YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የዩክሬን ኤምባሲ ሩሲያ ኢትዮጵያውያንን ለመመልመል ጥረት እያደረገች ነው አለ!

ሩሲያ አሁን ላይ ከኢትዮጵያ ወጣቶችን ለመመልመል ሙከራ እያደረገች ትገኛለችም ብሏል ኤምባሲው፡፡የኤምባሲው የሚሽን ሃላፊ አሌክሳንደር ከሰሞኑ አንድ የሩሲያን ወታደራዊ የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም) የለበሰ ሰው አዲስ አበባ ገብቷል ሲሉ ነው ለአል ዐይን የተናገሩት፡፡

ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ:

https://am.al-ain.com/article/ukraine-s-embassy-says-russia-is-trying-to-recruit-ethiopians

@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ከሚያዚያ 20 ጀምሮ ባሉ 10 የስራ ቀናት የ"ይዞታ ይረጋገጥልኝ" ማመልከቻ መቅረብ አለባቸው አለ፡፡

ኤጀንሲው ከሚያዚያ 5 እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ ባሉት አምስት ወራት በሁሉም ክፍለ ከተሞች በተመረጡ 25 ቀጠናዎች ውስጥ የሚገኙ 21,436 ይዞታዎችንና 40,625 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በመስክና በሰነድ አረጋግጨ በህጋዊ ካዳስተር ሲስተም ለመመዝገብ ተዘጋጅቻለሁ ብሏል።

የኤጀንሲው የይዞታ ማረጋገጥና አድራሻ ዝርጋታ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬከተሩ ጀማል ሀጅ በሰጡት መግለጫ ለይዞታ ማረጋገጥ የተመረጡ ወረዳ፣ ቀበሌና ሰፈሮች የትኞቹ እንደሆኑ በዝርዝር የሚያሳይ መረጃ ከሚያዚያ 5 እስከ ሚያዚያ 10 በወጣው የአዲስ ልሳን ጋዜጣ እትም፣ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችና በተቋሙ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ መለቀቁን ገልፀዋል።

ኤጀንሲው አረጋግጦ ላልመዘገበው ይዞታ ምንም ዓይነት ሕጋዊ ዋስትናና ከለላ የማይሰጥ ስለሆነም ባለይዞታዎች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ከሚያዚያ 20 ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ቅ/ጽ/ቤቶች በሚያወጡት ፕሮግራም መሰረት "የይዞታ ይረጋገጥልኝ" ማመልከቻ እንዲያቀርቡ ሲሉ አሳስበዋል።

ከዚህም ጋር ተያይዞ በተመረጡት 25 ቀጠናዎች ውስጥ ብቻ የመረጃ ልዩነት እንዳይፈጠር ሲባል ለአምስት ወራት ያክል ምንም አይነት የስም ዝውውር አይከናወንም ብለዋል።ኤጀንሲው ባለፉት 9 ዓመታት ለ4 ጊዜያት ባከናወንሁት የማረጋገጥ ስራ ከ288 ሺህ በላይ ይዞታዎችንና የጋራ መኖሪያ ቤቶችን አረጋግጨ በሕጋዊ ካዳስተር ሲስተም በመመዝገብ አገልግሎት እየሰጠሁ መሆኔ ይታወቅልኝ ብሏል።

[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
ጤና ይስጥልን የተወደዳችሁ ቤተሰቦች

መሪጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ከአባቶቻችን በተሰጠንና ባገኘነው ጥበብ መሰረት የተለያዩ የጤና መፍትሄወችን እንሰጣለን።

የምንሰጣቸው አገልግሎቶችም:-

- የኪንታሮት መድሀኒት በሚቀባ ታማሚው ወደቤቱ ወስዶ ሌላ ገላ ሳይነካ በመቀባት ሳያቆስል ስራወትን ሳያስተጓጉል በሽታውን ለይቶ በማውጣት ሁለተኛም እንዳይተካ አድርጎ ይፈውሳል።
-የሪህ መድሀኒት ወስዶ በመቀባት ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል።
- የአስም
_ የስንፈተ ወሲብ
_የአይነጥላ
_የገርጋሪ
_ለመፍትሄ ስራይ
እነዚህንና ሌሎችን አገልግሎቶችን እንሰጣለን
በሁሉም አገልግሎቶቻችን ውጤቱን እንዳዩ ክፍያ ይፈፅማሉ።
የሚፈልጉትን መድሀኒት ያሉበት ቦታ መላላክ ይቻላል።


