ብሔራዊ ባንኩ በአገሪቱ ያለው የዋጋ ግሽበት በኢኮኖሚ እድገቱ ላይ ተጽእኖ አይኖረውም አለ
🔸የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በአገሪቱ ያለው የዋጋ ግሽበት በኢኮኖሚ እድገቱ ላይ ተጽእኖ አይኖረውም አለ፡፡
🔸የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ትናንት ባወጣው ምክረሃሳብ የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየረገበ በመሄድ አሁን ላይ 15 በመቶ መድረሱን አረጋግጫለሁም ብሏል።
🔸ምግብ ነክ የዋጋ ግሽበት በየካቲት ወር 14 ነጥብ 6 በመቶ መሆኑን የጠቆመው ባንኩ ይህም ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረበት 31 በመቶ በእጅጉ የቀነስ መሆኑን ነው የተናገረው።
🔸ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶች ደግሞ 15 ነጥብ 6 በመቶ መሆኑን ያመለክተው የባንኩ መረጃ ይህም ከባለፈው ዓመት አንፃር ቅናሽ ቢኖረውም ባለፉት ጥቂት ወራት ጭማሪ የማሳየት አዝማሚያ ማሳየቱ ነው የተመለከተው።
🔸የየካቲት ወር ወርሃዊ የዕድገት መጠን 0 ነጥብ 5 መሆኑን ያሳወቀው የባንኩ መረጃ ይህም ለ4 ተከታታይ ወራት የተመዘገበ ዝቅተኛ የዕድገት መጠን እንደሆነ ነው የተነገረው።
🔸ይህም ሊሆን የቻለው ብሔራዊ ባንኩ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ከመከተሉ ባሻገር የግብርና ምርት መጨመሩና አስተዳደራዊ ዋጋዎች ላይ የተወሰዱ ማሻሻያዎች ቀስ በቀስ በመተግበራቸው እንደሆነ አመልክቷል።
🔸የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ኮሚቴ ሁለተኛ ስብሰባውን በትላንትናው ዕለት ማድረጉ የተገለፀ ሲሆን የዋጋ ንረትን ጨመሮ በተለያዩ የገንዘብ ፖሊሲ ግምገማዎችን እና ምክረ ሃሳቦችን አቅርቧል፡፡
ሙሉ መግለጫውን ከላይ አያይዘንላችኋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
🔸የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በአገሪቱ ያለው የዋጋ ግሽበት በኢኮኖሚ እድገቱ ላይ ተጽእኖ አይኖረውም አለ፡፡
🔸የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ትናንት ባወጣው ምክረሃሳብ የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየረገበ በመሄድ አሁን ላይ 15 በመቶ መድረሱን አረጋግጫለሁም ብሏል።
🔸ምግብ ነክ የዋጋ ግሽበት በየካቲት ወር 14 ነጥብ 6 በመቶ መሆኑን የጠቆመው ባንኩ ይህም ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረበት 31 በመቶ በእጅጉ የቀነስ መሆኑን ነው የተናገረው።
🔸ምግብ ነክ ያልሆኑ ምርቶች ደግሞ 15 ነጥብ 6 በመቶ መሆኑን ያመለክተው የባንኩ መረጃ ይህም ከባለፈው ዓመት አንፃር ቅናሽ ቢኖረውም ባለፉት ጥቂት ወራት ጭማሪ የማሳየት አዝማሚያ ማሳየቱ ነው የተመለከተው።
🔸የየካቲት ወር ወርሃዊ የዕድገት መጠን 0 ነጥብ 5 መሆኑን ያሳወቀው የባንኩ መረጃ ይህም ለ4 ተከታታይ ወራት የተመዘገበ ዝቅተኛ የዕድገት መጠን እንደሆነ ነው የተነገረው።
🔸ይህም ሊሆን የቻለው ብሔራዊ ባንኩ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ከመከተሉ ባሻገር የግብርና ምርት መጨመሩና አስተዳደራዊ ዋጋዎች ላይ የተወሰዱ ማሻሻያዎች ቀስ በቀስ በመተግበራቸው እንደሆነ አመልክቷል።
🔸የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ኮሚቴ ሁለተኛ ስብሰባውን በትላንትናው ዕለት ማድረጉ የተገለፀ ሲሆን የዋጋ ንረትን ጨመሮ በተለያዩ የገንዘብ ፖሊሲ ግምገማዎችን እና ምክረ ሃሳቦችን አቅርቧል፡፡
ሙሉ መግለጫውን ከላይ አያይዘንላችኋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
😁37👎23👍20🔥1
ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርቧል
ዛሬ ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበው ድምፃዊ አንዱዓለም ፖሊስ አንዳንድ ምርመራ ውጤቶች ስላልደረሱልኝ ተጨማሪ ቀናት ይሰጠኝ ባለው መሰረት ተጨማሪ 12 ቀን ተፈቅዶለታል።
የድምፃዊ አንዱዓለም ጠበቃ በበኩሉ የዋስ መብት ይፈቀድለት ብሎ ቢጠይቅም
ፖሊስ ማስረጃዎችን ያጠፋብኛል መፈቀድ የለበትም በማለቱ ሳይፈቀድ ቀርቷል።
መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓም ቀጠሮ ተሰርቷል።
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
ዛሬ ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበው ድምፃዊ አንዱዓለም ፖሊስ አንዳንድ ምርመራ ውጤቶች ስላልደረሱልኝ ተጨማሪ ቀናት ይሰጠኝ ባለው መሰረት ተጨማሪ 12 ቀን ተፈቅዶለታል።
የድምፃዊ አንዱዓለም ጠበቃ በበኩሉ የዋስ መብት ይፈቀድለት ብሎ ቢጠይቅም
ፖሊስ ማስረጃዎችን ያጠፋብኛል መፈቀድ የለበትም በማለቱ ሳይፈቀድ ቀርቷል።
መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓም ቀጠሮ ተሰርቷል።
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
👍38👎3❤2😭2
YeneTube
Photo
በወጣቷ ላይ የደረሰው ሰቆቃ በቅርብ ጊዜያት በአገራችን ለተፈጸሙ ግፎች በቂ ማሳያ ነው።
🗣 እናት ፓርቲ
(በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከመኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄና እናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)
ከምትማርበት ዩኒቨርስቲ ከዓመታት በፊት ከሌሎች ጓደኞቿ ጋር ታፍና ተወስዳ እጅግ አሰቃቂ በደል ከደረሰባቸው አንዷ እንደሆነች የገለጸችው ወጣት ብርቱካን ተመስገን የደረሰባትን ግፍና አኹን እየመራች ያለችውን እጅግ ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረድ የዚህ ዓይነት ጥቃት ሰለባ የሆኑ ሰዎች በማይደፍሩት መልኩ በድፍረት በሚዲያ ቀርባ አስረድታለች። ይኼ በሕዝባችን ዘንድ በከፍተኛ ኹኔታ ሲጠየቅ የነበረና አንዳች መፍትሔ ሳይሰጠው ይባስ ብሎ በመንግሥት አካላት ዘንድ እጅግ የተጣረሱና የተድበሰበሱ መረጃዎች ሲቀርብበት የኖረ ግፍ ነው። ብርትኳን ላይ የደረሰው ግፍ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈጸሙ መዋቅራዊና ሥርዓታዊ በደሎች ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ እንጂ ብቸኛው አይደለም። በዚኹ አጋጣሚ የልጅቷ ደህንነት ተጠብቆና መቋቋሚያ አግኝታ ስለሌሎች ደብዛቸው ስለጠፋ ተማሪዎች አንዳች ፍንጭ የሚሰጡ መረጃዎችን ለማገጣጠም መጣር ሲገባ ልጅቷ ጋር ያለውን እውነት ለማዳፈን ሙከራ ማድረግ የግፉ ተባባሪ ከመኾን ተለይቶ አይታይም። በትብብር የምንሠራ ፓርቲዎች በወጣቷ ጉዳይ የቅርብ ክትትል እንደምናደርግ ቃል እንየገባን ሕዝባችን ችግሮቹ ሥርዓት ወለድ መኾናቸውን በውል ተገንዝቦ እርስ በእርስ ጣት ከመጠቋቆም እንዲወጣና በጋራ እንዲታገል ከከፋው ሰቆቃም በአንድነት እንድንወጣ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
