የመመሪያ ጥሰት በፈጸሙ 106 የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አስታወቀ።
እርምጃ የተወሰደባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዝርዝር (በፎቶ)⬆️
@YeneTube @FikerAssefa
እርምጃ የተወሰደባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዝርዝር (በፎቶ)⬆️
@YeneTube @FikerAssefa
በጦርነት እና እገዳ ከሌላዉ የኢትዮጵያ ክፍል በተገለለችዉ ትግራይ አለቅጥ የናረዉ የምግብ ሸቀጦች ዋጋ የሕዝቡን ኑሮ እያቃወሰዉ መሆኑ ተዘገበ።
ዶይቸ ቨለ እንደዘገበዉ መቀሌ ዉስጥ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ 5 ብር ይሸጥ የነበረዉ 50 ግራም ዳቦ (ፉርኖ) ሰሞኑን 8 ብር ገብቷል።የፉርኖ ዱቄት፣የጤፍ፣ የበርበሬና የመሰል የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ ሲጨምር ማኮሮኒና ፓስታን የመሳሰሉ የፋብሪካ ምርቶችን ገበያ ላይ ማግኘት ሲበዛ ከባድ ነዉ።የዚያኑ ያክል እዚያዉ ትግራይ የሚመረቱ እንደ ሽንኩርትና ቲማቲም የመሳሰሉ ማጣፈጫዎች ዋጋ ብዙ ለዉጥ አላሳየም።የከብትና የስጋ ዋጋ ግን ቀንሷል።
@YeneTube @FikerAssefa
ዶይቸ ቨለ እንደዘገበዉ መቀሌ ዉስጥ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ 5 ብር ይሸጥ የነበረዉ 50 ግራም ዳቦ (ፉርኖ) ሰሞኑን 8 ብር ገብቷል።የፉርኖ ዱቄት፣የጤፍ፣ የበርበሬና የመሰል የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ ሲጨምር ማኮሮኒና ፓስታን የመሳሰሉ የፋብሪካ ምርቶችን ገበያ ላይ ማግኘት ሲበዛ ከባድ ነዉ።የዚያኑ ያክል እዚያዉ ትግራይ የሚመረቱ እንደ ሽንኩርትና ቲማቲም የመሳሰሉ ማጣፈጫዎች ዋጋ ብዙ ለዉጥ አላሳየም።የከብትና የስጋ ዋጋ ግን ቀንሷል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ግጭቶች ከመከሰታቸው በፊት ለግጭት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች እና ሁኔታዎች ላይ ጥናት እንዲደረግ አሳሰበ፡፡
ቋሚ ኮሚቴው በዛሬው ዕለት የሰላም ሚኒስቴርን የሥራ እንቅስቃሴ ተዘዋውሮ ከተመለከተ በኋላ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶክተር ዲማ ነገዎ ሰላም ሚኒስቴር ባለፉት 20 እና 30 ዓመታት የነበሩ ግጭቶች ምንጮቻቸውን እና የአፈታት ሥርዓታቸውን በማጥናት ላይ ትኩረቱን ማሳረፍ እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡
በኢትዮጵያ የተለያዩ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች መኖራቸውን ጠቁመው ÷ የግጭት አፈታቶቹ ምን ያህል ውጤት አምጥተዋል በሚለው ላይም ጥናት ሊካሄድ ይገባል ብለዋል፡፡
ተቋሙ በዘመናዊ አደረጃጀት ተልዕኮውን ለመፈጸም በሚያስችል ቁመና ላይ እንዳለ የተረዳ መሆኑን የጠቆመው ቋሚ ኮሚቴው÷ግጭቶች ከመከሰታቸው በፊት የመከታተያ ዘዴ በቴክኖሎጂ መደገፉ የሚበረታታ መሆኑን አንስቷል፡፡
በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደአ በበኩላቸው÷በተቋሙ አዲስ የተሠራው አደረጃጀት ዕውቀትን መሠረት ያደረገ እንደሆነ መግለጻቸውን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ግጭቶች ከመከሰታቸው በፊት መከላከል የሚያስችሉ ሥርዓቶችን ዘርግቶ እየሠራ መሆኑን ያነሱት አቶ ታዬ÷በግጭት አፈታት ዙሪያ ከክልሎች እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
[AMN]
@YeneTube @FikerAssefa
ቋሚ ኮሚቴው በዛሬው ዕለት የሰላም ሚኒስቴርን የሥራ እንቅስቃሴ ተዘዋውሮ ከተመለከተ በኋላ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶክተር ዲማ ነገዎ ሰላም ሚኒስቴር ባለፉት 20 እና 30 ዓመታት የነበሩ ግጭቶች ምንጮቻቸውን እና የአፈታት ሥርዓታቸውን በማጥናት ላይ ትኩረቱን ማሳረፍ እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡
በኢትዮጵያ የተለያዩ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓቶች መኖራቸውን ጠቁመው ÷ የግጭት አፈታቶቹ ምን ያህል ውጤት አምጥተዋል በሚለው ላይም ጥናት ሊካሄድ ይገባል ብለዋል፡፡
ተቋሙ በዘመናዊ አደረጃጀት ተልዕኮውን ለመፈጸም በሚያስችል ቁመና ላይ እንዳለ የተረዳ መሆኑን የጠቆመው ቋሚ ኮሚቴው÷ግጭቶች ከመከሰታቸው በፊት የመከታተያ ዘዴ በቴክኖሎጂ መደገፉ የሚበረታታ መሆኑን አንስቷል፡፡
በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደአ በበኩላቸው÷በተቋሙ አዲስ የተሠራው አደረጃጀት ዕውቀትን መሠረት ያደረገ እንደሆነ መግለጻቸውን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ግጭቶች ከመከሰታቸው በፊት መከላከል የሚያስችሉ ሥርዓቶችን ዘርግቶ እየሠራ መሆኑን ያነሱት አቶ ታዬ÷በግጭት አፈታት ዙሪያ ከክልሎች እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
[AMN]
@YeneTube @FikerAssefa
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማስገኘቱ ተሰማ!
የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘ።የኢፌዴሪ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን ለዚህ ታሪካዊ ላሉት ስኬት እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።የቡና ምርት ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ ከምታቀርባቸው የግብርና ምርቶች መካከል ግንባር ቀደም ሆኖ ቀጥሏል።ሀገሪቱ በተለይም ወደ ቻይና የምትልከው የቡና ምርት በከፍተኛ መጠን አድጓል።
በፈረንጆቹ 2021 ዓመተ ምህረት ላይ ቻይና ከኢትዮጵያ ያስገባቸው የቡና ምርት መጠን ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ196 በመቶ አድጓል።በቅርቡ የኢትዮጵያን የቡና ምርት በቻይና ገበያ የበለጠ ለማስተዋወቅ በተዘጋጀ መድረክ ላይ የሀገሪቱ የቡና ማህበር እንዳስታወቀው፥ በቻይና ከትላልቅ ከተሞች እስከ መለስተኛ ከተሞች የቡና ተጠቃሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ ዕድገት ያሳየ ሲሆን፥ ይህም ለኢትዮጵያ ቡና አምራቾች እና ላኪዎች ሰፊ የገበያ ዕድል መፈጠሩ ተመልክቷል።ሚኒስትሩ ባለፉት የበጀት ዓመቱ ወራት የተገኘው የውጭ ምንዛሪ ምን ያህል የቡና መጠን ወደ ውጭ ተልኮ እንደሆነ አልጠቆሙም።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘ።የኢፌዴሪ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን ለዚህ ታሪካዊ ላሉት ስኬት እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።የቡና ምርት ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ ከምታቀርባቸው የግብርና ምርቶች መካከል ግንባር ቀደም ሆኖ ቀጥሏል።ሀገሪቱ በተለይም ወደ ቻይና የምትልከው የቡና ምርት በከፍተኛ መጠን አድጓል።
በፈረንጆቹ 2021 ዓመተ ምህረት ላይ ቻይና ከኢትዮጵያ ያስገባቸው የቡና ምርት መጠን ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ196 በመቶ አድጓል።በቅርቡ የኢትዮጵያን የቡና ምርት በቻይና ገበያ የበለጠ ለማስተዋወቅ በተዘጋጀ መድረክ ላይ የሀገሪቱ የቡና ማህበር እንዳስታወቀው፥ በቻይና ከትላልቅ ከተሞች እስከ መለስተኛ ከተሞች የቡና ተጠቃሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ ዕድገት ያሳየ ሲሆን፥ ይህም ለኢትዮጵያ ቡና አምራቾች እና ላኪዎች ሰፊ የገበያ ዕድል መፈጠሩ ተመልክቷል።ሚኒስትሩ ባለፉት የበጀት ዓመቱ ወራት የተገኘው የውጭ ምንዛሪ ምን ያህል የቡና መጠን ወደ ውጭ ተልኮ እንደሆነ አልጠቆሙም።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ህዝብ “ለመጨረሻው ምዕራፍ ትግል” እንዲዘጋጅ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥሪ አቀረቡ!
የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል ከማዕከላዊው መንግስት ጋር ችግሮችን በዲፕሎማሲ ለመፍታት ሲደረግ የነበረው ጥረት “ባለመሳካቱና የሰላም መንገድ በመዘጋቱ የትግራይን ሕዝብ ነፃነት ለማረጋገጥ” የክልሉ ህዝብ እንዲዘጋጅ ጥሪ አቀረቡ።
ደብረፅዮን በመቀሌ ሌሎች የሕወሃት አመራሮች ደግሞ በተለያዩ የትግራይ ዞኖች ከነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የትግራይ ህዝብ አሁን ያለበት የከፋ ስቃይ እንዲቀለበስና የትግራይ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እንዲረጋገጥ ለማድረግ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰናል ብለዋል።
“ኹሉም የፖለቲካ ችግር በሰላምና በዲፕሎማሲ እንደማይፈታ ብናውቅም አሁን የገባንበት ጦርነት ከመጀመሩ አስቀድመን እንዲሁም በጦርነቱ ወቅት ለሰላም ቅድሚያ ሰጥተናል” ብለዋል ደብረፅዮን በመቀሌ ከነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ።
በአለም አቀፉ ማህበረሰብ አሸማጋይነት ጊዚያዊ ሥምምነት ተደርጎ ወደ ክልሉ እህል መድሀኒትና ሌሎች ድጋፎች እንዲገቡ ጥረት ብናደርግም እስከ አሁን ድረስ የተገኘው ድጋፍ ችግሩን ለማቃለል በቂ አይደለም ብለዋል።
መላክ ያለበትን መልዕክት ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ባለን የመገናኛ መንገድ አድርሰናል ያሉት ደብረፅዮን የሚመለከታቸው ያሏቸውን አካላት አልዘረዘሩም።
መንግስት የተኩስ አቁም በሚል ሽፋን የመሳሪያና የሰራዊት ማሰባሰብ ስራ ላይ ነው ሲሉ የከሰሱት ርዕሰ መስተዳድሩ የትግራይ ሕዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት የሚረጋገጠው የኀይል የበላይነትን በመያዝ ብቻ መሆኑን ለተሰብሳቢዎች አስረድተዋል።
ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር(ሞንጀሪኖ)፣ አለም ገብረሐዋድና ጌታቸው ረዳን ጨምሮ የሕወሓት ከፍተኛ አመራሮች በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች ነዋሪዎችን ያወያዩ ሲሆን ሕዝቡ ለመጨረሻው ምዕራፍ ትግል እንዲዘጋጅ መጠየቃቸውን ዋዜማ ራዲዮ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ መንግስት ለትግራይ የሰብዓዊ ዕርዳታ እንዲደርስ ሁኔታዎችን ባመቻችም ሕወሃት ራሱ ዕርዳታ በማስተጓጎልና ተጎራባች ክልሎችን በመውረር እንቅፋት መፍጠሩን ይናገራል። የትግራይ አማፅያን በቅርቡ ይዘውት ከነበረው የአፋር ክልል ሙሉ በሙሉ ለቀው መውጣታቸውን አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ባለፈው ሳምንት የምዕራብ ዕዝ የመከላከያ ሰራዊትን በቦታው ተገኝተው ያበረታቱ ሲሆን ወታደራዊ ብቃቱን የሚያሳይ ትርዒትም መመልከታቸው ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል ከማዕከላዊው መንግስት ጋር ችግሮችን በዲፕሎማሲ ለመፍታት ሲደረግ የነበረው ጥረት “ባለመሳካቱና የሰላም መንገድ በመዘጋቱ የትግራይን ሕዝብ ነፃነት ለማረጋገጥ” የክልሉ ህዝብ እንዲዘጋጅ ጥሪ አቀረቡ።
ደብረፅዮን በመቀሌ ሌሎች የሕወሃት አመራሮች ደግሞ በተለያዩ የትግራይ ዞኖች ከነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የትግራይ ህዝብ አሁን ያለበት የከፋ ስቃይ እንዲቀለበስና የትግራይ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እንዲረጋገጥ ለማድረግ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰናል ብለዋል።
“ኹሉም የፖለቲካ ችግር በሰላምና በዲፕሎማሲ እንደማይፈታ ብናውቅም አሁን የገባንበት ጦርነት ከመጀመሩ አስቀድመን እንዲሁም በጦርነቱ ወቅት ለሰላም ቅድሚያ ሰጥተናል” ብለዋል ደብረፅዮን በመቀሌ ከነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ።
በአለም አቀፉ ማህበረሰብ አሸማጋይነት ጊዚያዊ ሥምምነት ተደርጎ ወደ ክልሉ እህል መድሀኒትና ሌሎች ድጋፎች እንዲገቡ ጥረት ብናደርግም እስከ አሁን ድረስ የተገኘው ድጋፍ ችግሩን ለማቃለል በቂ አይደለም ብለዋል።
መላክ ያለበትን መልዕክት ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ባለን የመገናኛ መንገድ አድርሰናል ያሉት ደብረፅዮን የሚመለከታቸው ያሏቸውን አካላት አልዘረዘሩም።
መንግስት የተኩስ አቁም በሚል ሽፋን የመሳሪያና የሰራዊት ማሰባሰብ ስራ ላይ ነው ሲሉ የከሰሱት ርዕሰ መስተዳድሩ የትግራይ ሕዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት የሚረጋገጠው የኀይል የበላይነትን በመያዝ ብቻ መሆኑን ለተሰብሳቢዎች አስረድተዋል።
ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር(ሞንጀሪኖ)፣ አለም ገብረሐዋድና ጌታቸው ረዳን ጨምሮ የሕወሓት ከፍተኛ አመራሮች በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች ነዋሪዎችን ያወያዩ ሲሆን ሕዝቡ ለመጨረሻው ምዕራፍ ትግል እንዲዘጋጅ መጠየቃቸውን ዋዜማ ራዲዮ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ መንግስት ለትግራይ የሰብዓዊ ዕርዳታ እንዲደርስ ሁኔታዎችን ባመቻችም ሕወሃት ራሱ ዕርዳታ በማስተጓጎልና ተጎራባች ክልሎችን በመውረር እንቅፋት መፍጠሩን ይናገራል። የትግራይ አማፅያን በቅርቡ ይዘውት ከነበረው የአፋር ክልል ሙሉ በሙሉ ለቀው መውጣታቸውን አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ ባለፈው ሳምንት የምዕራብ ዕዝ የመከላከያ ሰራዊትን በቦታው ተገኝተው ያበረታቱ ሲሆን ወታደራዊ ብቃቱን የሚያሳይ ትርዒትም መመልከታቸው ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
በቻይና በደረሰ የአውሮፕላን አደጋ በ25 ሰዎች ላይ ጉዳት ደረሰ
ደቡብ ምዕራብ ቻይና ቾንግኪንግ፤ አንድ የመንገደኞች አውሮፕላን በመነሳት ላይ እያለ ከመንደርደሪያው በመውጣቱ 25 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተሰማ።
አደጋው ከደረሰ በኋላ፤ መንግደኞቹን ሙሉ በሙሉ ከአውሮፕላን የማስወጣት ስራ የተሰራ ሲሆን፤ ጉዳት የደረሰባቸው ለህክምና ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው ተገልጿል።
ንብረትነቱ የቲቤት አየር መንገድ የሆነው አውሮፕላን በውስጡ 113 መንገደኞችን እና 9 የበረራ አባላትን አሳፍሮ ነበር ተብሏል።
Via Al ain
@Yenetube @Fikerassefa
ደቡብ ምዕራብ ቻይና ቾንግኪንግ፤ አንድ የመንገደኞች አውሮፕላን በመነሳት ላይ እያለ ከመንደርደሪያው በመውጣቱ 25 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተሰማ።
አደጋው ከደረሰ በኋላ፤ መንግደኞቹን ሙሉ በሙሉ ከአውሮፕላን የማስወጣት ስራ የተሰራ ሲሆን፤ ጉዳት የደረሰባቸው ለህክምና ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው ተገልጿል።
ንብረትነቱ የቲቤት አየር መንገድ የሆነው አውሮፕላን በውስጡ 113 መንገደኞችን እና 9 የበረራ አባላትን አሳፍሮ ነበር ተብሏል።
Via Al ain
@Yenetube @Fikerassefa
በሶማሌ ክልል በባህላዊ የምርጫ ሥነ ሥርዓት ላይ በፀጥታ ኃይሎች የተፈጸመውን ግድያ ኢሰመኮ ኮነነ!