አድርሻ:-
ባህር ዳር:- ቀበሌ 11
ለበለጠ መረጃ:-በ0917040506
0912718883
ይደውሉ።

መሪጌታ ጥበቡ ባህላዊ መድሀኒት መስጫ

ለጤናወ መፍትሄ👇

https://tttttt.me/meritibe
በአዳማ ከተማ መናሀሪያ ውስጥ የዝርፊያ ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 19 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በአዳማ ከተማ መስተዳድር ሉጎ ክፍለ ከተማ በፒኮክ መናሀሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የዝርፊያ ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የከተማው ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት እና ከፍተኛ ባለሙያ ረዳት ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

ለበዓል የተለያዩ ቦታዎች ላይ ለመሄድ በመናሀሪያ ውስጥ የሚገኙ ህብረተሰቡን ሲያጉላሉ የነበሩት 19 ተጠርጣሪዎች ናቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት፡፡ተጠርጣሪዎቹ ከታሪፍ በላይ በማስከፈል፣ተጓዦች ይዘው የሚንቀሳቀሱትን ንብረት በመንጠቅ እና በማታለል ፣ሰልፍ የሌለው ቦታ እንውሰዳችሁ በማለት መንገድ በማስቀየስ የያዙትን ንብረት በመዝረፍ ተግባር ተሰማርተዉ ቆይተዋል፡፡

ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ውለው የክስ መዝገባቸው በመጣራት ላይ እንደሚገኝ ተገልፆል፡፡በቀጣይ የበዓል ወቅት በመሆኑ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት እና አጠራጣሪ ነገሮች ሲመለክት አቅራቢያ በሚገኙ የፖሊስ ጣቢያ ሪፖርት ማድረግ እንዳለበት ረዳት ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

[ዳጉ ጆርናል]
@Yenetube @Fikerassefa
ተመድ በጸጥታው ምክር ቤት ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ያላቸውን ሀገራት ስልጣን ሊገድብ መሆኑን አስታወቀ፡፡

የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ በዚህ ጉዳይ ላይ የሚመክረው ከአሜሪካ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት ሲሆን ምክክሩ የሚካሄደው የተመድ አባል ሀገራት በተገኙበት መሆኑም ተገልጿል፡፡
አሜሪካ ቻይና፣ ሩሲያ፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ ሲሆኑ አምስቱም አባል አገራት በማንኛውም ጉዳይ ላይ ውሳኔዎችን የመሻር መብት አላቸው፡፡

የተመድ ጠቅላላ ጉባኤም የነዚህን ሀገራት ድምጽን በድምጽ የመሻር ስልጣን በተወሰነ ደረጃ መገደብ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ እንደሚመክር ይጠበቃል፡፡

ደምጽን በድምጽ የመሻር መብት ካላቸው አምስት ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሩሲያ በዩክሬን እያካሄደችው ያለው ጦርነት ለተመድ ጠቅላላ ጉባኤ መጠራት ምክንያት ሆኗልም ተብሏል፡፡

የዓለምን ጸጥታ ለመጠበቅ እንደተቋቋመ የሚነገረው የጸጥታው ምክር ቤትም የሩሲያን እና ዩክሬንን ጦርነት ሊያስቆም ባለመቻሉ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ያላት ሩሲያን ስልጣን ለመገደብ እንደሚወያይም ይጠበቃልም ተብሏል፡፡

የዛሬው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ አሜሪካንን ጨምሮ በ50 ሀገራት ድጋፍ የተጠራ ሲሆን ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ያላቸው አራቱ ቀሪ ሀገራት ድጋፍ እንዳልቸሩ የተመድ ሪፖርት አስታውቋል፡፡

ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተመሰረተው የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት አምስት ቋሚ እና ሁለት ዓመቱ የሚቀያየሩ 10 ቋሚ ያልሆኑ ሀገራትን ይዟል፡፡

Via Al Ain
@Yenetube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ምድባቸውን አውቀዋል!

በ2023 በአይቮሪኮስት አዘጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከደቂቃዎች በፊት ይፋ በተደረገው የምድብ ድልድል እጣ ማዉጣት ላይ ዋልያዎቹ ተጋጣሚዎቻቸውን አውቀዋል።

ዋልያዎቹ በምድብ አራት ከግብፅ ፣ ማላዊ እና ጊኒ ጋር መደልደላቸው ይፋ ተደርጓል። ከየምድቡ አንደኛ እና ሁለተኛ ሁነዉ የሚያጠናቅቁ ብሔራዊ ቡድኖች ወደ ኮትዲቯር የአፍሪካ ዋንጫ የሚያመሩ ይሆናል።

@YeneTube @FikerAssefa
የሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ የተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም አስጀመረ!

የሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ የተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም ማስጀመሩን አስታወቀ፡፡የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራሙ በዘጠኝ ወረዳዎች በ67 የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ 35 ሺህ 350 ተማሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል፡፡የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊ÷ የፕሮግራሙ መጀመር በምግብ እጥረት ምክንያት የሚታየውን የተማሪዎች ማቋረጥና የመድገም ምጣኔን ለመቀነስ እና ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ለመሳብ እንደሚጠቅም ተናግረዋል፡፡አያይዘውም የፕሮግራሙ መጀመር 600 ለሚሆኑ ወገኖች የስራ ዕድልን እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ለሩሲያ መዋጋት እንፈልጋለን ስላሉ በርካታ ኢትዮጵያውያን የሩስያ ኤምባሲ ምላሽ

አዲስ አበባ የሚገኘው የሩስያ ኤምባሲ ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ኤምባሲው «የሩስያ ጦር ሠራዊት ውስጥ ለመቀጠር ማንኛውንም ማመልከቻ አይቀበልም ሲል ጻፈ

በርካታ ኢትዮጵያውያን ለሩስያ ተሰልፈው ለመዋጋት ማመልከቻቸውን ይዘው እስከ ትናንት ድረስ አዲስ አበባ የሚገኘው የሩስያ ኤምባሲ መታየታቸውን ዶይቸ ቬለ (DW) በስፍራው ተገኝቶ ተመልክቷል።

ዩክሬን ውስጥ ጦርነት ለገጠመችው ሩሲያ «መዋጋት እንፈልጋለን» ያሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ለምዝገባ አዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ ፊት ለፊት እንደተሰለፉ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ ትናንት ተመልክቶ በቦታው የተሰለፉትን ኢትዮጵያውያን አነጋግሯቸውም ነበር።ዶይቸ ቬለ ካነጋገራቸው ወጣቶች መካከል አንዱ፦ «ከመከላከያ የተሰናበተበትን» መረጃ ይዞ በሥፍራው በመገኘት መመዝገቡን ገልጧል።

ለመመዝገብ ወደ ኤምባሲው አቅንቶ ሳይሳካለት እንደቀረ ለዶይቸ ቬለ የተናገረ አንድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሦስተኛ ዓመት የአካውንቲንግ ተማሪ ወጣት ከዚህ ቀደም በውትድርና ሞያ የሰለጠነበት ማስረጃ ስለሌለው ምዝገባው ሳይሳካለት በመቅረቱ እንደሚቆጨው ገልጧል።

አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የአዲስ አበባ የሩሲያ ኤምባሲ ባለስልጣናት ለሩሲያ የሚዋጉ ወታደሮችን ከኢትዮጵያ እየመለመሉ አለመሆኑን ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል። ሩስያ ለሚጓዙ ግን እንደ ሁልጊዜው የቪዛ አገልግሎት እንደሚሰጡ አክለዋል።

Via DW
@Yenetube @Fikerassefa
በ2014 የትምህርት ዘመን የክፍያ ጭማሪ ያደረጉ የግል ትምህርት ቤቶች በቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጭማሪ ማድረግ እንደማይችሉ ተነገረ፡፡

የአዲስ አበባ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2015 የትምህርት ዘመንን የክፍያ ጭማሪ አስመልክቶ ከትምህርት ቤቶቹ ጋር ባደረገው ምክክር በ2014 አ.ም ጭማሪ ያደረጉ ትምህርት ቤቶች በ2015 የትምህርት ዘመን ምንም አይንት ጭማሪ ማድረግ እንደማይችሉ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ህይወት ጉግሳ ተናገረዋል፡፡

ነገር ግን ላለፉት ሁለት እና ሶስት አመታት ጭማሪ ሳያደርጉ የቆዩ ትምህርት ቤቶች በሚያቀርቡት ፕሮፖዛል እና ከወላጅ ጋር በሚያደርጉት መግባባት መሰረት ጭማሪ ማድረግ እንደሚችሉም ተነግሯል፡፡ ከመደበኛ የአገልግሎት ክፍያ ውጭ በአይነትም ሆነ በገንዘብ ትምህርት ቤቶች ክፍያ መጠየቅ አይችሉም ያሉት የአዲስ አበባ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፍቅርተ አበራ ከዚህ ቀደም ያለ አግባብ ጭማሪ ያደረጉ ትምህርት ቤቶች እርምት እንዲወስዱ መደረጉንም ገልጸዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ቅርንጫፎቻቸውን ጨምሮ 2 ሺህ ገደማ የግል ትምህርት ቤቶች አሉ፡፡ እነዚህ ትምህርት ቤቶች 400ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎችን እንደሚያስተናግዱ የገለጸው የአዲስ አበባ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ይህም ከአጠቃላይ የአዲስ አበባ የተማሪ ሽፋን 43 በመቶውን ይይዛል፡፡

