ አማርኛ፤ "ከናይሮቢ - አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት ተጀመረ" በሚል ያሰራጨው ዘገባ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እውቅና ውጪ ነው።
ቢቢሲ አማርኛ በድረገጹ፣ "አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች' የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት፣ ከኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ በአውቶብስ ተጓዦችን ማመላለስ መጀመሩን አስታወቀ" ሲል ዘግቦ፣ ይህንን መረጃ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ህጋዊነቱን ሳያረጋግጡ ሌሎችም ሚዲያዎች አሰራጭተዋል።
ሆኖም ይህንን ጉዳይ በሀገሪቱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ጉዳዮች ላይ በአዋጅ ሀላፊነት የተሰጠው ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን የማያውቀው መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን ።
እንደ ሀገር በ2018 በጀት አመት በሁለቱ ሀገራት መካከል ትስስር ለመፍጠር፣ ይህንን አገልግሎት ለመጀመር እቅድ የተያዘ ቢሆንም፣ ሂደቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል የትብብር ስምምነት መፈራረም፣ ታሪፍ በጋራ መወሰንና ሌሎች የዲፕሎማሲ ጉዳዮች የሚፈልግ በመሆኑ ከሚመለከተው መንግስታዊ መስሪያ ቤት ጋር በመተባበር የሚሰራበት መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር!
ቢቢሲ አማርኛ፤ "ከናይሮቢ - አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት ተጀመረ" በሚል ያሰራጨው ዘገባ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እውቅና ውጪ ነው።
ቢቢሲ አማርኛ በድረገጹ፣ "አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች' የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት፣ ከኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ በአውቶብስ ተጓዦችን ማመላለስ መጀመሩን አስታወቀ" ሲል ዘግቦ፣ ይህንን መረጃ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ህጋዊነቱን ሳያረጋግጡ ሌሎችም ሚዲያዎች አሰራጭተዋል።
ሆኖም ይህንን ጉዳይ በሀገሪቱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ጉዳዮች ላይ በአዋጅ ሀላፊነት የተሰጠው ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን የማያውቀው መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን ።
እንደ ሀገር በ2018 በጀት አመት በሁለቱ ሀገራት መካከል ትስስር ለመፍጠር፣ ይህንን አገልግሎት ለመጀመር እቅድ የተያዘ ቢሆንም፣ ሂደቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል የትብብር ስምምነት መፈራረም፣ ታሪፍ በጋራ መወሰንና ሌሎች የዲፕሎማሲ ጉዳዮች የሚፈልግ በመሆኑ ከሚመለከተው መንግስታዊ መስሪያ ቤት ጋር በመተባበር የሚሰራበት መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር!
😁8❤6
ልዩ መረጃ
የሱዳን ጦር በሱዳን ዳርፉር በኒያላ አየር ማረፊያ ሲያርፍ የነበረ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አይሮፕላን ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ተሰማ።
የሱዳን ጦር የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አውሮፕላን በዳርፉር ግዛት ስትራቴጅካዊቷ ኒያላ ከተማ ሲያርፍ ኢላማ አድርጓል ሲል የሱዳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።
አውሮፕላኑ የኮሎምቢያ ቅጠረኛ ተዋጊዎችን ይዞ እንደነበር እና ሲያርፍ በትናንትናው ዕለት August 6/2025 በሱዳን ጦር ጥቃት እንደደረሰበት ዘገባው ጠቅሷል። በጥቃቱ ከ40 በላይ የኮሎምቢያ ቅጥረኛ ወታደሮች/Colombian mercenaries/ መሞታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