መንግሥት የብርቱካንና መሰል ጓደኞቿን እገታ ቢያንስ ለችግሩ እውቅና ሰጥቶና ሕዝብን አስተባብሮ ወደ መፍትሔው መሔድ ሲገባው ማድበስበስን በመምረጡ እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ችግሩ ሥር ሰዶ ከእለት እለት እየከፋ ሄዷል፡፡ መጋቢት ፰ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል እየተጓዘ በነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ላይ በኦሮሚያ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን፣ ወረ ጃርሶ ወረዳ፣ ልዩ ስሙ አሊዶሮ በተባለ ቦታ አሽከርካሪውን ጨምሮ መላ ተሳፋሪዎች መታገታቸውንና ለማስለቀቂያ የሚኾን በነፍስ ወከፍ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እየተጠየቀባቸው መኾኑን ሰምተናል፡፡
በተመሳሳይ መጋቢት ፲፬ ቀን በዚኹ ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ጎርፎ ከተማ አካባቢ የታጠቁ ቡድኖች ከቀኑ ፲ ሰዓት ገደማ በኹለት ተሽከርካሪዎች ላይ በፈጸሙት እገታ አርባ ያኽል ሰዎች መታፈናቸውን ሰምተናል፡፡ ለጊዜው ለኹለቱም እገታዎች በይፋ ኃላፊነት የወሰደ አካል ባይኖርም በአካባቢው መሰል ድርጊት ፈጻሚዎች ያለምንም ከልካይ ባሻቸው ወቅትና በተደጋጋሚ ጊዜያት እገታ እየፈጸሙ አሰቃቂ ግድያ የሚፈጸምበትና ብዙ ሚሊዮን ብር ካሳ የሚጠየቅበት መሥመር አካባቢው ደግሞ “የሞት ቀጠና” ከኾነ ውሎ አድሯል፡፡
በተደጋጋሚ እንደገለጽነው መንግሥት ተቀዳሚ ተግባሩ የኾነውን የዜጎችን ወጥቶ የመግባት ዋስትና ማስጠበቅ አለመቻል፣ ፍትሕ አለመስፈን በአገር ደረጃ መግደልና ማገት ቀላል እንዲኾን አልፎ ተርፎም ለእነዚኽና መሰል ቡድኖች የገቢ ምንጭ ጭምር ተደርጎ እንዲታይ አድርጎታል፡፡ በትብብር የምንሠራ ፓርቲዎች በእገታው የተሳተፈ የትኛውም ቡድን በንጹሓን ሕይወት መቆመሩን እንዲያቆምና የታገቱ ዜጎች ያለምንም ቅድመ ኹኔታ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
እግዚአብሔር አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!
@Yenetube @Fikerassefa
🗣 እናት ፓርቲ
(በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከመኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄና እናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)
ከምትማርበት ዩኒቨርስቲ ከዓመታት በፊት ከሌሎች ጓደኞቿ ጋር ታፍና ተወስዳ እጅግ አሰቃቂ በደል ከደረሰባቸው አንዷ እንደሆነች የገለጸችው ወጣት ብርቱካን ተመስገን የደረሰባትን ግፍና አኹን እየመራች ያለችውን እጅግ ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረድ የዚህ ዓይነት ጥቃት ሰለባ የሆኑ ሰዎች በማይደፍሩት መልኩ በድፍረት በሚዲያ ቀርባ አስረድታለች። ይኼ በሕዝባችን ዘንድ በከፍተኛ ኹኔታ ሲጠየቅ የነበረና አንዳች መፍትሔ ሳይሰጠው ይባስ ብሎ በመንግሥት አካላት ዘንድ እጅግ የተጣረሱና የተድበሰበሱ መረጃዎች ሲቀርብበት የኖረ ግፍ ነው። ብርትኳን ላይ የደረሰው ግፍ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈጸሙ መዋቅራዊና ሥርዓታዊ በደሎች ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ እንጂ ብቸኛው አይደለም። በዚኹ አጋጣሚ የልጅቷ ደህንነት ተጠብቆና መቋቋሚያ አግኝታ ስለሌሎች ደብዛቸው ስለጠፋ ተማሪዎች አንዳች ፍንጭ የሚሰጡ መረጃዎችን ለማገጣጠም መጣር ሲገባ ልጅቷ ጋር ያለውን እውነት ለማዳፈን ሙከራ ማድረግ የግፉ ተባባሪ ከመኾን ተለይቶ አይታይም። በትብብር የምንሠራ ፓርቲዎች በወጣቷ ጉዳይ የቅርብ ክትትል እንደምናደርግ ቃል እንየገባን ሕዝባችን ችግሮቹ ሥርዓት ወለድ መኾናቸውን በውል ተገንዝቦ እርስ በእርስ ጣት ከመጠቋቆም እንዲወጣና በጋራ እንዲታገል ከከፋው ሰቆቃም በአንድነት እንድንወጣ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
መንግሥት የብርቱካንና መሰል ጓደኞቿን እገታ ቢያንስ ለችግሩ እውቅና ሰጥቶና ሕዝብን አስተባብሮ ወደ መፍትሔው መሔድ ሲገባው ማድበስበስን በመምረጡ እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ችግሩ ሥር ሰዶ ከእለት እለት እየከፋ ሄዷል፡፡ መጋቢት ፰ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል እየተጓዘ በነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ላይ በኦሮሚያ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን፣ ወረ ጃርሶ ወረዳ፣ ልዩ ስሙ አሊዶሮ በተባለ ቦታ አሽከርካሪውን ጨምሮ መላ ተሳፋሪዎች መታገታቸውንና ለማስለቀቂያ የሚኾን በነፍስ ወከፍ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እየተጠየቀባቸው መኾኑን ሰምተናል፡፡
በተመሳሳይ መጋቢት ፲፬ ቀን በዚኹ ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ ጎርፎ ከተማ አካባቢ የታጠቁ ቡድኖች ከቀኑ ፲ ሰዓት ገደማ በኹለት ተሽከርካሪዎች ላይ በፈጸሙት እገታ አርባ ያኽል ሰዎች መታፈናቸውን ሰምተናል፡፡ ለጊዜው ለኹለቱም እገታዎች በይፋ ኃላፊነት የወሰደ አካል ባይኖርም በአካባቢው መሰል ድርጊት ፈጻሚዎች ያለምንም ከልካይ ባሻቸው ወቅትና በተደጋጋሚ ጊዜያት እገታ እየፈጸሙ አሰቃቂ ግድያ የሚፈጸምበትና ብዙ ሚሊዮን ብር ካሳ የሚጠየቅበት መሥመር አካባቢው ደግሞ “የሞት ቀጠና” ከኾነ ውሎ አድሯል፡፡
በተደጋጋሚ እንደገለጽነው መንግሥት ተቀዳሚ ተግባሩ የኾነውን የዜጎችን ወጥቶ የመግባት ዋስትና ማስጠበቅ አለመቻል፣ ፍትሕ አለመስፈን በአገር ደረጃ መግደልና ማገት ቀላል እንዲኾን አልፎ ተርፎም ለእነዚኽና መሰል ቡድኖች የገቢ ምንጭ ጭምር ተደርጎ እንዲታይ አድርጎታል፡፡ በትብብር የምንሠራ ፓርቲዎች በእገታው የተሳተፈ የትኛውም ቡድን በንጹሓን ሕይወት መቆመሩን እንዲያቆምና የታገቱ ዜጎች ያለምንም ቅድመ ኹኔታ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
እግዚአብሔር አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!
@Yenetube @Fikerassefa
👍97😭12👎7❤3😁1👀1
የሱዳን ጦር የካርቱምን አየር ማረፊያ መቆጣጠሩን አስታወቀ
የሱዳን ጦር ሃይል (SAF) እኤአ ከሚያዝያ 2023 አጋማሽ ጀምሮ በፓራሚትሪ ፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሃይሎች (RSF) ተይዞ የነበረውን የካርቱም አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መቆጣጠሩን የካርቱም አካባቢ ወታደራዊ ምንጮች ገለፁ።
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
የሱዳን ጦር ሃይል (SAF) እኤአ ከሚያዝያ 2023 አጋማሽ ጀምሮ በፓራሚትሪ ፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሃይሎች (RSF) ተይዞ የነበረውን የካርቱም አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መቆጣጠሩን የካርቱም አካባቢ ወታደራዊ ምንጮች ገለፁ።
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
👍14❤5
የአማራ ክልል መንግስት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የአድማ መከላከል እና መደበኛ ፖሊሶችን እያሰለጠነ መሆኑን ተገለጸ!
በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአሥተዳደር ጉዳዮች ክላስተር አስተባባሪ እና የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኀላፊ ደሳለኝ ጣሰው በብር ሸለቆ መሠረታዊ የውትድርና ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት ተገኝተው በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የአድማ መከላከል እና የመደበኛ ፖሊስ ምልምል ሠልጣኞችን “አበረታትተዋል”።
ደሳለኝ ጣሰው በጉበኝቱ ወቅት “የክልልሉን ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ እና የሕዝብ እና የመንግሥትን ፍላጎት” አስመልክተው ለሠልጣኞች ማብራሪያም ሰጥተዋል። በተጨማሪም “የሥልጠናውን ዓላማ፣ አስፈላጊነት እና ግቦች በተመለከተም ለሠልጣኞች ግልጽ አድርገዋል” ሲል የክልሉ ሚዲያ ዘግቧል።
ሥልጠናው “በዋናነት ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ወታደራዊ ሥነ ምግባር የተላበሰ፣ በሥነ ልቦናው ያደገ እና በራስ አቅም የክልሉን ሰላም ማረጋገጥ የሚችሉ ሠልጣኞችን ማፍራት እንደኾነም” አቶ ደሳለኝ ገልጸዋል።
ሠልጣኞች “የክልሉን ሰላም በዘላቂነት በማረጋገጥ ሕዝቡን ከገባበት ፈተና ለማላቀቅ እና ፊቱን ወደ ልማት እንዲያዞር በማድረግ ረገድ ትልቅ ኀላፊነት እንዳለባቸው” ተናግረዋል። ሰልጣኞች “ከክልሉ አልፎ የሀገርን ደኅንነት ለመጠበቅ የሚያስችል ዝግጁነት ላይ መሆናቸውም” ተገልጿል።አቶ ደሳለኝ ጣሰው አክለውም ሠልጣኞቹ “በጥሩ ቁመና፣ ቁርጠኝነት እና የሥነ ልቦና ዝግጁነት” ላይ መኾናቸውን አረጋግጠዋል ተብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአሥተዳደር ጉዳዮች ክላስተር አስተባባሪ እና የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኀላፊ ደሳለኝ ጣሰው በብር ሸለቆ መሠረታዊ የውትድርና ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት ተገኝተው በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የአድማ መከላከል እና የመደበኛ ፖሊስ ምልምል ሠልጣኞችን “አበረታትተዋል”።
ደሳለኝ ጣሰው በጉበኝቱ ወቅት “የክልልሉን ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ እና የሕዝብ እና የመንግሥትን ፍላጎት” አስመልክተው ለሠልጣኞች ማብራሪያም ሰጥተዋል። በተጨማሪም “የሥልጠናውን ዓላማ፣ አስፈላጊነት እና ግቦች በተመለከተም ለሠልጣኞች ግልጽ አድርገዋል” ሲል የክልሉ ሚዲያ ዘግቧል።
ሥልጠናው “በዋናነት ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ወታደራዊ ሥነ ምግባር የተላበሰ፣ በሥነ ልቦናው ያደገ እና በራስ አቅም የክልሉን ሰላም ማረጋገጥ የሚችሉ ሠልጣኞችን ማፍራት እንደኾነም” አቶ ደሳለኝ ገልጸዋል።
ሠልጣኞች “የክልሉን ሰላም በዘላቂነት በማረጋገጥ ሕዝቡን ከገባበት ፈተና ለማላቀቅ እና ፊቱን ወደ ልማት እንዲያዞር በማድረግ ረገድ ትልቅ ኀላፊነት እንዳለባቸው” ተናግረዋል። ሰልጣኞች “ከክልሉ አልፎ የሀገርን ደኅንነት ለመጠበቅ የሚያስችል ዝግጁነት ላይ መሆናቸውም” ተገልጿል።አቶ ደሳለኝ ጣሰው አክለውም ሠልጣኞቹ “በጥሩ ቁመና፣ ቁርጠኝነት እና የሥነ ልቦና ዝግጁነት” ላይ መኾናቸውን አረጋግጠዋል ተብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
😁35👍13❤9👎2
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖን በአዲስ አበባ ልታዘጋጅ ነው!
ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላትን አቅም ለአለም ለማሳየት እና የአፍሪካ የቴክኖሎጂ ማዕከል ለመሆን የሚያስችላትን ጉዞ ያጠናክራል የተባዉ አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ (ETEX 2025) በአዲስ አበባ ልታዘጋጅ መሆኑ ተገለፀ።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት (EAll) በጋራ የሚያዘጋጁት ይህ ኤክስፖ ከ100 በላይ የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ድርጅቶች፣ ከ50 በላይ ስታርታፖች እንዲሁም ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች የሚሳተፉበት ነው።
ከግንቦት 8 እስከ 10 ፤2017 ዓ.ም. በሚካሄደዉ ኤክስፖው ላይ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና አገልግሎቶች የሚቀርቡበት ዓውደ ርዕይ፣ ወርክሾፖች፣ ጥናታዊ ወረቀቶች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የሃካቶን እና የ AI ሮቦቲክስ ውድድሮች እንደሚቀርብ ካፒታል ሰምቷል።
ኤክስፖው በሳይበር ደህንነት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት(Al)፣ ፋይናንስ ቴክኖሎጂ (FinTech)፣ ስማርት ከተማ (Smart City)፣ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ትምህርት (Tech Education) ላይ እንደሚያተኩር ተነግሯል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላትን አቅም ለአለም ለማሳየት እና የአፍሪካ የቴክኖሎጂ ማዕከል ለመሆን የሚያስችላትን ጉዞ ያጠናክራል የተባዉ አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ (ETEX 2025) በአዲስ አበባ ልታዘጋጅ መሆኑ ተገለፀ።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት (EAll) በጋራ የሚያዘጋጁት ይህ ኤክስፖ ከ100 በላይ የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ድርጅቶች፣ ከ50 በላይ ስታርታፖች እንዲሁም ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች የሚሳተፉበት ነው።
ከግንቦት 8 እስከ 10 ፤2017 ዓ.ም. በሚካሄደዉ ኤክስፖው ላይ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና አገልግሎቶች የሚቀርቡበት ዓውደ ርዕይ፣ ወርክሾፖች፣ ጥናታዊ ወረቀቶች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የሃካቶን እና የ AI ሮቦቲክስ ውድድሮች እንደሚቀርብ ካፒታል ሰምቷል።
ኤክስፖው በሳይበር ደህንነት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት(Al)፣ ፋይናንስ ቴክኖሎጂ (FinTech)፣ ስማርት ከተማ (Smart City)፣ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ትምህርት (Tech Education) ላይ እንደሚያተኩር ተነግሯል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
👍28👎14😁7❤1
ሕወሓት "ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀጣይ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳዳሪነት በኢሜል ጥቆማ ስጡኝ" ማለታቸውን ተቃወመ
"ብቻቸውን መሾም አይችሉም" ብሏል።
እኛ ጄኔራል ታደሰ ወረደን ፕሬዚዳንት አድርገን ሾመናል ነገር ግን የፌደራል መንግሥቱ ችላ ብሎታል ብሏል።
መንግሥት የፕርቶሪያን ስምምነት በመጣስ የትግራይን ህዝብ ትዕግሥት እየተፈታተነ ነው ብሏል።
ድርጅቱ አሁን ባወጣው መግለጫ እንዲህ ብሏል "የኢትዮጵያ መንግስት አሁንም የተኩስ አቁም ስምምነቱን መንፈስ እና ይዘት ወደ ጎን በመተው በተዋዋይ ወገኖች የጋራ ስምምነት ሳይሆን ተገቢ ባልሆኑ ህጎች (አዋጅ 359/1995፣ ደንብ 533/2015) ብቻውን ለመወሰን እየሰራ ነው። በፕሪቶሪያ ስምምነት አንቀፅ 10 መሰረት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተመሰረተው በህወሓት እና በኢትዮጵያ መንግስት ድርድር ነው።
ስለዚህ በትግራይ የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሪቶሪያ ስምምነት ውጤት እንጂ የኢትዮጵያ መንግስት ብቸኛ ውሳኔ አይደለም። ሆኖም ይህንን የሚጥስ ግልጽ እንቅስቃሴ አለ።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ህወሓት ከስልጣን መወገዱን ተከትሎ በጊዜያዊው ፕሬዝደንት መተካት ላይ ውይይት አድርገዋል። በጉባኤው የእስካሁኑን ጊዜያዊ አስተዳደሩ የስራ አፈጻጸም የገመገመ ሲሆን፥ ጊዜያዊ አስተዳደሩን ፕሬዝዳንት ለመቀየር ተስማምቷል። ስለሆነም የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ጄኔራል ታደሰ ወረዳን በፕሬዝዳንትነት እንዲሾም ወስኗል። ነገር ግን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የቀረበው የአስተያየት ጥሪ ስምምነቱን ችላ ብሎታል። ፕሬዚዳንቱን የመሾም ስልጣን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብቸኛ ውሳኔ መስሎ የፕሪቶሪያን ስምምነት ስለሚጥስ ተቀባይነት የለውም"ብሏል።
@Yenetube @Fikerassefa
"ብቻቸውን መሾም አይችሉም" ብሏል።
እኛ ጄኔራል ታደሰ ወረደን ፕሬዚዳንት አድርገን ሾመናል ነገር ግን የፌደራል መንግሥቱ ችላ ብሎታል ብሏል።
መንግሥት የፕርቶሪያን ስምምነት በመጣስ የትግራይን ህዝብ ትዕግሥት እየተፈታተነ ነው ብሏል።
ድርጅቱ አሁን ባወጣው መግለጫ እንዲህ ብሏል "የኢትዮጵያ መንግስት አሁንም የተኩስ አቁም ስምምነቱን መንፈስ እና ይዘት ወደ ጎን በመተው በተዋዋይ ወገኖች የጋራ ስምምነት ሳይሆን ተገቢ ባልሆኑ ህጎች (አዋጅ 359/1995፣ ደንብ 533/2015) ብቻውን ለመወሰን እየሰራ ነው። በፕሪቶሪያ ስምምነት አንቀፅ 10 መሰረት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተመሰረተው በህወሓት እና በኢትዮጵያ መንግስት ድርድር ነው።
ስለዚህ በትግራይ የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሪቶሪያ ስምምነት ውጤት እንጂ የኢትዮጵያ መንግስት ብቸኛ ውሳኔ አይደለም። ሆኖም ይህንን የሚጥስ ግልጽ እንቅስቃሴ አለ።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ህወሓት ከስልጣን መወገዱን ተከትሎ በጊዜያዊው ፕሬዝደንት መተካት ላይ ውይይት አድርገዋል። በጉባኤው የእስካሁኑን ጊዜያዊ አስተዳደሩ የስራ አፈጻጸም የገመገመ ሲሆን፥ ጊዜያዊ አስተዳደሩን ፕሬዝዳንት ለመቀየር ተስማምቷል። ስለሆነም የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ጄኔራል ታደሰ ወረዳን በፕሬዝዳንትነት እንዲሾም ወስኗል። ነገር ግን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የቀረበው የአስተያየት ጥሪ ስምምነቱን ችላ ብሎታል። ፕሬዚዳንቱን የመሾም ስልጣን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብቸኛ ውሳኔ መስሎ የፕሪቶሪያን ስምምነት ስለሚጥስ ተቀባይነት የለውም"ብሏል።
@Yenetube @Fikerassefa
👍57👎10😁8❤7
የቶኪቻው ሙዚቃ በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ በየትኛውም አከባቢ እንዳይከፈት መደረጉን የቻናላችን ቤተሰቦች አመልክተዋል
አርቲስት ቶኪቻው(ዮሐንስ በቀለ) በሲዳማ ክልል የተንሰራፋውን የመልካም አስተዳደር እጦት፣ በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ ጠንከር ያለ ትችት በተከታታይነት መሰንዘሩን ተከትሎ የዘንድሮው የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ ፍቼ ጨምበላላ ላይ የአርትስቱ ሙዝቃ እንዳይከፈት መደረጉን ተዟዝረው የተመለከቱ የቻናላችን ቤተሰቦች ጠቁመዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
አርቲስት ቶኪቻው(ዮሐንስ በቀለ) በሲዳማ ክልል የተንሰራፋውን የመልካም አስተዳደር እጦት፣ በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ ጠንከር ያለ ትችት በተከታታይነት መሰንዘሩን ተከትሎ የዘንድሮው የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ ፍቼ ጨምበላላ ላይ የአርትስቱ ሙዝቃ እንዳይከፈት መደረጉን ተዟዝረው የተመለከቱ የቻናላችን ቤተሰቦች ጠቁመዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
😁146👎45👍15❤4
👍 ተከታዮችን በፍጥነት ማግኘት ይፈልጋሉ?
Boostgram Promo ይጠቀሙ - ተከታዮችዎን በአጭር ጊዜ ይጨምሩ!
Boostgram Promo መፍትሄው ነው!
👉 ዛሬውኑ ይሞክሩት: https://tttttt.me/boostgramPromoBot/boostgram
ከሌሎች ጀማሪዎች ልዩ ይሁኑ - የማህበራዊ ሚዲያ ተከታታዮችዎን በቀላሉ ያሳድጉ!
Boostgram Promo ይጠቀሙ - ተከታዮችዎን በአጭር ጊዜ ይጨምሩ!
ጀማሪ ኢንፍሉዌንሰር ከሆኑ
ተከታዮችን በፍጥነት ማሳደግ ከፈለጉ
ተጽዕኖዎን ለማሳደግ ከፈለጉ
Boostgram Promo መፍትሄው ነው!
👉 ዛሬውኑ ይሞክሩት: https://tttttt.me/boostgramPromoBot/boostgram
ከሌሎች ጀማሪዎች ልዩ ይሁኑ - የማህበራዊ ሚዲያ ተከታታዮችዎን በቀላሉ ያሳድጉ!
👍5❤2
በትግራይ ክልል ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች እስካሁን ወደ ትምህርት ገበታቸው አልተመለሱም ተባለ!
በትግራይ ክልል ሙሉ በሙሉ የወደሙ እና ወደ ሥራ ያልተመለሱ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ስዩም ሀጎስ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ምዕራብ ትግራይ በሌሎች ኃይሎች ቁጥጥር ሥር በመሆኑ ትምህርት ለማስጀመር እንዳልተቻለ የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ እንደ እቅድ ወደ ትምህርት ገበታ ለመመለስ ከታሰበው 2 ነጥብ 45 ሚሊየን ተማሪዎች ውስጥ እስካሁን ወደ ትምህርት መመለስ የተቻለው 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ያክል ተማሪዎችን ብቻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ከነዚህም ውስጥ ባለው ችግር ምክንያት ትምህርታቸውን የሚያቋርጡ ተማሪዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡"በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ቢሞከርም፤ ባለው የምግብ አቅርቦት ችግር እና በሌሎችም ተደራራቢ ጫናዎች ምክንያት ታዳጊዎቹ ለልመና እና ለቀን ሥራ እየተዳረጉ በመሆኑ ጥረቱን አስቸጋሪ አድርጎታል" ብለዋል፡፡
"በመጠለያ ውስጥ ያለው የእርዳታ አቅርቦት የሚፈለገውን ያህል ባለመሆኑ ወላጆቻቸውም ሰርተው ልጆቻቸውን ማስተማር የሚችሉበት ሁኔታ ላይ ባለመሆናቸው፤ በተለይም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናት ምግብ ለማግኘት ወደ ልመና ይሰማራሉ" ሲሉም ተናግረዋል፡፡
አክለውም አሁን በክልሉ የሚስተዋለው ፖለቲካዊ ውጥረትም ለችግሩ መባባስ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል፡፡መንግሥትም ሆነ ረጂ ተቋማት እጃቸውን እንዲዘረጉ የጠየቁት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ፤ "እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱት ሕጻናት እንዲማሩ ለማድረግ መረባረብ የሕፃናቱን ነገ መስራት ነው" ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ግጭት ብሎም ሰው ሠራሽ እና የተፈጥሮ አደጋ በተከሰተባቸው ክልሎች በርካታ ሕጻናት እና ወጣቶች ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸው የሚገለጽ ሲሆን፤ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚህ ዓመት እንደ ሀገር ከ7 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ ክልል ሙሉ በሙሉ የወደሙ እና ወደ ሥራ ያልተመለሱ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ስዩም ሀጎስ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ምዕራብ ትግራይ በሌሎች ኃይሎች ቁጥጥር ሥር በመሆኑ ትምህርት ለማስጀመር እንዳልተቻለ የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ እንደ እቅድ ወደ ትምህርት ገበታ ለመመለስ ከታሰበው 2 ነጥብ 45 ሚሊየን ተማሪዎች ውስጥ እስካሁን ወደ ትምህርት መመለስ የተቻለው 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ያክል ተማሪዎችን ብቻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ከነዚህም ውስጥ ባለው ችግር ምክንያት ትምህርታቸውን የሚያቋርጡ ተማሪዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡"በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ቢሞከርም፤ ባለው የምግብ አቅርቦት ችግር እና በሌሎችም ተደራራቢ ጫናዎች ምክንያት ታዳጊዎቹ ለልመና እና ለቀን ሥራ እየተዳረጉ በመሆኑ ጥረቱን አስቸጋሪ አድርጎታል" ብለዋል፡፡
"በመጠለያ ውስጥ ያለው የእርዳታ አቅርቦት የሚፈለገውን ያህል ባለመሆኑ ወላጆቻቸውም ሰርተው ልጆቻቸውን ማስተማር የሚችሉበት ሁኔታ ላይ ባለመሆናቸው፤ በተለይም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናት ምግብ ለማግኘት ወደ ልመና ይሰማራሉ" ሲሉም ተናግረዋል፡፡
አክለውም አሁን በክልሉ የሚስተዋለው ፖለቲካዊ ውጥረትም ለችግሩ መባባስ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል፡፡መንግሥትም ሆነ ረጂ ተቋማት እጃቸውን እንዲዘረጉ የጠየቁት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ፤ "እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱት ሕጻናት እንዲማሩ ለማድረግ መረባረብ የሕፃናቱን ነገ መስራት ነው" ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ግጭት ብሎም ሰው ሠራሽ እና የተፈጥሮ አደጋ በተከሰተባቸው ክልሎች በርካታ ሕጻናት እና ወጣቶች ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸው የሚገለጽ ሲሆን፤ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚህ ዓመት እንደ ሀገር ከ7 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
😭12👍7👀3❤1
የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንት በቁጥጥር ስር ዋሉ!
የደቡብ ሱዳን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ሪክ ማቻር (ዶር) በጁባ ከተማ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፓርቲያቸው የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሊቀመንበር በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
የፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር የረጅም ጊዜ ተፎካካሪ የሆኑት ማቻር "20 ከባድ የጦር መሳሪያ የታጠቁ ተሽከርካሪዎች" በተሳተፉበት ኦፕሬሽን ከቤታቸው ተወስደዋል ሲል ፓርቲያቸው ኤስፒኤልኤም-አይኦ (SPLM-IO) አስታውቋል።
ፓርቲው የፀጥታ ኃላፊዎች "ኢ-ሕገመንግስታዊ ድርጊት" ፈጸመዋል ሲል ድርጊቱን አውግዟል። በተጨማሪም ሪክ ማቻር በቁጥጥር ስር የዋሉበት ምክንያት "ግልፅ አለመሆኑንም" ገልጿል።
በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተልዕኮ እስሩ ሀገሪቷን ወደ አዲስ ግጭት እንዳያስገባ አስጠንቅቋል። የድርጅቱ ኃላፊ ኒኮላስ ሃይሶም መሪዎቹ ወደ ሰፊ ግጭት መመለስን ለማስወገድ ራሳቸውን መቆጣጠር እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንደገለጸው፤ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ለኪር እና ለማቻር ታማኝ በሆኑ ኃይሎች መካከል ግጭት ተከስቷል። የተፈጠረው ውጥረትም እያየለ ባለበት ወቅት ኖርዌይ እና ጀርመን ኤምባሲዎቻቸውን ለጊዜው ዘግተዋል።
ካለፈው ወር ጀምሮ ወደ 50,000 የሚጠጉ ሰዎች ከእላኛው ናይል አካባቢ መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል ሲል የጀርመን ድምጽ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
የደቡብ ሱዳን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ሪክ ማቻር (ዶር) በጁባ ከተማ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፓርቲያቸው የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሊቀመንበር በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
የፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር የረጅም ጊዜ ተፎካካሪ የሆኑት ማቻር "20 ከባድ የጦር መሳሪያ የታጠቁ ተሽከርካሪዎች" በተሳተፉበት ኦፕሬሽን ከቤታቸው ተወስደዋል ሲል ፓርቲያቸው ኤስፒኤልኤም-አይኦ (SPLM-IO) አስታውቋል።
ፓርቲው የፀጥታ ኃላፊዎች "ኢ-ሕገመንግስታዊ ድርጊት" ፈጸመዋል ሲል ድርጊቱን አውግዟል። በተጨማሪም ሪክ ማቻር በቁጥጥር ስር የዋሉበት ምክንያት "ግልፅ አለመሆኑንም" ገልጿል።
በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተልዕኮ እስሩ ሀገሪቷን ወደ አዲስ ግጭት እንዳያስገባ አስጠንቅቋል። የድርጅቱ ኃላፊ ኒኮላስ ሃይሶም መሪዎቹ ወደ ሰፊ ግጭት መመለስን ለማስወገድ ራሳቸውን መቆጣጠር እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንደገለጸው፤ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ለኪር እና ለማቻር ታማኝ በሆኑ ኃይሎች መካከል ግጭት ተከስቷል። የተፈጠረው ውጥረትም እያየለ ባለበት ወቅት ኖርዌይ እና ጀርመን ኤምባሲዎቻቸውን ለጊዜው ዘግተዋል።
ካለፈው ወር ጀምሮ ወደ 50,000 የሚጠጉ ሰዎች ከእላኛው ናይል አካባቢ መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል ሲል የጀርመን ድምጽ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍19👀4❤2
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአፍሪካ የመጀመሪያው ነው የተባለለትን የማስተር ካርድ የክፍያ ሥርዓት አስጀመረ!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የካርድ ክፍያ ሥርዓቱን አንድ ደረጃ ከፍ ያደርጋል የተባለለትና በኢንተርኔት ኦን ላይን መጠቀም የሚያስችል ቨርቿል ማስተር ካርድ በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከማስተር ካርድ ጋር በመተባበር ያቀረበው ማስተር ካርድ፤ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ የዓለም አቀፍ ዲጂታል ክፍያዎችን በቨርቹዋል ካርዶችን ለመጠቀም የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
ይህም የቨርቿዋል ቴክኖሎጂ ካርድ ወደ ሥራ ማስገባቱን በዛሬው ዕለት ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ በሞባይል ባንኪንግ ቨርቹዋል ካርዱን ማግኘት እንደሚቻል ተነግሯልል።
ባንኩ ዓለም አቀፍ ግልጋሎት የሚያስገኝለትን ቨርቿል ካርድ ማስጀመሩ በተመለከተ ሀሳባቸውን የሰጡት የባንኩ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ፤ 85 በመቶ የሚሆነው ዜጋ የኦንላይን ባንኪንግ የሚጠቀምበት ደረጃ ላይ መድረሱን የገለጹ ሲሆን፤ "ለዲጂታል ኢትዮጵያ ዕውን መሆን ትልቅ እርምጃ የሚሆን ሥራ ነው" ብለዋል።
ከ40 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የባንኩ ደንበኞች አገልግሎቱን ለማስጀመር ከማስተር ካርድ ጋር የተሰራው ሥራ ከፍተኛ የሆነ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጥምረት ለመስራት ያደረገውን ሥራ ያደነቁት የማስተር ካርድ የአፍሪካ ፕሬዝዳንት ማርክ ኤሊየት በበኩላቸው፤ "በዛሬዉ ዕለት አዲስ ካርድ ሳይሆን እያስተዋወቅን ያለነው ለማህበረሰቡ የሚረዳ ቨርቹዋል ካርድ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
ዲጂታል የክፍያ አማራጮችን በማቅረብ፣ ንግድ ባንክ እና ማስተር ካርድ በፋይናንሺያል አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ያለውን ክፍተት ለመቅረፍ፣ የላቀ ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎን ለማጎልበት እና የፋይናንስ አካታችነትን ለማጎልበት የታለመ መሆኑንም አንስተዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት በ2025 የዲጂታል ኢትዮጵያን ለመመስረት እያደረገው ያለው ሥራ የሚበረታታ መሆኑን በማንሳት፤ "አካታች የሆነ የኢኮኖሚ ዕድገት ለመፍጠር ይረዳል" ብለዋል።ማስተር ካርድ በ200 ሀገራት ደንበኞችን በማፍራት የሚታወቅ ሲሆን፤ ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመግንባት እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የካርድ ክፍያ ሥርዓቱን አንድ ደረጃ ከፍ ያደርጋል የተባለለትና በኢንተርኔት ኦን ላይን መጠቀም የሚያስችል ቨርቿል ማስተር ካርድ በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከማስተር ካርድ ጋር በመተባበር ያቀረበው ማስተር ካርድ፤ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ምቹ የዓለም አቀፍ ዲጂታል ክፍያዎችን በቨርቹዋል ካርዶችን ለመጠቀም የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
ይህም የቨርቿዋል ቴክኖሎጂ ካርድ ወደ ሥራ ማስገባቱን በዛሬው ዕለት ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ በሞባይል ባንኪንግ ቨርቹዋል ካርዱን ማግኘት እንደሚቻል ተነግሯልል።
ባንኩ ዓለም አቀፍ ግልጋሎት የሚያስገኝለትን ቨርቿል ካርድ ማስጀመሩ በተመለከተ ሀሳባቸውን የሰጡት የባንኩ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ፤ 85 በመቶ የሚሆነው ዜጋ የኦንላይን ባንኪንግ የሚጠቀምበት ደረጃ ላይ መድረሱን የገለጹ ሲሆን፤ "ለዲጂታል ኢትዮጵያ ዕውን መሆን ትልቅ እርምጃ የሚሆን ሥራ ነው" ብለዋል።
ከ40 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የባንኩ ደንበኞች አገልግሎቱን ለማስጀመር ከማስተር ካርድ ጋር የተሰራው ሥራ ከፍተኛ የሆነ ጠቀሜታ የሚያስገኝ መሆኑንም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጥምረት ለመስራት ያደረገውን ሥራ ያደነቁት የማስተር ካርድ የአፍሪካ ፕሬዝዳንት ማርክ ኤሊየት በበኩላቸው፤ "በዛሬዉ ዕለት አዲስ ካርድ ሳይሆን እያስተዋወቅን ያለነው ለማህበረሰቡ የሚረዳ ቨርቹዋል ካርድ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
ዲጂታል የክፍያ አማራጮችን በማቅረብ፣ ንግድ ባንክ እና ማስተር ካርድ በፋይናንሺያል አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ያለውን ክፍተት ለመቅረፍ፣ የላቀ ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎን ለማጎልበት እና የፋይናንስ አካታችነትን ለማጎልበት የታለመ መሆኑንም አንስተዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት በ2025 የዲጂታል ኢትዮጵያን ለመመስረት እያደረገው ያለው ሥራ የሚበረታታ መሆኑን በማንሳት፤ "አካታች የሆነ የኢኮኖሚ ዕድገት ለመፍጠር ይረዳል" ብለዋል።ማስተር ካርድ በ200 ሀገራት ደንበኞችን በማፍራት የሚታወቅ ሲሆን፤ ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመግንባት እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍37❤6😁4👎2🔥1
የፋኖ ታጣቂዎች በሚፈልጓቸው የአውሮፓ ሀገሮችና አደራዳሪዎች አማካይነት ድርድር እንዲደረግ መንግሥት ‘ፈቃደኛ’ ነው ተባለ!
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት የፋኖ ታጣቂዎች በሚፈልጓቸው የአውሮፓ አገሮችና አደራዳሪዎች አማካይነት ድርድሮች እንዲደረጉ መንግሥት ‘ፈቃደኛ’ መሆኑን የአማራ ክልል የሠላም ምክር ቤት አስታወቀ።የምክር ቤቱ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ያየህይራድ በለጠ፣ ምክር ቤቱ ሁለት ዓመቱን ሊደፍን የተቃረበውን የአማራ ክልል ጦርነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሁለቱም አካላት ወደ ድርድርና ውይይት እንዲመጡ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።
በዚህም በሁለቱም አካላት በኩል ለውይይትና ለድርድር “ፈቃደኛነት መታየቱን” ገልጸው "የፌደራል መንግሥት በየጊዜው ለሠላምና ለድርድር ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ዝግጁነቱን በተደጋጋሚ ገልጧል፤ በፋኖ ወገኖቻችን በኩልም በምናደርገው ግንኙንት ድርድርና ውይይት እንደማይጠሉ ነግረውናል" ብለዋል።አንደኛው ሌላኛውን ያለማመን አዝማሚያ ለውይይት የሚደረገውን ጥረት አስቸጋሪ እንዳደረገው ጠቅሰው አለመተማመኑን ለማስወገድ የፋኖ ታጣቂዎች በሚፈልጓቸው የአውሮፓ አገሮችና አደራዳሪዎች አማካይነት ድርድሮች እንዲደረጉ መንግሥት ‘ፈቃደኝነት’ ማሳየቱን ጠቁመዋል።
ይህን አስመልክቶ ከአብዛኛዎቹ የፋኖ ታጣቂዎች ጋር “ውይይቶችን እንዳደረጉ” የገለፁት አቶ ያየህይራድ፣ ከፋኖ አመራሮች ምላሽ በመጠበቅ ላይ መሆናቸውን አመልክተዋል።የአማራ ክልል የሠላም ምክር ቤት በክልሉ በሚንቀሳቀሱት የፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግሥት መካከል እየተካሄደ የሚገኘውን ጦርነት በውይይት እና በድርድር ለመቋጨት የአመቻችነት ሚናውን እንዲወጣ ሰኔ 18 ቀን 2016 ዓ.ም መመስረቱ የሚታወስ ነው።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት የፋኖ ታጣቂዎች በሚፈልጓቸው የአውሮፓ አገሮችና አደራዳሪዎች አማካይነት ድርድሮች እንዲደረጉ መንግሥት ‘ፈቃደኛ’ መሆኑን የአማራ ክልል የሠላም ምክር ቤት አስታወቀ።የምክር ቤቱ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ያየህይራድ በለጠ፣ ምክር ቤቱ ሁለት ዓመቱን ሊደፍን የተቃረበውን የአማራ ክልል ጦርነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሁለቱም አካላት ወደ ድርድርና ውይይት እንዲመጡ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።
በዚህም በሁለቱም አካላት በኩል ለውይይትና ለድርድር “ፈቃደኛነት መታየቱን” ገልጸው "የፌደራል መንግሥት በየጊዜው ለሠላምና ለድርድር ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ዝግጁነቱን በተደጋጋሚ ገልጧል፤ በፋኖ ወገኖቻችን በኩልም በምናደርገው ግንኙንት ድርድርና ውይይት እንደማይጠሉ ነግረውናል" ብለዋል።አንደኛው ሌላኛውን ያለማመን አዝማሚያ ለውይይት የሚደረገውን ጥረት አስቸጋሪ እንዳደረገው ጠቅሰው አለመተማመኑን ለማስወገድ የፋኖ ታጣቂዎች በሚፈልጓቸው የአውሮፓ አገሮችና አደራዳሪዎች አማካይነት ድርድሮች እንዲደረጉ መንግሥት ‘ፈቃደኝነት’ ማሳየቱን ጠቁመዋል።
ይህን አስመልክቶ ከአብዛኛዎቹ የፋኖ ታጣቂዎች ጋር “ውይይቶችን እንዳደረጉ” የገለፁት አቶ ያየህይራድ፣ ከፋኖ አመራሮች ምላሽ በመጠበቅ ላይ መሆናቸውን አመልክተዋል።የአማራ ክልል የሠላም ምክር ቤት በክልሉ በሚንቀሳቀሱት የፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግሥት መካከል እየተካሄደ የሚገኘውን ጦርነት በውይይት እና በድርድር ለመቋጨት የአመቻችነት ሚናውን እንዲወጣ ሰኔ 18 ቀን 2016 ዓ.ም መመስረቱ የሚታወስ ነው።
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
👍65😁37👎12❤9🔥1
አየር መንገዱ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አውሮፕላኖችን አገልግሎት ላይ ለማዋል ስምምነት ተፈራረመ!