[AMN]
@YeneTube @FikerAssefa
የዊክሊክስ መስራች የሆነዉ ጁሊያን አሳንጅ ለአሜሪካ መንግስት ተላልፎ እንዲሰጥ የእንግሊዝ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡

አዉስትራሊያዊዉ ኤዲተር፣ ጸሀፊ እና አክቲቪስት ጁሊያን አሳንጅ እ.ኤ.አ በ2010 በአሜሪካ የጦር ሃይሎች መረጃ ተንታኝ ቼልሲማኒንግ አማካኝነት ባገኘዉ እና ባሰራጨዉ ሾልኮ የወጣ መረጃ ምክንያት አለምአቀፋዊ ትኩረትን አግኝቶ ነበር፡፡

የለንደን ፍርድ ቤት አሳንጅ ለአሜሪካ መንግስት ተላልፎ ይሰጥ የሚለዉን የርክክብ ትዕዛዝ ለእንግሊዝ መንግስት ከላከ በኋላ ፣ እዛዉ አሜሪካ ዉስጥ በስለላ ህግ እንደሚዳኝ ተገልጿል፡፡

በ 2010 ዊክሊክስ ባሳተመዉ በሺዎች የሚቆጠሩ ምስጢራዊ ፋይሎች እና ዲፕሎማቲክ ግንኙነቶች ላይ ያተኮረ ጽሁፍ አሳንጅ በአሜሪካ መንግስት በ18 የወንጀል ክሶች የሚፈለግ ሲሆን፣ በዚህ ጉዳይ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ እስከ 175 አመታት የሚደርስ የእስር ፍርድ እንደሚጠብቀዉም አልጄዚራ ዘግቧል።

Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በቅርስነት ከየተመዘገበው አንበሳ መድኃኒት ቤት በር ተሰብሮ ዕቃዎች እንዲወጡ ተደረገ!

(በዶይቸ ቨለ)

አዲስ አበባ ከተማ ፒያሳ የሚገኘው እድሜ ጠገቡ አንበሳ መድኃኒት ቤት ለረጅም ዐመታት ከነበረበትና በቅርስነት ከተመዘገበው ቤት ዛሬ ማለዳ ዕቃዎቹ እንዲወጡ ተደረገ። የመድኃኒት ቤቱ ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፀጋዬ ታደሰ በተለይም ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት፦ ዛሬ ማለዳ «ከ12 ሰዓት ጀምሮ የድርጅቱ የጥበቃ ሠራተኞች የመድኃኒት ቤቱ መግቢያ በር እየተሰበረ መሆኑን እንደነገሯቸውና ቦታው ላይ ሲደርሱ በር ተሰብሮ ዕቃዎች እየተጫኑ እንዳገኟቸው» ተናግረዋል።

ይህንን ድርጊት የፈፀሙት እነማን እንደሆኑ ተጠይቀው ሲመልሱ «ማን እንደሆኑ አናውቅም፣ ከክፍለ ከተማ ታዘን ነው የሚሉ ናቸው» ብለዋል። የአዲስ አበባ መስተዳድር ፖሊሶች ነበሩ የሚሉት ወይዘሮ ፀጋዬ ወደ ሥፍራው ስንደርስ «እኛም ለሰላሳ ደቂቃ እንዳንገባ ተከልክለን ቆይተን መታወቂያችን እየታየ ነው የገባነው» ብለዋል።

ዶይቼ ቬለ በሥፍራው ተገኝቶ ባደረገው ምልከታ ከመድኃኒት ቤቱ ውስጥ ዕቃዎች «አይሱዙ» ተብለው በሚጠሩት የጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ እየተጫኑ ተሽከርካሪዎቹም የጫኑትን እየያዙ ሽቅብ ወደ ጣይቱ ሆቴል በሚወስደው መንገድ ሲጓዙ ተመልክቷል።

መድኃኒት ቤቱ በሚገኝበት መስመር ቁልቁል ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ የሚወስደው መንገድ እስከ ረፋዱ 4 ሰዓት ለተሽከርካሪዎች ዝግ ሆኖ፣ አሽከርካሪዎች በዚያ መስመር ማለፍ እንደማይችሉ በፖሊሶች እየተገለፀላቸው ሲመለሱ እንደነበርም ታዝቧል። የዜናው ዘጋቢም የመድኃኒት ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ገብቶ ቀረፃ ለማድረግ ፈቃድ አላገኘም።

ዕቃው ወዴት እየተጫነ እየተወሰደ ነው? ያልናቸው ሥራ አስኪያጇ «የመድሃኒት ቤቱ ንብረት የሆኑ አነስተኛ ተሽከርካሪዎችን ተጠቅመን በየ ዘመድ ቤት እየጫንን ነው» የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ከመንግሥት በኩል የተዘጋጀ ምትክ ቤት ወይም ቦታ ስለመኖሩም ጠይቀናቸው «የለም» ብለው መልሰዋል።አክለው እንደነገሩንም የመድኃኒት ቤቱ ሠራተኞች ወደ ቤቱ ገብተው ዕቃዎችን በመጫን ሲያግዙ ውለዋል።

በጉዳዩ ላይ የተጠየቀው በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወይዘሮ አንክ ዶንኮህ ጉዳዩ እጅግ እንዳሳሰባቸው ገልፀው «ክስተቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ እና መዋዕለ ንዋይ ፈሰስ በሚያደረጉ የጀርመን ባለሀብቶች ላይ ትልቅ ተፅእኖ ይሮረዋል» ብለዋል።

አንበሳ መድኃኒት ቤት ላለፉት ስምንት ዐሥርት ዐመታት ለኢትዮጵያ ሕዝብ መድኃኒት የሚያቀርብ ጥንታዊ የጀርመን ድርጅት መሆኑንም ተናግረዋል።ፒያሳ የሚገኘዉ እና በቅርስነት የተመዘገበዉ የአንበሳ መድሐኒት ቤት ባለቤት ጀርመናዊዉ ካርል ሂልደብራንት በንጉሱ ዘመን አባታቸዉ ኩርት ሂልደብራንድት የመሰረቱትን መድሐኒት ቤት በማስቀጠል የቆየ መሆኑ ይታወቃል።ድርጅቱ የመድሃኒት ሽያጭ አገልግሎት፣ የቅመማ እና የሕክምና ቁሳቁስ ማስምጣት ላይ የተሰማራ ነው።

የቤቱ ባለቤት የሆነው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ «አንበሳ ፋርማሲ እና ኒዮን አዲስ የተባሉ ድርጅቶች በኪራይ ሲገለገሉበት የነበሩበት እና የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ንብረት የሆኑ ቤቶች፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቅርስነት ይዘታቸው ሳይቀየር፣ ባሉበት ምንም ዓይነት የቅርጽና የይዘት ለውጥ ሳይደርግባቸው በአካባቢው ከሚገነባው አዲስ ግንባታ ጋር ለአልሚው ባለሀብት እንዲተላለፉ ተደርጓል» ብሏል።

በቅርሶቹ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደማይደርስባቸው በኮርፖሬሽኑ እና በከተማ አስተዳደሩ መካከል ሥምምነት ላይ መደረሱንም ዐስታውቋል።«ቅርሶችን በመጠበቅ እና በመንከባከብ፤ ቅርስ ጥበቃ እና ልማት ሚዛኑን አስጠብቆ እንዲሔድ ማድረግ ሌላኛው ከድህነት መውጫ መንገድ ሊሆን ይገባል» ያለው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን «በእርጅና ምክንያት የተጎዱ አካባቢዎችን እና ቤቶችን ደግሞ ለኹላችን ጥቅምና እድገት በሚያስገኝ መልኩ ማልማትም ተገቢ ነው» ብሎ እንደሚያምንም ዐስታውቆ ነበር።

@YeneTube @FikerAssefa
ጤና ይስጥልን የተወደዳችሁ ቤተሰቦች

መሪጌታ ጥበቡ የባህል ህክምና መስጫ ከአባቶቻችን በተሰጠንና ባገኘነው ጥበብ መሰረት የተለያዩ የጤና መፍትሄወችን እንሰጣለን።

የምንሰጣቸው አገልግሎቶችም:-

- የኪንታሮት መድሀኒት በሚቀባ ታማሚው ወደቤቱ ወስዶ ሌላ ገላ ሳይነካ በመቀባት ሳያቆስል ስራወትን ሳያስተጓጉል በሽታውን ለይቶ በማውጣት ሁለተኛም እንዳይተካ አድርጎ ይፈውሳል።
-የሪህ መድሀኒት ወስዶ በመቀባት ዘላቂ ፈውስ ይሰጣል።
- የአስም
_ የስንፈተ ወሲብ
_የአይነጥላ
_የገርጋሪ
_ለመፍትሄ ስራይ
እነዚህንና ሌሎችን አገልግሎቶችን እንሰጣለን
በሁሉም አገልግሎቶቻችን ውጤቱን እንዳዩ ክፍያ ይፈፅማሉ።
የሚፈልጉትን መድሀኒት ያሉበት ቦታ መላላክ ይቻላል።


አድርሻ:-
ባህር ዳር:- ቀበሌ 11
ለበለጠ መረጃ:-በ0917040506
0912718883
ይደውሉ።

መሪጌታ ጥበቡ ባህላዊ መድሀኒት መስጫ

ለጤናወ መፍትሄ👇

https://tttttt.me/meritibe
የሱዳን ተቃዋሚዎች በተመድ እና በአፍሪካ ህብረት የቀረበውን የ‘እናደራድራችሁ’ ጥያቄ ሳይቀበሉ ቀሩ!

ተቃዋሚዎቹ ከድርድሩ በፊት ጦሩ ስልጣን እንዲያስረክብ ጠይቀዋል

የሱዳን ተቃዋሚዎች በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በአፍሪካ ህብረት የቀረበላቸውን የየ‘እናደራድራችሁ’ ጥያቄ ሳይቀበሉ ቀሩ፡፡
ተቃዋሚዎቹ ከድርድሩ በፊት ሊተገበሩ ይገባል ያሏቸውን ቅድመ ሁኔታዎች አስቀምጠዋል፡፡

ከቅደመ ሁኔታዎቹ አንዱ በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ይመራ የነበረውን የሲቪሊያን አስተዳደር ከሽግግር መንግስቱ አስወግዶ ስልጣን የያዘው የሃገሪቱ ጦር ስልጣኑን ያስረክብ የሚል ነው፡፡

በሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን የሚመራው የሃገሪቱ ጦር ባሳለፍነው ወርሃ ጥቅምት መጨረሻ "የእርምት ነው" በሚል በወሰደው እርምጃ የሃምዶክን አስተዳደር በአዲስ መተካቱ ይታወሳል፡፡

Via Al ain
@Yenetube @Fikerassefa
የሳተላይ ምስሎች ታጣቂዎች ዶግ አመድ ያደረጓትን የኦሮሚያ አንስተኛ ከተማ አሳዩ!

ሰኞ ጥር 16/2014 ያጋጠመው ክስተት የአንዲት መንደር ነዋሪ አርሶ አደሮችን ሕይወት እስከ ወዲያኛው የቀየረ ክስተት ነበር።በዕለቱ በምዕራብ ኦሮሚያ በምትገኘው እና ፊጤ በቆ ወደ ምትሰኘው መንደር ታጣቂዎች ዘልቀው ገብተው፤ ተኩስ ከፈቱ፤ መኖሪያ ቤቶች ላይ እሳት ለኮሱ፣ የሰው ሕይወት ቀጠፉ።ከጥቃቱ ያመለጡ የመንደሯ ነዋሪዎች ሕይወታቸውን ለማዳን እግሬ አውጪኝ ብለው ቀያቸውን ጥለው ተሰደዱ። ይህ ዘገባ እስከ ተጠናከረበት ጊዜ ድረስ የፊጤ በቆ ነዋሪዎች ወደ መንደሯ አልተመለሱም።

ፊጤ በቆ የምትገኘው በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ሊሙ ገሊላ ወረዳ ውስጥ ነው።ቢቢሲ የሳተላይት ምስሎችን በመጠቀም፣ በአካባቢው የተነሱ ፎቶ እና ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በመመርመር እንዲሁም ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ እና ቤታቸው የተቃጠለባቸው ሰዎችን በማነጋገር በመንደሯ የተፈጠረው ምን እንደሆነ ማረጋገጥ ችሏል።በተለያዩ የወለጋ ዞኖች ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎች በተደጋጋሚ ለሚከሰተው ግድያ፣ ማፈናቀል፣ መኖሪያ ቤት እና እህል የማቃጠል ተግባራት ሶስት ቡድኖችን ተጠያቂ ያደርጋሉ።

እራሱን የኦሮሞ ነጻነት ጦር (መንግሥት ሸኔ) የሚለው ቡድን፣ የአማራ ታጣቂዎችን እንዲሁም የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ናቸው በነዋሪዎች በጥፋት የሚወነጀሉት።ለደኅንነታቸው ሲባል ስማቸውን እንዳይጠቀስ የጠየቁ የ54 ዓመት አዛውንት ተወልደው ካደጉባት መንደር ተፈናቅለው ከስምንት የቤተሰብ አባላታቸው ጋር ተደብቀው ይገኛሉ።

"ከባድ መሳሪያዎች የታጠቁ ናቸው። የግንቦት 7 የሚባለውን ባንዲራ ነው የሚይዙት። ዱላ ይይዛሉ እንዲሁም ባንዲራውን ግንባራቸው ላይ አስረው ነው የሚንቀሳቀሱት።"

በመንደሯ የሆነውን አይቻለሁ የሚሉት እኚህ አዛውንት "የአማራ ታጣቂዎች ናቸው" የሚሏቸው ቡድኖች በመንደሯ ላይ ሰኞ ጥር 16/2014 አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የጀመሩት ጥቃት እስከ ምሽት 3 ሰዓት መዝለቁን ያስረዳሉ።

"እስከ ሶስት ሰዓት ድረስ እዛው ነበሩ። ሲዘፍኑ ነበር። የሚያቃጥሉትን አቃጥለው የሚወስዱትን ወስደው [ሄዱ] . . . የተመቻቸውን ነው የወሰዱት፤ የቀረውን ደግሞ በመጥረቢያ ነው የፈለጡት።" በማለት የነበረውን ሁኔታ አስረድተዋል።

እኚህ አዛውንት መኖሪያ ቤታቸው መቃጠሉን እና በገንዘብ "ይህ ነው" ብለው መገመት ያልቻሉት ንብረት እንደወደመባቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል።

"ከሶስት ሄክታር መሬት ተሰብስቦ የነበረው በቆሎ እዛው ተቃጥሏል። ሞተር ወስደውብኛል። ቤቴ ከነ ሙሉ ንብረቱ ተቃጥሏል። ሕይወታችን ብቻ ነው የተረፈው. . . ።" ይላሉ

ዘገባው የቢቢሲ ነው ሙሉውን ለማንበብ:

https://www.bbc.com/amharic/news-61153195?at_custom2=facebook_page&at_medium=custom7&at_custom3=BBC+News+Amharic&at_campaign=64&at_custom4=BA3DBCAA-C132-11EC-AA64-17B096E8478F&at_custom1=%5Bpost+type%5D

@YeneTube @FikerAssefa
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ በእስር ላይ የነበሩት አመራሮቹና ልዑካን ፣ ከእስር መፈታታቸው አሳውቋል።

በአሁን ሰዓት አመራሮቹ እና ልዑካኑ ጉዟቸውን ለማድረግ ወደ አውሮፕላን ማረፊያ ሄደዋል ሲል አሳውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
በጦርነቱ ጉዳት ከደረሰባቸው 42 ሆስፒታሎቹ መካከል 36 ወደ ስራ ገቡ!

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ የህወኃት ቡድን በተቆጣጠራቸው የአማራ እና አፋር ክልሎች የሚገኙ ከሶስት ሺ በላይ የጤና ተቋማት ውድመት እና ዝርፊያ እንደደረሰባቸው ተናግረዋል። ውድመት ከደረሰባቸው የጤና ተቋማት ውስጥ 42ቱ ሆስፒታሎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 532 ያህል ጤና ጣቢያዎችና የጤና ኬላዎች ናቸው።

ጉዳት ከደረሰባቸው 42 ሆስፒታሎች መካከል 40 የሚሆኑት በአማራ ክልል ሲሆኑ ቀሪ ሁለት ሆስፒታሎች በአፋር ክልል ናቸው።የጤና ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች እና በአዲስ አበባ እና ሌሎች ክልሎች ከሚገኙ ሆስፒታሎች በተደረገ ድጋፍ እና ጥራት 36 ሆስፒታሎች ወደ ስራ እንዲገቡ እና አገልግሎት እንዲሰጡ መደረጉን ዶክተር ተሾመ ጨምረው ተናግረዋል።

ዳግም ወደስራ ከገቡት 36 ሆስፒታሎች ውስጥ 35ቱ በአማራ ክልል ሲሆን አንድ ሆስፒታል ደግሞ በአፋር ሲሆን በአማራ ክልል አምስት በአፋር አንድ ሆስፒታል ባለው የፀጥታ ችግር ወደ ስራ ማስገባት አለመቻሉን ዶክተር ተሾመ አንስተዋል። 26 የሚሆኑት ሆስፒታሎች አገልግሎት እንዲሰጡ የተደረገው በአዲስ አበባ እና ሌሎች ክልሎች ከሚገኙ ሆስፒታሎች በተደረገ ድጋፋ ሲሆን አስሩ ሆስፒታሎች በጤና ሚኒስቴር አጋር አካላትን በማስተባበር የህክምና ግብዓት በማቅረብ እና ጥገና በማድረግ ወደስራ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡

[ዳጉ ጆርናል/Bisrat FM]
@YeneTube @FikerAssefa
የጸሎተ ሐሙስ የተለያዩ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓቶች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት እና ገዳማት እየተካሄደ ይገኛል።

በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንም ከማለዳው አንስቶ የተለያዩ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓቶች እየተከናወኑ ነው።

በመርሐ-ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስን ጨምሮ ብፁዓን ሊቃነ ጻጻሳት፣ ካህናት እና ምዕመናን ተገኝተዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
"ትክክለኛው ተወካይ ወደ መድረኩ እንዲመጣ እንሰራለን" - አገራዊ የምክክር ኮሚሽን

11 ኮሚሽነሮች ያሉት የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና ሀላፊዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።በመድረኩ ኮሚሽኑ የውይይት ሂደቱ ካቀፋቸው አራት ምዕራፎች (ቅድመ-ዝግጅት፣ ዝግጅት፣ ሂደትና አተገባበር) መካከል በቀዳሚው ሰራሁ ያላቸውን ተግባራት አብራርቷል።

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ " የኮሚሽኑ አባላት እርስ በእርስ ትውውቅ እንዲያደርጉ፣ የምክክር ፅንሰ ሀሳብ ላይ ውይይት በማድረግ ኮሚሽነሮቹ ተቀራራቢ አረዳድ እንዲኖራቸው ተጥሯል።" ብለዋል።በዚሁ ቀዳሚ ምዕራፍ "አመቺ የስራ ከባቢን መፍጠር፣ ሎጂስቲክ ማሟላት" ሌላኛው የተከናወነ ስራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ከመድረኩ " ኮሚሽኑ የታችኛው የህብረተሰብ ክፍልን የሚያገኝበት መንገድ እንዴት ያለ ነው?፤ በቀደመው የግንኙነት ሰንሰለት ከሆነ "በካድሬዎች ሊጠለፍ ይችላል" የሚል አስተያየት ተሰንዝሯል።

ለዚህ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ዋና ኮሚሽነሩ "ትክክለኛውን ተወካይ ለማግኘት ኮሚሽኑ የራሱን "ሜካኒዝም" ይከተላል፤ ትክክለኛውን ወኪል ለማግኘትም እንሰራለን።" ብለዋል።ኮሚሽኑ ከመገናኛ ብዙሃን ሃላፊና ባለሙያዎች ጋር ከመምከሩ አስቀድሞ ከሀይማኖት አባቶችና ሀገር ሽማግሌዎች ጋር መወያየቱም ተነግሯል።

[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም ባንክ በጦርነቱ የተከሰተው የምግብ ቀውስ 'ሰብአዊ ጥፋት' ያስከትላል ሲል አስጠነቀቀ!

ሩሲያ ዩክሬንን መውረሯን ተከትሎ በተከሰተው የምግብ ቀውስ ዓለም "የሰብዓዊ ጥፋት" እያጋጠማት ነው ሲሉ የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማልፓስ ገለጹ።በዓለም አቀፍ ደረጃ ድህነትን ለማቃለል የተቋቋመውን ተቋም የሚመሩት ማልፓስ ከቢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ቀውሱ ከቀጠለ የምግብ ዋጋ ንረት በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ወደ ድህነት እንደሚገፋና የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እንደሚያስከትል አስጠንቅቀዋል።

"ይህ የሰብዓዊ ጥፋት ነው። የተመጣጠነ ምግብ እየቀነሰ ይሄዳል። ምንም ማድረግ ለማይችሉ መንግስታት የፖለቲካ ፈተና ይሆናል። መንስኤ ባይሆንም የዋጋ መናር ያጋጥማቸዋል" ሲሉ ተናግረዋል።

የዓለም ባንክ የምግብ ዋጋ በ37 በመቶ ሊጨምር እንደሚችል ግምቱን አስቀምጧል።፣ ይህም "ለድሆች ከፍተኛ የሚባል" ሲሆን "ትንሽ እንዲመገቡ እና እንደ ትምህርት ቤት ላሉት የሚኖራቸውን ወጪ ያሳንሳል። በእውነቱ ይህ ፍትሃዊ ያልሆነ ቀውስ ነው። በጣም ድሃ የሆኑት ላይ የበለጠ ጫናው ያርፋል። ይህ በኮቪድ ወቅት ተመሳሳይ ነበር ።

ተጨማሪ ለማንበብ:

https://www.bbc.com/amharic/news-61172475

@YeneTube @FikerAssega
የሩሲያ ጦር ከቧት የነበረችውን የዩክሬኗን ማሪዎፖል ከተማ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ!

የሩሲያ ጦር የማሪዎፖልን ከተማ ዶምባስ ግዛት ለመቀንቀሳቀስ የሚያችል ስትራቴጅካዊ ቦታ መሆኑን ሩሲያ ስትገልጽ ቆይታለች፡፡የሩሲያ መከላከያ አሁንም በማሪዎፖል የመሸጉ የዩክሬን ወታደሮች መኖራቸውን ገልጿል፡፡

[Alain]
@YeneTube @FikerAssefa