YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የአፍሪካ ህብረት ኒጀርን ከአባልነት ተሳትፎ አገደ!

የአፍሪካ ህብረት በፈረንጆቹ ሐምሌ 26 ቀን 2023 የተካሄደውን መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ ኒጀርን ከሁሉም እንቅስቃሴዎቹ እንዳትሳተፍ ማገዱን አስታወቀ፡፡ህብረቱ ዛሬ በሰጠው መግለጫ የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች በምርጫ ስልጣን የያዙትን ፕሬዚዳንት መሃመድ ባዙምን ከእስር እንዲፈቱ እና ወደ ቤታቸው እንዲመልሱ ጥሪ አቅርቧል።

የአፍሪካ ህብረት የሰላም እና የፀጥታው ምክር ቤት÷ የምዕራብ አፍሪካ ህብረት (ኢኮዋስ) ለወታደራዊ ጣልቃገብነት ተጠባባቂ ሃይል ለማንቀሳቀስ ያሳለፈውን ውሳኔ መመልከቱንም ሬውተርስ ዘግቧል፡፡የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እንደዚህ አይነት ሃይል ማሰማራት ያለውን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና የደህንነት አንድምታ እንዲገመግም ጠይቋል።የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማህበረሰብ (ኢኮዋስ) ዲሞክራሲን ወደነበረበት ለመመለስ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ካልተሳካ ወታደሮቹን ወደ ኒጀር ለመላክ መዘጋጀቱን አስታውቋል።

የአፍሪካ ህብረት ሁሉም አባል ሀገራቱ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የኒጀርን ወታደራዊ ኃይል ህጋዊ ሊያደርግ ከሚችል ማንኛውም እርምጃ እንዲቆጠቡ ጠይቋል፡፡ከአፍሪካ ውጭ የትኛውም ተዋናይም ሆነ ሀገር የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት እንደማይቀበለውም በአጽንኦት አስታውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
መንግሥት በሳዑዲ በድንበር ጠባቂዎች ተፈጽሟል ስለተባለው የኢትዮጵያዊያን ግድያ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን ገለጸ!

የኢትዮጵያ መንግሥት በሳዑዲ አረቢያና የመን ድንበር ላይ “በድንበር ጠባቂዎች ተፈጽሟል” የተባለውን የኢትዮጵያዊያን ግድያ በቅርበት እየተከታተለ እንደሚገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ለመሻገር ሲሞክሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ- የመን ድንበር ላይ “በጅምላ ተገድለዋል” በሚል ሂውማን ራይትስ ዎች ባወጣው ሪፖርት ላይ የተላለፈውን መረጃ በትኩረት እየተከታተልኩኝ ነው ብሏል፡፡

መንግሥት ከሳዑዲ መንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን ጉዳዩን በአስቸኳይ በማጣራት እንደሚያሳውቅ የገለጸ ሲሆን፤ ምርመራው እስኪጠናቀቅ ድረስም አላስፈላጊ የሆኑ ግምቶችን ከማድረግ መቆጠብ እንደሚገባም አሳስቧል።ኢትዮጵያና ሳዑዲ አረብያ መሰል አሰቃቂ ድርጊቶችን እንደሚያወግዙ የገለጸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ኹለቱ አገራትም የረዥም ጊዜ ጠንካራና ጥሩ የኹለትዮሽ ግንኙነት እንዳላቸው አስታውቋል፡፡

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅት ሂዩውማን ራይትስ ዎች እ.ኤ.አ ከመጋቢት 2022 እስከ ሰኔ 2023 ወር ድረስ፤ የየመን ድንበርን ለመሻገር የሞከሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ ድንበር ጠባቂዎች መገደላቸውን ትናንት ነሐሴ 15/2015 ባወጣው የምርመራ ሪፖርት ማስታወቁን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ድርጅቱ እማኞች “የሳዑዲ ወታደሮች ከባድ መሳሪያዎች በመጠቀም ድንበሩ ለማቋረጥ በሚሞክሩ ሰዎች ላይ ኹሉ ተኩስ እንደሚከፍቱና ጉዳት ደርሶባቸዉ ሕይወታቸዉ ያላለፈ ሰዎችንም እየፈለጉ ወደ ማጎሪያ ካምፕ እንደሚያስገቡ ነግረውኛል” ሲል ባወጣው ሪፖርት ላይ ገልጿል።ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተከራካሪ ድርጅቱ፤ ለእነዚህ በመቶዎች ለሚቆጠሩ ሕጻናት እና ሴቶች ሞት፣ የአካል ጉዳት እና ስቃይም የሳዑዲ ባለስልጣናትን ተጠያቂ አድርጓል።

Via Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው ዓመት ጀምሮ የቅደመ ምረቃ ተማሪዎችን በውድድር ብቻ እንደሚቀበል ገለጸ!

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን የሚቀበለው በምደባ ሳይሆን በውድድር መሆኑን አስታወቀ። ዩኒቨርስቲው ክፍያ የሚፈጸሙ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን “በልዩ” ሁኔታ ለማስተማር እንዳቀደም ገልጿል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ይህንን ያስታወቀው የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ መሆኑን አስመልክቶ ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 16፤ 2015 በዋናው ቅጥር ግቢ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።መግለጫውን የሰጡት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ራስ ገዝ ለመሆን ላለፉት ሁለት ዓመታት ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር ስር ያሉ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ የተዘጋጀው አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀው ባለፈው ግንቦት ወር ነበር።የዚህን አዋጅ መውጣት ተከትሎም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ያስቻለው ደንብ፤ ከሶስት ሳምንት በፊት ሐምሌ 28፤ 2015 በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቋል።የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት በዛሬው መግለጫቸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ወደ ራስ ገዝነት የሚያደርገውን ሽግግር “ሁለት ዓመት ባልሞላ” ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ማቀዱን አስታውቀዋል።

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@YeneTube @FikerAssefa
የመከላከያ ሚኒስትሩ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ምዕራብ ትግራይ ወደነበረበት ይመለሳል አሉ!

መከላከያ ሚንስትር አብርሃም በላይ የምዕራብና ደቡባዊ ትግራይ አካባቢዎች በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት መሠረት "ወደነበሩበት ይመለሳሉ" በማለት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።

ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የአሸንዳ በዓልን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው መሆኑ ታውቋል።

ዶ/ር አብርሃም በመልዕክታቸው ፣ ከግዛቶቹ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎች "በሕገ መንግሥታዊ አግባብ" ይስተናገዳሉ ብለዋል።

መንግሥት የምዕራብ እና ደቡባዊ ትግራይ የጦርነት ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው ለመመለስ እንቅስቃሴዎች እያደረገ መኾኑን የጠቀሱት ሚንስትሩ ፣ በግዛቶቹ በጦርነቱ ወቅት በተቋቋሙ አስተዳደራዊ መዋቅሮች ሕዝብ በሚመርጠው መዋቅሮች እንደሚተኩም አብርሃም ጠቁመዋል።

[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
ደረቅ ሳሙና በተለያዩ ክፍለ ሀገራት ላይ ማከፋፈል የምትፈልጉ አከፋፋዮች በውስጥ መስመር ያናግሩን።

የሳሙናው ይዘት

የሳሙናው አይነት:- ደረቅ ሳሙና
ከለር :- ቀለም ነጭ
ግራም :- 200

የፋብሪካ ቦታ :- ሀዋሳ

@AbelAbi123
በ1500 ሜትር ፍፃሜ ኢትዮጵያ በድርብ ወልተጂ የብር ሜዳሊያ አገኘች !

@YeneTube @FikerAssefa
በቡዳፔስት የ3000 ሜትር መሰናክል ወንዶች ለሜቻ ግርማ ለኢትዮጲያ የብር ሜዳሊያ አስገኘ።ሞሮኳዊው አትሌት በአንደኛነት አጠናቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
Facebook, Twitter, Instagram እና በመሳሳሉት የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ድርጅትዎን ፤ አገልግሎትዎን እና ምርትዎን ማስተዋወቅ ፈልገዋል? እንግዲያውስ መፍትሄው እኛ ጋር ነው።

በማንኛውም Social Media  Boost ለማድረግ ካሰቡ ይደውሉልን፤ በተመጣጣኝ ዋጋ ታማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን::

ከዚህም በተጨማሪ የቴሌግራም ፕሪሚየም ጨምሮ ለተለያዩ ኢንተርናሽናል አገልግሎቶች ክፍያዎችን መፈጸም ካስፈለግዎ ከስር በተቀመጡ አድራሻዎች ያናግሩን።

Telegram: @adsommar
📞0929334267
👍1
💥💥ዘመኑ የሚፈልገውን የቴክኖሎጂ ባለሙያ ሆነው በቀላሉ ከቤት ሆነው የሚሰሩበትን የሶሻል ሚድያ ማስታወቂና አሰራር ስልጠና እንዲሁም መሰረታዊ የኮምፒውተር ኘሮግራሚንግ በቤቶ ሆነው በ 2 ወር ብቻ የተፈላጊ ሙያ ባለቤት ይሁኑ!

- ስልጠናው ቨርቹዋል ስለሆነ በየትኛውም ቦታ ሆነው መማር ይችላሉ!

- ስልጠናውን ሲወስዱ በተግባር የታገዘ ልምምድ እንዲሁም ሲጨርሱ የስራ እድል እናመቻቻለን!

- ስልጠናውን ሲጨርሱ ሰርተፊኬት ያገኛሉ!

- ከተለያዩ ውጭ ሀገር መግዛት የሚችሉበት እንዲሁም የሶሻል ሚድያ ማስታወቂያ መስራት የሚችሉበት የራሳቹን የቨርቹዋል ማስተር ካርድ ያገኛሉ!

