Facebook, Twitter, Instagram እና በመሳሳሉት የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ድርጅትዎን ፤ አገልግሎትዎን እና ምርትዎን ማስተዋወቅ ፈልገዋል? እንግዲያውስ መፍትሄው እኛ ጋር ነው።
በማንኛውም Social Media Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::
ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።
Telegram: @adsommar
📞0929334267
በማንኛውም Social Media Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::
ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።
Telegram: @adsommar
📞0929334267
👍10❤1
ፓስፖርት ለማግኘት የሚጠባበቁ ከ 300 ሺህ በላይ ሰዎች መኖራቸውን የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አሳወቀ!
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ አመራር ከተሾመለት ወዲህ ላለፈዉ አንድ ወር ያከናወነዉን የማሻሻያ ስራ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዛሬዉ እለት ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአሁኑ ሰዓት በአገልግሎቱ ፓስፖርት ለማግኘት ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ያሉ ከ 300 ሺህ በላይ ዜጎች መኖራቸዉን ዋና ዳይሬክተሯ ገልጸዋል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲሷ ዳይሬክተር ፤ ላለፈዉ አንድ ወር በተቋማቸዉ አሉ ያሏቸዉን ችግሮች ለመቅረፍ ምልከታ ማድረጋቸዉን ተናግረዋል።
በዚህም ተቋሙ የአጭር ፣ መካከለኛ እና የረጅም ጊዜ እቅድ ነድፎ እየሰራ ነዉ ብለዋል። በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የሚነሳዉን እና ዜጎችን ያማረረዉ የሌብነት እና ብልሹ አሰራር ለመቅረፍ አዲስ የአሰራር መንገድ በመዘርጋት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በርከት ባሉ የተቋሙ ዳይሬክተሮች ፣ ሰራተኞች እና በጊቢዉ ዙሪያ ባሉ ማስረጃ በተገኘባቸዉ ደላሎች ላይ ከአስተዳደራዊ እስከ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የተከሰተዉን ከፍ ያለ የፓስፖርት እጥረት ለመቅረፍ በዉጪ ከሚገኝ አምራች ተቋም ጋር ከስምምነት መድረሳቸዉን ጠቅሰዋል። ለእጥረቱ የዉጪ ምንዛሬ እጥረት እና አለማቀፍ ምክኒያቶች መንስኤ ነበሩ ብለዋል። ችግሩ አሁን በመጠኑ በመቀረፉ 190 ሺህ አዲስ ፓስፖርት ማተም መቻሉን ገልጸዉ ፤ አንገብጋቢ ለሆኑ ጉዳዮች ማለትም በአረቡ አለም ለሚገኙና በተለያዩ የዉጪ ሀገራት ካለ ፓስፖርት ለሚኖሩ ዜጎች ቅድሚያ መሰጠቱን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ባለፉት 90 ቀናት ዉስጥ የፓስፖርት ቀጠሮአቸው በተለያዩ ምክኒያቶች ያለፋቸዉ ሰዎች ዘወትር ቅዳሜ አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቅሰዋል። ወደ ኢትዮጵያ ከዉጭ በሚመጡ ሰዎች ላይም ቪዛ ለማግኘት በነበረዉ ሂደት ይፈጸም ነበር ያሉትን ሌብነት ለመቀነስ ዘመናዊ አሰራር ተዘርግቷል ነዉ ያሉት። ወደ ኢትዮጵያ በገቡበት ሰዓትም ወዲያዉኑ ቪዛ የሚያገኙበትን On Arrival Visa ከመስከረም 15 ቀን ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል ብለዋል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ፤ የቀጠሮ መያዣ ስርዓቱ የመሳስሎ ተሰርቶ ለደላሎች እና ሌቦች ተጋልጦ የነበረ መሆኑን ፣ አሰራሩ ዘመኑን ያልዋጀ እና ኋላ ቀር የነበረ መሆኑን ፣ እነዚህና ሌሎች ጥቃቅን ችግሮችን በተደራራቢነት የሚያመጡ ክፍተቶች ነበሩበት ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ አመራር ከተሾመለት ወዲህ ላለፈዉ አንድ ወር ያከናወነዉን የማሻሻያ ስራ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በዛሬዉ እለት ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአሁኑ ሰዓት በአገልግሎቱ ፓስፖርት ለማግኘት ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ያሉ ከ 300 ሺህ በላይ ዜጎች መኖራቸዉን ዋና ዳይሬክተሯ ገልጸዋል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲሷ ዳይሬክተር ፤ ላለፈዉ አንድ ወር በተቋማቸዉ አሉ ያሏቸዉን ችግሮች ለመቅረፍ ምልከታ ማድረጋቸዉን ተናግረዋል።
በዚህም ተቋሙ የአጭር ፣ መካከለኛ እና የረጅም ጊዜ እቅድ ነድፎ እየሰራ ነዉ ብለዋል። በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የሚነሳዉን እና ዜጎችን ያማረረዉ የሌብነት እና ብልሹ አሰራር ለመቅረፍ አዲስ የአሰራር መንገድ በመዘርጋት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በርከት ባሉ የተቋሙ ዳይሬክተሮች ፣ ሰራተኞች እና በጊቢዉ ዙሪያ ባሉ ማስረጃ በተገኘባቸዉ ደላሎች ላይ ከአስተዳደራዊ እስከ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የተከሰተዉን ከፍ ያለ የፓስፖርት እጥረት ለመቅረፍ በዉጪ ከሚገኝ አምራች ተቋም ጋር ከስምምነት መድረሳቸዉን ጠቅሰዋል። ለእጥረቱ የዉጪ ምንዛሬ እጥረት እና አለማቀፍ ምክኒያቶች መንስኤ ነበሩ ብለዋል። ችግሩ አሁን በመጠኑ በመቀረፉ 190 ሺህ አዲስ ፓስፖርት ማተም መቻሉን ገልጸዉ ፤ አንገብጋቢ ለሆኑ ጉዳዮች ማለትም በአረቡ አለም ለሚገኙና በተለያዩ የዉጪ ሀገራት ካለ ፓስፖርት ለሚኖሩ ዜጎች ቅድሚያ መሰጠቱን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ባለፉት 90 ቀናት ዉስጥ የፓስፖርት ቀጠሮአቸው በተለያዩ ምክኒያቶች ያለፋቸዉ ሰዎች ዘወትር ቅዳሜ አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቅሰዋል። ወደ ኢትዮጵያ ከዉጭ በሚመጡ ሰዎች ላይም ቪዛ ለማግኘት በነበረዉ ሂደት ይፈጸም ነበር ያሉትን ሌብነት ለመቀነስ ዘመናዊ አሰራር ተዘርግቷል ነዉ ያሉት። ወደ ኢትዮጵያ በገቡበት ሰዓትም ወዲያዉኑ ቪዛ የሚያገኙበትን On Arrival Visa ከመስከረም 15 ቀን ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል ብለዋል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ፤ የቀጠሮ መያዣ ስርዓቱ የመሳስሎ ተሰርቶ ለደላሎች እና ሌቦች ተጋልጦ የነበረ መሆኑን ፣ አሰራሩ ዘመኑን ያልዋጀ እና ኋላ ቀር የነበረ መሆኑን ፣ እነዚህና ሌሎች ጥቃቅን ችግሮችን በተደራራቢነት የሚያመጡ ክፍተቶች ነበሩበት ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍24❤2🔥1
አጎአን ጨምሮ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ የጣለውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት አራዘመ!
