YeneTube
116K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ኹለተኛው ምዕራፍ የኦነግ ሸኔ እና የመንግሥት ድርድር በቅርቡ እንደሚደረግ ተሰማ

ለኹለተኛ ጊዜ በፌዴራል መንግሥት እና በኦነግ ሸኔ መካከል የሚደረገው ድርድር በቅርቡ እንደሚጀመር የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ አስታወቀ፡፡

የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ለኹለተኛ ጊዜ በፌዴራል መንግሥት እና በኦነግ ሸኔ መካከል የሚደረገው ድርድር በቅርቡ እንደሚጀመር አሳውቀዋል፡፡

ኃላፊው በሰጡት ማብራሪያ መንግሥት ከመቼውም ጊዜ በላይ ግጭትን በዘላቂነት ለማቆም፣ የሕዝብን እና የአገርን ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስጠበቅ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተለይም በኦሮሚያ ክልል በሀሳብ አለመግባባት በመንግሥት እና በኦነግ ሸኔ ኃይሎች መካከል እየተፈጠሩ ባሉ ግጭቶች እየተሰቃየ የሚገኘውን ሕዝብ በዘላቂነት ሰላሙን ለመመለስ እና በነጻነት ወጥቶ እንዲገባ ለማስቻል በሰለጠነ መንገድ ከመወያየት እና ውሳኔ ላይ ከመድረስ በቀር ሌላ አማራጭ የለንም ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

ለዚህም <<መንግሥት በክልሉ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን ወደ ሠላም መንገድ ለመመለስ ብሎም ሃሳባቸውን ለመስማት ዝግጁ ነው።>> ያሉ ሲሆን፤ ሕዝቡ ከጦርነት ወሬ ወጥቶ ወደ መደበኛ ሕይወቱ እንዲመለስ እንዲሁም ኑሮውን እንዲያሻሽል መግባባት እና ሠላም ማውረዱ አማራጭ የሌለው መፍትሄ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
 
በታንዛኒያ ሲደረግ በነበረው ድርድር የተሻለ መቀራረብ እና መግባባት እንደነበረ ያስታወሱት ኃላፊው፤ በቅርቡ በሚደረገው ኹለተኛ ዙር የድርድር መድረክ ይህንኑ ምህዳር በማስፋት ዘላቂነት ያለው ሰላም ለማስፈን መንግሥት አጽንኦት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

የትኛውም የፖለቲካ ኃይል ከዚህ በፊት ካሳለፍናቻው ጥፋቶች በመማር እና አሁን የተመቻቸውን የውይይት እንዲሁም የድርድር ጅማሮ በመጠቀም ወደ ሰላም መንገድ እንዲመጣም የኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አሳስበዋል፡፡

የሕዝባችንን እና የአገራችንን ሰላም ለመመለስ የተጀመረውን የሰላም ድርድር ለማደናቀፍ እና ከግብ እንዳይደርስ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ሠላም ጠል አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡም ኃላፊው ጠይቀዋል፡፡

የተጀመርው ድርድር በስኬት እንዲጠናቀቅም የሐይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ የአገር ሽማግሌዎች ምሁራን እና መላው ሠላም ወዳድ የኢትዮጵያ ሕዝብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በኦሮሞ ነጻነት ስራዊት እና የፌዴራል መንግሥት መካከል ሲደረግ የነበረው የመጀመሪያው ዙር ድርድር በታንዛኒያ ራስ ገዝ በሆነቸው ዛንዚባር ደሴት በኬንያ እና በታንዛኒያ አደራዳሪነት ሲደረግ እንደነበር ይታወሳል።

በመጀመሪያው ዙር ድርድር ኹለቱ ኃይሎች ባደረጉት ድርድር ያለ ስምምነት መለያየታቸውን ያስታወቁ ሲሆን፤ ስምምንት ላይ ያልተደረሰባቸው ጉዳዮች ውሳኝ የሚባሉ የፖለቲካ ጉዳዮች መሆናቸውም ገልጸዋል፡፡

Via:- አዲስ ማለዳ
@Yenetube @Fikerassefa
በአዲስ አበባ የወረዳ አመራሩ በፖሊስ ተገደሉ!

በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ አለባቸው አሞኜ በዛሬው ዕለት በቢሮአቸው ሥራ ላይ እንዳሉ ተገደሉ።የክፍለ ከተማው ኮሚኒኬሽን ባሰራጨው መረጃ ፤ " አቶ አለባቸው አሞኜ ቢሯቸው ውስጥ ቁጭ ብለው የህዝብ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ከአንድ ተገልጋይ በደረሰባቸው ጥቃት ህይወታቸው አልፏል" ብሏል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ፣ "በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 8 ዋና ስራ አስፈፃሚ የእለት ከእለት ተግባራቸውን በማከናወን ላይ እንዳሉ ግንቦት 4 ቀን 2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ በፖሊስ አባል ተገድለዋል" ብሏል፡፡

ግድያውን የፈፀመው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካሳንቺስ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የቀጠና ኦፊሰር መሆኑን የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ፣ የፖሊስ አባሉ የግል ጉዳዩ እንዲፈፀምለት ለወረዳ 8 አስተዳደር ጽ/ቤት አመልክቶ ለጉዳዩ ምላሽ እንደሚሰጠው የተገለፀለት ቢሆንም ጥያቄዬ እንዳይፈፀም የከለከልከው አንተነህ በሚል ምክንያት የወረዳውን ዋና ስራ አስፈፃሚን ቢሯቸው ውስጥ በስራ ላይ እንዳሉ በታጠቀው ሽጉጥ እንደገደላቸው መታወቁን አብራርቷል።ወንጀሉን የፈፀመው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራው እየተጣራ መሆኑን የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በአመራሩ መገደል ማዘኑንም አስታውቋል።

[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል በባህርዳር እና በሌሎችም ትልልቅ ከተሞች ታግዶ የነበረው የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት ተለቋል።

በአማራ ክልል ከልዩ ኃይል እንደገና መደራጀት ጋር ተያይዞ በተከሰተው አለመግባባት በትልልቅ ከተሞች የኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጦ እንደቆየ ሲገለጽ ነበር።

ካሳለፍነው ረቡዕ ግንቦት 2/2015 ምሽት ጀምሮ ግን አገልግሎቱ መለቀቁን ኢትዮ ኤፍ ኤም ከነዋሪዎቹ አረጋግጧል።የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩት ጎንደር፣ ባህርዳር እና ወልዲያ ከዕረቡ ምሽት ጀምሮ መስራት እንደጀመረ ታውቋል፡፡

የሞባይል ዳታ አገልግሎት በአማራ ክልል በጎንደር፣ በባህርዳር እና በወልዲያ ከተማ ከተዘጋ ከኹለት ሳምንታት በላይ ያስቆጠረ ሲሆን፣ የተዘጋበት ዋና ምክንያት በክልሉ ከሚንቀሳቀሰው ታጣቂ ኃይልና ከክልሉ ልዩ ኃይል ጋር በተገናኘ በተፈጠረው ውጥረት እንደነበር ተነግሯል፡፡

[ኢትዮ ኤፍ ኤም]
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በደቡብ አፍሪካ የአሜሪካ አምባሳደር ሩበን ብሪጌቲ ደቡብ አፍሪካ ለሩሲያ ጦር መሳሪያዎችንና ተተኳሾችን ሰጥታለች በማለት ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ መክሰሳቸውን የውጭ ዜና ወኪሎች ዘግበዋል።