- የተለያዩ ኘሮጀክቶችን በመስራት ልምድ ይቀስማሉ!

- የተለያዩ ኦላይን ኮርሶችን በነፃ በቤቶ የሚማሩበት እድል እንሰጣለን!

🎓 ለአዳዲስ ተመራቂ ተማራዎች ልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል!

ለተጨማሪ መረጃ 0954742475 ይደውሉ
ወይንም በቴሌግራም @Bekalu_gebremariam ያዋሩን
👍2
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ አፓርትመንቶችን በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
🌹 የኔክሰስ ሆቴል
🌹 የግራንድ ሆቴል
🌹 የኢግል ፓክ ኢንዱስትሪያል እና
🌹 የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
👉ባለ 2 መኝታ
👉ባለ 3 መኝታ
👉የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
👉ግንባታቸው 90% የደረሰ !!!
👉ማስረከቢያ ጊዜ ከ6 ወር -1 አመት
👉ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
✍️100% በ1 አመት በ"4"ዙር
✍️50/50 ከባንክ ጋር ከ5-20 አመት
🙏🙏🙏🙏🙏
ለበለጠ መረጃ
@setu1988
+251936606665
👍1
በሰሜን ሸዋ እና በደቡብ ወሎ ዞኖች በተደረጉ የተኩስ ልውውጦች ሰብአዊ እና ቁሳዊ ጉዳት መድረሱ ተገለጸ!

በዐማራ ክልል በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተስፋፋው ግጭት፣ በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ ግድም ወረዳ በማጀቴ ከተማ እና በዙሪያው፣ እንዲሁም በደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ወረዳ ወግዲ ከተማ እና አካባቢው ጉድት መድረሱን ነዋሪዎች ገለፁ።

በግጭቱ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን፣ ለአካል ጉዳት ስለ መዳረጋቸው ነዋሪዎቹ ገልፀዋል። በመሠረተ ልማቶች እና በግለሰቦች ንብረት ላይም ቁሳዊ ጥፋቶች ስለ መድረሳቸው፣ ለቪኦኤ አስተያየታቸውን የሰጡ ግለሰቦች ተናግረዋል፡፡

በማጀቴ ከተማ እና አካባቢው ያለው የግጭት ሁኔታ በውጊያው የቆሰሉትን ወደ ሕክምና ተቋማት ማድረስን አዳጋች እንዳደረገውና ወደ ግለሰቦች ቤቶች በማግለል ጭምር ለመስጠት እየተሞከረ እንደኾነ፣ የመረጃ ምንጮቹ ጠቅሰዋል፡፡

ከ15 ቀናት በፊት፣ በወግዲ ከተማ አካባቢ በነበረ ውጊያ፣ የደረሱበት የማይታወቅ ሰዎች ስለ መኖራቸውና ነዋሪው በጸጥታ ስጋት፣ በመንግሥታዊ አገልግሎት ዕጦት እና በኑሮ ውድነት እንደተቸገረም፣ አስተያየት ሰጭዎቹ አመልክተዋል፡፡ የወረዳው መንግሥታዊ መዋቅር ለጊዜው አገልግሎት እየሰጠ ባለመኾኑ፣ ደረሰ ስለተባለው ጉዳት፣ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት አልተቻለም፡፡ከዐማራ ክልል እና ፌደራል መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ሓላፊዎች ምላሽ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ አልተሳካም።

Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ በመጪው ዓመት ጥር ወር ዋናውን ኮንፍረንስ ለማካሄድ “የሚቻለውን ጥረት እያደረግኩ ነው” አለ!

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመጪው ዓመት ጥር ወር ላይ ዋናውን የምክክር ጉባኤ ለመጥራት “የሚቻለውን ጥረት” እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።ኮሚሽኑ ከነገ ነሐሴ 18፤ 2015 ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የጉባኤውን ተሳታፊዎች መለየት እንደሚጀምርም ይፋ አድርጓል።

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ይህን ይፋ ያደረገው፤ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 17 በዋና ጽህፈት ቤቱ እየሰጠ ባለው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።ባለፈው ዓመት ታህሳስ ወር ላይ በአዋጅ የተቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ እስካሁን ድረስ በአምስት ክልሎች እና አንድ ከተማ አስተዳደር የጉባኤ ተሳታፊዎች ልየታን አከናውኗል።

ኮሚሽኑ የጉባኤ ተሳታፊዎችን የለየባቸው አካባቢዎች፤ በሐረሪ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ ናቸው። በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የተገኙት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ፤ “እስከ ጥር ድረስ ዋናውን ሀገራዊ ምክክር ኮንፍረንስ ለመጥራት የሚቻለንን ጥረት እያደረግን ነው” ብለዋል።

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@YeneTube @FikerAssefa
👍1