YeneTube
117K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.9K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና ሳፋሪኮም-ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የኮንክሪት ምሰሶ ኪራይ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላና የሳፋሪኮም-ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሚስተር አንዋር ሶውሳ ናቸው፡፡በፌርማ ስነ-ስርዓቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ የተፈረመው የምሰሶ ኪራይ ስምምነት የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶችን ለቴሌኮም አገልግሎት ለመጠቀም የሚያስችል መሆኑን ገልፀው፤ መሰረተ-ልማቶችን በጋራ መጠቀም መቻሉ ጥራት ያለውና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ብለዋል፡፡

ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለውም የኪራይ አገልግሎቱ በሃገሪቱ የተዘረጉ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ከመሆኑም በላይ የተቋሙን ገቢ ለማሳደግም ፋይዳው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡የሳፋሪኮም-ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ አንዋር ሶውሳ በበኩላቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር አብረው ለመስራት ዕድሉ በማግኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው፤ የተፈረመው የምሰሶ ኪራይ የሁለቱን ተቋማት ሃብት በጋራ ለመጠቀም የሚያስችልና ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የምሰሶ ኪራይ ስምምነቱ ዋና አላማ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተዘረጉ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በተለይም ደግሞ የኮንክሪት ፖሎችን በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል መሆኑን በፌርማ ስነ-ስርዓቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ስምምነቱ ተግባራዊ የሚደረገው በታላላቅ የሃገሪቱ ከተሞች ላይ በተተከሉ የኮንክሪት ምሰሶዎች ላይ ሲሆን፤ ውሉን የፈረመው ሳፋሪኮም በሚያገኘው አገልግሎት በዓመት 988 ብር ከ70 ሳንቲም ለአንድ ምሰሶ ኪራይ የሚከፍል መሆኑን ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተከላቸው የኮንክሪት ምሰሶዎች ኪራይ ተጨማሪ ገቢ ማግኘቱ በእርጅና ምክንያት የወደቁና የዘመሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ማሻሻልና የመልሶ ግንባታ ስራ ማከናወን የሚያስችለው ይሆናል፡፡

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ የሁለቱን ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያና ሌሎች የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በህንድ በኬረላ ማላፑራም አውራጃ ስታድየም ተደርምሶ ከ200 በላይ ተጎዱ!

ቅዳሜ እለት በተደረገ የእግር ኳስ ጨዋታ ላይ  የተመልካቾች  መቀመጫው ሲናድ ትልቅ የስታድየም መብራት ወደ ሜዳው ወድቋል።ከሜዳው ተቃራኒው ክፍል የመጡ ደጋፊዎች የተጎዱትን ለመርዳት ወደ ሜዳ ሲሮጡ የሚያሳይ ቪድዮ  የሀገር ውስጡ ጋዜጣ ኤቢፒ አሳይቷል።ድርጊቱ የተከሰተው የህንድ ሰቨንስ እግር ኳስ ውድድር የፍጻሜ ጨዋታ በሚካሄድበት በፖንጎድ ስታዲየም ውስጥ ነው።

@Yenetube @Fikerassefa
ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በ9ኛው የዓለም የውሃ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ሴኔጋል ገቡ፡፡

በፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የተመራ እና የውሀ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)ን ያካተተው የልዑካን ቡድን በ9ኛው የዓለም የውሃ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ዳካር ገብቷል።

በየሦስት ዓመቱ የሚካሄደው የዓለም የውሃ ፎረም በዓለም ዐቀፍ ደረጃ በውሃ እና በንፅህና አገልግሎት ረገድ እጅግ አንገብጋቢ የሆኑ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል እንደሆነ የታመነበት ሲሆን ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት ሲካሄድ የመጀመሪያው ነው።

የመድረኩ ዋንኛ ትኩረት ድንበር ተሻጋሪ ውሃማ አካላት ዘላቂ እና ሰላማዊ አጠቃቀም እና ለጸጥታ፣ መረጋጋት እና ኢኮኖሚያዊ ልማት ያላቸው ጠቀሜታዎች እንዲሁም በድርቅ እየተጎዱ ባሉ በርካታ የዓለም ክልሎች ላይ ይሆናል ተብሏል።

በዚህ መድረክ ለመሳተፍ ሴኔጋል ዳካር የገቡት ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴም በመድረኩ ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa
መንግሥት እንዴት ድርቁን መከላከል እንዳልቻለ ማብራሪያ እንዲሰጥ ተጠየቀ!

ኢትዮጵያ ውስጥ መረጃዎችን የሚሰበስብና የሚተነትን የቅድመ ትንበያ ሥርዓት ከተዘረጋ በርካታ ዓመታት በተቆጠረበትና የብሔራዊ ሚቲዎሮሎጂ የአየርና የዝናብ ሁኔታ የመተንበይ አቅም ባደገበት ሁኔታ፣ መንግሥት በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች ከ1.7 ሚሊዮን በላይ እንስሳትን የገደለውን ድርቅ ለምን አስቀድሞ መከላከል እንዳልቻለ ማብራሪያ እንዲሰጥ ተጠየቀ፡፡

መንግሥት ድርቁ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጣር አለመቻሉን በመጥቀስ ወቀሳውንና ጥያቄውን ያቀረበው የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ሲሆን፣ መንግሥት ተግባራዊ እየሆነ ያለውን የብሔራዊ አደጋ ሥጋት ፖሊሲና ስትራቴጂ፣ በአገሪቱ እያደገ የመጣውን የመረጃ ቴክኖሎጂ እንዲሁም የተሻለ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ቅድመ ማሰጠንቀቂያ ሥርዓት ተጠቅሞ፣ ድርቁን ማስወገድ ወይም መቀነስ ይችል እንደነበር ገልጿል፡፡

ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል በተነሳው ጦርነት፣ በርካታ ዜጎች ለዕርዳታና ለረሃብ መጋለጣቸውን ያስረዳው ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ በአገሪቱ የተከሰተው ድርቅም በሶማሌ ክልል በአብዛኛው ዞኖች፣ በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞንና በባሌ ቆላማ ክፍሎች፣ በደቡብ በጥቂት አካባቢዎች ላይ ሰዎችን ለረሃብ፣ እንስሳት ለሞት መዳረጉን አስታውቋል፡፡

መንግሥት ድርቁን የተመለከቱ የቅድመ መከላከል ሥራዎች ባለመሥራቱም በኦሮሚያ ክልል 3.7 ሚሊዮን ሰዎችን እንዳጠቃና በሶማሌ ክልል የዕርዳታ ፈላጊዎችን ቁጥር ወደ 3.4 ሚሊዮን ከፍ እንዳደረገ ተቋሙ መጋቢት 7 ቀን 2014 ዓ.ም. ለሪፖርተር በላከው መግለጫ ላይ አትቷል፡፡

Via Reoprter
@YeneTube @FikerAssefa
ሰበር ዜና!

133 ሰዎችን ያሳፈረ የቻይና ኢስተርን አየርመንገድ ንብረት የሆነ ቦይንግ 737 የመንገደኞች አውሮፕላን ተከሰከሰ!

133 ሰዎችን አሳፍሮ በሀገር ውስጥ በረራ ኩንሚግ ከተባለች ከተማ ወደ ጓንዡ ሲያቀና የነበረ ቦይንግ 737 አውሮፕላን ጓንዢ በተባለ ኮረብታማ አካባቢ መከስከሱን የተለያዩ አለምአቀፍ ሚዲያዎች እየዘገቡ ይገኛሉ።እስከአሁን የደረሰው ጉዳት አልታወቀም።

@YeneTube @FikerAssefa
ዩኒሴፍ ከ9 ሚሊዮን በላይ ህፃናት የፖሊዮ ክትባትን በዘመቻ ሊሰጥ መሆኑን አስታውቋል፡፡

በደቡብ አፍሪካዊቷ ሀገር ማላዊ የፖሊዮ ወረርሽኝ መኖሩ ከተረጋገጠ በኋላ ፣ዩኒሴፍ በምስራቅና በደቡብ አፍሪካ ሀገራት የሚገኙ ከዘጠኝ ሚሊዮን በላይ ህፃናት በዘመቻው መልክ ክትባቱን ሊሰጥ እንደሆነ የድርጅቱ የምስራቅ እና የደቡብ አፍሪካ ቀጠናዊ ዳሬክተር ተናግረዋል፡፡የቀጠናዊ ዳይሬክተር የሆኑት ሞሃመድ ኤም ፎል እንደተናገሩት ከሆነ "ይህ በአፍሪካ ውስጥ ከአምስት አመታት በላይ የተገኘ የዱር በሽታ የመጀመሪያው ምልክት ነው " ያሉ ሲሆን " ዩኒሴፍ ቫይረሱን ለመከላከል ከመንግስታት እና አጋር አካላት ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል ።

ፖሊዮን ለማስወገድ ያስችላል የተባለውን ዘመቻ ዩኒሴፍ የዓለም ጤና ድርጅትን ጨምሮ ከሌሎችም አጋር ተቋማት ጋር በትላንትናው እለት በማላዊ ያስጀመረ ሲሆን ዘመቻ በሌሎች የቀጠናው ሀገራት እንደሚያስቀጥል አስታውቋል።

ሞዛምቢክ ፣ ታንዛኒያ እና ዛምቢያ ፣ ከማላዊ በመቀጠል የፊታችን ሃሙስ በዘመቻው አማካይነት ህፃናቶቻቸውን በመጀመሪያው ዙር ያስከትባሉ ተብሏል።ግብረ ሰናይ ድርጅቱ በሁለት ዙሮች ተጠቃሚ ይሆናሉ ላላቸው 9 ሚሊዮን ህጻናት ከ36 ሚሊዮን በላይ የፖሊዮ ክትባት መግዛቱን ሲጂቲኤን ዘግቧዋል፡፡ከእነዚህ ዙሮች በኋላ ከ20 ሚሊዮን የሚልቁ ህፃናትን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የክትባት ዘመቻዎች በቀጣይ ዙሮች እንደሚከናወኑ ዩኒሴፍ አስታውቋል፡፡

[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የተማሪዎችን ፈተና ሂደት የሚያጣራ ቡድን ወደ ስፍራው መላኩን አስታወቀ!

የ2013 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የክልሉ ተማሪዎች የውጤት ችግር መግጠሙን ተከትሉ የተፈጠረውን ከፍተኛ ቅሬታ የሚያጣራ ቡድን ወደ አዲስ አበባ መላኩን አስታውቋል፡፡የተማሪዎች ውጤት ያሳሰበው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮም ችግሩን ለመፍታት በርካታ ተግባራትን ሲፈጽም መቆየቱን ቢሮው ገልጿል፡፡በአሁን ሰዓትም ከክልሉ ትምህርት ቢሮ አመራሮቸና ባለሙያዎች፣ከአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ፣ከዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ከትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራንና መምህራን የተውጣጣ ቡድን ወደ ፈተናወች ኤጀንሲ መላኩን አስታውቋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
በምሥራቅ ሸዋ ቡልቡላ ከተማ በሚሊሻ ምርቃት ላይ በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ ቢያንስ አራት ሰዎች ሞቱ!

በአዳሚ ቱሉ ጂዶ ኮምቦልቻ ቡልቡላ ከተማ ከ200 በላይ የሚሊሻ አባላት በተመረቁበት ወቅት በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ የ12 ዓመት ታዳጊን ጨምሮ የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የወረዳው አስተዳዳሪ አስታውቀዋል።

ፍንዳታው የተከሰተው የምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ተጠናቅቆ የመንግሥት ባለሥልጣናት ከመድረኩ ከተሸኙ በኋላ ሕዝቡና የሚሊሻ አባላት በደስታ እየጨፈሩ እያለ መሆኑን ነው የተናገሩት።

ከሞቱን ውጭም 35 የሚሆኑ ደግሞ መቁሰላቸውን ባለሥልጣኑ ገልፀዋል።

አቶ ሙሐመድ አክለውም ፍንዳታውን በማድረስ የተጠረጠሩ ሦስት ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ከምረቃ ፕሮግራሙ በፊት አነስተኛ ፕሮግራሞች እንደነበሩ ያስታወሱት ኃላፊው፣ ዋናው የምረቃ ፕሮግራም ከመጀመሩ በፊት ጥብቅ ፍተሻ እንደነበር በመግለጽ፣ የቦንብ ፍንዳታው የደረሰው ተቀብሮ ይሆን ተወርውሮ እየተጣራ ነው ብለዋል።

በፍንዳታው ጉዳት ደርሶባቸው የሕክምና እርዳታ ያገኙ ተጎጂዎች አብዛኛዎቹ ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ገልፀው፣ ስድስት ሰዎች ግን እስካሁን ድረስ የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።

"ይህንን ቦንብ ያፈነዳው ጠላት" ነው ሲሉ የገለፁት ባለሥልጣኑ ፍንዳታውን ያደረሰው ማን እነደሆነ እየተጣራ መሆኑን ተናግረዋል። ለቦንብ ፍንዳታው እስካሁን ድረስ ኃላፊነቱን የወሰደ አካል የለም።

በዚህ ቦንብ ፍንዳታ ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎች በትናንትናው ዕለት የቀብር ሥነ ስርዓታቸው መፈፀሙን ተናግረዋል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው።

@YeneTube @FikerAssefa
The Right Time,
The Right Moves!
Join The Global Education Expo Today.
www.backtoschoolafrica.com

List of Exhibitors:

Schools & Colleges/Universities
School Management Solution Providers
Software developers
App developers & Coders
Start-ups & TECH Entrepreneurs
Education Consultants
STEM Education Incubators,
Digital Service Providers
Education Material Producers & Suppliers
Digital Libraries
NGOs & related.

To Reserve Your Booth:
Call us:
+251 974 0820 36
+251 974 0820 37
በደቡብ ክልል ጌዴኦ ዞን የወሊድ አገልግሎት ፈልገው የመጡ አይነ ሥውር አራስ አናትን በመጸዳጃ ቤት አስተኝተዋል በተባሉ የጤና ባለሙያዎች ላይ መንግሥት ተከታትሎ እርምጃ እንዲወስድ የዞኑ አይነ ሥውራን ማህበር ጠየቀ፡፡

አራስ እናት እና ልጅ በመጸዳጃ ቤት ተኝተው የሚያሳየው የፎቶ ግራፍ ምስል በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች መሰራጨቱን ተከትሎ የጤና ተቋማቱና የአካል ጉዳተኞች ማህበር በጉዳዩ ላይ እየተወዛገቡ ይገኛሉ፡፡ዶቼ ቬለ ያነጋገራችው የአካባቢው የጤና ተቋማ ሃላፊዎች ድርጊቱን ፈጽመዋል የተባሉ አንድ የሥራ ሃላፊና ሦስት ባለሙያዎችን ከሥራ ማገዳቸውን ቢገልጹም የአካል ጉዳተኞች ማህበር አመራሮቸ ግን ጉዳዩ በህግ ሊታይ ይገባል እያለ ነው፡፡

ዶይቸ ቨለ እንደዘገበው ተጎጂዋ መጀመሪያ መጥፎ ጠርን እንሸተታቸው እና መጸዳጃ ቤት እንዳስተኟቸው የተረዱት ግን ዘግይተው እንደነበር ተናግረዋል።በተፈጸመባቸው ድርጊትም እጅጉን ማዘናቸውን ወይዘሮ ስምረት ጥላሁን ገልጸዋል፡፡በርካቶች በተጋሩት የወይዘሮዋ ፎቶ ግራፍ ላይ አራስ ልጃቸውን እንደታቀፉ ከተኙበት ራስጌአቸው አጠገብ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ወይም ሲንክ ይስተዋላል፡፡

[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጭ ግንባር የሱማሌ ክልል ልዩ ኃይሎች በጉርሱም ወረዳ ስምንት ሰላማዊ ሰዎችን ገድለዋል ሲል በትዊተር ገጹ ከሷል። ኦብነግ የክልሉ ልዩ ኃይሎች ግድያውን ፈጸሙ ያለው ባንባስ ጉርሱም በተባለች የወረዳው ከተማ ባንድ የጎሳ ስነ ሥርዓት ላይ በታደሙ ሰዎች ላይ በከፈቱት ተኩስ ነው። የክልሉ ልዩ ኃይሎች በአካባቢው የሚያካሂዱትን "የዘመቻ ተልዕኮ" እንዲያቆሙ እና በሰላማዊ ሰዎች ላይ ለምን ግድያ እንደተፈጸመ ፌደራል መንግሥቱ እንዲያጣራ ጠይቋል። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ የክልሉ መንግሥት ለውንጀላው ምላሽ አልሰጠም።

[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ፓትርያርክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ የመንግሥት የፀጥታ አካላት  የትግራይ ተወላጅ  እሳት ውስጥ ወርውረው መግደላቸውንና ይህም እጅግ እንዳሳዘናቸው በገለጹበት በሰሞኑ ንግግራቸው ላይ የሰጡትን አስተያየት፣ ለአንድ ወገና ያደላና የተሳሳተ ሲል መንግሥት ተቃወመ።

ቅዱስ ፓትርያርኩ «ትግራይ ሚዲያ ሀውስ» በተባለው መገናኛ ብዙሀን ባሰሙት ንግግራቸው በ2013 ዓ. ም "ትግሬዎችን ለማጥፋት ፣ የተጀመረው" ያሉት ጦርነት "አሁን በሌላው የኢትዮጵያ ክፍል ተስፋፍቶ በአብዛኛው ቦታ ሁከት ፣ ብጥብጥ ፣ ረሃብና ችግር እየደረሰ ነው" ሲሉ ተናግረው ነበር።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሠ ቱሉ "ፓትርያርኩ ያቀረቡት ክስ ለአንድ ወገን ያደላ፣ በቁጥር የጠቀሱት መረጃም የተሳሳተ እና ሆን ተብሎ መንግሥት ላይ ጫና ለማሳደር የተደረገ ነው።" ብለዋል። መንግሥት ድርጊታቸውን ሕዝብን ለመከፋፈል ሲባል የተደረገ አድርጎ ያየዋልም ብለዋል ሚኒስትሩ። የፓትርያርኩ ንግግር ከወጣበት ዕለት ጀምሮ በሕዝብ ዘንድ የድጋፍም ፣ የተቃውሞም  ሀሳቦች በስፋት እየተንሸራሸሩ ይገኛል። 

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ወደ አገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ የሚያመቻች የመንግስት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ሳዑዲ አረቢያ መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ዜጎቹን ከረመዳን ጾም መግባት በፊት ወደ አገራቸው መመለስ እንደሚጀምሩ ገልጿል።

በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ የሚያመቻችና የሚከታተል የመንግስት ከፍተኛ የመንግስት ልዑካን ቡድን ሳዑዲ አረቢያ መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዜጎቹ ከእስልምና እምነት ተከታዮች የረመዳን ጾም መግባት በፊት ወደ አገራቸው መመለስ እንደሚጀምሩ ተናግረዋል።

መንግስት በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎችን በአጭር ጊዜ ለመመለስ ከሳዑዲ አረቢያ መንግስት ጋር በቅርበት እየሰራ ይገኛል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

አምባሳደር ዲና ባለፈው ሳምንት በነበራቸው ሳምንታዊ መግለጫ በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ወደ አገራቸው ለመመለስ እስካሁን 35 ሺህ ዜጎች መመዝገባቸውንና ተገቢው ማጣራት እየተካሄደ መሆኑን መግለጻቸው የሚታወስ ነው።

@YeneTube @FikerAssefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሳምንታት የቀሩት አለም አቀፍ የትምህርት ኤክስፖ
በታላቁ አብርሆት ቤተ መፃህፍትና በቨርቹዋል መድረክ
ላይ ይካሄዳል።

ብዙዎች ተመዝግበዋል! እርሶስ?

ከነዚህ መሃል ከሆኑ አሁኑኑ ይመዝገቡ

👉 ትምህርት ቤቶች
👉 ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች
👉 የሶፍትዌር ገንቢዎች
👉 ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች
👉 ት/ቤት አስተዳደር ዲጂታል መፍትሔ አቅራቢዎች፣
👉 አለም አቅፍ የትምህርት እድል አማካሪዎች
👉 ኢንኩቤተሮች
👉 የዲጂታል አገልግሎት አቅራቢዎች
👉 የትምህርት ቁሳቁስ አምራቾች እና አቅራቢዎች
👉 ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት እና
👉 ተያያዥነት ያላቸው።

ለመመዝገብ ይህችን ሊንክ ይጫኑ👇!
www.backtoschoolafrica.com

☎️ : +251 974 08 2036
+251 974 08 2037
🖲ሴኩሪቲ ካሚራ ከነፃ ገጠማ ጋር...

📍በተጨማሪም በቻናላችን join በማለት እቃዎችን ማየት ይችላሉ👇👇

join :- @Dawitengineering

📍የፈለጉትን ይዘዙን እኛን ለማግኘት ከታች ባለው አድራሻ ያገኙናል።


ስልክ :- 0920757958
inbox :- @Dawit757985
https://tttttt.me/sabinaadvisor

የስራ ጉዞ ወደ # Europe
#Schengen_visa

👉 የሚሰራበት አገር - geneva, Swaziland
👉 የስራው አይነት :- accounting
👉 የስራ ቀናት - 6 ቀናት/ week

👉 የወር ደሞዝ - €10000_13000 and more
👉 ፆታ - አይጠይቅም
👉 ዕድሜ - 25እስከ 45
👉 መኖሪያ ቤት - በነፃ
👉 ፕሮሰሱ የሚፈጀው ግዜ ከ 2 - 3 ወር ነው

#10 persons
#Requirements
👉 Passport
👉photo
👉Degree documents
👉Work experience
Contact:
@Sabinavisa
+251118683939
0936363639
0936363680
በነገው እለት በመላው አዲስ አበባ የህዝብ ውይይት ይደረጋል ተባለ!

ነገ ረቡዕ 14/07/14 ዓ.ም በመላው አዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ወረዳዎች ፤በክ/ከተማ እንዲሁም በከተማ ደረጃ የህዝብ ውይይቶች ይካሄዳሉ፡፡በውይይቱ በየደረጃው ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎችና ሃሳቦች ይደመጣሉ ብሏል የከተማ አስተዳደሩ።

@YeneTube @FikerAssefa