Betስኬት ለስፖርታዊ ውርርዶች የሚጠቅሙ መረጃዎችን ይዞ ወደናንተ መጥቷል።
ስፖርታዊ ውርርድ(ቤቲንግ) መጫወት ሚያዘወትሩ ከሆነ ይህ ዌብሳይት ጨዋታዎችን ከቁጥራዊ መረጃዎች በመነሳት በጥልቀት በመተንተን የትኛውን ቡድን ወይም Possibility መምረጥ እንዳለብዎ ስራዎን እናቀልሎታለን፤ ትንተናዎቻችንን ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ።
ወደፊትን መገመት ከባድ ቢሆንም እኛ ግን ለእርሶ ለማቅለል ተግተን እንሰራልን!
ለዛሬ የመረጥንላችሁ ጨዋታዎች:
👇👇👇
https://www.betsket.com/ጋላታሳራይ፤-ኢንተር-ማያሚን፤-ቦካ-ጁኒዮ/
ስፖርታዊ ውርርድ(ቤቲንግ) መጫወት ሚያዘወትሩ ከሆነ ይህ ዌብሳይት ጨዋታዎችን ከቁጥራዊ መረጃዎች በመነሳት በጥልቀት በመተንተን የትኛውን ቡድን ወይም Possibility መምረጥ እንዳለብዎ ስራዎን እናቀልሎታለን፤ ትንተናዎቻችንን ሊንኩን በመጫን በነጻ ያንብቡ።
ወደፊትን መገመት ከባድ ቢሆንም እኛ ግን ለእርሶ ለማቅለል ተግተን እንሰራልን!
ለዛሬ የመረጥንላችሁ ጨዋታዎች:
👇👇👇
https://www.betsket.com/ጋላታሳራይ፤-ኢንተር-ማያሚን፤-ቦካ-ጁኒዮ/
❤1👍1
የ11 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብስብ መንግሥት የፖለቲካ አለመረጋጋቶችንና ግጭቶችን "በኃይል ለመፍታት" የሚያደርገው ጥረት እንዳሳሰበው ዛሬ አስታውቋል።
ስብስቡ፣ መንግሥት በትግራይ፣ በኦሮሚያና በቅርቡ በአማራ ክልል ግጭቶችን በኃይል ርምጃ ለመፍታት ያደረገው ሙከራ ለፖለቲካዊ አለመረጋጋቱና ውጥረቱ "ዘላቂ መፍትሄ አላመጣም" ብሏል።
"አስቸኳይ" እና የ"አፋጣኝ ዘላቂ የመፍትሄ ርምጃ" አስፈላጊነት የማይቀለበስ ደረጃ ላይ ደርሷል ያለው ስብስቡ፣ "አካታችና ኹሉን ዓቀፍ" የፖለቲካ ኃይሎች ውይይት እንዲደረግ፣ በመንግሥትና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል የተቋረጠው ድርድር እንዲቀጥል፣ በመንግሥትና በአማራ ፋኖ ታጣቂዎች መካከል "ግጭት እንዲቆም" እና "ውይይት ወይም ድርድር እንዲጀመር" ጠይቋል። መግለጫውን ካወጡት የስብስቡ አባላት መካከል፣ ኦፌኮ፣ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ አረና ትግራይና የአፋር ነጻነት ፓርቲ ይገኙበታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ስብስቡ፣ መንግሥት በትግራይ፣ በኦሮሚያና በቅርቡ በአማራ ክልል ግጭቶችን በኃይል ርምጃ ለመፍታት ያደረገው ሙከራ ለፖለቲካዊ አለመረጋጋቱና ውጥረቱ "ዘላቂ መፍትሄ አላመጣም" ብሏል።
"አስቸኳይ" እና የ"አፋጣኝ ዘላቂ የመፍትሄ ርምጃ" አስፈላጊነት የማይቀለበስ ደረጃ ላይ ደርሷል ያለው ስብስቡ፣ "አካታችና ኹሉን ዓቀፍ" የፖለቲካ ኃይሎች ውይይት እንዲደረግ፣ በመንግሥትና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል የተቋረጠው ድርድር እንዲቀጥል፣ በመንግሥትና በአማራ ፋኖ ታጣቂዎች መካከል "ግጭት እንዲቆም" እና "ውይይት ወይም ድርድር እንዲጀመር" ጠይቋል። መግለጫውን ካወጡት የስብስቡ አባላት መካከል፣ ኦፌኮ፣ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ አረና ትግራይና የአፋር ነጻነት ፓርቲ ይገኙበታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በመጪዎቹ ሶስት ዓመታት “በአማካይ 8.3 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል”- ዶ/ር ፍጹም አሰፋ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት በአማካይ 8.3 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በዚህ ዓመት በ9.2 በመቶ ያድጋል በሚል እቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፤ ከሶስት ዓመት በኋላም በዚህ የእድገት መጠን ደረጃ ላይ እንደማይደርስ የፌደራል መንግስት ይፋ ያደረገው ሰነድ አመልክቷል።
የፌደራል መንግስት የልማት እቅድ ሲያዘጋጅ የረጅም ጊዜውን በአስር ዓመት እና የመካከለኛ ጊዜውን ደግሞ በሶስት ዓመት ይከፋፈላል። በዚህ አሰራር መሰረት የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት፤ ከ2013 ዓ.ም እስከ 2015 ድረስ የቆየ የመጀመሪያውን የመካከለኛ ጊዜ እቅድ አዘጋጅቶ እስከተጠናቀቀው በጀት ዓመት መጨረሻ ድረስ ሲተገብር ቆይቷል።
በዚህ እቅድ የመጀመሪያ ዓመት፤ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ 8.5 በመቶ እድገት ያስመዘግባል ተብሎ እቅድ ተይዞ ነበር። በ2014 ዓ.ም ወደ 8.7 በመቶ ከፍ እንደሚል የተገመተው የእድገት ምጣኔ፤ በዘንድሮው ዓመት ወደ 9.2 በመቶ እንደሚመነደግ በፌደራል መንግስት የእቅድ ሰነድ ላይ ሰፍሯል። ሆኖም ይህ እቅድ በተከታታይ ሶስት ዓመታት አለመሳካቱ ባለፉት ቀናት በተደረገ “የመካከለኛ ጊዜ አፈጻጸም” ግምገማ ላይ ይፋ ተደርጓል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት በአማካይ 8.3 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በዚህ ዓመት በ9.2 በመቶ ያድጋል በሚል እቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፤ ከሶስት ዓመት በኋላም በዚህ የእድገት መጠን ደረጃ ላይ እንደማይደርስ የፌደራል መንግስት ይፋ ያደረገው ሰነድ አመልክቷል።
የፌደራል መንግስት የልማት እቅድ ሲያዘጋጅ የረጅም ጊዜውን በአስር ዓመት እና የመካከለኛ ጊዜውን ደግሞ በሶስት ዓመት ይከፋፈላል። በዚህ አሰራር መሰረት የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት፤ ከ2013 ዓ.ም እስከ 2015 ድረስ የቆየ የመጀመሪያውን የመካከለኛ ጊዜ እቅድ አዘጋጅቶ እስከተጠናቀቀው በጀት ዓመት መጨረሻ ድረስ ሲተገብር ቆይቷል።
በዚህ እቅድ የመጀመሪያ ዓመት፤ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ 8.5 በመቶ እድገት ያስመዘግባል ተብሎ እቅድ ተይዞ ነበር። በ2014 ዓ.ም ወደ 8.7 በመቶ ከፍ እንደሚል የተገመተው የእድገት ምጣኔ፤ በዘንድሮው ዓመት ወደ 9.2 በመቶ እንደሚመነደግ በፌደራል መንግስት የእቅድ ሰነድ ላይ ሰፍሯል። ሆኖም ይህ እቅድ በተከታታይ ሶስት ዓመታት አለመሳካቱ ባለፉት ቀናት በተደረገ “የመካከለኛ ጊዜ አፈጻጸም” ግምገማ ላይ ይፋ ተደርጓል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
የሩሲያው ቅጥረኛ ተዋጊ ቡድን መሪ የቭጌኒ ፕሪጎዢን በአውሮፕላን አደጋ ሞተ!
