በደቡብ አፍሪካ የዩክሬን አምባሳደር ከዲፕሎማሲያዊ መስመር ዉጪ ፕሬዝደንት ሲሪል ራማፎዛን ለማነጋገር መሞከራቸዉን ደቡብ አፍሪቃ አወገዘች።
የዩክሬኗ አምባሳደር ሊዩቦቭ አብራቪቶቫ ፕሬዝደንቱን ለማነጋገር የፈለጉት ሐገራቸዉ ከሩሲያ ጋር ስለገጠመችዉ ጦርነት ለማስረዳት ነበር።ይሁንና አምባሳደሯ መደበኛዉን የዲፕሎማሲ መስመር ጥሰዉ በትዊተር ቀጠሮ መጠየቃቸዉ የደቡብ አፍሪቃ ባለስልጣናትን አስቆጥቷል።አምባሳደር አብራቪቶቫ በትዊተር ቀጠሮ እንዲሰጣቸዉ የጠየቁት ራማፎዛንና ሌሎች ባለልስጣናት ለመነጋገር «በተደጋጋሚ ያቀረብኩትን ጥያቄ የደቡብ አፍሪቃ ባለስልጣናት ባለመቀበላቸዉ ነዉ» ይላሉ።
የደቡብ አፍሪቃ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ከፍተኛ ባለስልጣን ክሌይሰን ሞንዬላ ግን የአምባሳደሯን ወቀሳ አጣጥለዉታል።ሞንዬላ እንደሚሉት አምባሳደሯ ከተለያዩ ባለስልጣናት ጋር ተነጋግረዋል።ፕሬዝደንት ራማፎዛ የዩክሬኑን ፕሬዝደንት ለማነጋገር ለቀረበዉ ጥያቄም አምባሳደሯ መልስ አልሰጡም። በሩሲያና በምዕራባዉያን መንግስታት በምትደገፈዉ ዩክሬን መካከል በሚደረገዉ ጦርነት ደቡብ አፍሪቃ ገለልተኛ አቋም መያዝዋ የኪየቭና የረዳቶችዋን መንግስታት አስቀይሟል።
ሩሲያ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ምክር ቤት አባልነት እንድትወጣ የድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ ድምፅ ሲሰጥ ደቡብ አፍሪቃ ድምፅዋን አቅባለች።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የዩክሬኗ አምባሳደር ሊዩቦቭ አብራቪቶቫ ፕሬዝደንቱን ለማነጋገር የፈለጉት ሐገራቸዉ ከሩሲያ ጋር ስለገጠመችዉ ጦርነት ለማስረዳት ነበር።ይሁንና አምባሳደሯ መደበኛዉን የዲፕሎማሲ መስመር ጥሰዉ በትዊተር ቀጠሮ መጠየቃቸዉ የደቡብ አፍሪቃ ባለስልጣናትን አስቆጥቷል።አምባሳደር አብራቪቶቫ በትዊተር ቀጠሮ እንዲሰጣቸዉ የጠየቁት ራማፎዛንና ሌሎች ባለልስጣናት ለመነጋገር «በተደጋጋሚ ያቀረብኩትን ጥያቄ የደቡብ አፍሪቃ ባለስልጣናት ባለመቀበላቸዉ ነዉ» ይላሉ።
የደቡብ አፍሪቃ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ከፍተኛ ባለስልጣን ክሌይሰን ሞንዬላ ግን የአምባሳደሯን ወቀሳ አጣጥለዉታል።ሞንዬላ እንደሚሉት አምባሳደሯ ከተለያዩ ባለስልጣናት ጋር ተነጋግረዋል።ፕሬዝደንት ራማፎዛ የዩክሬኑን ፕሬዝደንት ለማነጋገር ለቀረበዉ ጥያቄም አምባሳደሯ መልስ አልሰጡም። በሩሲያና በምዕራባዉያን መንግስታት በምትደገፈዉ ዩክሬን መካከል በሚደረገዉ ጦርነት ደቡብ አፍሪቃ ገለልተኛ አቋም መያዝዋ የኪየቭና የረዳቶችዋን መንግስታት አስቀይሟል።
ሩሲያ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ምክር ቤት አባልነት እንድትወጣ የድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ ድምፅ ሲሰጥ ደቡብ አፍሪቃ ድምፅዋን አቅባለች።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ አካባቢን የኤሌክትሪክ ችግር በአጭር ጊዜ ለመፍታት አለመቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል!
ቀጦርነቱ ምክንያት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ኃይል ከተቋረጠ ከአንድ ዓመት በላይ ሲሆን፤ የላሊበላ እና የዋግ ኽምራ ዞን በርካታ አካባቢዎችም ለወራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኙ አይደለም፡፡
ላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ ወልቃይት፣ ጠገዴ እና ሰቲት ሑመራ አካባቢዎች ኃይል ያገኙ የነበረው በሽብር ቡድኑ በተያዙ አካባቢዎች ከሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከተዘረጉ መሥመሮች እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡በመሆኑም የተቋረጡትን መሥመሮች ለመጠገንና አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ ተቋሙ መቸገሩን አስታውቋል፡፡
ሆኖም ላሊበላና አካባቢው በሌሎች አማራጮች ኃይል ለመስጠት ተቋሙ እያጠኔ መሆኑን የገለፀ ሲሆን፤ ለወልቃይት ጠገዴ አካባቢ መፍትሔ ለመስጠት ከጎንደር ወይም ከመተማ ኃይል ለመዘርጋት ረጅም ጊዜ እንደሚጠይቅ ጠቅሷል፡፡
በወልቃይት ጠገዴ ያለው ችግር ከሌሎች አካባቢዎች በተለየ ከዓመት በላይ የቆየው በአካባቢው አማራጭ መስመር ባለመኖሩና የአዲስ መስመር ዝርጋታው ትልቅ ኢንቨስትመንት ከመጠየቁ በተጨማሪ ጊዜ የሚጠይቅ በመሆኑ እንደሆነም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ገልጿል፡፡
ከዚህ በፊት ላሊበላን በጄኔሬተር ኤሌክትሪክ ለመስጠት የተደረገው ሙከራ በነዳጅ አቅርቦት ምክንያት መስተጓጎሉ ተቋሙ አስታውቋል፡፡ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች ይህንን ተገንዝበው የተፈጠረው ችግር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት እንዲጠባበቁ ተጠይቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ቀጦርነቱ ምክንያት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ኃይል ከተቋረጠ ከአንድ ዓመት በላይ ሲሆን፤ የላሊበላ እና የዋግ ኽምራ ዞን በርካታ አካባቢዎችም ለወራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኙ አይደለም፡፡
ላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ ወልቃይት፣ ጠገዴ እና ሰቲት ሑመራ አካባቢዎች ኃይል ያገኙ የነበረው በሽብር ቡድኑ በተያዙ አካባቢዎች ከሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከተዘረጉ መሥመሮች እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡በመሆኑም የተቋረጡትን መሥመሮች ለመጠገንና አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ ተቋሙ መቸገሩን አስታውቋል፡፡
ሆኖም ላሊበላና አካባቢው በሌሎች አማራጮች ኃይል ለመስጠት ተቋሙ እያጠኔ መሆኑን የገለፀ ሲሆን፤ ለወልቃይት ጠገዴ አካባቢ መፍትሔ ለመስጠት ከጎንደር ወይም ከመተማ ኃይል ለመዘርጋት ረጅም ጊዜ እንደሚጠይቅ ጠቅሷል፡፡
በወልቃይት ጠገዴ ያለው ችግር ከሌሎች አካባቢዎች በተለየ ከዓመት በላይ የቆየው በአካባቢው አማራጭ መስመር ባለመኖሩና የአዲስ መስመር ዝርጋታው ትልቅ ኢንቨስትመንት ከመጠየቁ በተጨማሪ ጊዜ የሚጠይቅ በመሆኑ እንደሆነም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ገልጿል፡፡
ከዚህ በፊት ላሊበላን በጄኔሬተር ኤሌክትሪክ ለመስጠት የተደረገው ሙከራ በነዳጅ አቅርቦት ምክንያት መስተጓጎሉ ተቋሙ አስታውቋል፡፡ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች ይህንን ተገንዝበው የተፈጠረው ችግር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት እንዲጠባበቁ ተጠይቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ 247 የሚሆኑ የጉህዴን ታጣቂ ዎች እጅ መስጠታቸውን የዳንጉር ወረዳ ኮማንድ ፖስት አስታወቀ፡፡
የወረዳው ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ሻለቃ ደምስ ዳኘ÷ በወረዳው የአሸባሪውን ህውሓት ተልዕኮ ተቀብለው የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) በሚል ስም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 247 ታጣቂዎች ለፀጥታ ኃይሉ በሰላማዊ መንገድ እጅ መስጠታቸውን ገልጸው÷ ከነዚህም ውስጥ በዛሬው ዕለት 57 ሽፍቶች ከነትጥቃቸው መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡
የጥፋት ኃይሎች በሰላማዊ መንገድ እጅ እንዲሰጡ ከቀረበላቸው የሰላም ጥሪ ባለፈ÷ በመከላከያ ሰራዊት፣ ልዩ ኃይል እና የሚሊሻ አባላት ቅንጅት ሕግን ለማስከበር እየተወሰደ ባለው የኦፕሬሽን ሥራ ብዙዎች እጅ እየሰጡ መሆኑንም ጨምረው መግለጻቸውን ከመተከል ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የወረዳው ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ሻለቃ ደምስ ዳኘ÷ በወረዳው የአሸባሪውን ህውሓት ተልዕኮ ተቀብለው የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) በሚል ስም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 247 ታጣቂዎች ለፀጥታ ኃይሉ በሰላማዊ መንገድ እጅ መስጠታቸውን ገልጸው÷ ከነዚህም ውስጥ በዛሬው ዕለት 57 ሽፍቶች ከነትጥቃቸው መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡
የጥፋት ኃይሎች በሰላማዊ መንገድ እጅ እንዲሰጡ ከቀረበላቸው የሰላም ጥሪ ባለፈ÷ በመከላከያ ሰራዊት፣ ልዩ ኃይል እና የሚሊሻ አባላት ቅንጅት ሕግን ለማስከበር እየተወሰደ ባለው የኦፕሬሽን ሥራ ብዙዎች እጅ እየሰጡ መሆኑንም ጨምረው መግለጻቸውን ከመተከል ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የ10 ዓመት ታዳጊን የኩላሊት ሕመምተኛ በማስመሰል ሲለምኑ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ዋሉ!
የ10 ዓመት ታዳጊን የኩላሊት ሕመምተኛ በማስመሰል ሲለምኑ የነበሩ 11 ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት አስታወቀ።
ተጠርጣሪዎቹ ታዳጊውን የኩላሊት ሕመምተኛ በማስመሰል እና የሐሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት ገንዘብ ሲያሰባስቡ በመገኘታቸው በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አበራ ገልጸዋል።
እንደ አቶ ጌታሁን መግለጫ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት በ3 ክፍለ ከተሞች ስም የተዘጋጁ ሐሰተኛ ሰነድ እንዲሁም የሐኪም ማስረጃዎችን ከሚለምኑባቸው 2 ሚኒባስ መኪኖች ጋር በኅብረተሰቡ በተደረገ ጥቆማ እና በፀጥታ አካላት ክትትል በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል።
በተደረገው የክትትል ሥራ ለሕገ-ወጥ ሥራው የተዘጋጁ ሐሰተኛ ሰነዶችን፣ ታርጋ ቁጥር 58456 እና 79169 ኮድ 3 ኦሮሚያ የሆኑ ሚኒባስ ታክሲዎችን እንዲሁም 9 ሴት እና 2 ወንዶች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል ብለዋል።
አሁን ላይ በከተማዋ የተለያዩ ሐሰተኛ መረጃዎችን በማዘጋጀት እና ያልታመመ ሰውን ታመመ በማለት የሚመለከተው የሕክምና ተቋም ማረጋገጫ ሳይሰጥ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚካሄዱ ልመናዎች መብዛታቸውን የጠቆሙት ኃላፊው ኅብረተሰቡም ከአጭበርባሪ ወንጀለኞች ራሱን እና ንብረቱን እንዲጠብቅ ሲሉ ጥሪያቸውን ማስተላለፋቸውን ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የ10 ዓመት ታዳጊን የኩላሊት ሕመምተኛ በማስመሰል ሲለምኑ የነበሩ 11 ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የጉለሌ ክፍለ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት አስታወቀ።
ተጠርጣሪዎቹ ታዳጊውን የኩላሊት ሕመምተኛ በማስመሰል እና የሐሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት ገንዘብ ሲያሰባስቡ በመገኘታቸው በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አበራ ገልጸዋል።
እንደ አቶ ጌታሁን መግለጫ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት በ3 ክፍለ ከተሞች ስም የተዘጋጁ ሐሰተኛ ሰነድ እንዲሁም የሐኪም ማስረጃዎችን ከሚለምኑባቸው 2 ሚኒባስ መኪኖች ጋር በኅብረተሰቡ በተደረገ ጥቆማ እና በፀጥታ አካላት ክትትል በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል።
በተደረገው የክትትል ሥራ ለሕገ-ወጥ ሥራው የተዘጋጁ ሐሰተኛ ሰነዶችን፣ ታርጋ ቁጥር 58456 እና 79169 ኮድ 3 ኦሮሚያ የሆኑ ሚኒባስ ታክሲዎችን እንዲሁም 9 ሴት እና 2 ወንዶች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል ብለዋል።
አሁን ላይ በከተማዋ የተለያዩ ሐሰተኛ መረጃዎችን በማዘጋጀት እና ያልታመመ ሰውን ታመመ በማለት የሚመለከተው የሕክምና ተቋም ማረጋገጫ ሳይሰጥ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚካሄዱ ልመናዎች መብዛታቸውን የጠቆሙት ኃላፊው ኅብረተሰቡም ከአጭበርባሪ ወንጀለኞች ራሱን እና ንብረቱን እንዲጠብቅ ሲሉ ጥሪያቸውን ማስተላለፋቸውን ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በመረጃ ክልከላ፣ በመገናኛ ብዙሃን እና ባለሙያዎች ላይ እየደረሰ ያለውን እንግልት መፍታት የሚያስችል ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ሊገባ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የአገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ መንግስት መገናኛ ብዙሃን የሚጠበቅባቸውን የምርመራ ስራዎች እና መረጃዎችን ተደራሽ እንዲያደርጉ ቁርጠኝነት ቢኖረውም የመረጃ ፍሰቱ ላይ ከትናንት የተረከብናቸው ከፍተኛ ችግሮች አሉ ብለዋል።
የስራ ሃላፊዎች እና ተቋማት በአብዛኛው ለቦታው አዲስ ነኝ፤አይመለከተኝም እና ሌሎች ምክንያት በማቅረብ ለመገናኛ ብዙሃኑ ተግበራት ማነቆ ይሆናሉ ነው ያሉት።ይህን በአገሪቱ በስፋት የሚስተዋልን ችግር ለመቅረፍ የተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ውይይት ተደርጎበት ለትግበራ ዝግጁ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
መመሪያው ከፌደራል ጀምሮ እስከ ታችኛው የኮሙኒኬሽን እርከን የግንኙነት አሰራር የሚፈጥር ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፥ የህዝብ ግንኙነት ባለሞያዎች ተቋማቸውን የሚያስተዋውቁበት እንዲሁም ከመገናኛ ብዙሃን ጋር ያላቸው ግንኙነት የሚጠናክሩበትን እድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል፡፡በተጨማሪም የህዝብ ግንኙነት ባለሞያዎችን በስልጠናዎች የማገዝ፣ የአቅም ግንባታ ስራዎች እና ሌሎች ተግባራትም በቀጣይ በትኩረት የሚሰራባቸው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
የአገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ መንግስት መገናኛ ብዙሃን የሚጠበቅባቸውን የምርመራ ስራዎች እና መረጃዎችን ተደራሽ እንዲያደርጉ ቁርጠኝነት ቢኖረውም የመረጃ ፍሰቱ ላይ ከትናንት የተረከብናቸው ከፍተኛ ችግሮች አሉ ብለዋል።
የስራ ሃላፊዎች እና ተቋማት በአብዛኛው ለቦታው አዲስ ነኝ፤አይመለከተኝም እና ሌሎች ምክንያት በማቅረብ ለመገናኛ ብዙሃኑ ተግበራት ማነቆ ይሆናሉ ነው ያሉት።ይህን በአገሪቱ በስፋት የሚስተዋልን ችግር ለመቅረፍ የተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ውይይት ተደርጎበት ለትግበራ ዝግጁ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