ኒያላ አየር ማረፊያ በጄኔራል ሀምዳን ደጋሎ በሚመራው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ቁጥጥር ስር ይገኛል።
የሱዳን ጦር አረብ ኢምሬትስ ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ድጋፍ ታደርጋለች ብሎ ያምናል።
አዩ ዘሀበሻ
@Yenetube @Fikerassefa
የሱዳን ጦር በሱዳን ዳርፉር በኒያላ አየር ማረፊያ ሲያርፍ የነበረ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አይሮፕላን ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ተሰማ።
የሱዳን ጦር የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አውሮፕላን በዳርፉር ግዛት ስትራቴጅካዊቷ ኒያላ ከተማ ሲያርፍ ኢላማ አድርጓል ሲል የሱዳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።
አውሮፕላኑ የኮሎምቢያ ቅጠረኛ ተዋጊዎችን ይዞ እንደነበር እና ሲያርፍ በትናንትናው ዕለት August 6/2025 በሱዳን ጦር ጥቃት እንደደረሰበት ዘገባው ጠቅሷል። በጥቃቱ ከ40 በላይ የኮሎምቢያ ቅጥረኛ ወታደሮች/Colombian mercenaries/ መሞታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
ኒያላ አየር ማረፊያ በጄኔራል ሀምዳን ደጋሎ በሚመራው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ቁጥጥር ስር ይገኛል።
የሱዳን ጦር አረብ ኢምሬትስ ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ድጋፍ ታደርጋለች ብሎ ያምናል።
አዩ ዘሀበሻ
@Yenetube @Fikerassefa
❤23👍6🔥1
የኢትዮጵያ ጦር ለሶማሊያ ወታደሮች ሰጠ የተባለው ማስጠንቀቂያ ምንድን ነው?
በሶማሊያ ጌዶ ክልል የሚገኘው የኢትዮጵያ ሠራዊት የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ወታደሮች በቅርቡ ከያዙት የድንበር ከተማ፣ በለድ ሀዋ በሦስት ቀን ውስጥ ለቅቀው እንዲወጡ ለአገር ሽማግሌዎች መናገራቸው ተገለፀ።
ከተማዋ በለድ ሀዋ ቁልፍ የሶማሊያ የድንበር ከተማ ስትሆን ኢትዮጵያን እና ኬንያን የምታዋስን እና የኢትዮጵያ ሠራዊት የሚገኝባት ነች።
ባለፉት ሳምንታት የሶማሊያ የከፊል ራስ ገዝ ክልል ጁባላንድ ታጣቂዎች እና የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ወታደሮች በአካባቢው ውጊያ አካሂደው፣ የሶማሊያ መንግሥት ባለፈው ቅዳሜ ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም. ከተማዋን በቁጥጥሩ ስር አውሏል።
ከፍተኛ የኢትዮጵያ ወታደራዊ መኮንኖች ከሶማሊያ የጎሳ መሪዎች ጋር በዶሎ ከተማ መነጋገራቸውን እና የሶማሊያ ፌደራል መንግሥቱ ወታደሮች ከበለድ ሀዋ በሦስት ቀን ውስጥ ለቅቀው እንዲወጡ ማዘዛቸውን የአገር ሽማግሌዎች ለቢቢሲ ሶማሊኛ ተናግረዋል።
በሶማሊያ የፌደራል መንግሥት የጌዶ አስተዳዳሪ የሆኑት አብዱላሂ አብዲ ጃማ (ሺምቢር) በዶሎ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሠራዊት በበለድ ሀዋ የሚገኘውን የሶማሊያ መንግሥት ኃይል በሦስት ቀናት ውስጥ ለቅቆ እንዲወጣ በአገር ሽማግሌዎች እንደተነገራቸው ገልፀዋል።
የጌዶ አስተዳዳሪ አብዱላሂ አብዲ ጃማ (ሺምቢር) ከፌደራል መንግሥቱ ጋር በጥምረት የሚሠራ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ ሠራዊት በኩል ተላለፈ በተባለው ትዕዛዝ ምክንያት ከበለድ ሀዋ የሚወጣ የፌደራል ጦር የለም ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
👇👇
https://www.bbc.com/amharic/articles/c5y3edzy2zyo
@YeneTube @FikerAssefa
በሶማሊያ ጌዶ ክልል የሚገኘው የኢትዮጵያ ሠራዊት የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ወታደሮች በቅርቡ ከያዙት የድንበር ከተማ፣ በለድ ሀዋ በሦስት ቀን ውስጥ ለቅቀው እንዲወጡ ለአገር ሽማግሌዎች መናገራቸው ተገለፀ።
ከተማዋ በለድ ሀዋ ቁልፍ የሶማሊያ የድንበር ከተማ ስትሆን ኢትዮጵያን እና ኬንያን የምታዋስን እና የኢትዮጵያ ሠራዊት የሚገኝባት ነች።