- እ.ኤ.አ. መስከረም 2021 ከሁለት ዓመታት በፊት በአሜሪካ ኤግዚኪዩቲቭ ኦርደር 14046 መሰረት በብሄራዊ ደህንነት እና የውጭ ፖሊሲ ላይ የተደቀነ ስጋትን ለመቋቋም በሚል ከትግራይ ክልል ጦርነት ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የጣለውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት አራዝሟል።
- የኢትዮጵያ መንግስት እና ባለስልጣናት ማዕቀቡን በተደጋጋሚ “በውስጥ ጉዳይ ተገብቶ የተጣለ ማዕቀብ” በማለት የሚጠሩት ሲሆን በ2013 ዓ.ም. በድሬዳዋ ከተማ የተደረገውን ጨምሮ የአሜሪካ ማዕቀብ በኢትዮጵያ ላይ ሊያሳድር በሚችለው ጫና ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ሲደረጉ ተስተውሏል።
- ማዕቀቦቹ የኢትዮጵያ እንዲሁም የኤርትራ ባለስልጣናት፣ ወታደራዊ ሰራተኞች እና ሌሎች ግለሰቦች የቪዛ እገዳ፣ በትግራይ ክልል እና በኢትዮጵያ ለተስፋፋው ብጥብጥ፣ ግፍ እና ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጠያቂ የሆኑ አካላት እና ግለሰቦች ላይም ልዩ ማዕቀቦችን ያካተተ ነው።
- በተጨማሪም የመከላከያ አገልግሎቶችም ሆኑ መሳሪያዎች ለኢትዮጵያ እና ኤርትራ የታጠቁ ኃይሎች፣ ለፖሊስ፣ ለስለላ ወይም ለሌሎች የውስጥ ደኅንነት ኃይሎች እንዳይላኩ እንዲሁም ኢትዮጵያ በዓመት እስከ 100 ሚልየን ዶላር ገቢ ታገኝበት የነበረው የአፍሪካ የዕድገትና ዕድል ሕግ (አጎአ) ከቀረጥ ነፃ የአሜሪካን ገበያ ተጠቃሚነትን ማሳጣት ለሚቀጥለው አንድ ዓመት ከሚቀጥሉ ማዕቀቦች ዋነኞቹ ናቸው።
- ማዕቀቦቹ አሁን ለሁለተኛ ጊዜ የተራዘሙ ሲሆን እስከ መስከረም 2024 ይፀናሉ።
✍️Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
- እ.ኤ.አ. መስከረም 2021 ከሁለት ዓመታት በፊት በአሜሪካ ኤግዚኪዩቲቭ ኦርደር 14046 መሰረት በብሄራዊ ደህንነት እና የውጭ ፖሊሲ ላይ የተደቀነ ስጋትን ለመቋቋም በሚል ከትግራይ ክልል ጦርነት ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የጣለውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት አራዝሟል።
- የኢትዮጵያ መንግስት እና ባለስልጣናት ማዕቀቡን በተደጋጋሚ “በውስጥ ጉዳይ ተገብቶ የተጣለ ማዕቀብ” በማለት የሚጠሩት ሲሆን በ2013 ዓ.ም. በድሬዳዋ ከተማ የተደረገውን ጨምሮ የአሜሪካ ማዕቀብ በኢትዮጵያ ላይ ሊያሳድር በሚችለው ጫና ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ሲደረጉ ተስተውሏል።
- ማዕቀቦቹ የኢትዮጵያ እንዲሁም የኤርትራ ባለስልጣናት፣ ወታደራዊ ሰራተኞች እና ሌሎች ግለሰቦች የቪዛ እገዳ፣ በትግራይ ክልል እና በኢትዮጵያ ለተስፋፋው ብጥብጥ፣ ግፍ እና ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጠያቂ የሆኑ አካላት እና ግለሰቦች ላይም ልዩ ማዕቀቦችን ያካተተ ነው።
- በተጨማሪም የመከላከያ አገልግሎቶችም ሆኑ መሳሪያዎች ለኢትዮጵያ እና ኤርትራ የታጠቁ ኃይሎች፣ ለፖሊስ፣ ለስለላ ወይም ለሌሎች የውስጥ ደኅንነት ኃይሎች እንዳይላኩ እንዲሁም ኢትዮጵያ በዓመት እስከ 100 ሚልየን ዶላር ገቢ ታገኝበት የነበረው የአፍሪካ የዕድገትና ዕድል ሕግ (አጎአ) ከቀረጥ ነፃ የአሜሪካን ገበያ ተጠቃሚነትን ማሳጣት ለሚቀጥለው አንድ ዓመት ከሚቀጥሉ ማዕቀቦች ዋነኞቹ ናቸው።
- ማዕቀቦቹ አሁን ለሁለተኛ ጊዜ የተራዘሙ ሲሆን እስከ መስከረም 2024 ይፀናሉ።
✍️Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
👍50👎14❤2
በፀጥታ ችግር ፈተና ያልወሰዱ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ከመስከረም 8 ቀን ጀምሮ ይፈተናሉ!