የሩሲያው ቅጥረኛ ተዋጊ ቡድን (ቫግነር) መሪ የቭጌኒ ፕሪጎዢን ሩሲያ ውስጥ ባጋጠመ የአውሮፕላን አደጋ ሕይወቱ አለፈ።ከፕሪጎዢን በተጨማሪም በአውሮፕላኑ ውስጥ አብረውት የነበሩት ዘጠኝ ሰዎችም ሞተዋል።
ቀደም ሲል ከቅጥረኛ ቡድኑ ቫግነር ጋር ግንኙነት ያለውና ግሬይ ዞን የተሰኘ የቴሌግራም ቻናል እንደዘገበው ፕሪጎዢን ተሳፍሮበት የነበረው ጄት በአየር መከላከያ መመታቱን ነው።እንደ ዘገባው ከሆነ ጄቱ የተመታው በሰሜናዊ ሞስኮ ቴቨር ክልል ውስጥ ነው።
ፕሪጎዢን ከጥቂት ወራት በፊት በሩሲያ ጦር ላይ ያልተሳካ አመጽ መምራቱ ይታወሳል።ዮቭጌኒ ፕሪጎዢን በአገሩ ላይ ያስነሳው ነውጥ ከከሸፈ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ መልዕክቱን በቪዲዮ ከሰሞኑ አስተላልፎ ነበር።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የሩሲያው ቅጥረኛ ተዋጊ ቡድን (ቫግነር) መሪ የቭጌኒ ፕሪጎዢን ሩሲያ ውስጥ ባጋጠመ የአውሮፕላን አደጋ ሕይወቱ አለፈ።ከፕሪጎዢን በተጨማሪም በአውሮፕላኑ ውስጥ አብረውት የነበሩት ዘጠኝ ሰዎችም ሞተዋል።
ቀደም ሲል ከቅጥረኛ ቡድኑ ቫግነር ጋር ግንኙነት ያለውና ግሬይ ዞን የተሰኘ የቴሌግራም ቻናል እንደዘገበው ፕሪጎዢን ተሳፍሮበት የነበረው ጄት በአየር መከላከያ መመታቱን ነው።እንደ ዘገባው ከሆነ ጄቱ የተመታው በሰሜናዊ ሞስኮ ቴቨር ክልል ውስጥ ነው።
ፕሪጎዢን ከጥቂት ወራት በፊት በሩሲያ ጦር ላይ ያልተሳካ አመጽ መምራቱ ይታወሳል።ዮቭጌኒ ፕሪጎዢን በአገሩ ላይ ያስነሳው ነውጥ ከከሸፈ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ መልዕክቱን በቪዲዮ ከሰሞኑ አስተላልፎ ነበር።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
Forwarded from YeneTube
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
👍2
ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራትን ተቀላቅላለች።
በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ያለው 15ኛው የብሪክስ አባል ሀገራት ጉባኤ ኢትዮጵያን ጨምሮ፥ አርጀንቲና፣ ግብጽ፣ ኢራን፣ ሳዑዲ አረቢያን እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶችን በአዲስ አባልነት ተቀብሏል።
“ብሪክስ” በፈረንጆቹ ሠኔ 16 ቀን 2009 የተመሠረተ ሲሆን “ብሪክ” በሚል ምኅፃረ-ቃል ይጠራ ነበር፡፡
የተመሠረተውም ÷ በብራዚል ፣ ሩሲያ ፣ ሕንድ እና ቻይና የጋራ አነሳሽነት ነው፡፡
“ብሪክ” ኋላ ላይ “ብሪክስ” የሚለውን ሥያሜ ያገኘው በፈረንጆቹ 2010 ላይ የደቡብ አፍሪካን የአባልነት ጥያቄ ተቀብሎ ወደ ቡድኑ ከቀላቀላት በኋላ ነው፡፡
“ብሪክስ” አባል-ሀገራቱ በምጣኔ-ሐብት ለመዋኀድ ዓላማ ሰንቀው ያቋቋሙት ቡድን ነው፡፡
ቡድኑ ፈጣን ዕድገት በማስመዝገብ እስከ ፈረንጆቹ 2050 የዓለምን ምጣኔ-ሐብት ለመቆጣጠር ግብ አስቀምጧል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ያለው 15ኛው የብሪክስ አባል ሀገራት ጉባኤ ኢትዮጵያን ጨምሮ፥ አርጀንቲና፣ ግብጽ፣ ኢራን፣ ሳዑዲ አረቢያን እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶችን በአዲስ አባልነት ተቀብሏል።
“ብሪክስ” በፈረንጆቹ ሠኔ 16 ቀን 2009 የተመሠረተ ሲሆን “ብሪክ” በሚል ምኅፃረ-ቃል ይጠራ ነበር፡፡
የተመሠረተውም ÷ በብራዚል ፣ ሩሲያ ፣ ሕንድ እና ቻይና የጋራ አነሳሽነት ነው፡፡
“ብሪክ” ኋላ ላይ “ብሪክስ” የሚለውን ሥያሜ ያገኘው በፈረንጆቹ 2010 ላይ የደቡብ አፍሪካን የአባልነት ጥያቄ ተቀብሎ ወደ ቡድኑ ከቀላቀላት በኋላ ነው፡፡
“ብሪክስ” አባል-ሀገራቱ በምጣኔ-ሐብት ለመዋኀድ ዓላማ ሰንቀው ያቋቋሙት ቡድን ነው፡፡