በሶማሌ ክልል ቦምባስ ከተማ በባህላዊ ሥነ ሥርዓት የጎሳ መሪ ለመምረጥ በተሰበሰቡ ሰዎች ላይ በፀጥታ ኃይሎችና በታጠቁ ግለሰቦች በተፈጸሙ ጥቃቶች የ11 ሰዎች ህይወት መጥፋቱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮነነ።በሶማሌ ክልል ከሚገኙት የሶማሌ ጎሳዎች መካከል የሆኑት የአኪሾ ጎሳ አባላት መጋቢት 11 እና 12 ቀን 2014 ዓ.ም. የጎሳ መሪያቸውን ለመምረጥ በተሰበሰቡበት ዕለት ከግድያ በተጨማሪ 33 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ማረጋገጡን ኢሰመኮ ዛሬ ግንቦት 04/2014 ዓ.ም. ባወጣው የምርመራ ሪፖርቱ አስታውቋል።
ኢሰመኮ በስፍራው ተገኝቶ ባደረገውም ምርመራ የክልሉ መንግሥት የፀጥታ አካላት ከመጠን ያለፈ የኃይል አጠቃቀም ለሞትና ለአካል ጉዳት ምክንያት ሆኗል ብሏል።ኢሰመኮ በሁለቱ ቀናት ስለተፈጸሙ ግድያዎችና የአካል ጉዳቶች የደረሰውን ጥቆማ ተከትሎ በቦታው በመገኘት የዓይን ምስክሮችን፣ ተጎጂዎችን፣ የተጎጂ ቤተሰቦችን፣ የአገር ሽማግሌዎችን ማናገሩን አስታውቋል።
በተጨማሪም ከሆስፒታል ምንጮች መረጃ በማሰባሰብ እንዲሁም ፈቃደኛ የሆኑ የክልሉ ኃላፊዎችን በማነጋገር የምርመራውን ሪፖርት አጠናቅሯል።በተጨማሪም ቦምባስ ከተማ የሚገኝ የጥቃቱ ሰለባዎች የተቀበሩበትን መካነ መቃብር መጎብኘቱን ገልጾ በዚህም በመጀመሪያው ቀን የተገደሉ ሰዎች የተቀበሩበትን የጅምላ መቃብር እንዲሁም በሁለተኛው ቀን የተገደለች ሴት ተቀብራበታለች የተባለ መካነ መቃብር መመልከቱንም በዚሁ የምርመራ ሪፖርቱ አካቷል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://bbc.in/39h6k3i
@YeneTube @FikerAssefa
በሶማሌ ክልል ቦምባስ ከተማ በባህላዊ ሥነ ሥርዓት የጎሳ መሪ ለመምረጥ በተሰበሰቡ ሰዎች ላይ በፀጥታ ኃይሎችና በታጠቁ ግለሰቦች በተፈጸሙ ጥቃቶች የ11 ሰዎች ህይወት መጥፋቱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮነነ።በሶማሌ ክልል ከሚገኙት የሶማሌ ጎሳዎች መካከል የሆኑት የአኪሾ ጎሳ አባላት መጋቢት 11 እና 12 ቀን 2014 ዓ.ም. የጎሳ መሪያቸውን ለመምረጥ በተሰበሰቡበት ዕለት ከግድያ በተጨማሪ 33 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ማረጋገጡን ኢሰመኮ ዛሬ ግንቦት 04/2014 ዓ.ም. ባወጣው የምርመራ ሪፖርቱ አስታውቋል።
ኢሰመኮ በስፍራው ተገኝቶ ባደረገውም ምርመራ የክልሉ መንግሥት የፀጥታ አካላት ከመጠን ያለፈ የኃይል አጠቃቀም ለሞትና ለአካል ጉዳት ምክንያት ሆኗል ብሏል።ኢሰመኮ በሁለቱ ቀናት ስለተፈጸሙ ግድያዎችና የአካል ጉዳቶች የደረሰውን ጥቆማ ተከትሎ በቦታው በመገኘት የዓይን ምስክሮችን፣ ተጎጂዎችን፣ የተጎጂ ቤተሰቦችን፣ የአገር ሽማግሌዎችን ማናገሩን አስታውቋል።
በተጨማሪም ከሆስፒታል ምንጮች መረጃ በማሰባሰብ እንዲሁም ፈቃደኛ የሆኑ የክልሉ ኃላፊዎችን በማነጋገር የምርመራውን ሪፖርት አጠናቅሯል።በተጨማሪም ቦምባስ ከተማ የሚገኝ የጥቃቱ ሰለባዎች የተቀበሩበትን መካነ መቃብር መጎብኘቱን ገልጾ በዚህም በመጀመሪያው ቀን የተገደሉ ሰዎች የተቀበሩበትን የጅምላ መቃብር እንዲሁም በሁለተኛው ቀን የተገደለች ሴት ተቀብራበታለች የተባለ መካነ መቃብር መመልከቱንም በዚሁ የምርመራ ሪፖርቱ አካቷል።
ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://bbc.in/39h6k3i
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ የ8ተኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 30 ይሰጣል ተባለ!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከተማ አቀፍ የሆነው የ8ተኛ ክፍል (ሚኒስትሪ) ፈተናን ከ71 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች ከሰኔ 27 እስከ ሰኔ 30 2014 ድረስ ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ፡፡
በአጠቃላይ 71 ሺህ 661 የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች ለማስፈተን ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑን በትምህርት ቢሮ ፈተና ዝግጅት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዲናኦል ጫላ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
የፈተና ዝግጅቱ ተጠናቆ የህትመት ሥራዉ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በዕለቱ የማሰራጨት ሥራ ብቻ እንደሚቀርም ገልጸዋል፡፡የፈተናዉን ምዝገባ በተመለከተ የተማሪዎች የአድሚሽ ካርድ በሚቀጥለው ሳምንት በየትምህርት ቤቶቹ እንደሚላክ እና ለተማሪዎቹም እንደሚተላለፍ ተናግረዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስምንተኛ ክፍል ፈተና 211 የመፈተኛ ጣቢያዎች የተዘጋጁ ሲሆን፤ ጣቢያዎቹን ምቹ ናቸው የሚለውን ምልከታ እየተደረገ መሆኑን በማንሳት ቁጥሩ ከፍ አልያም ዝቅ ሊደረግ እንደሚችል ዳይሬክተሩ ለሬዲዮ ጣቢያው አብራርተዋል።ፈተናው በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች እንደሚሰጥም ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከተማ አቀፍ የሆነው የ8ተኛ ክፍል (ሚኒስትሪ) ፈተናን ከ71 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች ከሰኔ 27 እስከ ሰኔ 30 2014 ድረስ ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ፡፡