ባለፉት ሳምንታት የሶማሊያ የከፊል ራስ ገዝ ክልል ጁባላንድ ታጣቂዎች እና የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት ወታደሮች በአካባቢው ውጊያ አካሂደው፣ የሶማሊያ መንግሥት ባለፈው ቅዳሜ ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም. ከተማዋን በቁጥጥሩ ስር አውሏል።
ከፍተኛ የኢትዮጵያ ወታደራዊ መኮንኖች ከሶማሊያ የጎሳ መሪዎች ጋር በዶሎ ከተማ መነጋገራቸውን እና የሶማሊያ ፌደራል መንግሥቱ ወታደሮች ከበለድ ሀዋ በሦስት ቀን ውስጥ ለቅቀው እንዲወጡ ማዘዛቸውን የአገር ሽማግሌዎች ለቢቢሲ ሶማሊኛ ተናግረዋል።
በሶማሊያ የፌደራል መንግሥት የጌዶ አስተዳዳሪ የሆኑት አብዱላሂ አብዲ ጃማ (ሺምቢር) በዶሎ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሠራዊት በበለድ ሀዋ የሚገኘውን የሶማሊያ መንግሥት ኃይል በሦስት ቀናት ውስጥ ለቅቆ እንዲወጣ በአገር ሽማግሌዎች እንደተነገራቸው ገልፀዋል።
የጌዶ አስተዳዳሪ አብዱላሂ አብዲ ጃማ (ሺምቢር) ከፌደራል መንግሥቱ ጋር በጥምረት የሚሠራ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ ሠራዊት በኩል ተላለፈ በተባለው ትዕዛዝ ምክንያት ከበለድ ሀዋ የሚወጣ የፌደራል ጦር የለም ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
👇👇
https://www.bbc.com/amharic/articles/c5y3edzy2zyo
@YeneTube @FikerAssefa
1❤20😁4👍1
YeneTube
Photo
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ካመነጨሁት ሀይል 33.2 በመቶው የተገኘው ከህዳሴ ግድቡ ነው አለ።
በበጀት ዓመቱ ከተገኘው ሀይል 93 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የተቀረው 7 በመቶ ደግሞ ለውጪ ሀገራት የተሸጠ መሆኑ ተነግሯል።
ተቋሙ ይህንን ያለው የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀሙን እና የ2018 በጀት ዓመት እቅዱን በተመለከተ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ነው።በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 29,480 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨቱን ተናግሯል።
ይህም ካቀድኩት በላይ ነው ያለው ተቋሙ በበጀት ዓመቱ 25,423 ጊጋ ዋት ሰዓት የማምረት እቅድ ነው የነበረኝ ብሏል።ከሀይል ሽያጩ 75.4 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ ተናግረዋል።
ከመነጨው ሀይልም 33.2 በመቶው የተገኘው ከህዳሴ ግድቡ መሆኑን ያብራሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው ኢንጅነር አሸብር ባልቻ 93 በመቶው የመነጨው ሀይል ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የተቀረው 7 በመቶ ደግሞ ለውጭ ሀገራት የተሸጠ ነው ብለዋል።ለሀገር ውስጥ ከቀረበው 93 በመቶ ሀይል 60 በመቶው ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተሸጠ፣ 27 በመቶው ለዳታ ማይኒንግ እና 6 በመቶው ደግሞ ለኢንዱስትሪዎች የተሸጠ መሆኑን ከተቋሙ ሰምተናል።
ከአጠቃላይ የመነጨ ሀይል 7 በመቶው ለውጭ ሽያጭ መቅረቡን ያስረዱት ሀላፊው ለውጭ ሀገራት በሽያጭ ከቀረበው 5 በመቶው ለኬኒያ እና 2 በመቶው ለጅቡቲ እንደተሸጠ ተናግረዋል።በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በተጠናቀቀው በጀት አመት ችግር ሆነውብኛል ስላላቸው ጉዳዮችም አንስቷል።
የመሰረተ ልማት ስርቆት ሲፈትነኝ ቆይቷል ያለው ተቋሙ፤በ43 የሀይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶብኛል ብሏል።በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ያለው የሰላም እጦት እንደልብ ስራዎችን ተዘዋውሬ መስራት እንዳልችል ያደረገኝ ሌላኛው ችግር ነው ሲል ተናግሯል።
Via Sheger
@YeneTube @FikerAssefa
በበጀት ዓመቱ ከተገኘው ሀይል 93 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የተቀረው 7 በመቶ ደግሞ ለውጪ ሀገራት የተሸጠ መሆኑ ተነግሯል።