አምባሳደር ብሪጌቲ፣ ባለፈው ታኅሳስ "ሌዲ አር" የተባለች የሩሲያ መርከብ ደቡብ አፍሪካ ለሩሲያ የሰጠችውን ጦር መሳሪያ ከኬፕታውኑ ከደቡብ አፍሪካ ወደብ ጭና ወደ ሩሲያ ስለመጓጓዟ "አሜሪካ ርግጠኛ ናት" ማለታቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። አምባሳደሩ አያይዘውም፣ ደቡብ አፍሪካ በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ላይ ይዠዋለኹ የምትለውን "ገለልተኛ አቋም" አለማክበሯ፣ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናትን "በእጅጉ አሳስቧል" በማለት ተናግረዋል ተብሏል።የአምባሳደሩን ውንጀላ ተከትሎ፣ የፕሬዝዳንት ሴሪል ራማፎዛ ጽሕፈት ቤት በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል። አምባሳደሩ ውንጀላውን ያቀረቡት፣ ደቡብ አፍሪካ በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ላይ የያዘችውን አቋም ለአሜሪካ ባለሥልጣናት ለማስረዳት ልዐካን ቡድኗን ወደ ዋሽንግተን በላከች ማግስት ነው።

Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
Are you the one?

👉  Learning Management System Developers
👉  Tech Startups & Incubators
👉  Digital Solution Providers
👉  Music Streaming Service Providers
👉  Coding Learning Centers
👉  Digital Library Service Providers
👉  Social Media Training Centers
👉  Student Tutorial Service Providers
👉  Professional Toastmaster's Clubs
👉  Student Club Association
👉  Online Education Service Providers
👉  Digital Theology Service Platforms
👉  Distance Education Learning Centers
👉  Short-term Training Service Institutes

When Yes:
Don't miss a chance to exhibit at the

Edition
5th

Event
Back to School Africa
Festival, 2023.

When
May 19 - 21/2023

Dates
Friday, Saturday, & Sunday

Duration
9am - 7pm

Visit event website👇!  
www.backtoschoolafrica.com 

Follow us on👇
Facebook and LinkedIn

Contact us
 
    ☎️ :   +251 974 08 2036
              +251 974 08 2037

With Support of
FDRE Ministry of Education

     Sponsors
Oracle Academy
Study in Japan
BUKU Digital Platform
DSTV Ethiopia
መርጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ማዕከል በቲክቶክ መቷል።

የባህል መድሀኒት ከአባቶቻችን ባገኘነው ትምህርትና ጥበቡ እንዲሁም ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአረብ ሀገራት በምናመጣቸው መድለኒቾች ፍቱን ህክምናወችን
እንሰጣለን ።
👉ለኪንታሮት በሽታ ታማሚው ባለበት ከቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላ ሳይነካ ሳያቆስል ስራ ሳያስቆም ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል
👉በሌሊት ለሚሸና
👉ለነገረ በትን
👉ለደም ግፊት
👉ለስኳር ህመም መቀነሻ
👉ለሁሉም ቁርጥማት
👉ለዲስክ መንሸራተት ዘላቂ ፈውስ
👉ለፊት ማድያት
👉ለሳል በሽታ
👉ለግርማሞገስ ለህዝብ መስተፋቅር
👉ለማህጸን እንፌክሽን
👉ለአእምሮ ጭንቀት
👉ለወገብ ህመም
👉ለነርብ
👉ጋኔን አጋንንት የሰውጅ ለያዘው
👉የሚጥል በሽታ

👉ለበለጠ መረጃ አድራሻ ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በኮብሉ መጨረሻ ንግድ ባንኩ ላይ።

    ቅርንጫፍ አዲስ አበባ ሳሪስ አደይ አበባ

👉እኒህን እና ሌሎች አገልልግሎቶችን ለማግኔት
                   👎ይደውሉ
👉☎️0917040506
          0912718883

