YeneTube
117K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዕሮብ እና አርብን የቅሬታ የመቀበያ ዕለት እንዲሆን ወሰነ!

የመዲናዋ አስተዳደር ዕሮብ እና አርብን የቅሬታ የመቀበያ ዕለት እንዲሆን መወሰኑን አስታወቀ።ውሳኔው ከከተማ እስከ ወረዳ ድረስ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ለሚገኙ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች የነዳጅ ድጎማ ሊደረግላቸው ነው!

በአዲስ አበባ ለሚገኙ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች የነዳጅ ድጎማ ሊደረግላቸው መሆኑ ተገለፀ።የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ በላከው መግለጫ፤ በከተማው የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለሚሰጡ ተሸከርካሪዎች የነዳጅ ድጎማ ማድረግ በሚያስችል ረቂቅ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሂዷል።

የድጎማ ስርዓቱ በአግባቡ ስራ ላይ መዋሉ ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ የተሻለ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ቢሮው ገልጿል።በድጎማ ስርዓቱ GPS እንዲገጠም መደረጉም የትራንስፖርት ስምሪቱን በቴክኖሎጂ በማስተሳሰር ቁጥጥሩን ለማሳለጥ ዕድል ይፈጥራል።ድጎማው ከሀምሌ 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆንም የቢሮው መግለጫው ያስረዳል።

ሙሉ ዘገባው: https://am.al-ain.com/article/addis-ababa-to-subsidize-oil-price-for-public-transport

@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
#በራስ_መተማመን
4ተኛው ዕትም በገበያ ላይ

ይህ A Guide to confident Living የተባለው መጽሐፍ በራስ መተማመንን እርካታን መቀዳጀት እንችል ዘንድ ያስችላል።

ቀላል ለማንም ሰው ሊገባ በሚችል ቋንቋ የተጠቀመው
ዶ/ር ፒል በሕይወታችን ትልቅ መታደስ ማግኘት እንችል ዘንድ አዲስ የሆነ የኃይል መንገድን ይጠቁመናል።

ከሚለግሰን ምክሮች መካከል እንደ፤

* ውስጣዊኃ ይሎቻችንን ነጻ ማውጣት
* ችግሮቻችንን አውጥተን መናገር
* የበታችነት ኮምፕሌክሳችንን መውደድ
* ለሕይወታችን የተረጋጋ ማዕከልን ማግኘት
* የጸሎትን ኃይል መለማመድ
* ከፍርሃትና ሃዘን ነፃነትን ማግኘት
* የትዳር፣ ሙያዊ እና ግለሰባዊ ደስታን ማግኘት ያሉት ይጠቀሳሉ።

ኖርማን ቪንሰንት ፒል በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ሽያጭ ያስገኘለት The Power of Positive Thinkingን ጨምሮ የ46 ያህል መጽሐፎች ደራሲ ነው።

በኖረበት ዘመን ትልቅ ከተባሉ የሃይማኖት ሰዎች አንዱ የነበረው ዶ/ር ፒል ምንም እንኳ ሕይወቱ ቢያልፍም በስሙ በተከፈተው Peal Center For Chrisitian Living በተባለው ፋውንዴሽን አማካይነት ውርሱ ለመላው ዓለም እየተዳረሰ ይገኛል።

አሳታሚና አከፋፋይ- ዘላለም
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኙታል።

*
ቤተሰብ ይሁኑ
Facebook- https://www.facebook.com/booklandbook/

Telegram-
https://tttttt.me/teklu_tilahun
በ3 የቀድሞ የሜቴክ የሥራ ኃላፊዎች ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላለፈ!

ብርጋዴል ጄነራል ጠና ቁሩንዲን ጨምሮ በ3 የቀድሞ የሜቴክ የሥራ ኃላፊዎች ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላለፈ።ተከሳሾች ክስ ተመስረቶባቸው ጥፋተኛ የተባሉት ስልጣንን ያላግባብ በመገልገል፣ የመንግሥት ሥራን በማያመች አኳኋን በመምራት እና የሕዝብ እና የመንግሥትን ጥቅም የጎዳ ተግባር በመፈጸም የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32 (1) (ሀ)፣ 33 እና 407 (1) (ሀ)፣ (2)፣ (3)፣ 411 (1) (ሀ)፣ (ሐ) እና (3) ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው ነው።

ተከሳሾቹ የቀድሞው የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የኮርፖሬት ሲቪል ምርቶች ኦፕሬሽን ኃላፊ የነበሩት ብ/ጄነራል ጠና ቁሩንዲ߹ የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት ሌ/ኮሎኔል አሰፋ ዮሃንስ እና የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ፓወር ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ክንደያ ግርማይ እንዲሁም በቻይና ሕዝባዊት ሪፐብሊክ ቲምስ ኢንተርናሽናል (ሆ.ኮ) ኩባ. ሊሚትድ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ የነበሩትና (ያልተያዙት) ሚ/ር ዩዋን ሃን ናቸው።

Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስምንት ቢሊዮን ብር ሊያስገነባቸው የነበሩ ተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ በፍርድ ቤት ታገደ!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስምንት ቢሊዮን ብር በጀት ያስጀመረውና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት ወርቁ ሠፈር ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ሊያከናውነው የነበረው የአምስት ሺሕ ተገጣጣሚ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ሕንፃዎች ግንባታ፣ በፍርድ ቤት ዕግድ እንዲቆም መደረጉ ተገለጸ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ በ21.8 ሔክታር መሬት ላይ የተገጣጣሚ ቤቶች ግንባታ ለማስጀመር ጥር 4 ቀን 2014 ዓ.ም. መሠረተ ድንጋይ ቢያስቀምጥም፣ መሬቱ የባለቤትነት ጥያቄ ተነስቶበት ፍርድ ቤት ዕግድ በማውጣቱ ግንባታው እንዲቆም መደረጉን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮና የቤቶቹን ግንባታ የሚያካሂደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን አስታውቀዋል፡፡

የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምርያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጥንፉ ሙጬ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ግንባታው ይፋ ከተደረ በኋላ ኮርፖሬሽኑ 291 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የተገጣጣሚ ሕንፃ አካላት ኮንክሪትና ሌሎች ተያያዥ ምርቶችን ወደ ቦታው አስገብቷል፡፡ በግንባታ ቦታው ላይ አሥር ሚሊዮን ብር የሚያወጣ አፈር ጠረጋና ምንጣሮ ሥራ መካሄዱንም አስረድተዋል፡፡

ይሁንና የመሬቱ ባለቤትነት ይገባኛል ያለ ግለሰብ ጥያቄ በማንሳቱ፣ ኮርፖሬሽኑ ሥራ በጀመረ በቀናት ውስጥ ዕግድ ወጥቶበታል፡፡ ኮርፖሬሽኑ እግዱ ቢወጣም የግንባታ ሥራውን እንደቀጠለ ያስረዱት አቶ ጥንፉ፣ ለሁለተኛ ጊዜ ዕግድ ከመጣ በኋላ ግን መሬቱ ላይ ያለው ሥራ እንዲቆም መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ተጨማሪ ለማንበብ: http://bit.ly/3x8hgu4

@YeneTube @FikerAssefa
አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂዩማን ራይትስ ዎች ዛሬ በጋራ ያወጡትን ሪፖርት የኢትዮጵያ መንግስት "በጥንቃቄ እየመረመርኩት ነው" አለ!

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ማምሻውን ያወጣው መግለጫ "ሪፖርቱ በሰብአዊ መብት ላይ የሚነሱ ከባድ ጥሰቶች ከሚባሉት በተጨማሪ በሀገሪቱ ውስጥ የተከሰቱትንና በጥንቃቄ መታየት የሚገባቸውን የፖለቲካ ለውጦች፣ ሰላምና ደህንነት፣ የውስጥ ወሰን ጉዳዮችን ያካተተ መሆኑንም መገንዘብ ያስፈልጋል" ያለ ሲሆን "የዘር ማጽዳት፣ የጦር ወንጀል እና በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ክስንም ያቀረበ ሪፖርት ነው። የኢትዮጵያ መንግስት የሰብአዊ መብት ጥሰት የፈፀሙትን ሁሉ ተጠያቂ ለማድረግ ቁርጠኛ ነው" ብሏል።

@YeneTube @FikerAssefa
ከሳዑዲ አረቢያ አንድ ሺህ 103 ዜጎች ወደ ሀገራቸው ዛሬ ተመለሱ!

በሳዑዲ አረቢያ በሪያድ እና ጅዳ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎቻችን ወደ ሃገር ቤት የመመለሱ ተግባር ቀጥሎ ፤ በዛሬው ዕለት ከሪያድ 1103 ዜጎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።በሳምንት ለሶስት ቀናት በቀን ሶስት ጊዜ በሚደረግ በረራ ዜጎችን የመመለሱ ስራ እንደቀጠለ ነው።

ተመላሾች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰራተኞችና ሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ከመጋቢት 21 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎች የመመለሱ ሥራ እየተከናወነ ሲሆን እስካሁን የመጡት ሁሉም ተመላሾች ከአዲስ አበባ ወደቀያቸው እንዲሄዱ ተደርገዋል።

የጤና እክል የገጥማቸው በየአካባቢው ባሉ የሕክምና ተቋማት ህክምና እዲያገኙ በመደረግ ላይ ነው። ክልሎችም ተመላሽ ዜጎችን በመቀበል ረገድ ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በቅንጅት እየሰሩ ነው። በመኖሪያ አካባቢያቸው መልሶ ለማቋቋም የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

በሳኡዲ አረቢያ እስር ቤቶች እና ማዕከላት ውስጥ ያሉ ዜጎችን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ 16 መንግሰታዊ ተቋማትን በአባልነት ያቀፈና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰብሳቢነት የሚመራ ብሔራዊ ኮሚቴ ተቋቋሙ ስራውን በመፈፀም ላይ እንደሆነ የውጭ ጉዳ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መረጃ ያመለክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
👍1
#ችግሮችን_እንደ_ካርታ_ጨዋታ

#አሁኑኑ_አደርገዋለሁ መጽሐፍ በገበያ ላይ

ትክክለኛ አስተሳሰብ ያለው ሰው ችግር አያስጨንቀውም፡፡ ምክንያቱም በቀላሉ መፍትሄ ከመሻቱም በዘለለ ለሕይወቱ ጣዕም ይጨምርለታል፡፡ ካርታ በምትጫወትበት ወቅት የማይረቡ ካርታዎች ቢደርሱህ እድል ከእኔ ጋር አይደለችም ብለህ በራስህ ማዘን አትጀምርም፡፡

አዎ አታስብም!

እንደ ፈተና አይተኸው ካርታዎቹን በሚገባቸው ቦታ እየሰካካህ ለማሸነፍ ትጥራለህ፡፡ ስታሸንፍ ከፍተኛ ደስታ ይሰማሃል፡፡ችግሮችን በድል ትወጣ ዘንድ የዚህ ዓይነት ብሩህ አመለካከት ይኑርህ፡፡

ለራስህም ይህን በል፦

"ከራሴም ይሁን ከዓለም ጋር ጥሩ ግንኙነት አለኝ፡፡ የሚያጋጥሙኝ ችግሮች ያለኝን እውቀትና ኃይል ስለሚፈትኑት መጥፎ አይደሉም፡፡ በተገቢው ጊዜ ተገቢ ነገር ለመስራት እንቀሳቀሳለሁ፡፡"

አዎ ይህንንም አሁኑኑ ማድረግ ትችላለህ!

#አሁኑኑ_አደርገዋለሁ መጽሐፍ

በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኙታል፡፡

*
ቤተሰብ ይሁኑ
Telegram-
https://tttttt.me/teklu_tilahun
https://tttttt.me/sabinavisa1

😳በድጋሚ የወጣ የስራ ማስታወቂያ 🙄

🇬🇧 የስራ ጉዞ ወደ #UK 🇬🇧

👉 የሚሰራበት አገር - UK
👉 የስራው አይነት - Vegetables and fruits picker
👉 የስራ ቀናት - 5 - 6 ቀናት/ week
👉 የስራ ሰዓት - ከ8 - 10 hr/day
40/60 working hrs per week
👉 ደሞዝ - £8.91 per hr + bonuses for OT
👉 ፆታ - ወንድ እና ሴት
👉 ዕድሜ - 20 እስከ 45
👉 OT - ይቻላል
👉 ፕሮሰሱ የሚፈጀው ግዜ 2 _3 ወር