በአጠቃላይ 71 ሺህ 661 የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች ለማስፈተን ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑን በትምህርት ቢሮ ፈተና ዝግጅት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዲናኦል ጫላ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
የፈተና ዝግጅቱ ተጠናቆ የህትመት ሥራዉ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በዕለቱ የማሰራጨት ሥራ ብቻ እንደሚቀርም ገልጸዋል፡፡የፈተናዉን ምዝገባ በተመለከተ የተማሪዎች የአድሚሽ ካርድ በሚቀጥለው ሳምንት በየትምህርት ቤቶቹ እንደሚላክ እና ለተማሪዎቹም እንደሚተላለፍ ተናግረዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስምንተኛ ክፍል ፈተና 211 የመፈተኛ ጣቢያዎች የተዘጋጁ ሲሆን፤ ጣቢያዎቹን ምቹ ናቸው የሚለውን ምልከታ እየተደረገ መሆኑን በማንሳት ቁጥሩ ከፍ አልያም ዝቅ ሊደረግ እንደሚችል ዳይሬክተሩ ለሬዲዮ ጣቢያው አብራርተዋል።ፈተናው በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች እንደሚሰጥም ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በአዲስ አበባ ባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ ማቅረቢያ ቀነ ገደብ ነገ እንደሚጠናቀቅ ኤጀንሲው ገለፀ!
በአዲስ አበባ ባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ በተሰጠው የጊዜ ገደብ እንዲያቀርቡ የከተማዋ የመሬት ይዞታ፣ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አሳሰበ፡፡የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ጀማል ሀጅ እንደገለፁት፥ ለይዞታ ማርጋገጫ በተመረጡ 25 ቀጠናዎች እና 112 ሰፈሮች የሚገኙ የመሬት ባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ እያቀረቡ ነው፡፡
ኤጅንሲው የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ ሀሙስ ሚያዚያ 20 መቀበል ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባሉት 6 ተከታታይ የስራ ቀናት ከ11 ሺህ 300 በላይ ባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመለከቻዎችን ማቅረባቸውን ገልፀዋል፡፡
የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ የመቀበል ሂደቱ እስከ ግንቦት 5 ብቻ የሚቆይ በመሆኑ በተመረጡ ቀጠናዎች እና ሰፈሮች ውስጥ የሚገኙ ባለይዞታዎች ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድና አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት የክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤቶች ባዘጋጁት ቦታ በመገኘት ማመልከቻ እንዲያቀርቡ ጥሪ አስተላልዋል፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ ባለ ይዞታዎች ኤጀንሲው አረጋግጦ ላልመዘገበው ይዞታ ምንም ዓይነት ህጋዊ ዋስትናና ከለላ የማይሰጥ መሆኑን ተገንዝበው ቀነ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸው ሃላፊው አሳስበዋል፡፡የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ አቀራረቡንና አመዘጋገቡን ሂደት የሚታዘቡ ከህብረተሰቡ የተመረጡ 336 ታዛቢዎች እየተሳተፉ መሆናቸው ኤጅንሲው ለፋና ብሮድካስቲንግ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ በተሰጠው የጊዜ ገደብ እንዲያቀርቡ የከተማዋ የመሬት ይዞታ፣ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አሳሰበ፡፡የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ጀማል ሀጅ እንደገለፁት፥ ለይዞታ ማርጋገጫ በተመረጡ 25 ቀጠናዎች እና 112 ሰፈሮች የሚገኙ የመሬት ባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ እያቀረቡ ነው፡፡
ኤጅንሲው የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ ሀሙስ ሚያዚያ 20 መቀበል ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባሉት 6 ተከታታይ የስራ ቀናት ከ11 ሺህ 300 በላይ ባለይዞታዎች የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመለከቻዎችን ማቅረባቸውን ገልፀዋል፡፡
የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ የመቀበል ሂደቱ እስከ ግንቦት 5 ብቻ የሚቆይ በመሆኑ በተመረጡ ቀጠናዎች እና ሰፈሮች ውስጥ የሚገኙ ባለይዞታዎች ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድና አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት የክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤቶች ባዘጋጁት ቦታ በመገኘት ማመልከቻ እንዲያቀርቡ ጥሪ አስተላልዋል፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ ባለ ይዞታዎች ኤጀንሲው አረጋግጦ ላልመዘገበው ይዞታ ምንም ዓይነት ህጋዊ ዋስትናና ከለላ የማይሰጥ መሆኑን ተገንዝበው ቀነ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለባቸው ሃላፊው አሳስበዋል፡፡የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ አቀራረቡንና አመዘጋገቡን ሂደት የሚታዘቡ ከህብረተሰቡ የተመረጡ 336 ታዛቢዎች እየተሳተፉ መሆናቸው ኤጅንሲው ለፋና ብሮድካስቲንግ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በህገ- ወጥ መንገድ ሰባት ሕፃናትን ሲያዘዋውር የተገኘው ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የቤንች ሸኮ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።
በቤንች ሸኮ ዞን የዘረፋና ወንብድና ልዩ ልዩ ወንጀል ማስተባበሪያ ኃላፊ ም/ኢ/ር ወንዳየሁ ገ/ሚካኤል፣ ተጠርጣሪው ሸኮ ወረዳ ጉፊቃ ቀበሌ ግንቦት አንድ ቀን 2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 3:00 በተሽከርካሪ ይዞ በመጓዝ ላይ እንዳለ ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሆኖ ምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ተጠርጣሪው ግለሰብ ከካፋ ዞን ጨና ወረዳ ባላ ሻሻ ቀበሌ ከአስር ዓመት በታች የሆኑ ሰባት ሕፃናትን ከሚኖሩበት ቤተሰብ ከብቶችን ትጠብቃላችሁ በማለት ለጉልበት ብዝበዛ ወደ ቤንች ሸኮ ዞን ይዞ መጓዙን ገልጸዋል።
በህገ_ወጥ መንገድ ከቦታ ወደቦታ እያዘዋወሩ የጉልበት ብዝበዛ የሚዳርጉ ግለሰቦችን ህብረተሰቡ ለህግ አካላት አሳልፈዉ መስጠት እንዳለበት ፖሊስ ማሳሰቡን ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
በቤንች ሸኮ ዞን የዘረፋና ወንብድና ልዩ ልዩ ወንጀል ማስተባበሪያ ኃላፊ ም/ኢ/ር ወንዳየሁ ገ/ሚካኤል፣ ተጠርጣሪው ሸኮ ወረዳ ጉፊቃ ቀበሌ ግንቦት አንድ ቀን 2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 3:00 በተሽከርካሪ ይዞ በመጓዝ ላይ እንዳለ ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሆኖ ምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ተጠርጣሪው ግለሰብ ከካፋ ዞን ጨና ወረዳ ባላ ሻሻ ቀበሌ ከአስር ዓመት በታች የሆኑ ሰባት ሕፃናትን ከሚኖሩበት ቤተሰብ ከብቶችን ትጠብቃላችሁ በማለት ለጉልበት ብዝበዛ ወደ ቤንች ሸኮ ዞን ይዞ መጓዙን ገልጸዋል።
በህገ_ወጥ መንገድ ከቦታ ወደቦታ እያዘዋወሩ የጉልበት ብዝበዛ የሚዳርጉ ግለሰቦችን ህብረተሰቡ ለህግ አካላት አሳልፈዉ መስጠት እንዳለበት ፖሊስ ማሳሰቡን ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
ጤና ይስጥልን የተወደዳችሁ ቤተሰቦቼ
መሪጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ከአባቶቻችን በተሰጠንና ባገኘነው ጥበብ መሰረት የተለያዩ የጤና መፍትሄወችን እንሰጣለን።**
የምንሰጣቸው አገልግሎቶችም
👉የኪንታሮት መድኀኒት በሚቀባ ታማሚው ወደቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላ ሳይነካ ሳያቆስል ስራ ሳያስተጓጉል በሽታውን ለይቶ በማውጣት ሁለተኛም እንዳይተካ አድርጎ ይፈውሳል። 🍎
👉 የሪህ መድኀኒት ወስዶ በመቀባት ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል።
👉 ለመፍትሔ ሥራይ
👉 ፍቅር ለነሳው ለመስተፋቅር። 🍒
👉 ገንዘብ አልገባ ለሚለው ለሚበተንበት።
👉 ለአስም ለሳይነስ ።
👉 ለአይነጥላ ለገርጋሪ።
👉 ለስንፈተወሲብ ለሚቸኩልበት።
👉ገብያ ለሚገረግረው ለገብያ ።
👉 ለእራስ ሕመም።
👉እነዚህንና ሌሎችን አገልግሎቶች እንሰጣለን
በሁሉም አገልግሎቶቻችን ውጤቱ እዳዩ ክፍያ ይፈጽማሉ ።
የሚፈልጉትን መድኀኒት ያሉበት ቦታ መላላክ ይቻላል። 🥒
ለበለጠ መረጃ
አድራሻ ባህርዳር ፦ቀበሌ 11 🫑
☎️ 0917040506
📞 0912718883
ይደውሉ👍
መፍትሔ ሥራይ ወአይነ ጥላ ለጤናወ
መፍትሔ ከመሪጌታ ጥበቡ
ለጤናወ መፍትሄ የሚፈልጉትን ለማግኔት
🌿 ይሄን ቻናል ይቀላቀሉ 🌱
🩺
👇
https://tttttt.me/meritibe
https://tttttt.me/meritibe
መሪጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ከአባቶቻችን በተሰጠንና ባገኘነው ጥበብ መሰረት የተለያዩ የጤና መፍትሄወችን እንሰጣለን።**
የምንሰጣቸው አገልግሎቶችም
👉የኪንታሮት መድኀኒት በሚቀባ ታማሚው ወደቤቱ ወስዶ በመቀባት ሌላ ገላ ሳይነካ ሳያቆስል ስራ ሳያስተጓጉል በሽታውን ለይቶ በማውጣት ሁለተኛም እንዳይተካ አድርጎ ይፈውሳል። 🍎
👉 የሪህ መድኀኒት ወስዶ በመቀባት ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል።
👉 ለመፍትሔ ሥራይ
👉 ፍቅር ለነሳው ለመስተፋቅር። 🍒
👉 ገንዘብ አልገባ ለሚለው ለሚበተንበት።
👉 ለአስም ለሳይነስ ።
👉 ለአይነጥላ ለገርጋሪ።
👉 ለስንፈተወሲብ ለሚቸኩልበት።
👉ገብያ ለሚገረግረው ለገብያ ።
👉 ለእራስ ሕመም።
👉እነዚህንና ሌሎችን አገልግሎቶች እንሰጣለን
በሁሉም አገልግሎቶቻችን ውጤቱ እዳዩ ክፍያ ይፈጽማሉ ።
የሚፈልጉትን መድኀኒት ያሉበት ቦታ መላላክ ይቻላል። 🥒
ለበለጠ መረጃ
አድራሻ ባህርዳር ፦ቀበሌ 11 🫑
☎️ 0917040506
📞 0912718883