መመሪያው ከፌደራል ጀምሮ እስከ ታችኛው የኮሙኒኬሽን እርከን የግንኙነት አሰራር የሚፈጥር ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፥ የህዝብ ግንኙነት ባለሞያዎች ተቋማቸውን የሚያስተዋውቁበት እንዲሁም ከመገናኛ ብዙሃን ጋር ያላቸው ግንኙነት የሚጠናክሩበትን እድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል፡፡በተጨማሪም የህዝብ ግንኙነት ባለሞያዎችን በስልጠናዎች የማገዝ፣ የአቅም ግንባታ ስራዎች እና ሌሎች ተግባራትም በቀጣይ በትኩረት የሚሰራባቸው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
-200,000 ብር
በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ሰንጋ በሞርትና ጅሩ ወረዳ የሆሳዕና ገበያ በ200,000 ብር መሸጡን የወረዳው ኮምኒኬሽን ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ሰንጋ በሞርትና ጅሩ ወረዳ የሆሳዕና ገበያ በ200,000 ብር መሸጡን የወረዳው ኮምኒኬሽን ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከኢትዮ ቴሌኮም ለሚከራያቸው የቴሌኮም መሠረተ ልማቶች ኪራዩን በኢትዮጵያ ብር እና በአሜሪካ ዶላር ለመክፈል መስማማቱን ሪፖርተር ዘግቧል።
በስምምነቱ መሠረት ሳፋሪኮም ላንዳንድ መሠረተ ልማቶች በ70/30፣ ለሌሎች ደሞ በ40/60 ስሌት በብር እና ዶላት ይከፍላል። ኩባንያዎቹ በመርህ ደረጃ ለደረሱበት ስምምነት በቅርቡ ሕጋዊ ውል እንደሚፈራረሙ ይጠበቃል። ኢትዮ ቴሌኮም ኪራዩ በዶላር እንዲሆንለት ሲጠይቅ ሳፋሪኮም ደሞ ብርን በመምረጡ የተፈጠረው ልዩነት የተቀረፈው፣ በኢትዮጵያ ኮምንኬሽን ባለሥልጣን አደራዳሪነት ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
በስምምነቱ መሠረት ሳፋሪኮም ላንዳንድ መሠረተ ልማቶች በ70/30፣ ለሌሎች ደሞ በ40/60 ስሌት በብር እና ዶላት ይከፍላል። ኩባንያዎቹ በመርህ ደረጃ ለደረሱበት ስምምነት በቅርቡ ሕጋዊ ውል እንደሚፈራረሙ ይጠበቃል። ኢትዮ ቴሌኮም ኪራዩ በዶላር እንዲሆንለት ሲጠይቅ ሳፋሪኮም ደሞ ብርን በመምረጡ የተፈጠረው ልዩነት የተቀረፈው፣ በኢትዮጵያ ኮምንኬሽን ባለሥልጣን አደራዳሪነት ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
የቅዱስ ላልይበላ ገዳም ካህናትና አገልጋዮችን ለመደገፍ በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ 8 ሚሊዮን ብር ተሰበሰበ!
የቅዱስ ላልይበላ ገዳም ካህናትና አገልጋዮችን ለመደገፍ "ወደ ቅዱስ ላልይበላ ተመልክቱ!" በሚል ጥሪ በሸራተን አዲስ ሆቴል በተካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር 8 ሚሊዮን ብር ያህል መሰብሰቡ ተገለፀ።
በገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብሩ ላይ እንደተገለጸው፤ በመንፈሳዊ አገልግሎቱ ኢትዮጵያን ከዘመን ዘመን ሲያሻግር የኖረውና ለአገሪቱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ሆኖ ያገለገለው የቅዱስ ላልይበላ ቅርስ ጠባቂዎች በጥልቅ የመኖር አለመኖር ፈተና ውስጥ ወድቀዋል። በመሆኑም የቅርሱ ጠባቂዎች የህልውና ጥያቄ በቅርሱ ደህንነት ላይ ተጨማሪ ጫና ፈጥሯል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን (ከሚሴ ) አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመርሐግብሩ ላይ እንደተናገሩት፤ "በረዥም ዕድሜ ሳቢያ እንክብካቤ ለሚፈልገው ቅርስ በመንግሥት እገዛ ከፈረንሳይ መንግሥት ድጋፍ የተገኘ ቢሆንም፤ የቅርሱን ጉዳትና ደህንነት በቅርብ የሚያውቁትና የሚከታተሉት የቅዱስ ላልይበላ ካህናትና ነዋሪዎች ግን አስታዋሽ አላገኙም" ብለዋል።
በአካባቢው ባለፉት አሥር ወራት የመብራት አገልግሎት ከመቋረጡ ጋር ተያይዞ የውሃ፣ የህክምና፣ የወፍጮና ሌሎች መሠረታዊ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መጥፋቱን ብፁዕነታቸው አመልክተዋል። በአካባቢው በነበረው ጦርነት 4 ሺህ 322 ንፁሀን ወገኖች መሞታቸውንም ጠቅሰዋል።
ደብሩ በዚህ የከፋ ሁኔታ ውስጥ ላሉት ካህናት፣ የቅርሱ ጠባቂዎችና ነዋሪዎች ያለውን ጥሪት ቆጥቦና ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ተበድሮ ህዝቡን ለመመገብ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱንም ብፁዕነታቸው አያይዘው ገልጸዋል።
ሆኖም ግን፤ ያለው አቅም ሁሉ በመሟጠጡ መንግሥትና በመላው ዓለም የሚገኙ የቅርሱ ቤተሰቦች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪው መተላለፉን ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ አብራርተዋል።
በገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ባህል ሚኒስትር ዲኤታ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው "የአገር ውስጥና የውጭ አገር ቱሪስቶችን ወደ ሥፍራው ለጉብኝት ለመሳብ ሰፊ ጥረት ቢደረግም በተለይ በሰሜን ኢትዮጵያ የተካሄደው ጦርነት ትልቅ ጫና ፈጥሯል። ይህም በቅርሱ ዙሪያ ባሉ ነዋሪዎች ሕይወት ላይ ትልቅ ፈተና ሆኗል" ብለዋል።
በኢኦተቤ በሰሜን ወሎ አገረ ስብከት የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላልይበላ ገዳም ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በመሆን ባዘጋጀው የገቢ ማስገኛ መርሐ ግብር 8 ሚሊዮን ብር ያህል ተሰብስቧል።
በመርሐግብሩ ማጠናቀቂያ ላይ ብፁዕ አቡነ ሰላማ በሰሜን አሜሪካ የኦሃዮና አካባቢው አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፤ ስጦታው ጅምር መሆኑን ጠቅሰው በመላው ዓለም የሚገኙ የቅዱስ ላልይበላ ቤተሰቦች በሀሳብ በጸሎትና በገንዘብ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ ማስተላለፉቸውን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙሀን አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የቅዱስ ላልይበላ ገዳም ካህናትና አገልጋዮችን ለመደገፍ "ወደ ቅዱስ ላልይበላ ተመልክቱ!" በሚል ጥሪ በሸራተን አዲስ ሆቴል በተካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር 8 ሚሊዮን ብር ያህል መሰብሰቡ ተገለፀ።
በገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብሩ ላይ እንደተገለጸው፤ በመንፈሳዊ አገልግሎቱ ኢትዮጵያን ከዘመን ዘመን ሲያሻግር የኖረውና ለአገሪቱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ሆኖ ያገለገለው የቅዱስ ላልይበላ ቅርስ ጠባቂዎች በጥልቅ የመኖር አለመኖር ፈተና ውስጥ ወድቀዋል። በመሆኑም የቅርሱ ጠባቂዎች የህልውና ጥያቄ በቅርሱ ደህንነት ላይ ተጨማሪ ጫና ፈጥሯል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን (ከሚሴ ) አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመርሐግብሩ ላይ እንደተናገሩት፤ "በረዥም ዕድሜ ሳቢያ እንክብካቤ ለሚፈልገው ቅርስ በመንግሥት እገዛ ከፈረንሳይ መንግሥት ድጋፍ የተገኘ ቢሆንም፤ የቅርሱን ጉዳትና ደህንነት በቅርብ የሚያውቁትና የሚከታተሉት የቅዱስ ላልይበላ ካህናትና ነዋሪዎች ግን አስታዋሽ አላገኙም" ብለዋል።
በአካባቢው ባለፉት አሥር ወራት የመብራት አገልግሎት ከመቋረጡ ጋር ተያይዞ የውሃ፣ የህክምና፣ የወፍጮና ሌሎች መሠረታዊ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መጥፋቱን ብፁዕነታቸው አመልክተዋል። በአካባቢው በነበረው ጦርነት 4 ሺህ 322 ንፁሀን ወገኖች መሞታቸውንም ጠቅሰዋል።
