YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የመከላከያ ሚኒስትሩ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ምዕራብ ትግራይ ወደነበረበት ይመለሳል አሉ!

መከላከያ ሚንስትር አብርሃም በላይ የምዕራብና ደቡባዊ ትግራይ አካባቢዎች በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት መሠረት "ወደነበሩበት ይመለሳሉ" በማለት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።

ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የአሸንዳ በዓልን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው መሆኑ ታውቋል።

ዶ/ር አብርሃም በመልዕክታቸው ፣ ከግዛቶቹ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎች "በሕገ መንግሥታዊ አግባብ" ይስተናገዳሉ ብለዋል።

መንግሥት የምዕራብ እና ደቡባዊ ትግራይ የጦርነት ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው ለመመለስ እንቅስቃሴዎች እያደረገ መኾኑን የጠቀሱት ሚንስትሩ ፣ በግዛቶቹ በጦርነቱ ወቅት በተቋቋሙ አስተዳደራዊ መዋቅሮች ሕዝብ በሚመርጠው መዋቅሮች እንደሚተኩም አብርሃም ጠቁመዋል።

[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
ደረቅ ሳሙና በተለያዩ ክፍለ ሀገራት ላይ ማከፋፈል የምትፈልጉ አከፋፋዮች በውስጥ መስመር ያናግሩን።

የሳሙናው ይዘት

የሳሙናው አይነት:- ደረቅ ሳሙና
ከለር :- ቀለም ነጭ
ግራም :- 200

የፋብሪካ ቦታ :- ሀዋሳ

@AbelAbi123
በ1500 ሜትር ፍፃሜ ኢትዮጵያ በድርብ ወልተጂ የብር ሜዳሊያ አገኘች !

@YeneTube @FikerAssefa
በቡዳፔስት የ3000 ሜትር መሰናክል ወንዶች ለሜቻ ግርማ ለኢትዮጲያ የብር ሜዳሊያ አስገኘ።ሞሮኳዊው አትሌት በአንደኛነት አጠናቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
Facebook, Twitter, Instagram እና በመሳሳሉት የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ድርጅትዎን ፤ አገልግሎትዎን እና ምርትዎን ማስተዋወቅ ፈልገዋል? እንግዲያውስ መፍትሄው እኛ ጋር ነው።

በማንኛውም Social Media  Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::

ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።

Telegram: @adsommar
📞0929334267
👍1
💥💥ዘመኑ የሚፈልገውን የቴክኖሎጂ ባለሙያ ሆነው በቀላሉ ከቤት ሆነው የሚሰሩበትን የሶሻል ሚድያ ማስታወቂና አሰራር ስልጠና እንዲሁም መሰረታዊ የኮምፒውተር ኘሮግራሚንግ በቤቶ ሆነው በ 2 ወር ብቻ የተፈላጊ ሙያ ባለቤት ይሁኑ!

- ስልጠናው ቨርቹዋል ስለሆነ በየትኛውም ቦታ ሆነው መማር ይችላሉ!

- ስልጠናውን ሲወስዱ በተግባር የታገዘ ልምምድ እንዲሁም ሲጨርሱ የስራ እድል እናመቻቻለን!

- ስልጠናውን ሲጨርሱ ሰርተፊኬት ያገኛሉ!

- ከተለያዩ ውጭ ሀገር መግዛት የሚችሉበት እንዲሁም የሶሻል ሚድያ ማስታወቂያ መስራት የሚችሉበት የራሳቹን የቨርቹዋል ማስተር ካርድ ያገኛሉ!

- የተለያዩ ኘሮጀክቶችን በመስራት ልምድ ይቀስማሉ!

- የተለያዩ ኦላይን ኮርሶችን በነፃ በቤቶ የሚማሩበት እድል እንሰጣለን!

🎓 ለአዳዲስ ተመራቂ ተማራዎች ልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል!

ለተጨማሪ መረጃ 0954742475 ይደውሉ
ወይንም በቴሌግራም @Bekalu_gebremariam ያዋሩን
👍2
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
👍1
በሰሜን ሸዋ እና በደቡብ ወሎ ዞኖች በተደረጉ የተኩስ ልውውጦች ሰብአዊ እና ቁሳዊ ጉዳት መድረሱ ተገለጸ!