    ቻናሉን ይቀላቀሉ👇
https://tttttt.me/mergatah

👉ቻናሉን በመቀላቀል ሊንኳን በመጫን ጤናወ በቤትወ የባህል ህክምና የእጽዋት የህቡ ስም የጠልሰም ጥቅሞችን ይጋሩ ይፈወሱ

tiktok.com/@u0917040506_0912718883
አዲስ ነገር ከነዳጅ!!ስልፍ ቀረ‼️

በአንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚስተዋሉ ሠልፎች ፤ ኤሌክትሮኒክ የነዳጅ ግብይት ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ በአሽከርካሪዎች እንዲሁም በነዳጅ ማድያዎች በኩል ግብይት ለመፈፀም ቅድመ ዝግጅት ባለመደረጉ ብዙ ሰዓታትን በሰልፍ ላይ እንደሚያጠፉ የከተማዋ አሽከርካሪዎች ገልጸዋል።

ይህንንም ተግዳሮት ከግምት ውስጥ በማስገባት ነዳጅ በተሰኝው መተግበሪያ ላይ በነዳጅ ማደያዎች ያለውን ሰልፍ ለመቅረፍ አሽከርካሪዎች በመጅመሪያ

ነዳጅ መተግበሪያን በመክፈት
STANDBY ሚለውን ይምረጡ❗️

የመዘገቡትን መኪና ይምረጡ

ሚቀዱትን መጠንና ነዳጅ አይነት ያስግቡ፦

🚀ወድያውኑ ስታንድ ባይ ኮድ ይሰጦታል❗️
አሽከርካሪው የሚደርሰውን ኮድ ለነዳጅ ቀጂው በሚሰጥበት ወቅት መተግበሪያው ላይ የሚመጣለትን  ሙሉ መረጃ በማረጋገጥ ግብይቱን በቀላሉ ማጠናቀቅ ይችላል።

ይህም የነዳጅ ቀጂው ሙሉ መረጃ አስገብቶ ግብይት እስኪፈጠር ደረስ ያለውን ጊዜ በመቆጠብ ከአላስፈላጊ ሰልፍ እና መንገላታት የነዳጅ ግብይቱን እንደሚያሳልጥ ተነግሯል።

በነዳጅ አፕ ይጠቀሙ ግዚዎትን ይቆጥቡ።

አሁኑኑ ከ PLAY STORE እና APP STORE ያውርዱ፣ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ አካውንትዎ ጋር ያስተሳስሩ!

For Android: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj


For iOS:
https://apps.apple.com/us/app/nedaj/id1639807926

#Nedaj #nedajapp
ዘመኑን የዋጁ ዝንጥ ፣ ጥንቅቅ ብለው የተሰሩ ፈርኒቸሮችን እነሆ ከ #ላንጋኖ_ፈርኒቸር

ላንጋኖ  ፈርኒቸር
ዘመናዊነትና ውበትን የተላበሱ የሀገር ወስጥ የፈርኒቸር ምርቶቻችን፡-
✔️ ለዜርና የጨርቅ ሶፋዎች

✔️ የአዋቂ እና የህጻን ልጅ አልጋዎች በተለያዩ መጠን እና ዲዛይን

✔️  ቁ/ሳጥኖች በተለያዩ ዲዛይን

✔️ የምግብ ጠረጴዛዎች በተለያየ ዲዛይን፡-በ6ወንበር,በ8ወንበር፣በ4ወንበር

✔️ የሶፋ ጠረጴዛዎች በተለያዩ መጠንና ዲዛይን

✔️  ዘመናዊ ኪችኖች

✔️  የጫማ ሸልፍ በተለያዩ መጠንና ዲዛይን…..ወዘተ ሲሆን በእርስዎ ፍላት መሰረት የሚቀርቡ አዳዲስ ዲዛይኖችን ተቀብለን እናዘጋጃለን፡፡
       
       ልዩነታችን
♦️ ከጊዜ በኃላ ማሳደስ ቢፈልጉ እንደ አዲስ አድርገን መሳደሳችን፣

♦️ ያዘዙትን ፈርኒቸር በቁርጥ ቀጠሮ ቀን እናቀርባን፣

♦️ ከኛ የገዙትን ዕቃዎችን ከረጅም ጊዜ በኃላ በአዲስ መለወጥ ሲፈልጉ እንቀበላለን

♦️ መጓጓዣና ጫኝ እስከ ቤትዎ ድረስ ከኛው መሆኑ፣

♦️ ከደንበኞች ለሚቀርቡ ቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ መስጠታችን

♦️ በማንኛውም በዓላት ወቅት 5% የዋጋ ቅናሽ የሚናደርግ መሆናችን፣

♦️ አዲስ ደንበኛ በርሶዎ በኩል ሲመጣ ማበረታች አዘጋጅተናል
ስለሆነም ለዘላቂ ተጠቃሚነት እና እርካታ የሀገር ውስጥ ፈርኒቸር ምርቶችን ከእኛ ይግዙ፡፡