ቡድኑ ፈጣን ዕድገት በማስመዝገብ እስከ ፈረንጆቹ 2050 የዓለምን ምጣኔ-ሐብት ለመቆጣጠር ግብ አስቀምጧል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
👍1
ቻይና ÷ኢትዮጵያ ብሪክስን በመቀላቀሏ የደስታ መልዕክት አስተላለፈች
ቻይና ÷ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራትን በመቀላቀሏ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፋለች፡፡
የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ኢትዮጵያን ጨምሮ ስድስት ሀገራት ቡድኑን እንዲቀላቀሉ በዛሬው ዕለት ውሳኔ አሳልፏል፡፡
በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ጉዳዩን አስመልክቶ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ ÷ ቻይና ለብሪክስ መስፋፋት በተለይም የኢትዮጵያን በአባልነት መቀላቀል እንደምትደግፍ አስታውቋል፡፡
ቻይና ሁሉን አካታች እና ፍትሃዊ የዓለም ስርዓት ለመፍጠር የብሪክስ አባል ሀገራትን መስፋፋት እንደምትደግፍ በመግለጫው ተጠቁሟል፡፡
የቻይና ፕሬዚዳንት ሺ ጂን ፒንግ በጉባዔው ብሪክስን ለተቀላቀሉ አዳዲስ ሀገራት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸውም ተጠቅሷል፡፡
በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዢያን÷ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራትን በመቀላቀሏ ለኢትዮጵያ መንግስት እና ሕዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ቻይና በብሪክስ ማዕቀፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትብብር ለማጠናቀር ቁርጠኛ መሆኗንም አምባሳደሩ አረጋግጠዋል፡፡
#Ethiopia #BRIKS
@Yenetube @Fikerassefa
ቻይና ÷ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራትን በመቀላቀሏ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፋለች፡፡
የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ኢትዮጵያን ጨምሮ ስድስት ሀገራት ቡድኑን እንዲቀላቀሉ በዛሬው ዕለት ውሳኔ አሳልፏል፡፡
በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ጉዳዩን አስመልክቶ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ ÷ ቻይና ለብሪክስ መስፋፋት በተለይም የኢትዮጵያን በአባልነት መቀላቀል እንደምትደግፍ አስታውቋል፡፡
ቻይና ሁሉን አካታች እና ፍትሃዊ የዓለም ስርዓት ለመፍጠር የብሪክስ አባል ሀገራትን መስፋፋት እንደምትደግፍ በመግለጫው ተጠቁሟል፡፡
የቻይና ፕሬዚዳንት ሺ ጂን ፒንግ በጉባዔው ብሪክስን ለተቀላቀሉ አዳዲስ ሀገራት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸውም ተጠቅሷል፡፡
በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዢያን÷ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራትን በመቀላቀሏ ለኢትዮጵያ መንግስት እና ሕዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ቻይና በብሪክስ ማዕቀፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትብብር ለማጠናቀር ቁርጠኛ መሆኗንም አምባሳደሩ አረጋግጠዋል፡፡
#Ethiopia #BRIKS
@Yenetube @Fikerassefa
❤1👍1
የስልጤ ዞን የኩተሬ ከተማ ነዋሪዎች በወረዳ እንደራጅ የሚል ጥያቄን አንግበው ነሐሴ 18 ቀን 2015 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ፡፡