Accommodation is provided by the employer (~£55 per week)

#Requirements
👉 Passport
👉 Photo

#Urgent
የምንፈልገው የአመልካች ብዛት 20 ሰው ብቻ::

Contact:
@Sabinavisa
+251118683939
0936363639
0936363680
info@sabinaadvisor.com

https://tttttt.me/sabinaadvisor
👉ሴት እህቶቻችንን ዋጋችን ከ 300 እስከ 1,000 ብር ብቻ!!!

😱 3 ልብስ ለገዛ 1 በነፃ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ልዩ ቅናሽ።

ሰላም ውድ ደንበኞቻችን ጥራት ያላቸውን የሴት አልባሳት እና ጫማዎችን እጅግ በተመጣጣኝ ዋጋ ይዘን ቀርበናል።

👉የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ምርጥ ምርጥ ልብሶችን በቅናሽ ዋጋ ይግዙ።

https://tttttt.me/CITYFASHION321

📞ስ.ቁ
0975798585

አድራሻ: ከ 22 ወደ ቦሌ መድሃኒአለም (ኤድና ሞል) በሚወስደዉ መንገድ(New day) ኒው ዴይ ሆቴል አጠገብ ባማ ህንፃ 1ኛ ፎቅ ላይ ሱቅ ቁጥር 108 ላይ ያገኙናል።
በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የ30 ቀን ዕቅድ መሰረት በሸኔ ታጣቂዎች ላይ የተቀናጀና ጠንካራ እርምጃ እየተወሰደ ነው ተባለ!

የክልሉን ሰላም በማስፈን ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ለመመለስ በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሰላሳ ቀን ዕቅድ መሰረት በሸኔ ታጣቂዎች ላይ የተቀናጀና ጠንካራ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል የፀጥታና አስተዳደር ምክትል ቢሮ ኃላፊ ኮሎኔል አበበ ገረሱ አስታወቁ፡፡

ኮሎኔል አበበ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ሰሞኑን በጨፌ ጉባዔ ላይ ሽብር ቡድኑን በአንድ ወር ውስጥ አደብ ለማስገዛት ጠንካራ እርምጃ እንዲወሰድ ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት በክልሉ አራት ወሳኝ አካባቢዎች ላይ ጠንካራና የተቀናጀ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል ብለዋል፡፡

እንደ ምክትል ቢሮው ኃላፊ ገለጻ፤ ሽብር ቡድኑ በስፋት በመንቀሳቀስ በንጹሃን ዜጎች ላይ ሞትና በደል ያደረሰባቸው በወለጋ፣ በጉጂ፣ በምዕራብና ሰሜን ሸዋ አካባቢዎች በአሁኑ ጊዜ የክልሉና የፌዴራል የፀጥታ አካላት በሽብር ቡድኑ ላይ የተቀናጀ እርምጃ እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡

በተጀመረው ኦፕሬሽን በርካታ የሽብር ቡድኑ አባላት ተደምስሰዋል፡፡ የተመዘገቡ ድሎች በዝርዝር ለህዝብ ይፋ ይደረጋሉ ሲሉም ኮሎኔል አበበ ተናግረዋል፡፡

ሸኔ ከህወሓት ጋር በመሆን ኦሮሚያን የብጥብጥ ቀጠና በማድረግ አገር ለማፍረስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ የተናገሩት ኮሎኔል አበበ፤ ኦሮሚያ ብሎም ኢትዮጵያን ማፍረስ ከምናባዊ እሳቤና ከቀን ቅዥት ስሌት በዘለለ መቼም ቢሆን ሊሳካ የማይችል የሴረኞች ህልም ነው ብለዋል።

በቡድኑ ላይ እርምጃ እየተወሰዱ ባሉባቸው የሚገኙ የክልሉ ነዋሪዎች ከጸጥታ አካላት ጎን መሰለፋቸውን የጠቀሱት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ ስንቅ በማቀበል፣ ጥቆማ በመስጠትና ቀጥታ እርምጃ በመውሰድ ህዝቡ እያደረገ ያለው ተሳትፎ የሚደነቅና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት በጎ ተግባር መሆኑን አስገንዝበዋል።
እንደርሳቸው ማብራሪያ፤ የክልሉ መንግሥት ሽብተኝነትና ጽንፈኝነት ለክልሉም ሆነ ለአገር ህልውና አደገኛ መሆኑን በጽኑ ያምናል። በአሸባሪው ሸኔ ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ሲጠናቀቅ በሌሎች አካባቢዎች ያለውን የሰላም ችግር ለመፍታት በሚደረገው እንቅስቃሴ ክልሉ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣም አስታውቀዋል።

በአንዳንድ ክልሎች የአገር ሰላምና የህዝቦች አንድነት አደጋ ላይ የሚጥሉ የሽብር ተግባርና አስተሳሰብ በስፋት እየተስዋለ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሌሎች ክልሎችም ሰላም ለማስፈን ጠንካራ እርምጃ እንደሚወስዱ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

የኦሮሞ ህዝብ ከሌሎች ወንድም ህዝቦች ጋር በመሆን አገር የመገንባት ታሪክ እንጂ ጽንፈኛና ሽብርተኛን የማስታመም ህልውና የለውም ያሉት ኮሎኔል አበበ፤ በሸኔ ላይ የጀመረውን የማያዳግም እርምጃ በመሰሎቹ ላይም እንደሚወስድ አስታውቀዋል።የቡድኑ ታጣቂዎች በድርጊታቸው ተጸጽተው ወደ ሰላማዊ ኑሮ የመመለስ ፍላጎት ካላቸው የክልሉ መንግሥት የሰላም በሩ አሁንም ክፍት መሆኑንም አመልክተዋል።

[EPA]
@YeneTube @FikerAssefa
ኢሰመጉ በኦሮሚያ እና ሲዳማ ክልሎች አዋሳኝ ቦታዎች መጋቢት 25 በተፈጠረ ግጭት 5 ሰዎች እንደተገደሉ እና በ15 ሰዎች ላይ ደሞ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ባወጣው አዲስ መግለጫ አስታውቋል።

ግጭቱ የተፈጠረው፣ ከኦሮሚያ ክልል የተነሱ ታጣቂዎች በሲዳማው ጭሪ ወረዳ አንድ የሲዳማ ሽማግሌ መግደላቸውን ተከትሎ ሲሆን፣ በግጭቱ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል። ኢሰመጉ ሁለቱ ክልሎች ችግሩን በቶሎ በሰላም እንዲፈቱት ጠይቋል። በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን አማሮ ልዩ ወረዳ ከኦሮሚያ ጉጂ ዞን የተነሱ ታጣቂዎች ግድያ መፈጸማቸውንም ኢሰመጉ ገልጧል። ኢሰመጉ መንግሥት የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶች ማስከበር አልቻለም በማለት ወቅሷል።

[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትድጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣንን ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 1238/2ዐ13 መሠረት የቦርድ አባላት ተሹመዋል፡፡

በዚህም መሰረት
1. ክቡር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ሰብሳቢ
2. ክብርት አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ከቱሪዝም ሚኒስቴር፤ አባል
3. ክቡር አምባሳደር ሀሰን ኢብራሂም ከዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል፤ አባል
4. ዶ/ር አጋረደች ጀማነህ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፤ አባል
5. ዶ/ር በድሉ ዋቅጀራ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፤ አባል
6. ዶ/ም መሣይ ገ/ማሪያም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፤ አባል
7. ዶ/ር ወዳጀነህ ማዕረነ አማካሪ፤ አባል
8. ቀሲስ ታጋይ ታደለ ከሃይማኖት ተቋማት፤ አባል
9. ኡስታዝ ያሲን ኑሩ ከሃይማኖት ተቋማት፤ አባል ሆነው በውሳኔ ቁጥር 8/2ዐ14 በተቃውሞ በ11 እና በ17 ድምፀ ታአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል።

በዚህም መሠረት ተሿሚዎቹ ቃለ መሃላ ፈፅመዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል በድርቅ ምክንያት 3.1 ሚሊዮን ሰዎች ለውሃ እጥረት መዳረጋቸው ተገለጸ!

በኦሮሚያ ክልል በጉጂ፣በምእራብ ጉጂ፣ በባሌ፣በምስራቅ ባሌ፣ በምስራቅ ሃረርጌ እና በምዕራብ ሃረርጌ ያጋጠመው ድርቅ 3.2 ሚሊዮን ሰዎች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳት ፈላጊ እንዲሆኑ ማድረጉን በአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ ተናግረዋል፡፡

በሰባ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ 690 ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ 3.1 ሚሊዮን ሰዎችች ለውሃ እጥረት የተጋለጡ ሲሆን ያላቸው የውሃ አማራጭ በቦቴ የሚቀርብ ውሃ በመሆኑ አሁን ላይ በ76 ወረዳዎች በ121 የውሃ ቦቴዎች እደላ እየተከናወነ ይገኛል።ሆኖም ግን ባለው የቦቴ እጥረት የተነሳ ውሃ የማዳረስ ሂደቱ አዳጋች እየሆነ መምጣቱ ተገልጿል ።

የውሃ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ማሽኖች መበላሸት፣ የጉድጓድ ውሃ መጠን መቀነስ ፣የውሃ ቦቴ ፍላጎት እና አቅርቦት አለመመጣጠን ፣በህጻናት እና እናቶች ላይ የተመጣጣነ ምግብ እጥረት በክልሉ የሚኖረውን የበሽታ ክስተት እንዲጨምረ ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በአምስት ዞኖች ውስጥ በሚገኙ 49 ወረዳዎች ከ12 ሚሊዮን በላይ እንስሳት በድርቅ አደጋ ውስጥ ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ 572ሺህ 967 እንስሳት ሞተዋል፡፡1ሚሊዮን 896 ሺኀ 937 እንስሳት ደግሞ ያለ ሰው ድጋፍ መነሳት እንደማይችሉም አንስተዋል፡፡እንዲሁም በቦረና እና በምስራቅ ባሌ ዞን ብቻ በድርቁ 1079 ትምህርት ቤቶች ሲዘጉ በዚህም ከ352 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርት እንዲያቋርጡ መገደዳቸውን ጠቁመዋል ፡፡

ከሃምሌ ወር 2013 እሰከ መጋቢት 2014 አጋማሽ በኢትዮጲያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ፣በአጋር አካላት ፣ በክልሉ መስተዳዳሩ እና ከህብረተሰቡ በተሰበሰበ ገንዘብ 1ሚሊዮን 473 ሺኀ ኩንታል ምግብ ለተጎጂዎች የተከፋፋለ መሆኑን አቶ ደበበ ዘውዴ ጨምረው ተናግረዋል፡፡

Via Bisrat FM
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ አየር መንገድ " ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሀገር ቤት " ጥሪን ተቀብለው ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የአየር ጉዞ ትኬት ዋጋ ላይ 20 % ቅናሽ ማድረጉን አስታውቋል።

ወደ ሀገር ቤት ተጓዦች ትኬታቸውን እኤአ ሚያዝያ 6 እስከ ሚያዝያ 21 ቀን 2022 በመቁረጥ እና ጉዟቸውን ከሚያዝያ 25 እስከ ግንቦት 15 ቀን 2022 ድረስ በማመቻቸት የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
ከግማሽ ሚልዮን በላይ ተማሪዎች በድርቅ ሳቢያ ትምህርት አቋርጠዋል ተባለ!

በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተ ድርቅ ከግማሽ ሚልዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ውጪ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት የህፃናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ) አስታወቀ።አፍሪካኒውስ ዩኒሴፍን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው ከ400 በላይ ትምህርት ቤቶች ሙሉ ለሙሉ የተዘጉ ሲሆን 727 ትምህርት ቤቶች ደግሞ በከፊል እየሰሩ ይገኛሉ።

ዩኒሴፍ ህፃናቱን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ እየሰራሁ ነው ያለ ሲሆን ‘ቤቴ’ የተሰኘ ስርዓት በመፍጠር ደህንነታቸው የሚጠበቅበት፣ የስነ ልቦና ድጋፍ የሚያገኙበትና ትምህርታቸውን የሚቀጥሉበት ሁኔታ ይመቻቻል ተብሏል።በመንግስታቱ ድርጅት መረጃ መሰረት በሶማሌ እና ኦሮሚያ ክልል የመቀንጨር ችግር 20 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።

Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
#በራስ_መተማመን
4ተኛው ዕትም በገበያ ላይ

ይህ A Guide to confident Living የተባለው መጽሐፍ በራስ መተማመንን እርካታን መቀዳጀት እንችል ዘንድ ያስችላል።

ቀላል ለማንም ሰው ሊገባ በሚችል ቋንቋ የተጠቀመው
ዶ/ር ፒል በሕይወታችን ትልቅ መታደስ ማግኘት እንችል ዘንድ አዲስ የሆነ የኃይል መንገድን ይጠቁመናል።

ከሚለግሰን ምክሮች መካከል እንደ፤

* ውስጣዊኃ ይሎቻችንን ነጻ ማውጣት
* ችግሮቻችንን አውጥተን መናገር
* የበታችነት ኮምፕሌክሳችንን መውደድ
* ለሕይወታችን የተረጋጋ ማዕከልን ማግኘት
* የጸሎትን ኃይል መለማመድ
* ከፍርሃትና ሃዘን ነፃነትን ማግኘት
* የትዳር፣ ሙያዊ እና ግለሰባዊ ደስታን ማግኘት ያሉት ይጠቀሳሉ።

ኖርማን ቪንሰንት ፒል በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ሽያጭ ያስገኘለት The Power of Positive Thinkingን ጨምሮ የ46 ያህል መጽሐፎች ደራሲ ነው።

በኖረበት ዘመን ትልቅ ከተባሉ የሃይማኖት ሰዎች አንዱ የነበረው ዶ/ር ፒል ምንም እንኳ ሕይወቱ ቢያልፍም በስሙ በተከፈተው Peal Center For Chrisitian Living በተባለው ፋውንዴሽን አማካይነት ውርሱ ለመላው ዓለም እየተዳረሰ ይገኛል።

አሳታሚና አከፋፋይ- ዘላለም
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኙታል።

*
ቤተሰብ ይሁኑ
Facebook- https://www.facebook.com/booklandbook/

Telegram-
https://tttttt.me/teklu_tilahun
የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ሩሲያን ከሰብአዊ መብቶች ም/ቤት አገደ!

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ጠቅላላ ጉባኤ ሩሲያ በዩክሬን ባካሄደችው “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ወታደሮቿ መጠነ ሰፊ እና ስልታዊ የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈጽመዋል የሚሉ ሪፖርቶች መውጣታቸውን ተከትሎ ነው፡፡

ይህ ወሳኔ የተላለፈው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ባደረገው ስብሰባ ነው፡፡በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል ግልጽ ጦርነት የተጀመረ ሲሆን፤ ከ3 ሚሊየን በላይ ዜጎች ሀገራቸውን ለቀው ወደ ጎረቤት ሀገራት መሰደዳቸውን ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት በሪፖርት ገልጿል።
ሩሲያ ጎረቤቷ ዩክሬን ኔቶን እቀላቀላለሁ ማለቷን ተከትሎ ከፈረንጆች የካቲት 24፣ 2022 ጀምሮ ወታደራዊ ዘመቻ ወታደራዊ ዘመቻ ማካሄድ መጀመሯ ይታወቃል።

የዩክሬን ሃይሎች ጠንካራ ተቃውሟቸውን የፈጠሩ ሲሆን ምዕራባውያን ሩሲያ ኃይሏን እንድታስወጣ ከፍተኛ ማዕቀብ ጥለዋል።የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ጠቅላላ ጉባኤ ባደረገው ስብሰባ ሩሲያ ዩክሬንን መዉረሯን የሚያወግዘዉን የዉሳኔ ሀሳብ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል።

[Alain]
@YeneTube @FikerAssefa