🛑አድራሻችን፡-ሀዋሳ
ከሳሙኤል ገበያ አዳራሽ ተሻግሮ / ዋንዛ አደባባይ ሳይደርሱ

በሰልክ ቁጥሮቻችን ፡0916581884 /0907212223/0944221511

ይደውሉልን,ይጎበኙን!       
ላንጋኖ ፈርኒቸር
በሀዋሳ የአበራ ላንጋኖ ፈርኒቸር እህት ድርጅት
ምርጫ ቦርድ የሕወሓትን ሕጋዊ ሰውነት ሥረዛ ይነሣልኝ ጥያቄ ውድቅ አደረገ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ላይ ያስተላለፈውን የፓርቲውን ሕጋዊ ሰውነት ሥረዛ ፓርቲው ይነሣልኝ ሲል ያቀረበውን ጥያቄ ቦርዱ ውድቅ ያደረገበት ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።

@YeneTube @FikerAssefa
1
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር የኢትዮጵያው "ቦርከና" ጋዜጣ "በኤርትራና ኢትዮጵያ መካከል ውጥረት እየተፈጠረ ይኾን?" በማለት ያተመውን ሃተታ "በሐሰትና ግምታዊ ድምዳሜ የተሞላ" በማለት ተችቷል።

ሚንስቴሩ በመግለጫው፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በቅርቡ ስለ ሱዳኑ ግጭት በሰጡት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያን ጎሸም ያደረጉ አስመስሎ አቅርቧል በማለት ወቅሷል። ጋዜጣው "ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሥመራ መሄድ ፈልገው፣ የኤርትራ መንግሥት ሁለት ጊዜ ፍቃድ ነፍጓቸዋል" እንዲኹም "ኤርትራ ለአማራ ፋኖዎች ወታደራዊ ሥልጠና በመስጠቷ የዐቢይ ካድሬዎች ኢሳያስን እየተቹ ነው" በማለት የጻፋቸው ነገሮች "ሐሰት" መኾናቸውንም ሚንስቴሩ ገልጧል። ሚንስቴሩ፣ ኤርትራ አዲስ ወታደራዊ ዝግጅት እያደረገች እንደኾነ ጋዜጣው ያሰራጨውን ወሬም "የተሳሳተ" በማለት አስተባብሏል።

@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በአደጋ ስራ ላይ ህይወታቸዉን ላጡ ሰራተኞቹ እዉቅና ሰጠ!

የአዲስአበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በአደጋ መከላከል ወቅት አደጋ አጋጥሟቸዉ ህይወታቸዉን ላጡ የቀድሞ ሰራተኞቹ እዉቅና ሰጥቷል።

በዛሬዉ እለት በተካሄደዉ ስነስርዓት ከ 1981 ዓ.ም ጀምሮ በተከሰቱ አደጋዎች ህይወታቸዉን ላጡ የቀድሞ ሰራተኞች ቤተሰቦች የሜዳሊያ ፣ የእዉቅና ሰርተፍኬት እና የ 20 ሺህ ብር ቦንድ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።

ኮሚሽኑ ለቀድሞ 8 ሰራተኞቹ ነዉ እዉቅናዉን በዛሬው እለት የሰጠዉ። ሰራተኞቹ በእሳት አደጋ ፣ ከወንዝ ሰዎችን ለማዉጣት ባደረጉት ጥረት በተበከለ ዉሃ በመመረዛቸዉ ፣ በመኪና አደጋ እና በአደጋ መከላከል ወቅት በተለያዩ ጉዳቶች ህይወታቸዉን ያጡ ናቸዉ። ኮሚሽኑ ለሰራተኞች ቤተሰቦች እዉቅናዉን ሰጥቷል።