ተቋሙ ይህንን ያለው የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀሙን እና የ2018 በጀት ዓመት እቅዱን በተመለከተ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ነው።በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 29,480 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨቱን ተናግሯል።
ይህም ካቀድኩት በላይ ነው ያለው ተቋሙ በበጀት ዓመቱ 25,423 ጊጋ ዋት ሰዓት የማምረት እቅድ ነው የነበረኝ ብሏል።ከሀይል ሽያጩ 75.4 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ ተናግረዋል።
ከመነጨው ሀይልም 33.2 በመቶው የተገኘው ከህዳሴ ግድቡ መሆኑን ያብራሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው ኢንጅነር አሸብር ባልቻ 93 በመቶው የመነጨው ሀይል ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የተቀረው 7 በመቶ ደግሞ ለውጭ ሀገራት የተሸጠ ነው ብለዋል።ለሀገር ውስጥ ከቀረበው 93 በመቶ ሀይል 60 በመቶው ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተሸጠ፣ 27 በመቶው ለዳታ ማይኒንግ እና 6 በመቶው ደግሞ ለኢንዱስትሪዎች የተሸጠ መሆኑን ከተቋሙ ሰምተናል።
ከአጠቃላይ የመነጨ ሀይል 7 በመቶው ለውጭ ሽያጭ መቅረቡን ያስረዱት ሀላፊው ለውጭ ሀገራት በሽያጭ ከቀረበው 5 በመቶው ለኬኒያ እና 2 በመቶው ለጅቡቲ እንደተሸጠ ተናግረዋል።በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በተጠናቀቀው በጀት አመት ችግር ሆነውብኛል ስላላቸው ጉዳዮችም አንስቷል።
የመሰረተ ልማት ስርቆት ሲፈትነኝ ቆይቷል ያለው ተቋሙ፤በ43 የሀይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶብኛል ብሏል።በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ያለው የሰላም እጦት እንደልብ ስራዎችን ተዘዋውሬ መስራት እንዳልችል ያደረገኝ ሌላኛው ችግር ነው ሲል ተናግሯል።
Via Sheger
@YeneTube @FikerAssefa
😁24❤20👍2
በሲዳማና ኦሮሚያ ድንበር አከባቢ የተከሰተው አለመግባባት የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለጸ
ነሀሴ 1/2017 የሲዳማ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ
በሲዳማና ኦሮሚያ ድንበር አከባቢ የተከሰተው አለመግባባት የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለጸ። የቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ዳንጊሶ እንደገለጹት በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በበንሳና በቡራ ወረዳዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በኮኮሳና ላንሳቦ ወረዳዎች አካባቢ በጥቂት ግለሰቦች መካከል አለመግባባት መፈጠሩንና የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን ገልፀዋል ። አለመግባባቱ በጥቂት ግለሰቦች መካከል የተፈጠረ ክስተት መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል።
አለመግባባት ሊከሰት የሚችል ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የቢሮ ኃላፊው የተፈጠረውን ክስተት የሲዳማና የኦሮሚያ ክልል የዞንና የወረዳ አመራሮች ሁለቱን ወገኖች በማነጋገር በእርቅ ለመፍታት በትኩረት በመስራት ላይ እንደሚገኙም ገልጸዋል ።
በተያያዘም DW Amharic ከጉዳዩ ጋር አያይዞ ያሰራጨው ዘገባ ተዓማኒነት የጎደለውና የሚዲያ ሥነ_ምግባርን የጣሰ መሆኑን እንዲሁም ህዝብን ከህዝብ ጋር የሚያጋጭ ስለሆነ ከድርጊቱ ሊቆጠብ ይገባል ብለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
ነሀሴ 1/2017 የሲዳማ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ
በሲዳማና ኦሮሚያ ድንበር አከባቢ የተከሰተው አለመግባባት የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ገለጸ። የቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ዳንጊሶ እንደገለጹት በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በበንሳና በቡራ ወረዳዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በኮኮሳና ላንሳቦ ወረዳዎች አካባቢ በጥቂት ግለሰቦች መካከል አለመግባባት መፈጠሩንና የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን ገልፀዋል ። አለመግባባቱ በጥቂት ግለሰቦች መካከል የተፈጠረ ክስተት መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል።
አለመግባባት ሊከሰት የሚችል ጉዳይ መሆኑን የገለጹት የቢሮ ኃላፊው የተፈጠረውን ክስተት የሲዳማና የኦሮሚያ ክልል የዞንና የወረዳ አመራሮች ሁለቱን ወገኖች በማነጋገር በእርቅ ለመፍታት በትኩረት በመስራት ላይ እንደሚገኙም ገልጸዋል ።
በተያያዘም DW Amharic ከጉዳዩ ጋር አያይዞ ያሰራጨው ዘገባ ተዓማኒነት የጎደለውና የሚዲያ ሥነ_ምግባርን የጣሰ መሆኑን እንዲሁም ህዝብን ከህዝብ ጋር የሚያጋጭ ስለሆነ ከድርጊቱ ሊቆጠብ ይገባል ብለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
❤34👍12😁4🔥1
በአመቱ ከዴታ ማይኒንግ የተገኘው ገቢ ግንባር ቀደም ነው!
የዴታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ እየገቡ መስራታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሽያጭ ገቢ እያገኘ መሆኑ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡በተለይ በማይኒንግ ስራ የተሰማሩት ኩባንያዎች የሚከፍሉት በውጭ ምንዛሬ መሆኑ ለሃይል አቅራቢው ትልቅ እድል የፈጠረ ነው፡፡
በ2017 መጀት አመት ከአገር ውስጥ የሃይል ሽያጭ ከተገኘው 75.4 ቢሊየን ብር ገቢ የ39 በመቶ ድርሻ የነበረው የዴታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ሲሆን ለሰፊው ህዝብ ሃይል ለሚያቀርበው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከተሸጠው የተገኘው የ35 በመቶ እንዲሁም የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች የ4 በመቶ ድርሻ አላቸው፡፡
ሆኖም ለሽያጭ ከቀረበው ኃይል ውስጥ በመጠን ከፍተኛውን የወሰደው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሲሆን 60 በመቶ ነው፡፡የዳታ ማይኒንግ 27 በመቶ፣ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች 6 በመቶ ፣ ኬኒያ የ5 በመቶ እንዲሁም ለጅቡቲ 2 በመቶ እንደቀረበ ነው የሃይል አምራች ሻጩ የገለፀው።
[KGEthiopia]
@YeneTube @FikerAssefa
የዴታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ እየገቡ መስራታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሽያጭ ገቢ እያገኘ መሆኑ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡በተለይ በማይኒንግ ስራ የተሰማሩት ኩባንያዎች የሚከፍሉት በውጭ ምንዛሬ መሆኑ ለሃይል አቅራቢው ትልቅ እድል የፈጠረ ነው፡፡
በ2017 መጀት አመት ከአገር ውስጥ የሃይል ሽያጭ ከተገኘው 75.4 ቢሊየን ብር ገቢ የ39 በመቶ ድርሻ የነበረው የዴታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ሲሆን ለሰፊው ህዝብ ሃይል ለሚያቀርበው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከተሸጠው የተገኘው የ35 በመቶ እንዲሁም የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች የ4 በመቶ ድርሻ አላቸው፡፡
ሆኖም ለሽያጭ ከቀረበው ኃይል ውስጥ በመጠን ከፍተኛውን የወሰደው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሲሆን 60 በመቶ ነው፡፡የዳታ ማይኒንግ 27 በመቶ፣ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች 6 በመቶ ፣ ኬኒያ የ5 በመቶ እንዲሁም ለጅቡቲ 2 በመቶ እንደቀረበ ነው የሃይል አምራች ሻጩ የገለፀው።
[KGEthiopia]
@YeneTube @FikerAssefa
❤15😁9⚡1🔥1
Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
❤2
Forwarded from YeneTube
በ 25% ዲስካውንት ለገበያ አቅርበናል!
📌 ፒያሳ ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት
👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
✅ መገልገያዎች
👉 ሦስት ሊፍት
👉 ባለ 3 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ ቦታ
👉 ቴራስ
👉 ያልተገደበ የውሃ አቅርቦት
👉 የመጠባበቂያ ጀነሬተር
📌 የካሬ አማራጮች
👉ባለ 1መኝታ - 63 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 86 እስከ 103 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 132 እስከ 146 ካሬ
👉1 መኝታ 63ካሬ=
10% ቅድመ ክፍያ 693,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
👉2መኝታ 86 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 946,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 9,460,000 ብር
👉3መኝታ 114 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 1,219,800 ብር
ሙሉ ክፍያ 12,198,000 ብር
ለበለጠ መረጃ
☎️ +251976195835
Telegram username
@Ruthtemersales
What's app
https://wa.me/251976195835
TEMER PROPERTIES
Create | Construct | Deliver
#TemerProperties #Temerrealestate
📌 ፒያሳ ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት
👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
✅ መገልገያዎች
👉 ሦስት ሊፍት
👉 ባለ 3 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ ቦታ
👉 ቴራስ
👉 ያልተገደበ የውሃ አቅርቦት
👉 የመጠባበቂያ ጀነሬተር
📌 የካሬ አማራጮች
👉ባለ 1መኝታ - 63 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 86 እስከ 103 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 132 እስከ 146 ካሬ
👉1 መኝታ 63ካሬ=
10% ቅድመ ክፍያ 693,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
👉2መኝታ 86 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 946,000 ብር
ሙሉ ክፍያ 9,460,000 ብር
👉3መኝታ 114 ካሬ
10%ቅድመ ክፍያ 1,219,800 ብር
ሙሉ ክፍያ 12,198,000 ብር
ለበለጠ መረጃ
☎️ +251976195835
Telegram username
@Ruthtemersales
What's app
https://wa.me/251976195835
TEMER PROPERTIES
Create | Construct | Deliver
#TemerProperties #Temerrealestate
❤1
Forwarded from ALX Ethiopia
🚀 Want to become a Virtual Assistant? Join our live Telegram session to learn about the programme, how to apply, and get your questions answered!
Don’t miss it - happening this Saturday, 3 ነሐሴ 2017 (August 9, 2025) starting at 11፡00 (5:00 PM) in our Telegram group
👉🏾 t.me/virtualassistantapplicationguide
#ALXEthiopia #ALXAfrica #ALXTribe #AIwithALX #VirtualAssistant
Don’t miss it - happening this Saturday, 3 ነሐሴ 2017 (August 9, 2025) starting at 11፡00 (5:00 PM) in our Telegram group
👉🏾 t.me/virtualassistantapplicationguide
#ALXEthiopia #ALXAfrica #ALXTribe #AIwithALX #VirtualAssistant
❤4
ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል በነበረው ውይይት ላይ ከሁለት ፖርቲዎች ውጪ ሁሉም ፖርቲዎች መሳተፋቸውን ገለጸ!
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ባካሄደው ውይይት ላይ ከሁለት ፖርቲዎች በስተቀር ሁሉም በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፖርቲዎች መሳተፋቸውን አስታውቋል።ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል ምክክር ለመጀመር የሚያስችል ውጤታማ ውይይት መደረጉን በዛሬዉ ዕለት በሰጠው መግለጫ ላይ የገለጸ ሲሆን፤ "የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር 'የሀገራዊ ምክክር ሥራውን በበጎ እንደሚመለከተው' አስታውቋል"ም ብሏል።
በመግለጫውም በትግራይ አጀንዳ ማሰባሰብ የሚያስችል ሥራ ለመስራት የተለያዩ ጥረቶች ሲያደርግ ቆይቶ፤ ሐምሌ 22 ለመጀመሪያ ጊዜ በትግራይ በመገኘት ውይይት ማካሄዱን የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ ጥበብ ታደሰ ተናግረዋል።ኮሚሽኑ በትግራይ ከጊዚያዊ አስተዳደር፣ ከፖርቲዎች፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ጋር ውይይት ማካሄዱንም ገልጸዋል።
በውይይት ወቅት በርካታ ጉዳዮች ከተሳታፊዎች መነሳታቸውን የገለጹት ቃል አቀባዩ፤ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዲፈጸም፣ ተፈናቃዮች ወደቀዬአቸው እንዲመለሱ፣ የትግራይ ግዛታዊ አንድነት እንዲመለስ እንዲሁም፤ በትግራይ ከጦርነቱ በፊት ወደነበረችበት ሕገ-መንግሥታዊ ስርዓት እንድትመለስ የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በአሁን እያንዣበበ ያለው የጦርነት ሁኔታ መፍትሄ እንዲበጅለትም ከተጠየቁ ጉዳዮች መካከል እንደሚገኙበት አንስተዋል።"ይሁን እንጂ በትግራይ በኩል የቀረቡት እነዚህ ሁኔታዎች ምክክር ለማካሄድ ቅድመ ሁኔታዎች አይደሉም" ያሉት የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ፤ "ለምክክር ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ አያስፈልገውም" ብለዋል።
"ኮሚሽኑም የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የሀገራዊ ምክክር ሥራውን በበጎ ይመለከተዋል" ሲሉ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።
አሐዱም "በትግራይ በነበረው ውይይት ምን ያህል የፖለቲካ ፖርቲዎች ተሳትፈዋል?" ሲል የኮሚሽኑን ቃል አቀባይ ጠይቋል።
ቃል አቀባዩ አቶ ጥበቡ ታደሠ በሰጡት ምላሽ፤ በትግራይ ክልል በነበረው ውይይት ከሁለት የፖለቲካ ፖርቲዎች ማለትም ከ'አረና ልዓላዊ ፖርቲ' እና 'ውድብ ናፅነት ትግራይ' ውጪ በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ፖርቲዎች መሳተፋቸውን ገልጸዋል።
ቃለ አቀባዩ ይህንን ይበሉ እንጂ ባይቶና አባይ ፖርቲ እና ሳልሳይ ወያነ ትግራይን የመሱሉ ፖርቲዎችም፤ በመቀሌ በነበረው ውይይት ላይ አለመሳተፋቸውን አሐዱ ከዚህ ቀደም መዘገቡ ይታወሳል።
የሀገራዊ ምክክር ክሚሽን የተለያዩ ግብዓቶቸን በመውሰድ ተከታታይነት ያለው ውይይት በማድረግ በትግራይ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱን ለማከናወን አጠናክሮ ይቀጥላልም ተብሏል።
ኮሚሽኑ በዛሬው መግለጫው "በትግራይ ክልል ወደ ሃይል አማራጭ የሚሄዱ አካላቶች ከድርጊታቸወሰ እንዲቆጠቡ" ሲል ጥሪ አቅርቧል።በመግለጫው የዲያስፖራ አጀንዳ ማሰባሰብ ሥራው መቀጠሉ የተነገረ ሲሆን፤ በነገው ዕለት በደቡብ አፍሪካ የአጀንዳ ማሳሰብ ሥራ እንደሚካሄድም ተገልጿል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ባካሄደው ውይይት ላይ ከሁለት ፖርቲዎች በስተቀር ሁሉም በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፖርቲዎች መሳተፋቸውን አስታውቋል።ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል ምክክር ለመጀመር የሚያስችል ውጤታማ ውይይት መደረጉን በዛሬዉ ዕለት በሰጠው መግለጫ ላይ የገለጸ ሲሆን፤ "የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር 'የሀገራዊ ምክክር ሥራውን በበጎ እንደሚመለከተው' አስታውቋል"ም ብሏል።
በመግለጫውም በትግራይ አጀንዳ ማሰባሰብ የሚያስችል ሥራ ለመስራት የተለያዩ ጥረቶች ሲያደርግ ቆይቶ፤ ሐምሌ 22 ለመጀመሪያ ጊዜ በትግራይ በመገኘት ውይይት ማካሄዱን የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ ጥበብ ታደሰ ተናግረዋል።ኮሚሽኑ በትግራይ ከጊዚያዊ አስተዳደር፣ ከፖርቲዎች፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ጋር ውይይት ማካሄዱንም ገልጸዋል።
በውይይት ወቅት በርካታ ጉዳዮች ከተሳታፊዎች መነሳታቸውን የገለጹት ቃል አቀባዩ፤ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዲፈጸም፣ ተፈናቃዮች ወደቀዬአቸው እንዲመለሱ፣ የትግራይ ግዛታዊ አንድነት እንዲመለስ እንዲሁም፤ በትግራይ ከጦርነቱ በፊት ወደነበረችበት ሕገ-መንግሥታዊ ስርዓት እንድትመለስ የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በአሁን እያንዣበበ ያለው የጦርነት ሁኔታ መፍትሄ እንዲበጅለትም ከተጠየቁ ጉዳዮች መካከል እንደሚገኙበት አንስተዋል።"ይሁን እንጂ በትግራይ በኩል የቀረቡት እነዚህ ሁኔታዎች ምክክር ለማካሄድ ቅድመ ሁኔታዎች አይደሉም" ያሉት የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ፤ "ለምክክር ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ አያስፈልገውም" ብለዋል።
"ኮሚሽኑም የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የሀገራዊ ምክክር ሥራውን በበጎ ይመለከተዋል" ሲሉ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።
አሐዱም "በትግራይ በነበረው ውይይት ምን ያህል የፖለቲካ ፖርቲዎች ተሳትፈዋል?" ሲል የኮሚሽኑን ቃል አቀባይ ጠይቋል።
ቃል አቀባዩ አቶ ጥበቡ ታደሠ በሰጡት ምላሽ፤ በትግራይ ክልል በነበረው ውይይት ከሁለት የፖለቲካ ፖርቲዎች ማለትም ከ'አረና ልዓላዊ ፖርቲ' እና 'ውድብ ናፅነት ትግራይ' ውጪ በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ፖርቲዎች መሳተፋቸውን ገልጸዋል።
ቃለ አቀባዩ ይህንን ይበሉ እንጂ ባይቶና አባይ ፖርቲ እና ሳልሳይ ወያነ ትግራይን የመሱሉ ፖርቲዎችም፤ በመቀሌ በነበረው ውይይት ላይ አለመሳተፋቸውን አሐዱ ከዚህ ቀደም መዘገቡ ይታወሳል።
የሀገራዊ ምክክር ክሚሽን የተለያዩ ግብዓቶቸን በመውሰድ ተከታታይነት ያለው ውይይት በማድረግ በትግራይ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱን ለማከናወን አጠናክሮ ይቀጥላልም ተብሏል።
ኮሚሽኑ በዛሬው መግለጫው "በትግራይ ክልል ወደ ሃይል አማራጭ የሚሄዱ አካላቶች ከድርጊታቸወሰ እንዲቆጠቡ" ሲል ጥሪ አቅርቧል።በመግለጫው የዲያስፖራ አጀንዳ ማሰባሰብ ሥራው መቀጠሉ የተነገረ ሲሆን፤ በነገው ዕለት በደቡብ አፍሪካ የአጀንዳ ማሳሰብ ሥራ እንደሚካሄድም ተገልጿል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
❤19😁6