ደብሩ በዚህ የከፋ ሁኔታ ውስጥ ላሉት ካህናት፣ የቅርሱ ጠባቂዎችና ነዋሪዎች ያለውን ጥሪት ቆጥቦና ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ተበድሮ ህዝቡን ለመመገብ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱንም ብፁዕነታቸው አያይዘው ገልጸዋል።
ሆኖም ግን፤ ያለው አቅም ሁሉ በመሟጠጡ መንግሥትና በመላው ዓለም የሚገኙ የቅርሱ ቤተሰቦች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪው መተላለፉን ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ አብራርተዋል።
በገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ባህል ሚኒስትር ዲኤታ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው "የአገር ውስጥና የውጭ አገር ቱሪስቶችን ወደ ሥፍራው ለጉብኝት ለመሳብ ሰፊ ጥረት ቢደረግም በተለይ በሰሜን ኢትዮጵያ የተካሄደው ጦርነት ትልቅ ጫና ፈጥሯል። ይህም በቅርሱ ዙሪያ ባሉ ነዋሪዎች ሕይወት ላይ ትልቅ ፈተና ሆኗል" ብለዋል።
በኢኦተቤ በሰሜን ወሎ አገረ ስብከት የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላልይበላ ገዳም ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በመሆን ባዘጋጀው የገቢ ማስገኛ መርሐ ግብር 8 ሚሊዮን ብር ያህል ተሰብስቧል።
በመርሐግብሩ ማጠናቀቂያ ላይ ብፁዕ አቡነ ሰላማ በሰሜን አሜሪካ የኦሃዮና አካባቢው አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ፤ ስጦታው ጅምር መሆኑን ጠቅሰው በመላው ዓለም የሚገኙ የቅዱስ ላልይበላ ቤተሰቦች በሀሳብ በጸሎትና በገንዘብ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ ማስተላለፉቸውን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙሀን አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
348 ዜጎች ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ!
ዛሬ በተደረገው የመጀመሪያው በረራ 348 ዜጎች ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡ተመላሾች ሁሉም ወንዶች መሆናቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ በተደረገው የመጀመሪያው በረራ 348 ዜጎች ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡ተመላሾች ሁሉም ወንዶች መሆናቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በጦርነትና በግጭት ውስጥ ሆነው ተፈትነዋል ተብለው የተለዩ እና የ12ኛ ክፍል የማለፊያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎች በዚህ አመት ይፈተናሉ – ትምህርት ሚኒስቴር
በጦርነት እና በግጭት ውስጥ ሆነው ተፈትነዋል ተብለው የተለዩ እና የ12ኛ ክፍል የማለፊያ ውጤት ያላመጡ በዚህ ዓመት በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እንደ መደበኛ ተማሪ ሆነው መፈተን እንደሚችሉ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡የትምህርት ሚኒስቴር፣ ሁሉም ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በጋራ መግለጫ እየሰጡ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
በጦርነት እና በግጭት ውስጥ ሆነው ተፈትነዋል ተብለው የተለዩ እና የ12ኛ ክፍል የማለፊያ ውጤት ያላመጡ በዚህ ዓመት በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እንደ መደበኛ ተማሪ ሆነው መፈተን እንደሚችሉ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡የትምህርት ሚኒስቴር፣ ሁሉም ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በጋራ መግለጫ እየሰጡ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ ለተማሪዎች አዲስ ውሳኔ መተላለፉን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ!
በአማራ ክልል በ2013 የትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ ለክልሉ ተማሪዎች አዲስ ውሳኔ መተላለፉን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።
የ2013 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት ጉዳይ ከዚህ ቀጥሎ በተገለፁት ኹለት ውሳኔዎች የሚፈፀም ይሆናል ሲል ቢሮው ገልጿል፡፡
የመጀመሪያው ውሳኔ ከዚህ በፊት በተላለፈው የመቁረጫ ነጥብ መሰረት ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች መግባት ከቻሉት የክልሉ ተማሪዎች በተጨማሪ 4 ሺህ 339 ተማሪዎች በመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች ቅበላ የሚያገኙ ይሆናል ተብሏል።
እንዲሁም በ2013 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የመግቢያ ነጥብ ያላሟሉ የአማራ ክልል ኹሉም ዞኖች ተማሪዎች በ2014 በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በመደበኛ ተማሪነት መፈተን እንዲችሉ መወሰኑን ቢሮው በማኅበራዊ ትስስር ገፁ ባሰፈረው መረጃ አስታውቋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከተፈጠረው ችግር አኳያ ውሳኔው ያላረካቸው አካላት ሊኖሩ እንደሚችሉ ይገመታል ያለ ሲሆን፤ የክልሉ ተማሪዎች በመደበኛ ተማሪነት የመፈተን እድሉን በድጋሜ ማግኘታቸውን እንደ ትልቅ አጋጣሚ አድርገው ለውጤታማነት እንዲጠቀሙበት አሳስቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል በ2013 የትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ ለክልሉ ተማሪዎች አዲስ ውሳኔ መተላለፉን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።
የ2013 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት ጉዳይ ከዚህ ቀጥሎ በተገለፁት ኹለት ውሳኔዎች የሚፈፀም ይሆናል ሲል ቢሮው ገልጿል፡፡
የመጀመሪያው ውሳኔ ከዚህ በፊት በተላለፈው የመቁረጫ ነጥብ መሰረት ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች መግባት ከቻሉት የክልሉ ተማሪዎች በተጨማሪ 4 ሺህ 339 ተማሪዎች በመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች ቅበላ የሚያገኙ ይሆናል ተብሏል።
እንዲሁም በ2013 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የመግቢያ ነጥብ ያላሟሉ የአማራ ክልል ኹሉም ዞኖች ተማሪዎች በ2014 በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በመደበኛ ተማሪነት መፈተን እንዲችሉ መወሰኑን ቢሮው በማኅበራዊ ትስስር ገፁ ባሰፈረው መረጃ አስታውቋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከተፈጠረው ችግር አኳያ ውሳኔው ያላረካቸው አካላት ሊኖሩ እንደሚችሉ ይገመታል ያለ ሲሆን፤ የክልሉ ተማሪዎች በመደበኛ ተማሪነት የመፈተን እድሉን በድጋሜ ማግኘታቸውን እንደ ትልቅ አጋጣሚ አድርገው ለውጤታማነት እንዲጠቀሙበት አሳስቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ያሳለፍነው ወር የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ34.7 ከመቶ ጭማሪ አሳየ!