በነገዉ እለትም በአለማቀፍ ደረጃ ለ 24ኛ በአዲስአበባ ደረጃ ለ 2ኛ ግዚ በሚያከብረዉ የአደጋ ግዜ ሰራተኞች ቀንን "የሚጠብቁንን እናክብር በሚል ቃል" ነዉ።

[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
1
የአርቲስት ሒሩት በቀለ ስርዓተ ቀብር የፊታችን ሰኞ ይፈጸማል!

የአርቲስት ሒሩት በቀለ ስርዓተ ቀብር ከነገ በስቲያ ጉለሌ በሚገኘው ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር እንደሚፈጸም የቀብር ስነ ስርዓት አስፈጻሚ ኮሚቴው ገለጸ።

ኮሚቴው ዛሬ በሰጠው መግለጫ፣ የሒሩት በቀለ አስከሬን የፊታችን ሰኞ ሻላ መናፈሻ ጀርባ በሚገኘው መኖሪያ ቤቷ ከጠዋቱ 4 ሰዓት ሽኝት ከተደረገለት በኋላ ወደ ወዳጅነት አደባባይ እንደሚያመራ ገልጿል።

በወዳጅነት አደባባይ በሚኖረው መርሐ-ግብር በመሰረተ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን አማካኝነት የፀሎት ስነ ስርዓት፣የአበባ ማስቀመጥና የታዋቂ ሰዎች ንግግር እንደሚደረግ ኢዜአ ዘግቧል።

በመጨረሻም፣ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ጉለሌ በሚገኘው ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ስርዓተ ቀብሩ እንደሚፈጸም ኮሚቴው አስታውቋል።

[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ የመንግስት መ/ቤቶች የስራ ሰዓትን ወደ 16 ሰዓት ለማራዘም እየተሰራ ነው ተባለ!

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የመንግስት የስራ ተቋማት አገልግሎት የሚሰጡበትን ሰዓት ከ8 ሰዓት ወደ 16 ሰዓት ለማራዘም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተነግሯል፡፡መ/ቤቶቹ አገልግሎታቸውን እስከ ምሽት ድረስ እንዲሰጡ የማድረጉ ተግባር የከተማዋን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴም ያነቃቃል ተብሏል፡፡የከተማ አስተዳደሩ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ባካሄዱት የጋራ ውይይት ላይ ይፋ የተደረገው እቅድ እንደሚያመለክተው፤ በከተማዋ የሚታየውን የተገልጋዮችን ችግርና መጉላላት ለመቅረፍ የሚቻልበት መንገድ እየተፈለገ ነው፡፡

የመንግስት መ/ቤቶች ለተገልጋዮች በሚሰጡት አገልግሎት ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እየቀረቡ መሆኑን የሚጠቁመው ዕቅዱ፤ ይህን ቅሬታና ችግር ለመፍታት የአገልግሎት ሰዓቱን ወደ 16 ሰዓት ማራዘም እንደ አንድ መፍትሄ መወሰዱንና ይህም ለመተግበር እየተሰራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።በዚሁ የመንግስት ስራን ወደ 16 ሰዓት ለማራዘም በተያዘው እቅድ ሰራተኞች በፈረቃ የሚሰሩበት ሁኔታ ሊመቻች እንደሚችልና አሰራሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኞችን አዋጅ የማይጥስ እንደሚሆንም ተነግሯል፡፡ የከተማው አስተዳደር የመ/ቤቶቹን የአገልግሎት ሰዓት የማራዘም ፈቃዱን ተግባራዊ ለማድረግ ጥናት እያካሄደ መሆኑንና በመጪው በጀት ዓመት ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑም ተጠቅሷል፡፡

Via Addis Admass
@YeneTube @FikerAssefa
የሙዚቀኛ ዳዊት ፍሬው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ!