መንግስት በደቡብ ብሔር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል በክላስተር አደረጃጀት ካዋቀራቸው አራት ክልሎች መካከል አንዱ በሆነው ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ስር የተካተተው ስልጤ ዞን ውስጥ የምትገኘው የኩተሬ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ነሐሴ 18 ቀን 2015 ዓ.ም በወረዳ እንደራጅ ጥያቄያቸውን ይዘው ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል፡፡
የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪ ለአሻም እንደነገሯት ‹‹ የወረዳነት የጥያቄያቸው መነሻ የእድገት፣ የመልካም አስተዳደርና የመሰረተ ልማት መስፋፈት ፍላጎቶች እንዲሟሉላቸው ታስቦ መሆኑን ›› አስረድተዋል፡፡
ሰልፈኞቹ ‹‹ ከአምስት አመታት በፊት ጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት ነዋሪዎቹ ጥያቄያቸውን ሲያነሱ የፌደራል፣ የክልሉና የዞን አመራሮች በተገኙበት ብልፅግና ፓርቲ ምርጫን ካሸነፈ የመጀመሪያ የሚመለሰው ጥያቄ የኩተሬ የወረዳነት ጥያቄ መሆኑን ቃል መግባቱን ›› አስታውሰው ‹‹ ይህ ግን ተፈፃሚ አለመሆኑን ›› በመጥቀስ ይወቅሳሉ፡፡
አሻም የሰልፈኞችን ቅሬታ መነሻ በማድረግ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳዳሪ አማን ከድርን እንዲሁም የስልጤ ዞን አስተዳዳሪ አሊ ከድር ምላሽ በዘገባው ለማካተት ያደረገችው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም፡፡የሥራ ሃላፊዎች ምላሽ በሰጡበት አፍታ የምታስተናግድ ይሆናል፡፡
Via Asham
@YeneTube @FikerAssefa
መንግስት በደቡብ ብሔር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል በክላስተር አደረጃጀት ካዋቀራቸው አራት ክልሎች መካከል አንዱ በሆነው ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ስር የተካተተው ስልጤ ዞን ውስጥ የምትገኘው የኩተሬ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ነሐሴ 18 ቀን 2015 ዓ.ም በወረዳ እንደራጅ ጥያቄያቸውን ይዘው ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል፡፡
የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪ ለአሻም እንደነገሯት ‹‹ የወረዳነት የጥያቄያቸው መነሻ የእድገት፣ የመልካም አስተዳደርና የመሰረተ ልማት መስፋፈት ፍላጎቶች እንዲሟሉላቸው ታስቦ መሆኑን ›› አስረድተዋል፡፡
ሰልፈኞቹ ‹‹ ከአምስት አመታት በፊት ጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት ነዋሪዎቹ ጥያቄያቸውን ሲያነሱ የፌደራል፣ የክልሉና የዞን አመራሮች በተገኙበት ብልፅግና ፓርቲ ምርጫን ካሸነፈ የመጀመሪያ የሚመለሰው ጥያቄ የኩተሬ የወረዳነት ጥያቄ መሆኑን ቃል መግባቱን ›› አስታውሰው ‹‹ ይህ ግን ተፈፃሚ አለመሆኑን ›› በመጥቀስ ይወቅሳሉ፡፡
አሻም የሰልፈኞችን ቅሬታ መነሻ በማድረግ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳዳሪ አማን ከድርን እንዲሁም የስልጤ ዞን አስተዳዳሪ አሊ ከድር ምላሽ በዘገባው ለማካተት ያደረገችው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም፡፡የሥራ ሃላፊዎች ምላሽ በሰጡበት አፍታ የምታስተናግድ ይሆናል፡፡
Via Asham
@YeneTube @FikerAssefa
👍2❤1
Forwarded from YeneTube
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
👍1
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር ልትዘረጋ መሆኑ ተገለጸ!