የኢትዮጵያ አየር መንገድና አርቸር አቪዬሽን በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈራረማቸውን አየር መንገዱ አስታወቀ፡፡
ስምምነቱ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አውሮፕላኖችን በአየር ትርንስፖርት አገልግሎት ላይ ለማዋልና በአርቸር ኤር የበረራ ፕሮግራም መሰረት በሌሊት የሚደረጉ የጭነት በረራ አገልግሎቶችን ለመስጠት ያለመ ነው ተብሏል፡፡
ዘመኑ የደረሰበትን የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ከማስቻሉ ባለፈም ለአየር ንብረት ጥበቃ የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል ብሏል፤ አየር መንገዱ፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ አየር መንገድና አርቸር አቪዬሽን በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈራረማቸውን አየር መንገዱ አስታወቀ፡፡
ስምምነቱ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አውሮፕላኖችን በአየር ትርንስፖርት አገልግሎት ላይ ለማዋልና በአርቸር ኤር የበረራ ፕሮግራም መሰረት በሌሊት የሚደረጉ የጭነት በረራ አገልግሎቶችን ለመስጠት ያለመ ነው ተብሏል፡፡
ዘመኑ የደረሰበትን የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ከማስቻሉ ባለፈም ለአየር ንብረት ጥበቃ የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል ብሏል፤ አየር መንገዱ፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍21😁17👎10😭8❤4👀3
ፋና ሚዲያ ምሽት 3 ሰዓት ላይ "የብርቱካን እዉነት" የሚል ፕሮግራም በቴሌቪዥን ጣቢያዉ ላይ እንደሚያሰራጭ አሳዉቋል።
ከሰሞኑ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ላይ ቀርባ የነበረችዉ ብርቱካን ተመስገን ፕሮግራሟ ከተሰራጨ በኋላ ዉዝግብ አስነስቶ ጣቢያዉም ምላሽ ሰጥቶበት ነበር። በወቅቱ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ገጽ ላይ ተለጥፎ የነበረዉ የወጣቷ ታሪክን የሚዳስሰዉ ፕሮግራም ዉሉ ባልታወቀ ምክኒያት እንዲጠፋ ተደርጓል።
ብርቱካን በወቅቱ የደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ተማሪ በነበረችበት ወቅት "ታግቼ ነበር" ማለቷን ተከትሎም ዩኒቨርስቲው ማስተባበያ እንደሰጠ ዳጉ ጆርናል መረጃዉን ማድረሱ ይታወሳል።
ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት መነጋገሪያ የነበረዉ የብርቱካን ተመስገንን ጉዳይ ይሁን ሌላ በዉል ሳያሳዉቅ ግን መንግስታዊዉ ሚዲያ ፋና "የብርቱካን እዉነት" የሚል ፕሮግራሙ ዛሬ ምሽት 3 ሰዓት ይሰራጫል ብሏል።
@Yenetube @Fikerassefa
ከሰሞኑ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ላይ ቀርባ የነበረችዉ ብርቱካን ተመስገን ፕሮግራሟ ከተሰራጨ በኋላ ዉዝግብ አስነስቶ ጣቢያዉም ምላሽ ሰጥቶበት ነበር። በወቅቱ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ገጽ ላይ ተለጥፎ የነበረዉ የወጣቷ ታሪክን የሚዳስሰዉ ፕሮግራም ዉሉ ባልታወቀ ምክኒያት እንዲጠፋ ተደርጓል።
ብርቱካን በወቅቱ የደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ተማሪ በነበረችበት ወቅት "ታግቼ ነበር" ማለቷን ተከትሎም ዩኒቨርስቲው ማስተባበያ እንደሰጠ ዳጉ ጆርናል መረጃዉን ማድረሱ ይታወሳል።
ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት መነጋገሪያ የነበረዉ የብርቱካን ተመስገንን ጉዳይ ይሁን ሌላ በዉል ሳያሳዉቅ ግን መንግስታዊዉ ሚዲያ ፋና "የብርቱካን እዉነት" የሚል ፕሮግራሙ ዛሬ ምሽት 3 ሰዓት ይሰራጫል ብሏል።
@Yenetube @Fikerassefa
👎115👍44😁15❤2
የአዲስ አበባ ባንኮች እስከ ምሽት 3 ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ ተጠየቀ!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የንግድ ቢሮ ባንኮች እስከ ምሽት 3 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እንዲሰጡ ለብሔራዊ ባንክ ጥያቄ አቅርቧል።
የንግድ ቢሮው እንዳለዉ እንደማንኛውም አገልግሎት ሰጪ የንግድ ተቋማት ዋና ዋና መንገድ ላይ የሚገኙ ባንኮች እስከ ምሽቱ 3 : 30 ድረስ አገልግሎት የሚሰጡበት አሰራር እንዲዘረጋ የትብብር ጥያቄ የቀረበዉ።
ዋና ዋና መንገድ ላይ የሚገኙ የንግድ ተቋማት እስከ ምሽቱ 3:30 ድረስ እንዲሰሩ ከተወሰነ ብዙ ባንኮችም በዚሁ መስመር ላይ የሚገኙ በመሆኑ የአገልግሎት ሰዓታቸውን ማራዘም ለንግድ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ ያደርጋል ያደርጋል መባሉን ቅዳሜ ገበያ ሰምታለች።
ይህን ተከትሎ ቢሮው በቀጥታ ባንኮችን የማዘዝ ስልጣን ስለሌለው የትብብር ጥያቄው በደብዳቤ ለማዕከላዊ ባንኩ ማቅረቡን ነዉ ለመረዳት የተቻለዉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ደምብ 185/2017 የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ምሽት 4 ሰዓት ድረስ በመንገድ ዳር የሚገኙ የንግድ ተቋማት ደግሞ ምሽት 3:30 ድረስ እንዲቆዩ የሚያስገድድ ደምብ ከመጋቢት 10 ጀምሮ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል።
《ቅዳሜገበያ》
@YeneTube @Fikerassefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የንግድ ቢሮ ባንኮች እስከ ምሽት 3 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እንዲሰጡ ለብሔራዊ ባንክ ጥያቄ አቅርቧል።
የንግድ ቢሮው እንዳለዉ እንደማንኛውም አገልግሎት ሰጪ የንግድ ተቋማት ዋና ዋና መንገድ ላይ የሚገኙ ባንኮች እስከ ምሽቱ 3 : 30 ድረስ አገልግሎት የሚሰጡበት አሰራር እንዲዘረጋ የትብብር ጥያቄ የቀረበዉ።
ዋና ዋና መንገድ ላይ የሚገኙ የንግድ ተቋማት እስከ ምሽቱ 3:30 ድረስ እንዲሰሩ ከተወሰነ ብዙ ባንኮችም በዚሁ መስመር ላይ የሚገኙ በመሆኑ የአገልግሎት ሰዓታቸውን ማራዘም ለንግድ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ ያደርጋል ያደርጋል መባሉን ቅዳሜ ገበያ ሰምታለች።
ይህን ተከትሎ ቢሮው በቀጥታ ባንኮችን የማዘዝ ስልጣን ስለሌለው የትብብር ጥያቄው በደብዳቤ ለማዕከላዊ ባንኩ ማቅረቡን ነዉ ለመረዳት የተቻለዉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ደምብ 185/2017 የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ምሽት 4 ሰዓት ድረስ በመንገድ ዳር የሚገኙ የንግድ ተቋማት ደግሞ ምሽት 3:30 ድረስ እንዲቆዩ የሚያስገድድ ደምብ ከመጋቢት 10 ጀምሮ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል።
《ቅዳሜገበያ》
@YeneTube @Fikerassefa
👍96👎44😁23❤3