በዐማራ ክልል በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተስፋፋው ግጭት፣ በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ ግድም ወረዳ በማጀቴ ከተማ እና በዙሪያው፣ እንዲሁም በደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ወረዳ ወግዲ ከተማ እና አካባቢው ጉድት መድረሱን ነዋሪዎች ገለፁ።

በግጭቱ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን፣ ለአካል ጉዳት ስለ መዳረጋቸው ነዋሪዎቹ ገልፀዋል። በመሠረተ ልማቶች እና በግለሰቦች ንብረት ላይም ቁሳዊ ጥፋቶች ስለ መድረሳቸው፣ ለቪኦኤ አስተያየታቸውን የሰጡ ግለሰቦች ተናግረዋል፡፡

በማጀቴ ከተማ እና አካባቢው ያለው የግጭት ሁኔታ በውጊያው የቆሰሉትን ወደ ሕክምና ተቋማት ማድረስን አዳጋች እንዳደረገውና ወደ ግለሰቦች ቤቶች በማግለል ጭምር ለመስጠት እየተሞከረ እንደኾነ፣ የመረጃ ምንጮቹ ጠቅሰዋል፡፡

ከ15 ቀናት በፊት፣ በወግዲ ከተማ አካባቢ በነበረ ውጊያ፣ የደረሱበት የማይታወቅ ሰዎች ስለ መኖራቸውና ነዋሪው በጸጥታ ስጋት፣ በመንግሥታዊ አገልግሎት ዕጦት እና በኑሮ ውድነት እንደተቸገረም፣ አስተያየት ሰጭዎቹ አመልክተዋል፡፡ የወረዳው መንግሥታዊ መዋቅር ለጊዜው አገልግሎት እየሰጠ ባለመኾኑ፣ ደረሰ ስለተባለው ጉዳት፣ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት አልተቻለም፡፡ከዐማራ ክልል እና ፌደራል መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ሓላፊዎች ምላሽ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ አልተሳካም።

Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ በመጪው ዓመት ጥር ወር ዋናውን ኮንፍረንስ ለማካሄድ “የሚቻለውን ጥረት እያደረግኩ ነው” አለ!

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመጪው ዓመት ጥር ወር ላይ ዋናውን የምክክር ጉባኤ ለመጥራት “የሚቻለውን ጥረት” እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።ኮሚሽኑ ከነገ ነሐሴ 18፤ 2015 ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የጉባኤውን ተሳታፊዎች መለየት እንደሚጀምርም ይፋ አድርጓል።

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ይህን ይፋ ያደረገው፤ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 17 በዋና ጽህፈት ቤቱ እየሰጠ ባለው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።ባለፈው ዓመት ታህሳስ ወር ላይ በአዋጅ የተቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ እስካሁን ድረስ በአምስት ክልሎች እና አንድ ከተማ አስተዳደር የጉባኤ ተሳታፊዎች ልየታን አከናውኗል።

ኮሚሽኑ የጉባኤ ተሳታፊዎችን የለየባቸው አካባቢዎች፤ በሐረሪ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ ናቸው። በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የተገኙት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ፤ “እስከ ጥር ድረስ ዋናውን ሀገራዊ ምክክር ኮንፍረንስ ለመጥራት የሚቻለንን ጥረት እያደረግን ነው” ብለዋል።

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
ታሪካዊው የአክሱም ሐውልት በሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግር ምክንያት ወደ አንድ አቅጣጫ አዝምሟል ተባለ!

የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ‹‹ በአክሱም በተካሄደው ጥናት በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግር ምክንያት በአካባቢው ያለው ታሪካዊው ሃውልት ወደ አንድ አቅጣጫ የመዝመም ሁኔታ እንደተስተዋለበት መመልከቱን ›› ይፋ አድርጓል።ባለስልጣኑ ሃውልቱ ወደአንድ አቅጣጫ ለማዝመሙ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግር መንስዔ መሆናቸውን ይግለጥ እንጂ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ የተባሉት ችግሮች ምን እንደሆኑ በውል ስለመናገሩ በኢዜአ ዘገባ አልተካተተም፡፡

በባለስልጣኑ የቅርሶች ጥበቃና እንክብካቤ ዳይሬክተር ሃብታሙ አብረሃ ‹‹ 31 ሜትር ቁመት ያለውና ወደ ሰሜን አቅጣጫ የዘመመው የአክሱም ሃወልት ከአራት ዓመታት በፊት በ115 ሚሊዮን ብር በጀት ለመጠገን የፌዴራል መንግስት ከአንድ የጣሊያን ተቋራጭ ጋር ውል መግባቱን ›› አስታውሰዋል።

‹‹ በውሉ መሰረት ተቋራጩ ለጥገና የሚያስፈልጉ ዕቃዎች መጓጓዝ በጀመረበት ወቅት በኮሮናና በጦርነት ምክንያት እንደተቋረጠ ›› ያስታወሱት ሃብታሙ ‹‹ አሁን በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ውሉን በማደስ የጥገና ስራ በተያዘው በጀት ዓመት ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ›› ተናግረዋል።ባለሰልጣኑ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ተፈጥሯል ያለውን ‹‹ ሰላም በመጠቀም ቅርሶች ያሉበትን ደረጃ ለመለየት አስቸኳይ የዳሰሳ ጥናት መካሄዱን ›› ገልጿል።

ከእነዚህ ታሪካዊ ስፍራዎችና ቅርሶች መካከል የአክሱም ሃውልትና የላሊበላ ውቅር አቢያተ ክርስቲያናት እንደሚገኙበት ዳይሬክተሩ አክለዋል፡፡በሌላ በኩል ከአለት ተፈልፍሎ የተሰራው ታሪካዊው የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ማደስ የሚያስችል ከቀድሞ በተጨማሪ የባለሙያዎች ጥናት መካሄዱን ገልጸዋል።

[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
ተቋርጦ የነበረው የኩላሊት እጥበት አገልግሎት ተጀመረ፡፡

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና  ኮሌጅ የኩላሊት እጥበት መስጫ ማዕከል( Dialysis center ) የእጥበት አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ መሳሪያዎች ረዘም ላለ ጊዜ በማገልገላቸው እድሳት ስለሚያስፈልጋቸው ለተወሰነ ጊዜያት ማእከሉ አገልግሎቱን አቋርጦ ነበር፡፡

ይሁን እንጂ የማዕከሉ የእጥበት መሳሪያዎች እድሳት በመጠናቀቁና አስፈላጊ ግብኣት በመሟላቱ  አገልግሉቱን በያዝነው ሳምንት ሙሉ ለሙሉ መጀመሩ ሆስፒታሉ አሳዉቋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
በሀዋሳ ከተማ ያሉ የንግድ ተቋማት በአንድ ወር ውስጥ የደህንት ካሜራ እንዲገጥሙ የሚያስገድድ መመሪያ ወጣ!

የሲዳማ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ የንግድ ተቋማት በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የደህንት ካሜራ እንዲገጥሙ የሚያስገድድ መመሪያ አወጣ። መመሪያውን ተግባራዊ የማያደርጉ የንግድ ተቋማት ባለቤቶች ላይ የእስር አሊያም የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

ቢሮው መመሪያውን ይፋ ያደረገው፤ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 17፤ 2015 በሀዋሳ ከተማ ከሚገኙ የንግድ ተቋማት ባለቤቶች ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ ነው። የሲዳማ ክልል ዋና ከተማ በሆነችው ሀዋሳ የሚገኙ የንግድ ተቋማት፤ የደህንነት ካሜራ እንዲገጥሙ የሚስገድደው መመሪያ የወጣው በሁለት ምክንያቶች ነው ተብሏል።

በሀዋሳ ከተማ በሚገኙ አንዳንድ ድርጅቶች ፊት ለፊት “የሞተር ሳይክል ስርቆቶች” በተደጋጋሚ እንደሚፈጸሙ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተናገሩት የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ፤ ይህንን ድርጊት እና በድርጅቶቹ ውስጥ በሀሰተኛ የገንዘብ ኖት የሚደረጉ ግብይቶችን “ለመቆጣጠር” መመሪያው መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በአዲሱ መመሪያ መሰረት በከተማይቱ የሚገኙ የንግድ ተቋማት በድርጅታቸው ውስጥ እና ወደ ውጭ የሚመለከቱ የደህንነት ካሜራዎችን መግጠም ይኖርባቸዋል።

Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
👍1