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ የመጋቢት ወር 2014 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ34.7 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
የምግብ ዋጋ ግሽበት የመጋቢት ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ43.4 በመቶ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን ከየካቲት ወር 2014 ጋር ሲነጻጸር በ1.5 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ በያዝነውም ወር በአብዛኛው በእህሎች የዋጋ ጭማሪ የታየ ሲሆን የአትክልት ዋጋም ላይ መጠነኛ ጭማሪ ታይቷል፡፡
ሩዝ፣ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ሽንቡራና ምሥር በአብዛኛው የዋጋ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡በተጨማሪም ወተት፣ አይብና ዕንቁላል፣ ቅመማ ቅመም (በዋናነት ጨውና በርበሬ) ጭማሪ አሳይተዋል፡፡ የምግብ ዘይትና ቅቤ ዋጋ በፍጥነት የጨመረ ሲሆን ቡናና ለስለሳ መጠጦች ተከታታይ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ የመጋቢት ወር 2014 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ34.7 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
የምግብ ዋጋ ግሽበት የመጋቢት ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ43.4 በመቶ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን ከየካቲት ወር 2014 ጋር ሲነጻጸር በ1.5 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ በያዝነውም ወር በአብዛኛው በእህሎች የዋጋ ጭማሪ የታየ ሲሆን የአትክልት ዋጋም ላይ መጠነኛ ጭማሪ ታይቷል፡፡
ሩዝ፣ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ሽንቡራና ምሥር በአብዛኛው የዋጋ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡በተጨማሪም ወተት፣ አይብና ዕንቁላል፣ ቅመማ ቅመም (በዋናነት ጨውና በርበሬ) ጭማሪ አሳይተዋል፡፡ የምግብ ዘይትና ቅቤ ዋጋ በፍጥነት የጨመረ ሲሆን ቡናና ለስለሳ መጠጦች ተከታታይ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
ሩሲያ ኢትዮጵያውያን ወዶ ዘማቾችን እየመለመለች ነው መባሉን አስተባበለች!
የሩሲያ ኤምባሲ በር ላይ ኢትዮጵያዊያኑ ለምን ተሰለፉ ለሚለው ኤምባሲው አል-ዐይን አማርኛ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ መግቢያ በር ላይ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ለሩሲያ ዩክሬንን ለመውጋት ለመመዝገብ ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ናቸው የሚል ምስል በማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ በመሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡
አል ዐይን አማርኛ ጉዳዩን በሚመለከት በአዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ ጠይቋል።
የኤምባሲው ፕረስ አታቼ ማሪያ ቸርኑኪና ለአል ዐይን እንዳሉት “ሩሲያ ለዩክሬን ጦርነት ኢትዮጵያዊያንን ለመቅጠር ማስታወቂያ አላወጣችም፣ በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለው መረጃም ሀሰተኛ ነው” ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል።
ይሁንና ሩሲያ ከዩክሬን ጋር እያደረገችው ባለው ጦርነት “በርካታ ኢትዮጵያዊያን በኢሜይል እና በአካል ከሩሲያ ጎን መሆናቸውን እያሳወቁን ነው ለዚህ እናመሰግናለን” ሲሉም አክለዋል።
ኢትዮጵያዊያን ይሄንን እያደረጉ ያለው ረጅም እና ታሪካዊ በሆነው የኢትዮጵያ እና ሩሲያ ወዳጅነት ላይ ስለሚተማመኑ እንደሆነም ኤምባሲው ተገልጿል።
Via Alain
@YeneTube @FikerAssefa
የሩሲያ ኤምባሲ በር ላይ ኢትዮጵያዊያኑ ለምን ተሰለፉ ለሚለው ኤምባሲው አል-ዐይን አማርኛ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡
ከሰሞኑ በአዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ መግቢያ በር ላይ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ለሩሲያ ዩክሬንን ለመውጋት ለመመዝገብ ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ናቸው የሚል ምስል በማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ በመሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡
አል ዐይን አማርኛ ጉዳዩን በሚመለከት በአዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ ጠይቋል።
የኤምባሲው ፕረስ አታቼ ማሪያ ቸርኑኪና ለአል ዐይን እንዳሉት “ሩሲያ ለዩክሬን ጦርነት ኢትዮጵያዊያንን ለመቅጠር ማስታወቂያ አላወጣችም፣ በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለው መረጃም ሀሰተኛ ነው” ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል።
ይሁንና ሩሲያ ከዩክሬን ጋር እያደረገችው ባለው ጦርነት “በርካታ ኢትዮጵያዊያን በኢሜይል እና በአካል ከሩሲያ ጎን መሆናቸውን እያሳወቁን ነው ለዚህ እናመሰግናለን” ሲሉም አክለዋል።
ኢትዮጵያዊያን ይሄንን እያደረጉ ያለው ረጅም እና ታሪካዊ በሆነው የኢትዮጵያ እና ሩሲያ ወዳጅነት ላይ ስለሚተማመኑ እንደሆነም ኤምባሲው ተገልጿል።
Via Alain
@YeneTube @FikerAssefa
በሰሜን ሽዋ በተቀሰቀሰ ግጭት ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ የሚወስደው መንገድ መዘጋቱን ነዋሪዎቸ ገለጹ!
ግጭቱ ከአንድ ሳምንት በፊት ተከስቶ በውይይት የተፈታ ቢሆንም ከትናንት ጀምሮ ዳግም ማገርሸቱን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡በግጭቱ እስካሁን የስምንት ሰዎች ህይወት ማለፉንም ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
ግጭቱ ከአንድ ሳምንት በፊት ተከስቶ በውይይት የተፈታ ቢሆንም ከትናንት ጀምሮ ዳግም ማገርሸቱን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡በግጭቱ እስካሁን የስምንት ሰዎች ህይወት ማለፉንም ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
ገንዘብ ሚንስቴር በግል ባንኮች ሒሳብ የከፈቱ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ሒሳባቸውን ባስቸኳይ እንዲዘጉ ማዘዙን የኢትዮጵያ የባንክ ባለሙያዎች ማኅበር እንደተቃወመው ካፒታል ዘግቧል።
የግል እና የመንግሥት ባንኮች ፕሬዝዳንቶች ዓርብ'ለት ባደረጉት የማኅበሩ ስብሰባ፣ የግል ባንኮች ቅሬታ ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል እንዲቀርብ ተወስኗል። ብሄራዊ ባንክ የመንግሥት ተቋማት ገንዘብ እንዲያስቀምጡበት ውክልና የሰጠው ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ እንደሆነ በቅርቡ በደብዳቤ አስታውቆ ነበር። የግል ባንኮች ውሳኔውን የተቃወሙት፣ አድሏዊ እና ነጻ እና ፍትሃዊ የገበያ ውድድርን የሚገድብ መሆኑን በመግለጽ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
የግል እና የመንግሥት ባንኮች ፕሬዝዳንቶች ዓርብ'ለት ባደረጉት የማኅበሩ ስብሰባ፣ የግል ባንኮች ቅሬታ ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል እንዲቀርብ ተወስኗል። ብሄራዊ ባንክ የመንግሥት ተቋማት ገንዘብ እንዲያስቀምጡበት ውክልና የሰጠው ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ እንደሆነ በቅርቡ በደብዳቤ አስታውቆ ነበር። የግል ባንኮች ውሳኔውን የተቃወሙት፣ አድሏዊ እና ነጻ እና ፍትሃዊ የገበያ ውድድርን የሚገድብ መሆኑን በመግለጽ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
🥳መልካም የትንሳኤ በአል እያልን የበአል ልዩ ቅናሽ ይዘን መጥተናል🥳
https://tttttt.me/getitonlinee
የወንድም የሴትም
🎯ኦርጂናል ጥሩ ሽታ ያላቸው ሽቶዎች
🎯የስጦታ ጥቅሎች(package)🎁
🎯ኦርጂናል ሰአቶች
🎯 ቦርሳዎች እና የውበት መጠበቂያዎች
🎯 አልባሳት እና ጫማዎች
🎯ለተጨማሪ መረጃ ይደውሉ በ0929011031
🎯አድራሻ፣ ቦሌ መድሀኒያለም
ያሉበት ቦታ ድረስ በነጻ እናደርሳለን
የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቅለው ቤተሰብ ይሁኑ https://tttttt.me/getitonlinee
https://tttttt.me/getitonlinee
የወንድም የሴትም
🎯ኦርጂናል ጥሩ ሽታ ያላቸው ሽቶዎች
🎯የስጦታ ጥቅሎች(package)🎁
🎯ኦርጂናል ሰአቶች
🎯 ቦርሳዎች እና የውበት መጠበቂያዎች
🎯 አልባሳት እና ጫማዎች
🎯ለተጨማሪ መረጃ ይደውሉ በ0929011031
🎯አድራሻ፣ ቦሌ መድሀኒያለም
ያሉበት ቦታ ድረስ በነጻ እናደርሳለን
የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቅለው ቤተሰብ ይሁኑ https://tttttt.me/getitonlinee
በእነ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ ተካተው ከ3 ዓመት በላይ በእስር ላይ የነበሩ ግለሰቦች ከእስር እንዲፈቱ ታዘዘ!
የቀድሞ የደህንነት ቢሮ ዳይሬክተር በነበሩት በእነ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ ተካተው ከ3 ዓመት በላይ በእስር ላይ የነበሩ ግለሰቦች ከእስር እንዲፈቱ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ትዕዛዝ አስተላለፈ።አዲሱ በዳሳ፣ ሳሙኤል ጊዲሳና ደርሶ አየነው የተባሉ ተከሳሾች በትናንትናው ዕለት በፍርድ ቤት ከተወሰነባቸው የቅጣት ውሳኔ በላይ በእስር በማሳለፋቸው (የእስር ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው) ነው ከእስር እንዲፈቱ የታዘዘው።
በሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ከተከሰሱት በእነ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ ተካተው የነበሩት 17ኛ ተከሳሽ አዲሱ በዳሳ 18ኛ ሳሙኤል ጊዲሳ እና 24ኛ ተከሳሽ ደርሶ አየነው ከጥቅምት ወር 2011 ጀምሮ በእስር ላይ ሆነው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ቆይተዋል።እነዚሁ ሦስቱ ተከሳሾች በየካቲት 25 ቀን 2014 በነበረ የችሎት ቀጠሮ "ባልሰራንበት ወንጀል አራት ዓመት ታስረናል፤ የተፋጠነ ፍትህ ለማግኘት እንድንችል የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ አንፈልግም።" በማለት ጉዳያቸው ተነጥሎ ፍርድ እንዲሰጣቸው ጠይቀው እንደነበረም ይታወሳል።
በተለይም 24ኛ ተከሳሽ ደርሶ አየነው ያለጥፋቱ አራት ዓመት መታሰሩን ጠቅሶ በእያንዳንዷ ቀናት ቤተሰቦቹ ከቀለብ ጀምሮ መቸገራቸውን ገልጾ ነበር።ፍርድ ቤቱ የፈለገውን ፍርድ ይፍረድብን እና እንረፍ ሲሉ የተፋጠነ ፍትህ እንዲያገኙ እንደሚፈልጉ መግለጻቸው ይታወሳል።
በዚሁ የካቲት 25 ቀን 17ኛና 18ኛ ተከሳሽ የነበሩት አዲሱና ሳሙኤል የቅጣት ማቅለያ አስተያየት አያይዘው በጽሁፍ አቅርበው ነበር።ፍርድ ቤቱም ከክስ መዝገቡን የሦስቱን ተከሳሾች ጉዳይ ነጥሎ መርምሯል።
በዚህም ተከሳሾቹ የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸውና ለአገር ልማት ያደረጉትን አስተዋጾ አክለው ያቀረቡትን 5 የቅጣት ማቅለያ ፍርድ ቤቱ ይዞላቸዋል።በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ ትላንት ከሰዓት በኋላ በዋለው የችሎት ቀጠሮ፤ ፍርድ ቤቱ እንዲከላከሉ በተባሉበት አንቀጽ አዱሱ በዳሳና ሳሙኤል ጊዲሳን እያንዳንዳቸውን የ3 ዓመት እስራትና የ3 ሺህ 500 ብር የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ የሰጠ ሲሆን፤ 24ኛ ተከሳሽ ደርሶ አየነውን በተመለከተ ደግሞ በኹለት ዓመት እስራትና በ1 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚህም መሰረት አዲሱ በዳሳና ደርሶ አየነው ከታሰሩበት ከጥቅምት ወር 2011 ጀምሮ ታሳቢ ሲደረግ፤ ከቅጣቱ በላይ በመታሰራቸውና የእስር ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው ከትላንት ጀምሮ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ መሰጠቱን ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ ከችሎት ዘግባለች።ሳሙኤል ጊዲሳን በተመለከተም እስካሁን የታሰረበት ጊዜ በመዝገቡ ላይ ያልተካተተ ቢሆንም፤ የታሰረበት የጊዜ መጠን ተጣርቶ በተመሳሳይ ከእስር የሚፈታ ይሆናል ተብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞ የደህንነት ቢሮ ዳይሬክተር በነበሩት በእነ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ ተካተው ከ3 ዓመት በላይ በእስር ላይ የነበሩ ግለሰቦች ከእስር እንዲፈቱ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ትዕዛዝ አስተላለፈ።አዲሱ በዳሳ፣ ሳሙኤል ጊዲሳና ደርሶ አየነው የተባሉ ተከሳሾች በትናንትናው ዕለት በፍርድ ቤት ከተወሰነባቸው የቅጣት ውሳኔ በላይ በእስር በማሳለፋቸው (የእስር ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው) ነው ከእስር እንዲፈቱ የታዘዘው።
በሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ከተከሰሱት በእነ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ ተካተው የነበሩት 17ኛ ተከሳሽ አዲሱ በዳሳ 18ኛ ሳሙኤል ጊዲሳ እና 24ኛ ተከሳሽ ደርሶ አየነው ከጥቅምት ወር 2011 ጀምሮ በእስር ላይ ሆነው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ቆይተዋል።እነዚሁ ሦስቱ ተከሳሾች በየካቲት 25 ቀን 2014 በነበረ የችሎት ቀጠሮ "ባልሰራንበት ወንጀል አራት ዓመት ታስረናል፤ የተፋጠነ ፍትህ ለማግኘት እንድንችል የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ አንፈልግም።" በማለት ጉዳያቸው ተነጥሎ ፍርድ እንዲሰጣቸው ጠይቀው እንደነበረም ይታወሳል።
በተለይም 24ኛ ተከሳሽ ደርሶ አየነው ያለጥፋቱ አራት ዓመት መታሰሩን ጠቅሶ በእያንዳንዷ ቀናት ቤተሰቦቹ ከቀለብ ጀምሮ መቸገራቸውን ገልጾ ነበር።ፍርድ ቤቱ የፈለገውን ፍርድ ይፍረድብን እና እንረፍ ሲሉ የተፋጠነ ፍትህ እንዲያገኙ እንደሚፈልጉ መግለጻቸው ይታወሳል።
በዚሁ የካቲት 25 ቀን 17ኛና 18ኛ ተከሳሽ የነበሩት አዲሱና ሳሙኤል የቅጣት ማቅለያ አስተያየት አያይዘው በጽሁፍ አቅርበው ነበር።ፍርድ ቤቱም ከክስ መዝገቡን የሦስቱን ተከሳሾች ጉዳይ ነጥሎ መርምሯል።
በዚህም ተከሳሾቹ የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸውና ለአገር ልማት ያደረጉትን አስተዋጾ አክለው ያቀረቡትን 5 የቅጣት ማቅለያ ፍርድ ቤቱ ይዞላቸዋል።በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ ትላንት ከሰዓት በኋላ በዋለው የችሎት ቀጠሮ፤ ፍርድ ቤቱ እንዲከላከሉ በተባሉበት አንቀጽ አዱሱ በዳሳና ሳሙኤል ጊዲሳን እያንዳንዳቸውን የ3 ዓመት እስራትና የ3 ሺህ 500 ብር የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ የሰጠ ሲሆን፤ 24ኛ ተከሳሽ ደርሶ አየነውን በተመለከተ ደግሞ በኹለት ዓመት እስራትና በ1 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚህም መሰረት አዲሱ በዳሳና ደርሶ አየነው ከታሰሩበት ከጥቅምት ወር 2011 ጀምሮ ታሳቢ ሲደረግ፤ ከቅጣቱ በላይ በመታሰራቸውና የእስር ጊዜያቸውን በማጠናቀቃቸው ከትላንት ጀምሮ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ መሰጠቱን ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ ከችሎት ዘግባለች።ሳሙኤል ጊዲሳን በተመለከተም እስካሁን የታሰረበት ጊዜ በመዝገቡ ላይ ያልተካተተ ቢሆንም፤ የታሰረበት የጊዜ መጠን ተጣርቶ በተመሳሳይ ከእስር የሚፈታ ይሆናል ተብሏል።
@YeneTube @FikerAssefa
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በቪዛ ፖሊሲዋ ላይ አዳዲስ ማሻሻያ ማድረጓን አስታወቀች!
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በቪዛ ፖሊሲዋ ላይ የተለያዩ ለውጦችን ማድረጓን ያስታወቀች ሲሆን የሃገሪቱ ምክር ቤት የውጭ ዜጎች የመኖሪያ ፈቃዳቸው ከተሰረዘ ወይም ካለቀ በኋላ እስከ ስድስት ወር ድረስ በአገር ውስጥ እንዲቆዩ የሚያስችል ረጅም የእፎይታ ጊዜ ፈቅዷል።
ይሁን እንጂ ይህ በሁሉም የቪዛ ዓይነቶች ላይ ተፈፃሚ መሆን አለመሆኑ እስካሁን አልተገለፀም። የሀገሪቱ መንግስት አዲስ የመኖሪያ እና የቪዛ ስርዓት መዘርጋቱን ኻሊጅ ታይምስ ዘግቧል። አዲሱ ስርዓት የኤምሬትስ ዜጎች እድሜያቸው እስከ 25 ለሆኑ ህፃናትና ወጣቶች የጉዞ ቪዛ ስፖንሰር መሆን ይችላሉ። የተባበሩት ኤምሬትስ ነዋሪዎች ያላገቡ ሴቶችን ያለእድሜ ገደብ ቪዛ እንዲያገኙ ማስደረግ እንዲችሉም ተፈቅዷል።
ከዚህ ቀደም በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የቪዛ መመሪያ መሰረት የቪዛ ስፖንሰርሺፕ እድሜያቸው እስከ 18 ለሆኑ ታዳጊዎች ብቻ የተገደበ ነበር።ካቢኔው በቪዛ ማሻሻያው ላይ ለአምስት ዓመት ከሚያገለግል የአረንጓዴ ቪዛ እና ለ10 ዓመት የሚቆይ ወርቃማ ቪዛ ምድቦችን አስተዋውቋል።
እንደ ኻሊጅ ታይምስ ዘገባ በአዲሱ አሰራር ነዋሪዎች የትዳር ጓደኛ እና ልጆችን ጨምሮ ለቤተሰብ አባላት የመኖሪያ ፈቃድ በቀላሉ ሊያስገኙ ይችላሉ። አረንጓዴ የመኖሪያ ቪዛ ያላቸውም ለቅርብ የስጋ ዘመዶቻቸው የመኖሪያ ፈቃድ እንዲያሰጡ ተፈቅዶላቸዋል።በተጨማሪም ማሻሻያዎቹ ለወርቃማ ቪዛ ያዢዎች የቤተሰብ አባላትን፣ የትዳር ጓደኛ፣ ልጆችን ጨምሮ የቤት ውስጥ ሰራተኞችን ስፖንሰር እንዲያደርጉ ያስችላቸዋል።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በቪዛ ፖሊሲዋ ላይ የተለያዩ ለውጦችን ማድረጓን ያስታወቀች ሲሆን የሃገሪቱ ምክር ቤት የውጭ ዜጎች የመኖሪያ ፈቃዳቸው ከተሰረዘ ወይም ካለቀ በኋላ እስከ ስድስት ወር ድረስ በአገር ውስጥ እንዲቆዩ የሚያስችል ረጅም የእፎይታ ጊዜ ፈቅዷል።
ይሁን እንጂ ይህ በሁሉም የቪዛ ዓይነቶች ላይ ተፈፃሚ መሆን አለመሆኑ እስካሁን አልተገለፀም። የሀገሪቱ መንግስት አዲስ የመኖሪያ እና የቪዛ ስርዓት መዘርጋቱን ኻሊጅ ታይምስ ዘግቧል። አዲሱ ስርዓት የኤምሬትስ ዜጎች እድሜያቸው እስከ 25 ለሆኑ ህፃናትና ወጣቶች የጉዞ ቪዛ ስፖንሰር መሆን ይችላሉ። የተባበሩት ኤምሬትስ ነዋሪዎች ያላገቡ ሴቶችን ያለእድሜ ገደብ ቪዛ እንዲያገኙ ማስደረግ እንዲችሉም ተፈቅዷል።
ከዚህ ቀደም በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የቪዛ መመሪያ መሰረት የቪዛ ስፖንሰርሺፕ እድሜያቸው እስከ 18 ለሆኑ ታዳጊዎች ብቻ የተገደበ ነበር።ካቢኔው በቪዛ ማሻሻያው ላይ ለአምስት ዓመት ከሚያገለግል የአረንጓዴ ቪዛ እና ለ10 ዓመት የሚቆይ ወርቃማ ቪዛ ምድቦችን አስተዋውቋል።
እንደ ኻሊጅ ታይምስ ዘገባ በአዲሱ አሰራር ነዋሪዎች የትዳር ጓደኛ እና ልጆችን ጨምሮ ለቤተሰብ አባላት የመኖሪያ ፈቃድ በቀላሉ ሊያስገኙ ይችላሉ። አረንጓዴ የመኖሪያ ቪዛ ያላቸውም ለቅርብ የስጋ ዘመዶቻቸው የመኖሪያ ፈቃድ እንዲያሰጡ ተፈቅዶላቸዋል።በተጨማሪም ማሻሻያዎቹ ለወርቃማ ቪዛ ያዢዎች የቤተሰብ አባላትን፣ የትዳር ጓደኛ፣ ልጆችን ጨምሮ የቤት ውስጥ ሰራተኞችን ስፖንሰር እንዲያደርጉ ያስችላቸዋል።
[@AddisZeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
በሁሉም ዩኒየኖችና ሸማቾች በኩል ከ 30 ሺ በላይ የእርድ እንስሳት ሊቀርቡ ነው፡፡
ለመጪው የፋሲካ እና ለኢድ አልፈጥር በዓላት በሸማች ሱቆችና ፤በዩኒየኖች በኩል የሚቀርቡ የእርድ እንስሳት ግዢን እየፈጸምኩ ነው ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ህብረት ስራ ኤጀንሲ ለኢትዮ ኤፍኤም አስታውቋል።
ከ 500 በላይ ለቅርጫ የሚሆኑ የእርድ እንስሳትን በአሁኑ ሰዓት ግዢያቸው የተፈፀመ ሲሆን በአጠቃላይ ለመጪው የፋሲካ እና ለኢድ አልፈጥር በዓላት ከ 3 ሺ በላይ የሉካንዳ ከብቶች ግዢ በአማራና በኦሮሚያ አካባቢዎች ላይ የግዢው ሂደት እየተፈፀመ መሆኑን በኤጀንሲው የግብይት ዳይሬክተር ወይዘሮ ደብሪቱ ለአለም ተናግረዋል፡፡
እንደ ፤ዱቄት ፤ዘይት፤በተለይ የድጎማ ዘይት፤በ148 የሸማች ህብረት ስራ ማህበራትና በሁሉም ዩኒየኖች በኩል እየገባ መሆኑን የነገሩን ወ/ሮ ደብሪቱ በአነስተኛ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰበ ክፍሎችን ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ለማገልገል ፤መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን እያስገባን ነው ብለዋል፡፡
እነዚህን ምርቶች የሚሰራጩት በተወሰኑ ቦታዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ቦታዎች ላይ ባዛሮችንም በማዘጋጀት፤ ለበአሉ አስፈላጊ የሚባሉ ምርቶቸን ለህረተሰቡ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ለማቅረብ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ለመጪው የፋሲካ እና ለኢድ አልፈጥር በዓላት በሸማች ሱቆችና ፤በዩኒየኖች በኩል የሚቀርቡ የእርድ እንስሳት ግዢን እየፈጸምኩ ነው ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ህብረት ስራ ኤጀንሲ ለኢትዮ ኤፍኤም አስታውቋል።
ከ 500 በላይ ለቅርጫ የሚሆኑ የእርድ እንስሳትን በአሁኑ ሰዓት ግዢያቸው የተፈፀመ ሲሆን በአጠቃላይ ለመጪው የፋሲካ እና ለኢድ አልፈጥር በዓላት ከ 3 ሺ በላይ የሉካንዳ ከብቶች ግዢ በአማራና በኦሮሚያ አካባቢዎች ላይ የግዢው ሂደት እየተፈፀመ መሆኑን በኤጀንሲው የግብይት ዳይሬክተር ወይዘሮ ደብሪቱ ለአለም ተናግረዋል፡፡
እንደ ፤ዱቄት ፤ዘይት፤በተለይ የድጎማ ዘይት፤በ148 የሸማች ህብረት ስራ ማህበራትና በሁሉም ዩኒየኖች በኩል እየገባ መሆኑን የነገሩን ወ/ሮ ደብሪቱ በአነስተኛ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰበ ክፍሎችን ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ለማገልገል ፤መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን እያስገባን ነው ብለዋል፡፡
እነዚህን ምርቶች የሚሰራጩት በተወሰኑ ቦታዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ቦታዎች ላይ ባዛሮችንም በማዘጋጀት፤ ለበአሉ አስፈላጊ የሚባሉ ምርቶቸን ለህረተሰቡ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ለማቅረብ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በሸዋሮቢት በተፈጠረው ግጭት የተነሳ ከ2ሺህ በላይ ሰዎች ተፈናቅለው ወደ ደብረሲና ከተማ መግባታቸው ተሰማ!
በትላንትናው እለት በሸዋሮቢት ከተማ በተከሰተው ግጭት ምክንያት የሸዋሮቢት አካባቢ ነዋሪዎች ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት አካባቢ ጀምሮ 2ሺህ የሚሆኑ ተፈናቃዮች ወደ ደብረሲና ከተማ መግባታቸዉን የከተማዋ ከንቲባ የሆኑት አቶ መክብብ ከበደ በተለይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡በአሁኑ ሰዓት ተፈናቃዮቹ በደብረሲና ከተማ በሚገኙ ሁለት ቤተክርስትያኖች ዉስጥ ተጠልለው እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
በትላንትናው ዕለት በሸዋሮቢት ከተማ ሞላሌ በሚባል በአካባቢ በሽብርተኛዉ ቡድን ኦነግ ሸኔ በከፈተዉ ጥቃት የተጎዱ ሰዎች ሲኖሩ እስካሁን ባለው መረጃ ሶስት ሰዎች መገደላቸዉን ገልጸዋል፡፡ሆኖም ግን የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል እና በዛሬው እለት የአማራ ልዩ ሃይል አባለት በሸዋሮቢት ከተማ መግባታቸውን እና ከተማውም መረጋጋቱን አቶ መክብብ ከበደ ጨምረውም ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡የልዩ ሀይሉ ወደ ሸዋሮቢት መግባቱን ተከትሎ ከተማዋ ሙሉ ለሙሉ ሰላም መሆኗ ስትረጋገጥ ተፈናቃዮችን ወደነበሩበት የመመለስ ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
[Bisrat FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በትላንትናው እለት በሸዋሮቢት ከተማ በተከሰተው ግጭት ምክንያት የሸዋሮቢት አካባቢ ነዋሪዎች ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት አካባቢ ጀምሮ 2ሺህ የሚሆኑ ተፈናቃዮች ወደ ደብረሲና ከተማ መግባታቸዉን የከተማዋ ከንቲባ የሆኑት አቶ መክብብ ከበደ በተለይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡በአሁኑ ሰዓት ተፈናቃዮቹ በደብረሲና ከተማ በሚገኙ ሁለት ቤተክርስትያኖች ዉስጥ ተጠልለው እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
በትላንትናው ዕለት በሸዋሮቢት ከተማ ሞላሌ በሚባል በአካባቢ በሽብርተኛዉ ቡድን ኦነግ ሸኔ በከፈተዉ ጥቃት የተጎዱ ሰዎች ሲኖሩ እስካሁን ባለው መረጃ ሶስት ሰዎች መገደላቸዉን ገልጸዋል፡፡ሆኖም ግን የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል እና በዛሬው እለት የአማራ ልዩ ሃይል አባለት በሸዋሮቢት ከተማ መግባታቸውን እና ከተማውም መረጋጋቱን አቶ መክብብ ከበደ ጨምረውም ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡የልዩ ሀይሉ ወደ ሸዋሮቢት መግባቱን ተከትሎ ከተማዋ ሙሉ ለሙሉ ሰላም መሆኗ ስትረጋገጥ ተፈናቃዮችን ወደነበሩበት የመመለስ ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
[Bisrat FM]
@YeneTube @FikerAssefa