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር በ13 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር ልትዘረጋ መሆኑን አስታውቃለች፡፡
ኬንያ የምትዘረጋው ይህ ፈጣን የባቡር መስመር በኤሌክትሪክ የሚሰራ ሲሆን፤ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ ላሙ ወደብ በማድረግ ኢትዮጵያን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚያገናኝ ብሉምበርግ ዘግቧል።
በዓይነቱ ልዩ ነው የተባለው ይህ የባቡር መስመር በፈረንጆቹ 2025 ሥራ እንደሚጀመር እና 3 ሺሕ ከሎ ሜትር ወይም 1 ሺሕ 864 ማይል እንደሚረዝም ታውቋል፡፡
የባቡር መስመሩ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ አድርጎ፣ በኬንያዋ ማዕከላዊ ከተማ ኦሲዮሎን በኩል፣ ናይሮቢን እና አዲስ አበባን በማገናኘት የመጨረሻም መዳረሻውን ደቡብ ሱዳን ጁባ እንደሚያደርግ ተነግሯል፡፡
ይህ ፈጣን የባቡር መስመር “ኢትዮጵያ በአሰብ እና ምጽዋ እንዲሁም ጅቡቲ ወደቦች ላይ ያላትን ጥገኝነት የሚቀንስ ነው” የተባለ ሲሆን፤ ሌሎች በርካታ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች እንዳሉትም ተገልጿል፡፡
በዚሁ ፈጣን የባቡር መስመር ዝርጋታ አማካኝነት ደቡብ ሱዳን ኹለተኛ ወደብ እንደሚኖራትም ተመላክቷል።
የባቡር መስመር ዝርጋታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠጥ በሚጀምርበት ወቅት፣ ከላሞ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ውል የፈጸመው ላፕሴት፣ በዓመት ከ29 ሚሊዮን ቶን በላይ ጭነት እና 700 ሺሕ ተጓዦችን እንደሚያመላልስ አስታውቋል።
🖋Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር በ13 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር ልትዘረጋ መሆኑን አስታውቃለች፡፡
ኬንያ የምትዘረጋው ይህ ፈጣን የባቡር መስመር በኤሌክትሪክ የሚሰራ ሲሆን፤ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ ላሙ ወደብ በማድረግ ኢትዮጵያን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚያገናኝ ብሉምበርግ ዘግቧል።
በዓይነቱ ልዩ ነው የተባለው ይህ የባቡር መስመር በፈረንጆቹ 2025 ሥራ እንደሚጀመር እና 3 ሺሕ ከሎ ሜትር ወይም 1 ሺሕ 864 ማይል እንደሚረዝም ታውቋል፡፡
የባቡር መስመሩ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ አድርጎ፣ በኬንያዋ ማዕከላዊ ከተማ ኦሲዮሎን በኩል፣ ናይሮቢን እና አዲስ አበባን በማገናኘት የመጨረሻም መዳረሻውን ደቡብ ሱዳን ጁባ እንደሚያደርግ ተነግሯል፡፡
ይህ ፈጣን የባቡር መስመር “ኢትዮጵያ በአሰብ እና ምጽዋ እንዲሁም ጅቡቲ ወደቦች ላይ ያላትን ጥገኝነት የሚቀንስ ነው” የተባለ ሲሆን፤ ሌሎች በርካታ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች እንዳሉትም ተገልጿል፡፡
በዚሁ ፈጣን የባቡር መስመር ዝርጋታ አማካኝነት ደቡብ ሱዳን ኹለተኛ ወደብ እንደሚኖራትም ተመላክቷል።
የባቡር መስመር ዝርጋታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠጥ በሚጀምርበት ወቅት፣ ከላሞ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ውል የፈጸመው ላፕሴት፣ በዓመት ከ29 ሚሊዮን ቶን በላይ ጭነት እና 700 ሺሕ ተጓዦችን እንደሚያመላልስ አስታውቋል።
🖋Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
❤1👍1
የቻይና መንግስት በሰጠው የነፃ ትምህርት እድል አሸናፊ ለሆኑ ተማሪዎች ሽኝት ተደረገ።
የቻይና መንግስት በሰጠው የነጻ የትምህርት እድል አሸናፊ ለሆኑ 26 ተማሪዎች አዲስ አበባ በሚገኘው የቻይና ኢምባሲ ትናንት ሽኝት ተደርጓል።በሽኝት መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ የቻይና አምባስደር ዣዎ ዚዩአን ሀገራቸው በኢትዮጵያ የሚደረገውን የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግርን በዘላቂነት እንደምትደግፍ ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አያይዘውም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያና ቻይና መካከል ያለው ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂካዊ ትብብር የጋራ በሆኑ ጉዳዮች በዘላቂነት ለመስራት እንደሚያስችል አብራርተዋል።በትምህርት ሚንስቴር የከፍተኛ ትምህርት አለማቀፋዊነትና ስኮላርሺፕ ዴስክ ሀላፊ ዶ/ር ኢዶሳ ተርፋሳ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የሰለጠነ የሰው ሀይል ግንባታ ሂደት ውስጥ የቻይና መንግስት እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ተማሪዎች ተጨባጭ እውቀት በመቅሰምና ወደ ሀገራቸው በመመለስ በእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ግምባታ የበኩላቸውን አስተዋጾ እንዲያደርጉም አሳስበዋል።በተደረገው የሽኝት መርሃ ግብር ላይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎችና ቀደም ሲል በቻይና ትምህርታቸውን ተከታትለው የተመለሱ ምሁራን ልምዳቸውን አካፍለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የቻይና መንግስት በሰጠው የነጻ የትምህርት እድል አሸናፊ ለሆኑ 26 ተማሪዎች አዲስ አበባ በሚገኘው የቻይና ኢምባሲ ትናንት ሽኝት ተደርጓል።በሽኝት መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ የቻይና አምባስደር ዣዎ ዚዩአን ሀገራቸው በኢትዮጵያ የሚደረገውን የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግርን በዘላቂነት እንደምትደግፍ ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አያይዘውም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያና ቻይና መካከል ያለው ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂካዊ ትብብር የጋራ በሆኑ ጉዳዮች በዘላቂነት ለመስራት እንደሚያስችል አብራርተዋል።በትምህርት ሚንስቴር የከፍተኛ ትምህርት አለማቀፋዊነትና ስኮላርሺፕ ዴስክ ሀላፊ ዶ/ር ኢዶሳ ተርፋሳ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የሰለጠነ የሰው ሀይል ግንባታ ሂደት ውስጥ የቻይና መንግስት እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ተማሪዎች ተጨባጭ እውቀት በመቅሰምና ወደ ሀገራቸው በመመለስ በእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ግምባታ የበኩላቸውን አስተዋጾ እንዲያደርጉም አሳስበዋል።በተደረገው የሽኝት መርሃ ግብር ላይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎችና ቀደም ሲል በቻይና ትምህርታቸውን ተከታትለው የተመለሱ ምሁራን ልምዳቸውን አካፍለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
የአማራ ክልል ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ!
ለአንድ ቀን በባሕር ዳር ሲካሄድ የቆየው የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቋል፡፡
የቀድሞውን ርእሰ መሥተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለን የመልቀቂያ ጥያቄ ተቀብሎ የአቶ አረጋ ከበደን ርእሰ መሥተዳድርነት ሹመት ያጸደቀው ምክር ቤቱ በአዲሱ ርእሰ መሥተዳድር በእጩነት የቀረቡትን የተለያዩ ሹመቶች ተወያይቶ አጽዷል፡፡
በዚሁ መሠረት፤
1.አቶ አብዱ ሁሴን የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር
2.ዶክተር አህመዲን መሐመድ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተማ እና መሰረተ ልማት ቢሮ ኅላፊ
3.ዶክተር ድረስ ሳህሉ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኅላፊ
4.ዶክተር ሙሉነሽ ደሴ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማእረግ የማሕበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኅላፊ
5.አቶ ደሳለኝ ጣሰው በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ጉዳዮች አስተባባሪ እና የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኅላፊ
6.ዶክተር ጋሻው አወቀ የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ኅላፊ
7.አቶ ብርሃኑ ጎሽም የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኅላፊ
8.ዶክተር መንገሻ ፈንታው የአማራ ክልል ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ኅላፊ
9.ዶክተር ስቡህ ገበያው የአማራ ክልል ሥራ እና ስልጠና ቢሮ ኅላፊ
10.አቶ ክብረት አህመድ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኅላፊ
11.አቶ አብዱልከሪም መንግሥቱ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኅላፊ
12. ዶክተር ደመቀ ቦሩ የአማራ ክልል ፕላን እና ልማት ቢሮ ኅላፊ ሆነው ተሹመዋል።
ከላይ የተጠቀሱት ተሿሚዎች በእጩነት የቀረቡ ሲሆን ሌሎቹ ተቋማት ባሉበት እንደሚቀጥሉ ርእሰ መሥተዳድሩ መግለጻቸውን አሚኮ ዘግቧል። የምክር ቤት አባላቱ በእጩ ተሿሚዎች ላይ ሰፊ ውይይት እና ምክክር ካደረጉ በኋላ ሹመታቸውን አጽድቀዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ለአንድ ቀን በባሕር ዳር ሲካሄድ የቆየው የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቋል፡፡
የቀድሞውን ርእሰ መሥተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለን የመልቀቂያ ጥያቄ ተቀብሎ የአቶ አረጋ ከበደን ርእሰ መሥተዳድርነት ሹመት ያጸደቀው ምክር ቤቱ በአዲሱ ርእሰ መሥተዳድር በእጩነት የቀረቡትን የተለያዩ ሹመቶች ተወያይቶ አጽዷል፡፡
በዚሁ መሠረት፤
1.አቶ አብዱ ሁሴን የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር
2.ዶክተር አህመዲን መሐመድ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የከተማ እና መሰረተ ልማት ቢሮ ኅላፊ
3.ዶክተር ድረስ ሳህሉ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኅላፊ
4.ዶክተር ሙሉነሽ ደሴ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማእረግ የማሕበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኅላፊ
5.አቶ ደሳለኝ ጣሰው በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ጉዳዮች አስተባባሪ እና የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኅላፊ
6.ዶክተር ጋሻው አወቀ የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ኅላፊ
7.አቶ ብርሃኑ ጎሽም የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኅላፊ
8.ዶክተር መንገሻ ፈንታው የአማራ ክልል ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ኅላፊ
9.ዶክተር ስቡህ ገበያው የአማራ ክልል ሥራ እና ስልጠና ቢሮ ኅላፊ
10.አቶ ክብረት አህመድ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኅላፊ
11.አቶ አብዱልከሪም መንግሥቱ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኅላፊ
12. ዶክተር ደመቀ ቦሩ የአማራ ክልል ፕላን እና ልማት ቢሮ ኅላፊ ሆነው ተሹመዋል።
ከላይ የተጠቀሱት ተሿሚዎች በእጩነት የቀረቡ ሲሆን ሌሎቹ ተቋማት ባሉበት እንደሚቀጥሉ ርእሰ መሥተዳድሩ መግለጻቸውን አሚኮ ዘግቧል። የምክር ቤት አባላቱ በእጩ ተሿሚዎች ላይ ሰፊ ውይይት እና ምክክር ካደረጉ በኋላ ሹመታቸውን አጽድቀዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
👍2❤1