የሙዚቀኛ ዳዊት ፍሬው የቀብር ሥነ-ሥርዓት በዛሬው ዕለት በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሙዚቀኛው አድናቂዎች እና ዘመድ ወዳጆቹ ተገኝተዋል።

ሙዚቀኛ ዳዊት ፍሬው ኃይሉ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ትምህርቱን 'ሜጀር ክላርኔት' በማድረግ የተመረቀ ሲሆን የአልቶ ሳክስፎን እና ክራር ተጨዋችም ነበር።በአስደናቂ ክላርኔት ጨዋታው የሚታወቀው ዳዊት ፍሬው በሙዚቃ ትምህርት ቤት ቆይታው፣ የታላላቅ ሙዚቃ አቀናባሪዎች /ኮምፖዘሮችን/ የክላርኔት ሥራዎች ተጫውቷል።

[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
Are you the one?

👉  Learning Management System Developers
👉  Tech Startups & Incubators
👉  Digital Solution Providers
👉  Music Streaming Service Providers
👉  Coding Learning Centers
👉  Digital Library Service Providers
👉  Social Media Training Centers
👉  Student Tutorial Service Providers
👉  Professional Toastmaster's Clubs
👉  Student Club Association
👉  Online Education Service Providers
👉  Digital Theology Service Platforms
👉  Distance Education Learning Centers
👉  Short-term Training Service Institutes

When Yes:
Don't miss a chance to exhibit at the

Edition
5th

Event
Back to School Africa
Festival, 2023.

When
May 19 - 21/2023

Dates
Friday, Saturday, & Sunday

Duration
9am - 7pm

Visit event website👇!  
www.backtoschoolafrica.com 

Follow us on👇
Facebook and LinkedIn

Contact us
 
    ☎️ :   +251 974 08 2036
              +251 974 08 2037

With Support of
FDRE Ministry of Education

     Sponsors
Oracle Academy
Study in Japan
BUKU Digital Platform
DSTV Ethiopia
👍1
መርጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ማዕከል በቲክቶክ መቷል።

የባህል መድሀኒት ከአባቶቻችን ባገኘነው ትምህርትና ጥበቡ እንዲሁም ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአረብ ሀገራት በምናመጣቸው መድለኒቾች ፍቱን ህክምናወችን
እንሰጣለን ።
👉ለኪንታሮት በሽታ ታማሚው ባለበት ከቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላ ሳይነካ ሳያቆስል ስራ ሳያስቆም ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል
👉በሌሊት ለሚሸና
👉ለነገረ በትን
👉ለደም ግፊት
👉ለስኳር ህመም መቀነሻ
👉ለሁሉም ቁርጥማት
👉ለዲስክ መንሸራተት ዘላቂ ፈውስ
👉ለፊት ማድያት
👉ለሳል በሽታ
👉ለግርማሞገስ ለህዝብ መስተፋቅር
👉ለማህጸን እንፌክሽን
👉ለአእምሮ ጭንቀት
👉ለወገብ ህመም
👉ለነርብ
👉ጋኔን አጋንንት የሰውጅ ለያዘው
👉የሚጥል በሽታ

👉ለበለጠ መረጃ አድራሻ ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በኮብሉ መጨረሻ ንግድ ባንኩ ላይ።

    ቅርንጫፍ አዲስ አበባ ሳሪስ አደይ አበባ

👉እኒህን እና ሌሎች አገልልግሎቶችን ለማግኔት
                   👎ይደውሉ
👉☎️0917040506
          0912718883

    ቻናሉን ይቀላቀሉ👇
https://tttttt.me/mergatah

👉ቻናሉን በመቀላቀል ሊንኳን በመጫን ጤናወ በቤትወ የባህል ህክምና የእጽዋት የህቡ ስም የጠልሰም ጥቅሞችን ይጋሩ ይፈወሱ

tiktok.com/@u0917040506_0912718883