ይደውሉ👍
መፍትሔ ሥራይ ወአይነ ጥላ ለጤናወ
መፍትሔ ከመሪጌታ ጥበቡ
ለጤናወ መፍትሄ የሚፈልጉትን ለማግኔት
🌿 ይሄን ቻናል ይቀላቀሉ 🌱
🩺
👇
https://tttttt.me/meritibe
https://tttttt.me/meritibe
ኦፌኮ የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ባለፉት ጥቂት ወራት በኦሮሚያ ክልል 297 ሰዎችን ገድለዋል ሲል ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ መናገሩን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። በክልሉ መንግሥት ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ጋር በገባበት ግጭት ከግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ተፈናቅሏል በማለት ኦፌኮ በመግለጫው ጨምሮ ገልጧል። የፓርቲው መግለጫ ትኩረት ተባብሰው ቀጥለዋል ባላቸው የርስበርስ ግጭት፣ የፖለቲካ ውድቀትና የኢኮኖሚ ቀውስ ላይ ነው። አገሪቱ ከቀውስ የምትወጣው፣ ግጭቶችን አቁሞ ወደ ፖለቲካዊ ድርድር በመመለስ እንደሆነ ፓርቲው ገልጧል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
በጅማ ኢንደስትሪ ፓርክ ሲሰራ የነበረው ሁዋጂያን ግሩፕ የተሰኘው የቻይና ኩባንያ በአለም አቀፍ ወረርሽኝ ምክንያት ስራውን ካቆመ ከአንድ አመት በኋላ የተከራየውን ሼዶች በሙሉ አስረክቦ ፓርኩን ለቆ መውጣቱን የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ሳንዶካን ደበበ ተናግረዋል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ ዓሳ የማርባት ሥራ ተፈቀደ!
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የዓሳ ማርባት ሥራ መፈቀዱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። የዓሳ ሀብት ልማት ዕድሎችና ተግዳሮቶችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከዘርፉ ባለድርሻዎች ጋር ማክሰኞ ግንቦት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ምክክር ያደረገ ሲሆን፣ በዚሁ ወቅትም ኢትዮጵያ ከፍተኛ የዓሳ ሀብት ያላት ቢሆንም በተገቢው መንገድ ያልተያዘና ጥቅም ላይ ያልዋለ መሆኑ ተገልጿል።
በአሁኑ ወቅት የህዳሴ ግድብን ሳይጨምር በተደረጉ ጥናቶች ኢትዮጵያ በዓመት 94,500 ቶን ዓሳ የማምረት አቅም እንዳላት፣ በግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት አስቻለው ላቀው (ዶ/ር) ገልጸዋል። ሆኖም በአሁኑ ወቅት እየተመረተ የሚገኘው በዓመት ከ60 ሺሕ ቶን ያልበለጠ ዓሳ መሆኑን አክለዋል።
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ 200 ያህል የዓሳ ዝርያዎች መኖራቸውንና 40 የሚሆኑት በኢትዮጵያ ብቻ እንደሚገኙ ገልጸው፣ ከእነዚህም ውስጥ ስድስቱ ዝርያዎች አሁን ባለው ገበያ ተፈላጊ ናቸው ብለዋል። ነገር ግን ዓመታዊ ምርቱ በቂ ባለመሆኑ የአንድ ሰው ዓመታዊ የዓሳ ፍጆታ ግማሽ ኪሎ ግራም በታች መሆኑን ጠቁመው፣ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች የአንድ ሰው ዓመታዊ የዓሳ ፍጆታ እስከ 12 ኪሎ ግራም መድረሱን ተናግረዋል። በመሆኑም ያሉትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ የውኃ ሀብቶች በመጠቀም የተሻለ የቁጥጥር ሥርዓት ሊኖር እንደሚገባ አክለዋል።
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የዓሳ ማርባት ሥራ መፈቀዱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። የዓሳ ሀብት ልማት ዕድሎችና ተግዳሮቶችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከዘርፉ ባለድርሻዎች ጋር ማክሰኞ ግንቦት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ምክክር ያደረገ ሲሆን፣ በዚሁ ወቅትም ኢትዮጵያ ከፍተኛ የዓሳ ሀብት ያላት ቢሆንም በተገቢው መንገድ ያልተያዘና ጥቅም ላይ ያልዋለ መሆኑ ተገልጿል።
በአሁኑ ወቅት የህዳሴ ግድብን ሳይጨምር በተደረጉ ጥናቶች ኢትዮጵያ በዓመት 94,500 ቶን ዓሳ የማምረት አቅም እንዳላት፣ በግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት አስቻለው ላቀው (ዶ/ር) ገልጸዋል። ሆኖም በአሁኑ ወቅት እየተመረተ የሚገኘው በዓመት ከ60 ሺሕ ቶን ያልበለጠ ዓሳ መሆኑን አክለዋል።
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ 200 ያህል የዓሳ ዝርያዎች መኖራቸውንና 40 የሚሆኑት በኢትዮጵያ ብቻ እንደሚገኙ ገልጸው፣ ከእነዚህም ውስጥ ስድስቱ ዝርያዎች አሁን ባለው ገበያ ተፈላጊ ናቸው ብለዋል። ነገር ግን ዓመታዊ ምርቱ በቂ ባለመሆኑ የአንድ ሰው ዓመታዊ የዓሳ ፍጆታ ግማሽ ኪሎ ግራም በታች መሆኑን ጠቁመው፣ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች የአንድ ሰው ዓመታዊ የዓሳ ፍጆታ እስከ 12 ኪሎ ግራም መድረሱን ተናግረዋል። በመሆኑም ያሉትን ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ የውኃ ሀብቶች በመጠቀም የተሻለ የቁጥጥር ሥርዓት ሊኖር እንደሚገባ አክለዋል።
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የግብፅ አቻውን በማላዊ ስታዲየም ይገጥማል!