በፀጥታ ችግርና በሌሎች ምክንያቶች ፈተና ያልወሰዱ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን ለመፈተን መዘጋጀቱን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፊኬት (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሁለት ዙር መሰጠቱን አገልግሎቱ አስታውሷል፡፡
ይሁንና በጎንደርና በጋምቤላ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ እና በከፊል 14 ሺህ 891 ተማሪዎች እንዲሁም በሕህ ግ ጥላ ስር በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ 419 ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን ሳይወስዱ መቅረታቸው ተጠቅሷል፡፡
ተፈታኞችን ከመጪው መስከረም 8 እስከ መስከረም 11 ቀን 2016 ዓ.ም ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ውጤታቸውም ከመጀመሪያው ዙር ጋር እንደሚገለጽም የአገልግሎቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በፀጥታ ችግርና በሌሎች ምክንያቶች ፈተና ያልወሰዱ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን ለመፈተን መዘጋጀቱን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፊኬት (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሁለት ዙር መሰጠቱን አገልግሎቱ አስታውሷል፡፡
ይሁንና በጎንደርና በጋምቤላ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ እና በከፊል 14 ሺህ 891 ተማሪዎች እንዲሁም በሕህ ግ ጥላ ስር በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ 419 ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን ሳይወስዱ መቅረታቸው ተጠቅሷል፡፡
ተፈታኞችን ከመጪው መስከረም 8 እስከ መስከረም 11 ቀን 2016 ዓ.ም ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ውጤታቸውም ከመጀመሪያው ዙር ጋር እንደሚገለጽም የአገልግሎቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍15❤4
የዛሬ ጨዋታዎች የቤትስኬት ግምት
ማሊ፣ ስፔን፣ ፖርቹጋልን እና ሌቫንቴን የተመለከቱ የቤቲንግ መረጃዎች እና ግምቶች በቤትስኬት
ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ👇👇
http://www.betsket.com/የዛሬ-ጨዋታዎች-የቤትስኬት-ግምት/
ሁል ጊዜ የሚለቀቁ መረጃዎችን በአንድ ላይ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።👉 @betskett
ማሊ፣ ስፔን፣ ፖርቹጋልን እና ሌቫንቴን የተመለከቱ የቤቲንግ መረጃዎች እና ግምቶች በቤትስኬት
ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ👇👇
http://www.betsket.com/የዛሬ-ጨዋታዎች-የቤትስኬት-ግምት/
ሁል ጊዜ የሚለቀቁ መረጃዎችን በአንድ ላይ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።👉 @betskett
👍2❤1
የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ ለተጨዋቾች ግዥ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አደረገ!
የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ ለተጨዋቾች ግዥ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አደረገ።የዘንድሮው የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ሲዘጋ የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አውጥቷል።
አዲስ የእግር ኳስ መናኸሪያ መሆኗን ያስታወቀችው የነዳጅ ባለጸጋዋ ሳኡዲ አረቢያ ትናንት በባቃው የተጨዋቾች ዝውውር 1 ቢሊዮን ዶላር ማውጣቷን ኤፒ ዘግቧል።በቅርቡ ስሙ የገነነው የሳኡዲ ፕሮሊግ በበርካታ የአውሮፖ ሊግ ታዋቂ ተጨዋቾች መዳረሻ እየሆነ መጥቷል።
ሳኡዲ አረቢያ እግር ኳስን ጨምሮ በጎልፍ፣ በቦክስ፣ ፎርሙላ ዋን ሬሲንግ እና በቴኒስ ላይ ኢንቨስት እያደረገች።ፕሮሊግ በተጠናቀቀው የዝወውር መስኮት ያለወጣው ወጭ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ካወጫው ወጭ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ የሚቀመጥ መሆኑን ሮይተርስን ጠቅሶ አል-ዐይን ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ ለተጨዋቾች ግዥ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አደረገ።የዘንድሮው የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ሲዘጋ የሳኡዲ አረቢያው ፕሮሊግ 1 ቢሊዮን ዶላር ወጭ አውጥቷል።
አዲስ የእግር ኳስ መናኸሪያ መሆኗን ያስታወቀችው የነዳጅ ባለጸጋዋ ሳኡዲ አረቢያ ትናንት በባቃው የተጨዋቾች ዝውውር 1 ቢሊዮን ዶላር ማውጣቷን ኤፒ ዘግቧል።በቅርቡ ስሙ የገነነው የሳኡዲ ፕሮሊግ በበርካታ የአውሮፖ ሊግ ታዋቂ ተጨዋቾች መዳረሻ እየሆነ መጥቷል።
ሳኡዲ አረቢያ እግር ኳስን ጨምሮ በጎልፍ፣ በቦክስ፣ ፎርሙላ ዋን ሬሲንግ እና በቴኒስ ላይ ኢንቨስት እያደረገች።ፕሮሊግ በተጠናቀቀው የዝወውር መስኮት ያለወጣው ወጭ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ካወጫው ወጭ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ የሚቀመጥ መሆኑን ሮይተርስን ጠቅሶ አል-ዐይን ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍21👎2❤1
ዛሬ ምሽት በተካሄደው በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በግብፅ አቻው 1 ለ 0 ተሸንፏል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2023 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታ ከግብጽ አቻው ጋር አካሂዷል፡፡ሁለቱ ቡድኖች ጨዋታቸውን በካይሮ አየር ሃይል ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ አድርገዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ የግብጽ ብሄራዊ ቡድን ምድቡን በበላይነት አጠናቋል።በአንጻሩ ዋልያዎቹ የማጣሪያ ውድድራቸውን በአራቱ ተሸንፈው አንድ አቻ በመውጣት እና አንድ ጨዋታ በማሸነፍ በአራት ነጥብ የምድቡን የመጨረሻ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2023 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታ ከግብጽ አቻው ጋር አካሂዷል፡፡ሁለቱ ቡድኖች ጨዋታቸውን በካይሮ አየር ሃይል ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ አድርገዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ የግብጽ ብሄራዊ ቡድን ምድቡን በበላይነት አጠናቋል።በአንጻሩ ዋልያዎቹ የማጣሪያ ውድድራቸውን በአራቱ ተሸንፈው አንድ አቻ በመውጣት እና አንድ ጨዋታ በማሸነፍ በአራት ነጥብ የምድቡን የመጨረሻ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
👎50👍23❤2🔥1
የግል ንግድ ባንኮች በገጠማቸው የጥሬ ገንዘብ እጥረት መክፈል ወደማቆም መድረሳቸውን ቢናገሩም ፤ የብሔራዊ ባንክ ም/ል ገዢ ችግሩ የለም ብለዋል
👉🏼 ባለሃብቶች ወደ ኋላቀር የካዝና ቁጠባ ዘዴ መመለሳቸዉን ተናግረዋል
የግል ንግድ ባንኮች የገጠማቸው የጥሬ ገንዘብ እጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ቀጥሎ ለደንበኞቻቸው መክፈል የማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ዋዜማ ያሰባሰበችው መረጃ ያመለክታል። የጥሬ ገንዘብ ዕጥረቱን ተከትሎ፣ ባለሀብቶችና ነጋዴዎች ጥሬ ገንዘብ ወደ ባንክ ከማስገባት ይልቅ ሌሎች አማራጮችን ለመጠቀም እንደተገደዱ ነግረውናል ስትል ዋዜማ ራዲዮ ዘግባለች። ያነጋገርናቸው ነጋደዎች እና ባለሀብቶች፣ ገንዘባቸውን ቀስ በቀስ ከባንክ እያወጡ በግል ካዝናና ስውር ቦታዎች ማስቀመጥ መምረጣቸውን ይናገራሉ። የባለሀብቶቹ ስጋት በባንክ የተቀመጠ ገንዘባቸውን በፈለጉት ፍጥነት ለማግኘት በመቸገራቸውና የተለያዩ ገደቦች ስለተጣለባቸው ነው።
አንዳንድ ባንኮች ባለፉት ወራት አልፎ አልፎ ለተመረጡ ደንበኞች ሲፈቅዱ የነበረውን ከባንክ ወደ ባንክ የገንዘብ ዝውውር (RTGS) አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ወደማቆም እየመጡ መሆናቸው የባንክ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡ ዋዜማ ከነጋገረቻቸው የግል ንግድ ባንክ የሥራ ኃላፊዎች አንዱ “ዛሬ አንድ ሚሊየን ብር አስገብቶ ነገ ሲመጣ የሚፈልገውን ያክል ወጪ እንደማልሰጠው እያወቀ እንዴት ይመጣል?” ሲሉ የነጋዴዎች ጥሬ ገንዘብ መከዘን ገንዘባቸውን በፈለጉበት ጊዜ ማንቀሳቀስ አለመቻል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዋዜማ ያጋገረቻቸው የተለያዩ ባንኮች የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች፣ የሚመሩትን ቅርንጫፍ ከ50 ሺህ ብር ባነሰ አዳሪ ገንዘብ ዕለታዊ ሂሳባቸውን የሚዘጉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቁመዋል፡፡ የባንክ ቀርንጫፎች ለደንበኞቻቸው የሚከፍሉት ገንዘብ ሲያጥራቸው ከዋና መስሪያ ቤት (ትሬዠሪ) ገንዘብ እንዲላክላቸው በስፋት ጥያቄ እያቀረቡ ቢሆንም፣ ዋና መስሪያ ቤት ቋት ላይ እጥረቱ ስለበረታ የጠየቁትን ያክል ማግኘት አንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡
በተለይ ለተርታ ለደንበኞቻቸው የሚፈቅዱት ዕለታዊ ወጭ አንዳንዶ ከ10 ሺሕ ብር ያልበለጠ ሲሆን፣ ከፍተኛ የደንበኞች ቅሬታ እያስተገዱ ነው፡፡ በብሔራዊ ባንክ ሕግ መሰረት አንድ የባንክ ደንበኛ በቀን እስከ 50 ሺሕ ብር ጥሬ ገንዘብ የማውጣት መብት አለው፡፡ ከተከሰተ ወራት ያስቆጠረው የጥሬ ገንዘብ እጥረት አሁን ላይ በተለይ የግል ባንኮችን በእጅጉ እየፈተነ መሆኑን ዋዜማ ከተለያዩ የባንክ ምንጮቿ ሰምታለች፡፡
ቀድም ሲል በተለይ አነስተኛ አቅም ካለቸው ባንኮች መካከል የሚመደቡት ላይ በርትቶ የነበረው የጥሬ ገንዘብ እጥረት፣ አሁን ላይ አንጋፋ የግል ንግድ ባንኮች ላይም መበርታቱን ዋዜማ ከራሳቸው ከባንኮቹ ምንጮቿ አረጋግጣለች። ችግሩ ከበረታባቸው የግል ባንኮች መካከል አንዱ በተለይ የነዳጅ ክፍያ በቴሌ ብር አማካኝነት እንዲሰበሰብ መወሰኑን ተከትሎ፣ በየቀኑ ከነዳጅ አዳዮች የሚያገኘውን በሚሊየን የሚቆጠር የጥሬ ገንዘብ ገቢ ማጣቱ ችግር ውስጥ እንዳስገባው የባንኩ ምንጮች ነገረውናል፡፡ የግል ንግድ ባንኮች በገጠማቸው የመከፈል አቅም ውስንነት በርካታ የባንክ ደንበኞቻቸው የሚያንቀሳቅሱትን ገንዘብ ወደ መንግሥታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማዞራቸውን ከግል ባንኮች ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እስካሁን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ውስጥ ካለመግባቱም በላይ ከዚህ ቀደሙ የተሻለ ጥሬ ገንዘብ በስፋት እየሰበሰበ ነው፡፡ ባንኩ ደንበኞች ገንዘባቸውን በሚፈልጉበት ጊዜ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው ጣሪያ ልክ፣ ያለገደብ ጥሬ ገንዘብ ማውጣት የሚችሉበት ብቸኛ ባንክ ሆኗል፡፡ ዋዜማ በባንኮች በኩል ያገኘችውን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ችግር የባንኮች ተቆጣጣሪ አካል እንዴት እንደሚመለከተው የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥን ፍቃዱ ደግፌን የጠየቀች ሲሆን፣ ባንኮች በሚሉት ደረጃ እጥረት መኖሩን የባንኩ መረጃ እንደማያመላክት ነግረዋታል፡፡
ፍቃዱ ጉዳዩን “እኔ ባለኝ መረጃ ባንኮች ላይ በሚባለው ደረጃ የጥሬ ገንዘብ እጥረት (ሊኪዩዲቲ) የለም” ብለዋል፡፡ ባንኮች ከነዳጅ አዳዮችና ከሌሎች የተለያዩ ደንበኞች በየእለቱ ያገኙት የነበረውን የጥሬ ገንዘብ ገቢ በግዴታ ወደ ቴሌ ብር ስርዓት መቀየሩን ተክትሎ ገጥሞናል ያሉትን ችግር በተመለከተ፣ ምክትል ገዥው ለዋዜማ በሰጧት አስተያየት፣ “እጥረት አለብን ካሉ ተወዳድሮ መሰብሰብ ነው የሚከለክል ሕግ የለም” በማለት ገልጸውታል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
👉🏼 ባለሃብቶች ወደ ኋላቀር የካዝና ቁጠባ ዘዴ መመለሳቸዉን ተናግረዋል
የግል ንግድ ባንኮች የገጠማቸው የጥሬ ገንዘብ እጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ቀጥሎ ለደንበኞቻቸው መክፈል የማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ዋዜማ ያሰባሰበችው መረጃ ያመለክታል። የጥሬ ገንዘብ ዕጥረቱን ተከትሎ፣ ባለሀብቶችና ነጋዴዎች ጥሬ ገንዘብ ወደ ባንክ ከማስገባት ይልቅ ሌሎች አማራጮችን ለመጠቀም እንደተገደዱ ነግረውናል ስትል ዋዜማ ራዲዮ ዘግባለች። ያነጋገርናቸው ነጋደዎች እና ባለሀብቶች፣ ገንዘባቸውን ቀስ በቀስ ከባንክ እያወጡ በግል ካዝናና ስውር ቦታዎች ማስቀመጥ መምረጣቸውን ይናገራሉ። የባለሀብቶቹ ስጋት በባንክ የተቀመጠ ገንዘባቸውን በፈለጉት ፍጥነት ለማግኘት በመቸገራቸውና የተለያዩ ገደቦች ስለተጣለባቸው ነው።
አንዳንድ ባንኮች ባለፉት ወራት አልፎ አልፎ ለተመረጡ ደንበኞች ሲፈቅዱ የነበረውን ከባንክ ወደ ባንክ የገንዘብ ዝውውር (RTGS) አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ወደማቆም እየመጡ መሆናቸው የባንክ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡ ዋዜማ ከነጋገረቻቸው የግል ንግድ ባንክ የሥራ ኃላፊዎች አንዱ “ዛሬ አንድ ሚሊየን ብር አስገብቶ ነገ ሲመጣ የሚፈልገውን ያክል ወጪ እንደማልሰጠው እያወቀ እንዴት ይመጣል?” ሲሉ የነጋዴዎች ጥሬ ገንዘብ መከዘን ገንዘባቸውን በፈለጉበት ጊዜ ማንቀሳቀስ አለመቻል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዋዜማ ያጋገረቻቸው የተለያዩ ባንኮች የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች፣ የሚመሩትን ቅርንጫፍ ከ50 ሺህ ብር ባነሰ አዳሪ ገንዘብ ዕለታዊ ሂሳባቸውን የሚዘጉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ጠቁመዋል፡፡ የባንክ ቀርንጫፎች ለደንበኞቻቸው የሚከፍሉት ገንዘብ ሲያጥራቸው ከዋና መስሪያ ቤት (ትሬዠሪ) ገንዘብ እንዲላክላቸው በስፋት ጥያቄ እያቀረቡ ቢሆንም፣ ዋና መስሪያ ቤት ቋት ላይ እጥረቱ ስለበረታ የጠየቁትን ያክል ማግኘት አንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡
በተለይ ለተርታ ለደንበኞቻቸው የሚፈቅዱት ዕለታዊ ወጭ አንዳንዶ ከ10 ሺሕ ብር ያልበለጠ ሲሆን፣ ከፍተኛ የደንበኞች ቅሬታ እያስተገዱ ነው፡፡ በብሔራዊ ባንክ ሕግ መሰረት አንድ የባንክ ደንበኛ በቀን እስከ 50 ሺሕ ብር ጥሬ ገንዘብ የማውጣት መብት አለው፡፡ ከተከሰተ ወራት ያስቆጠረው የጥሬ ገንዘብ እጥረት አሁን ላይ በተለይ የግል ባንኮችን በእጅጉ እየፈተነ መሆኑን ዋዜማ ከተለያዩ የባንክ ምንጮቿ ሰምታለች፡፡
ቀድም ሲል በተለይ አነስተኛ አቅም ካለቸው ባንኮች መካከል የሚመደቡት ላይ በርትቶ የነበረው የጥሬ ገንዘብ እጥረት፣ አሁን ላይ አንጋፋ የግል ንግድ ባንኮች ላይም መበርታቱን ዋዜማ ከራሳቸው ከባንኮቹ ምንጮቿ አረጋግጣለች። ችግሩ ከበረታባቸው የግል ባንኮች መካከል አንዱ በተለይ የነዳጅ ክፍያ በቴሌ ብር አማካኝነት እንዲሰበሰብ መወሰኑን ተከትሎ፣ በየቀኑ ከነዳጅ አዳዮች የሚያገኘውን በሚሊየን የሚቆጠር የጥሬ ገንዘብ ገቢ ማጣቱ ችግር ውስጥ እንዳስገባው የባንኩ ምንጮች ነገረውናል፡፡ የግል ንግድ ባንኮች በገጠማቸው የመከፈል አቅም ውስንነት በርካታ የባንክ ደንበኞቻቸው የሚያንቀሳቅሱትን ገንዘብ ወደ መንግሥታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማዞራቸውን ከግል ባንኮች ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እስካሁን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ውስጥ ካለመግባቱም በላይ ከዚህ ቀደሙ የተሻለ ጥሬ ገንዘብ በስፋት እየሰበሰበ ነው፡፡ ባንኩ ደንበኞች ገንዘባቸውን በሚፈልጉበት ጊዜ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው ጣሪያ ልክ፣ ያለገደብ ጥሬ ገንዘብ ማውጣት የሚችሉበት ብቸኛ ባንክ ሆኗል፡፡ ዋዜማ በባንኮች በኩል ያገኘችውን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ችግር የባንኮች ተቆጣጣሪ አካል እንዴት እንደሚመለከተው የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥን ፍቃዱ ደግፌን የጠየቀች ሲሆን፣ ባንኮች በሚሉት ደረጃ እጥረት መኖሩን የባንኩ መረጃ እንደማያመላክት ነግረዋታል፡፡
ፍቃዱ ጉዳዩን “እኔ ባለኝ መረጃ ባንኮች ላይ በሚባለው ደረጃ የጥሬ ገንዘብ እጥረት (ሊኪዩዲቲ) የለም” ብለዋል፡፡ ባንኮች ከነዳጅ አዳዮችና ከሌሎች የተለያዩ ደንበኞች በየእለቱ ያገኙት የነበረውን የጥሬ ገንዘብ ገቢ በግዴታ ወደ ቴሌ ብር ስርዓት መቀየሩን ተክትሎ ገጥሞናል ያሉትን ችግር በተመለከተ፣ ምክትል ገዥው ለዋዜማ በሰጧት አስተያየት፣ “እጥረት አለብን ካሉ ተወዳድሮ መሰብሰብ ነው የሚከለክል ሕግ የለም” በማለት ገልጸውታል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
👍55❤5
አማራ ባንክ ከፋይናንሻል ቴክኖሎጂ አቅራቢዎች እና ኦኘሬተሮች ጋር ያለዉን ግንኙነት በማጠናከር የተለያዩ ዲጅታል ባንኪንግ ኘሮግራሞችን ለደንበኞቹ ለማቅረብ እቅድ ይዤ እየሰራሁ ነው አለ።
ባንኩ በዲጅታል የፋይናንስ እድገት ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑን የተናገሩት የባንኩ ምክትል ቺፍ አቶ በፍቃዱ ሸሪፍ አዳዲስ ከቴክኖሎጂን ከሚያቀርቡ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት በእቅድ ላይ ነን ብለዋል።ባንኩ ባሳለፍነው በጀት ዓመት ከቴክኖሎጂ አቅራቢዎች(ፊንቴኮች)ጋር በመስራት የተለያዩ የዲጂታል ባንኪንግ ስርአትን ለደንበኞቼ አቅርቤአለሁ ብሏል።
በዚህም መሰረት ባንኩ ለ 50 ሺህ ደንበኞች በአጭር ጊዜ የክፍያ ካርዶችን ማቅረቡን የተናገረ ሲሆን ለማንኛውም የቢል ክፍያ የቴክኖሎጂ ትስስር በመፍጠር ክፍያዎችን በሞባይል ባንኪንግ እንዲከፍሉ ማስቻሉን ተናግሯል።
የትምህርት ቤት ክፍያ አባስኩል ፔይ የተሰኘ አገልግሎት፣ የሆቴል መያዝ፣ የሜትር ታክሲ ክፍያን ደንበኞች በሞባይል ባንኪንግ መፈፀም እንዲችሉ ማድረግ፣ የኦንላይን ግብይት፣ የኪው አር (QR) የተሰኘ የመክፈያ አማራጭ ለንግድ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች አገልግሎቶችን ለደንበኞቹ ማቅረቡን ከባንኩ ሰምተናል።
ባንኩ በ2016 እሰራባቸዋለው ብሎ ካቀዳቸው መካከል የወኪል(ኤጀንሲ) ባንኪንግ መጀመር የሚለው ይገኝበታል።አማራ ባንክ ኦላይን ባንክ ተጠቃሚዎቼ 200 ሺህ ተጠግተዋል ያለ ሲሆን 1.3 ሚሊዮን ደንበኞች ማፍራት እንደቻለም ጠቅሷል፡፡
[Sheger FM]
@YeneTube @FikerAssefa
ባንኩ በዲጅታል የፋይናንስ እድገት ላይ አተኩሮ እየሰራ መሆኑን የተናገሩት የባንኩ ምክትል ቺፍ አቶ በፍቃዱ ሸሪፍ አዳዲስ ከቴክኖሎጂን ከሚያቀርቡ ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት በእቅድ ላይ ነን ብለዋል።ባንኩ ባሳለፍነው በጀት ዓመት ከቴክኖሎጂ አቅራቢዎች(ፊንቴኮች)ጋር በመስራት የተለያዩ የዲጂታል ባንኪንግ ስርአትን ለደንበኞቼ አቅርቤአለሁ ብሏል።
በዚህም መሰረት ባንኩ ለ 50 ሺህ ደንበኞች በአጭር ጊዜ የክፍያ ካርዶችን ማቅረቡን የተናገረ ሲሆን ለማንኛውም የቢል ክፍያ የቴክኖሎጂ ትስስር በመፍጠር ክፍያዎችን በሞባይል ባንኪንግ እንዲከፍሉ ማስቻሉን ተናግሯል።
የትምህርት ቤት ክፍያ አባስኩል ፔይ የተሰኘ አገልግሎት፣ የሆቴል መያዝ፣ የሜትር ታክሲ ክፍያን ደንበኞች በሞባይል ባንኪንግ መፈፀም እንዲችሉ ማድረግ፣ የኦንላይን ግብይት፣ የኪው አር (QR) የተሰኘ የመክፈያ አማራጭ ለንግድ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች አገልግሎቶችን ለደንበኞቹ ማቅረቡን ከባንኩ ሰምተናል።
ባንኩ በ2016 እሰራባቸዋለው ብሎ ካቀዳቸው መካከል የወኪል(ኤጀንሲ) ባንኪንግ መጀመር የሚለው ይገኝበታል።አማራ ባንክ ኦላይን ባንክ ተጠቃሚዎቼ 200 ሺህ ተጠግተዋል ያለ ሲሆን 1.3 ሚሊዮን ደንበኞች ማፍራት እንደቻለም ጠቅሷል፡፡
[Sheger FM]
@YeneTube @FikerAssefa
👍32❤3
በሞሮኮ በርዕደ መሬት ሳቢያ ቢያንስ 632 ሰዎች ሞቱ!
በሞሮኮ በመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ ቢያንስ 632 ሰዎች ሞቱ።የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳለው በ6.8 የተለካው የመሬት መንቀጥቀጥ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
በዋነኛነት የመሬት መንቀጥቀጡ የተሰማው በአትላስ ተራራ አካባቢ ነው።ይህም ከማራኬሽ በደቡብ ምዕራብ 71 ኪሎ ሜትር ርቆ ይገኛል። ጥልቀቱም 18.5 ኪሎ ሜትር ነው።
በማራኬሽና በሌሎችም ደቡባዊ አካባቢዎች ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።አል-ሀውዝ፣ ማራኬሽ፣ ኦራዛቴ፣ አዚል፣ ክሪቾዋ እና ታራውዳንት በተባሉት አካባቢዎች ነው ሰዎች የሞቱት።በመሬት መንቀጥቀጡ ሕንጻዎችና ጎዳናዎች ሲጎዱ የሚያሳዩ ቪድዮዎች ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ወጥተዋል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በሞሮኮ በመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ ቢያንስ 632 ሰዎች ሞቱ።የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳለው በ6.8 የተለካው የመሬት መንቀጥቀጥ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
በዋነኛነት የመሬት መንቀጥቀጡ የተሰማው በአትላስ ተራራ አካባቢ ነው።ይህም ከማራኬሽ በደቡብ ምዕራብ 71 ኪሎ ሜትር ርቆ ይገኛል። ጥልቀቱም 18.5 ኪሎ ሜትር ነው።
በማራኬሽና በሌሎችም ደቡባዊ አካባቢዎች ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።አል-ሀውዝ፣ ማራኬሽ፣ ኦራዛቴ፣ አዚል፣ ክሪቾዋ እና ታራውዳንት በተባሉት አካባቢዎች ነው ሰዎች የሞቱት።በመሬት መንቀጥቀጡ ሕንጻዎችና ጎዳናዎች ሲጎዱ የሚያሳዩ ቪድዮዎች ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ወጥተዋል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
👍19❤2
በጋምቤላ ክልል 13 አመራሮች ከኃላፊነታቸው ተነሱ!
ባለፈው ተከስቶ የነበረውን የፀጥታ ችግር ምክንያት በማድረግ በተካሄደ ግምገማ 13 አመራሮች ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ አስታወቁ፡፡እንዲሁም 55 አመራሮች አዲስና የሽግሽግ ሹመት መሰጠቱን ነው አቶ ኡሞድ ያስታወቁት፡፡
ሙሉ በሙሉ ከኃላፊነታቸው የተነሱት አመራሮች በብልሹ አሰራር፣ በአፈፃፀማቸውና በፀጥታ ችግር ክፍተት የታየባቸው ናቸው ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡አዲስና በሽግሽግ ወደ ሹመት የመጡ አመራሮች የክልሉን ህዝብ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ይፈታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡
በክልል ማዕከል የተጀመረው አመራሩን የማጥራት ተግባር በቀጣይ በዞንና በወረዳ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡ህዝቡ ለክልሉ ሰላምና ልማት ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ አሁንም ከመንግሥት ጎን በመሆን የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፈው ተከስቶ የነበረውን የፀጥታ ችግር ምክንያት በማድረግ በተካሄደ ግምገማ 13 አመራሮች ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ አስታወቁ፡፡እንዲሁም 55 አመራሮች አዲስና የሽግሽግ ሹመት መሰጠቱን ነው አቶ ኡሞድ ያስታወቁት፡፡
ሙሉ በሙሉ ከኃላፊነታቸው የተነሱት አመራሮች በብልሹ አሰራር፣ በአፈፃፀማቸውና በፀጥታ ችግር ክፍተት የታየባቸው ናቸው ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡አዲስና በሽግሽግ ወደ ሹመት የመጡ አመራሮች የክልሉን ህዝብ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ይፈታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡
በክልል ማዕከል የተጀመረው አመራሩን የማጥራት ተግባር በቀጣይ በዞንና በወረዳ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡ህዝቡ ለክልሉ ሰላምና ልማት ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ አሁንም ከመንግሥት ጎን በመሆን የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
👍16❤3
በሞሮኮ የመሬት መንቀጥቀጥ ሟቾች ቁጥር ከ1000 አልፈ!
ያልተለመደና እጅግ ክፉኛ የተባለው የሞሮኮ ርዕደ መሬት አርብ ምሽት ተከስቶ ከ1 ሽህ በላይ ሰዎችን ህይወት መቅጠፉ ተነግሯል።አደጋው በታሪካዊቷ ማራካሽ ከተማ ጥንታዊ ህንጻዎችን ዶግ አመድ ማድረጉ ታውቋል።
እስካሁን ድረስ የርዕደ መሬቱ ሙሉ የሟቾች ቁጥር ያልታወቀ ሲሆን፤ በአደጋው ክፉኛ በተጎዱ አካባቢዎች የነፍስ አድን ሰራተኞች መድረስ አለመቻላቸውን አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል። 6.8 ሬክተር ስኬል የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ በሞሮኮ ከ120 ዓመታት በኋላ በእጅጉ የከፋ ነው ተብሏል።
@YeneTube@FikerAssefa
ያልተለመደና እጅግ ክፉኛ የተባለው የሞሮኮ ርዕደ መሬት አርብ ምሽት ተከስቶ ከ1 ሽህ በላይ ሰዎችን ህይወት መቅጠፉ ተነግሯል።አደጋው በታሪካዊቷ ማራካሽ ከተማ ጥንታዊ ህንጻዎችን ዶግ አመድ ማድረጉ ታውቋል።
እስካሁን ድረስ የርዕደ መሬቱ ሙሉ የሟቾች ቁጥር ያልታወቀ ሲሆን፤ በአደጋው ክፉኛ በተጎዱ አካባቢዎች የነፍስ አድን ሰራተኞች መድረስ አለመቻላቸውን አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል። 6.8 ሬክተር ስኬል የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ በሞሮኮ ከ120 ዓመታት በኋላ በእጅጉ የከፋ ነው ተብሏል።
@YeneTube@FikerAssefa
👍14❤3
የ5 ጂ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ!
ኢትዮ ቴሌኮም የአምስተኛው ትውልድ (5 ጂ) የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በይፋ አስጀመረ።ኢትዮ ቴሌኮም የ5 ጂ አገልግሎትን በአዲስ አበባ በተለያዩ አካቢዎች በሚገኙ በ145 ስፍራዎች ማስጀመሩን በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል።
የ5 ጂ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት እስከ 10 ጊጋባይት በሰከንድ የሚደርስ ከፍተኛ ፍጥነት ያለው መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በይፋ ማድረጊያ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የ5 ጂ አገልግሎት ስራ ላይ መዋሉ የማህበረሰባችንን ህይወት የሚያቀሉ ዲጂታል መፍትሄዎችን በቀላሉ በማቅረብ ተሞክሯቸውን የሚያሻሽል መሆኑን ተናግረዋል።ደንበኞች የ5 ጂ አገልግሎትን ለመጠቀም የሚያስችሉ መሳሪያዎችና ቀፎዎች ሊኖራቸው እንደሚገባም ተመላክቷል።
Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮ ቴሌኮም የአምስተኛው ትውልድ (5 ጂ) የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በይፋ አስጀመረ።ኢትዮ ቴሌኮም የ5 ጂ አገልግሎትን በአዲስ አበባ በተለያዩ አካቢዎች በሚገኙ በ145 ስፍራዎች ማስጀመሩን በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል።
የ5 ጂ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት እስከ 10 ጊጋባይት በሰከንድ የሚደርስ ከፍተኛ ፍጥነት ያለው መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በይፋ ማድረጊያ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የ5 ጂ አገልግሎት ስራ ላይ መዋሉ የማህበረሰባችንን ህይወት የሚያቀሉ ዲጂታል መፍትሄዎችን በቀላሉ በማቅረብ ተሞክሯቸውን የሚያሻሽል መሆኑን ተናግረዋል።ደንበኞች የ5 ጂ አገልግሎትን ለመጠቀም የሚያስችሉ መሳሪያዎችና ቀፎዎች ሊኖራቸው እንደሚገባም ተመላክቷል።
Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
👍44👎24❤9
የህዳሴው ግድብ አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት ተጠናቋል - ጠ/ሚ ዐቢይ
የህዳሴው ግድብ አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ4ኛውን ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቅ አስመልክቶ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
“ኢትዮጵያውያን ተባብረን በመሥራታችን ፈጣሪ ረድቶናል፤ በገንዘባችሁ፣ በዕውቀታችሁ፣ በጉልበታችሁና በጸሎታችሁ በሥራው ውስጥ የተሳተፋችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ” ብለዋል።ኢትዮጵያውያን በግድቡ ግንባታ ያሳዩትን ህብረት በሌሎች ጉዳዮችም እንዲደግሙትም ጠይቀዋል።
በግድቡ ግንባታ ከውስጥን ከውጭም ጫናዎች እንደነበሩ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈተናዎችን በመቋቋም ለዚህ ስኬት ደርሰናል ብለዋል።“ለግድቡ የምናደርገውን ማናቸውንም ድጋፍ እስከ ፍጻሜው እንድንቀጥል በዚሁ አጋጣሚ አደራ እላለሁ” ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የህዳሴው ግድብ አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ4ኛውን ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቅ አስመልክቶ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
“ኢትዮጵያውያን ተባብረን በመሥራታችን ፈጣሪ ረድቶናል፤ በገንዘባችሁ፣ በዕውቀታችሁ፣ በጉልበታችሁና በጸሎታችሁ በሥራው ውስጥ የተሳተፋችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ” ብለዋል።ኢትዮጵያውያን በግድቡ ግንባታ ያሳዩትን ህብረት በሌሎች ጉዳዮችም እንዲደግሙትም ጠይቀዋል።
በግድቡ ግንባታ ከውስጥን ከውጭም ጫናዎች እንደነበሩ ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈተናዎችን በመቋቋም ለዚህ ስኬት ደርሰናል ብለዋል።“ለግድቡ የምናደርገውን ማናቸውንም ድጋፍ እስከ ፍጻሜው እንድንቀጥል በዚሁ አጋጣሚ አደራ እላለሁ” ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
👎76👍61🔥4❤3
11ኛው የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል!
11ኛው የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል፡፡በስነ ስርዓቱም ላይ በ10 ዘርፎች ለሀገራቸውና ለህዝባቸው የተለያዩ ተግባራትን ላከናወኑ ሰዎችና ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል።
በዚህም መሰረት የዓመቱ የበጎ ሰው እውቅና ከተሰጣቸው ውስጥ፡-
1. በመምህርነት ዘርፍ አዝማች ይርጋ ገብሬ፣
2. በባህል፣ቅርስ እና ቱሪዝም ዘርፍ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም፣
3. በንግድ ኢንዱስትሪና ሥራ ፈጠራ ዘርፍ ኩሪፍቱ ሪዞርት እና ስፓ፣
4. በበጎ አድራጎት ዘርፍ እቴነሽ ወንድምአገኘሁ
5. በኪነ ጥበብ (ስዕል) ዘርፍ ሰዓሊ ወርቁ ጎሹ፣
6. መንግስታዊ የስራ ኃላፊነትን በብቃት መወጣት ዘርፍ ያየህይራድ ቅጣው (ዶ/ር) እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
ስነ ስርዓቱ አሁንም እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን በቀሪ 4 ዘርፎች የሚካሄዱ ሽልማቶች ተጠባቂ ናቸው፡፡
Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
11ኛው የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል፡፡በስነ ስርዓቱም ላይ በ10 ዘርፎች ለሀገራቸውና ለህዝባቸው የተለያዩ ተግባራትን ላከናወኑ ሰዎችና ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል።
በዚህም መሰረት የዓመቱ የበጎ ሰው እውቅና ከተሰጣቸው ውስጥ፡-
1. በመምህርነት ዘርፍ አዝማች ይርጋ ገብሬ፣
2. በባህል፣ቅርስ እና ቱሪዝም ዘርፍ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም፣
3. በንግድ ኢንዱስትሪና ሥራ ፈጠራ ዘርፍ ኩሪፍቱ ሪዞርት እና ስፓ፣
4. በበጎ አድራጎት ዘርፍ እቴነሽ ወንድምአገኘሁ
5. በኪነ ጥበብ (ስዕል) ዘርፍ ሰዓሊ ወርቁ ጎሹ፣
6. መንግስታዊ የስራ ኃላፊነትን በብቃት መወጣት ዘርፍ ያየህይራድ ቅጣው (ዶ/ር) እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
ስነ ስርዓቱ አሁንም እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን በቀሪ 4 ዘርፎች የሚካሄዱ ሽልማቶች ተጠባቂ ናቸው፡፡
Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
👍41👎17❤5🔥3