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከግብፅ አቻው ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በማላዊ ቢንጉ ስታዲየም እንዲካሄድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ወስኗል።
ቀደም ሲል ለኢንተርናሽናል ጨዋታዎች የተመረጠው የባህርዳር ስታዲየም የካፍ ደረጃን ባለማሟላቱ ካፍ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምታደርገውን ጨዋታ በሌላ ሀገር ስታዲየም እንድታደርግ መወሰኑ የሚታወስ ነው።
በመሆኑም ካፍ ኢትዮጵያ የማጣሪያ ጨዋታዋን የምታደርግበትን ስታዲየም እንድታሳውቅ መጠየቁን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከግብፅ አቻው ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ የሚጫወትበትን ስታዲም አሳውቋል።
በዚህም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የግብፅ አቻውን በቀድሞው የማላዊ ፕሬዝዳንት ቢንጉ ዋ ሙታሪካ ስም በተሰየመው ቢንጉ ስታዲየም ጨዋታውን እንደሚያደርግ ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከግብፅ አቻው ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በማላዊ ቢንጉ ስታዲየም እንዲካሄድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ወስኗል።
ቀደም ሲል ለኢንተርናሽናል ጨዋታዎች የተመረጠው የባህርዳር ስታዲየም የካፍ ደረጃን ባለማሟላቱ ካፍ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምታደርገውን ጨዋታ በሌላ ሀገር ስታዲየም እንድታደርግ መወሰኑ የሚታወስ ነው።
በመሆኑም ካፍ ኢትዮጵያ የማጣሪያ ጨዋታዋን የምታደርግበትን ስታዲየም እንድታሳውቅ መጠየቁን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከግብፅ አቻው ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ የሚጫወትበትን ስታዲም አሳውቋል።
በዚህም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የግብፅ አቻውን በቀድሞው የማላዊ ፕሬዝዳንት ቢንጉ ዋ ሙታሪካ ስም በተሰየመው ቢንጉ ስታዲየም ጨዋታውን እንደሚያደርግ ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የዘኢኮኖሚስት ዘጋቢው ቶም ጋርድነር የስራ ፈቃድ ተሰረዘ!
የዘ ኢኮኖሚስት መጽሔት ዘጋቢው ቶም ጋርድነር በኢትዮጵያ የነበረው የሥራ ፈቃድ መሰረዙን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታውቋል።ባለስልጣኑ ለጋዜጠኛው በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንዳስታወቀው፤ ጋዜጠኛው ከሙያ ስነ ምግባር ውጭ በተደጋጋሚ ሲሰራ በመገኘቱ ተደጋጋሚ የቃል እና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶታል።
በተጨማሪም ከጋዜጠኛው ጋር ውይይት በማድረግ ከስህተቱ እንዲታቀብ ለማድረግ ጥረት መደረጉን ባላስልጣኑ ገልጿል።
ይሁን እንጂ ቶም ጋርድነር የሙያውን ስነ ምግባር በማክበር ለመስራት ባለመቻሉ ከዛሬ ግንቦት 5 ቀን 2014 ዓም ጀምሮ በኢትዮጵያ የነበረው የጋዜጠኝነት የስራ ፈቃድ መሰረዙንና ከዚህ በኋላ በጋዜጠኝነት ስራ በኢትዮጵያ ውስጥ መስራት እንደማይችል ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ዘ ኪኮኖሚስት በዚህ ጋዜጠኛ ምትክ ሌላ የሙያውን ሥነ ምግባር አክብሮና ገለልተኛ ሆኖ መስራት የሚችል ሰው መድቦ ማሰራት እንደሚችልም ባለስልጣኑ በዚሁ ደብዳቤ ላይ ገልጿል።
[EPA]
@YeneTube @FikerAssefa
የዘ ኢኮኖሚስት መጽሔት ዘጋቢው ቶም ጋርድነር በኢትዮጵያ የነበረው የሥራ ፈቃድ መሰረዙን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታውቋል።ባለስልጣኑ ለጋዜጠኛው በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንዳስታወቀው፤ ጋዜጠኛው ከሙያ ስነ ምግባር ውጭ በተደጋጋሚ ሲሰራ በመገኘቱ ተደጋጋሚ የቃል እና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶታል።
በተጨማሪም ከጋዜጠኛው ጋር ውይይት በማድረግ ከስህተቱ እንዲታቀብ ለማድረግ ጥረት መደረጉን ባላስልጣኑ ገልጿል።
ይሁን እንጂ ቶም ጋርድነር የሙያውን ስነ ምግባር በማክበር ለመስራት ባለመቻሉ ከዛሬ ግንቦት 5 ቀን 2014 ዓም ጀምሮ በኢትዮጵያ የነበረው የጋዜጠኝነት የስራ ፈቃድ መሰረዙንና ከዚህ በኋላ በጋዜጠኝነት ስራ በኢትዮጵያ ውስጥ መስራት እንደማይችል ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ዘ ኪኮኖሚስት በዚህ ጋዜጠኛ ምትክ ሌላ የሙያውን ሥነ ምግባር አክብሮና ገለልተኛ ሆኖ መስራት የሚችል ሰው መድቦ ማሰራት እንደሚችልም ባለስልጣኑ በዚሁ ደብዳቤ ላይ ገልጿል።
[EPA]
@YeneTube @FikerAssefa
የዩኤኢው ፕሬዚዳንት ሼህ ካሊፋ ቢን ዛይድ አረፉ!
የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ፕረዚዳንት ሼህ ካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ከዚህ አለም በሞት መለየታቸውን የኤሚሬትስ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ፕረዚዳንት ሼህ ካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ከዚህ አለም በሞት መለየታቸውን የኤሚሬትስ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa