የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ተጨማሪ እገዛ እንዲደረግላቸው የዩናይትድ ስቴትስን ኮንግረስ ጠየቁ፡፡
ዋሽንግተን በጦርነቱ እገዛ እያደረገችላቸው እንደሆነ ያስረዱት ዜሌንስኪ ነገር ግን ተጨማሪ ድጋፍ ያስፈልገናል ባይ ናቸው፡፡የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በግላቸው በጦርነቱ ውስጥ እያደረጉት ስላለው ተሳትፎ እውቅና ሰጥተዋል፡፡በዕርግጥ ሞስኮ በጉዳዬ ላይ ጣልቃ ገባችሁብኝ የሚል ስም ትሰጠዋለች፡፡
ዋሽንግተን ለኪዬቭ የተለያዩ እርዳታዎችን እና እገዛዎችን ስለማደረጓም ፕሬዚዳንቱ አልደበቁም፡፡ዩናይትድ ስቴትስ ተጨማሪ ማዕቀቦችን እንድትጥልም ለኮንግረሱ ጥሪ አቅረበዋል ፡፡
በሩሲያ ፌደሬሽን ውስጥ ያሉ ሁሉም ፖለቲከኞች ማዕቀብ እንዲጣልባቸው ምክረ ሀሳብ ያቀረቡት ዜሌንስኪ ዩክሬናውያንን አልታደጓቸውም በሚል ትችት ይሰነዘርባቸዋል፡፡ሁሉም የዩናይትድ ስቴትስ ኩባንያዎች ከሩሲያ ገበያ በአፋጣኝ መውጣት አለባቸውም ይላሉ፡፡ፕሬዚደንት ዜሌንስኪ የዩናይትድ ሰቴትሱ አቻቸው ጆ ባይደን የሰላም መሪ እንዲሆኑም ለማስገንዘብ ሞክረዋል፡፡
ዘገባው የቢቢሲ ነው
@YeneTube @FikerAssefa
ዋሽንግተን በጦርነቱ እገዛ እያደረገችላቸው እንደሆነ ያስረዱት ዜሌንስኪ ነገር ግን ተጨማሪ ድጋፍ ያስፈልገናል ባይ ናቸው፡፡የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በግላቸው በጦርነቱ ውስጥ እያደረጉት ስላለው ተሳትፎ እውቅና ሰጥተዋል፡፡በዕርግጥ ሞስኮ በጉዳዬ ላይ ጣልቃ ገባችሁብኝ የሚል ስም ትሰጠዋለች፡፡
ዋሽንግተን ለኪዬቭ የተለያዩ እርዳታዎችን እና እገዛዎችን ስለማደረጓም ፕሬዚዳንቱ አልደበቁም፡፡ዩናይትድ ስቴትስ ተጨማሪ ማዕቀቦችን እንድትጥልም ለኮንግረሱ ጥሪ አቅረበዋል ፡፡
በሩሲያ ፌደሬሽን ውስጥ ያሉ ሁሉም ፖለቲከኞች ማዕቀብ እንዲጣልባቸው ምክረ ሀሳብ ያቀረቡት ዜሌንስኪ ዩክሬናውያንን አልታደጓቸውም በሚል ትችት ይሰነዘርባቸዋል፡፡ሁሉም የዩናይትድ ስቴትስ ኩባንያዎች ከሩሲያ ገበያ በአፋጣኝ መውጣት አለባቸውም ይላሉ፡፡ፕሬዚደንት ዜሌንስኪ የዩናይትድ ሰቴትሱ አቻቸው ጆ ባይደን የሰላም መሪ እንዲሆኑም ለማስገንዘብ ሞክረዋል፡፡
ዘገባው የቢቢሲ ነው
@YeneTube @FikerAssefa
አሜሪካ 840 ሺሕ 60 ዶዝ ፋይዘር የኮቪድ-19 ክትባት ለኢትዮጵያ ድጋፍ ማድረጓን ገለፀች።
ድጋፉ አሜሪካ በዓለም ዐቀፍ ደረጃ የኮቪድ ወረርሽኝ ለመከላከል ለምታደርገው ጥረት አንድ አካል መሆኑ ተገልጿል።አሜሪካ እስካአሁን ለኢትዮጵያ ያደረገቸው የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ በጥቅሉ 7 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶዝ እንደደረሰም ተነግሯል።ክትባቱ በያዝነው ሳምንት በኮቫክስ ጥምረት አማካኝነት ወደ አዲስ አበባ አንደገባም በኢትዮጵያ ከአሜሪካ ኢምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ድጋፉ አሜሪካ በዓለም ዐቀፍ ደረጃ የኮቪድ ወረርሽኝ ለመከላከል ለምታደርገው ጥረት አንድ አካል መሆኑ ተገልጿል።አሜሪካ እስካአሁን ለኢትዮጵያ ያደረገቸው የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ በጥቅሉ 7 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶዝ እንደደረሰም ተነግሯል።ክትባቱ በያዝነው ሳምንት በኮቫክስ ጥምረት አማካኝነት ወደ አዲስ አበባ አንደገባም በኢትዮጵያ ከአሜሪካ ኢምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
‘ኦብነግ’ ከ25 ዓመታት በኋላ 2ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ እያካሄደ ነው!
በአሸባሪነት ተፈርጆ ለ25 ዓመታት ከሐገር ውጭ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በማካሄድ ላይ የነበረው፣ በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ምክርቤት 2 መቀመጫ ያለው፣ እኤአ በ1984 ዓ.ም. የተመሰረተው የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር /ኦብነግ/ ድርጅታዊ ጉባኤውን በጅግጅጋ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል። አዘጋጅ ኮሚቴው ጉባኤው ከመጋቢት 7 እስከ መጋቢት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ለአራት ተከታታይ ቀናት እንደሚያካሂድ አስታውቋል።
የኦብነግ የፓርቲ ጉዳዮች ኃላፊና የግንባሩ የጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሁሴን መሀመድ ኑር ለሁሉም የፓርቲው አባላት ክፍት እንደሚሆን በሚጠበቀው ጉባኤ ላይ “የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ይገኛሉ” ብለዋል። ከአጀንዳዎቹ መካከልም የግንባሩ ውስጣዊ ችግሮች ላይ መወያየትና የመፍትሔ አቅጣጫዎች ማስቀመጥ እንዲሁም በወቅታዊ እና ሐገራዊ ጉዳዮች ላይ መወያየት እንደሚገኙበት አቶ ሁሴን አብራርተዋል።
Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
በአሸባሪነት ተፈርጆ ለ25 ዓመታት ከሐገር ውጭ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በማካሄድ ላይ የነበረው፣ በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ምክርቤት 2 መቀመጫ ያለው፣ እኤአ በ1984 ዓ.ም. የተመሰረተው የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር /ኦብነግ/ ድርጅታዊ ጉባኤውን በጅግጅጋ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል። አዘጋጅ ኮሚቴው ጉባኤው ከመጋቢት 7 እስከ መጋቢት 10 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ለአራት ተከታታይ ቀናት እንደሚያካሂድ አስታውቋል።
የኦብነግ የፓርቲ ጉዳዮች ኃላፊና የግንባሩ የጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሁሴን መሀመድ ኑር ለሁሉም የፓርቲው አባላት ክፍት እንደሚሆን በሚጠበቀው ጉባኤ ላይ “የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ይገኛሉ” ብለዋል። ከአጀንዳዎቹ መካከልም የግንባሩ ውስጣዊ ችግሮች ላይ መወያየትና የመፍትሔ አቅጣጫዎች ማስቀመጥ እንዲሁም በወቅታዊ እና ሐገራዊ ጉዳዮች ላይ መወያየት እንደሚገኙበት አቶ ሁሴን አብራርተዋል።
Via Addis Zeybe
@YeneTube @FikerAssefa
የዝቋላ አቦ ገዳም በሚገኝበት ደናማ ተራራ ላይ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ተነስቶ ለአምስት ቀናት ያህል የቆየው የእሳት አደጋ ትናንት ሌሊት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተነገረ።
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሊበን ጩቃላ ወረዳ በተከሰተው በእዚህ የእሳት አደጋ ምክንያት የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉንም የአከባቢው ባለሥልጣን ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።የሊበን ወረዳ አከባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ኃላፊ አቶ ገመዳ ቢራ እንዳሉት፦ ባለፈው ሰኞ የዝቋላ አቦ ዓመታዊ ክብረ በዓል ለማክበር ከአዲስ አበባ ወደ ስፍራው እያቀኑ ከነበሩ ምእመን አንዱ ሰደድ እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ሲያደርግ ወደ ገደል ወድቆ ሕወይቱ ማለፉን ገልጸዋል።
ከመጋቢት 1 ቀን፣ 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ሲነድ የነበረውን አንድ ሺህ ሄክታር ገደማ ደናማ የዝቋላ ተራራን ለመታደግ የጸጥታ ኃይላት እና የመንግስት ሠራተኞች ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውንም ተናግረዋል። «እኛ አቅቶን ስንመለስ ማታ ኅብረተሰቡ በእድር በጥሩምባ ተጠራርቶ እሳቱን ለመቆጣጠር አመቺ ነው በተባለው ሌሊት ላይ ማጥፋት ችለዋል።
ኅብረተሰቡ ከዚህ በፊትም ልምድ ስላለው እሳቱን ለመቆጣጠር ተችሏል።»በወረዳ ደረጃ እሳቱን ለመቆጣጠር አቅም እንዳልነበራቸው የገለጹት ኃላፊው ለበላይ አካል ቢያሳውቁም አፋጣኝ ምላሽ ባለማግኘታቸው እሳቱ ለቀናት መስፋፋቱን አብራርተዋል።እሳቱ የተነሳው ዶዶቲ ከሚባል የደኑ ጠረፍ አከባቢ መሆኑ ተገልጧል። መንስዔው በውል ዐልታወቀም። በሰደድ እሳቱ በርካታ አገር በቀል እፅዋት እና የዱር እንስሳት መጎዳታቸውንም አቶ ገመዳ አመልክተዋል።እሳቱ በተራራው አናት ላይ ከሚገኘው የዝቋላ አቦ ቤተክርስቲያን እና የአከባቢው ማኅበረሰብ መኖሪያ ቤቶች እሩቅ በመሆኑ ጉዳት አለማድረሱን ዘጋቢችን ሥዩም ጌቱ ከአዲስ አበባ ያደረሰን መረጃ ያመለክታል። የዝቋላ ደናማ ተራራ 13 ሺህ 700 ሄክታር ገደማ ስፋት እንዳለው ይነገራል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሊበን ጩቃላ ወረዳ በተከሰተው በእዚህ የእሳት አደጋ ምክንያት የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉንም የአከባቢው ባለሥልጣን ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።የሊበን ወረዳ አከባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ኃላፊ አቶ ገመዳ ቢራ እንዳሉት፦ ባለፈው ሰኞ የዝቋላ አቦ ዓመታዊ ክብረ በዓል ለማክበር ከአዲስ አበባ ወደ ስፍራው እያቀኑ ከነበሩ ምእመን አንዱ ሰደድ እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ሲያደርግ ወደ ገደል ወድቆ ሕወይቱ ማለፉን ገልጸዋል።
ከመጋቢት 1 ቀን፣ 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ሲነድ የነበረውን አንድ ሺህ ሄክታር ገደማ ደናማ የዝቋላ ተራራን ለመታደግ የጸጥታ ኃይላት እና የመንግስት ሠራተኞች ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውንም ተናግረዋል። «እኛ አቅቶን ስንመለስ ማታ ኅብረተሰቡ በእድር በጥሩምባ ተጠራርቶ እሳቱን ለመቆጣጠር አመቺ ነው በተባለው ሌሊት ላይ ማጥፋት ችለዋል።
ኅብረተሰቡ ከዚህ በፊትም ልምድ ስላለው እሳቱን ለመቆጣጠር ተችሏል።»በወረዳ ደረጃ እሳቱን ለመቆጣጠር አቅም እንዳልነበራቸው የገለጹት ኃላፊው ለበላይ አካል ቢያሳውቁም አፋጣኝ ምላሽ ባለማግኘታቸው እሳቱ ለቀናት መስፋፋቱን አብራርተዋል።እሳቱ የተነሳው ዶዶቲ ከሚባል የደኑ ጠረፍ አከባቢ መሆኑ ተገልጧል። መንስዔው በውል ዐልታወቀም። በሰደድ እሳቱ በርካታ አገር በቀል እፅዋት እና የዱር እንስሳት መጎዳታቸውንም አቶ ገመዳ አመልክተዋል።እሳቱ በተራራው አናት ላይ ከሚገኘው የዝቋላ አቦ ቤተክርስቲያን እና የአከባቢው ማኅበረሰብ መኖሪያ ቤቶች እሩቅ በመሆኑ ጉዳት አለማድረሱን ዘጋቢችን ሥዩም ጌቱ ከአዲስ አበባ ያደረሰን መረጃ ያመለክታል። የዝቋላ ደናማ ተራራ 13 ሺህ 700 ሄክታር ገደማ ስፋት እንዳለው ይነገራል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በአንድ የዲሽ ሳህን እስከ 64 ቤቶችን እንሰራለን
ለአፓርትመንቶች
ለሪልስቴቶች
ለሆቴሎች
ለገስት ሀውስ
ለኮዶሚንየሞች
📍በተጨማሪም በቻናላችን join በማለት እቃዎችን ማየት ይችላሉ👇👇
join :- @Dawitengineering
📍የፈለጉትን ይዘዙን እኛን ለማግኘት ከታች ባለው አድራሻ ያገኙናል።
ስልክ :- 0920757958
inbox :- @Dawit757985
ለአፓርትመንቶች
ለሪልስቴቶች
ለሆቴሎች
ለገስት ሀውስ
ለኮዶሚንየሞች
📍በተጨማሪም በቻናላችን join በማለት እቃዎችን ማየት ይችላሉ👇👇
join :- @Dawitengineering
📍የፈለጉትን ይዘዙን እኛን ለማግኘት ከታች ባለው አድራሻ ያገኙናል።
ስልክ :- 0920757958
inbox :- @Dawit757985
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሳምንታት የቀሩት አለም አቀፍ የትምህርት ኤክስፖ
በታላቁ አብርሆት ቤተ መፃህፍትና በቨርቹዋል መድረክ
ላይ ይካሄዳል።
ብዙዎች ተመዝግበዋል! እርሶስ?
ከነዚህ መሃል ከሆኑ አሁኑኑ ይመዝገቡ
👉 ትምህርት ቤቶች
👉 ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች
👉 የሶፍትዌር ገንቢዎች
👉 ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች
👉 ት/ቤት አስተዳደር ዲጂታል መፍትሔ አቅራቢዎች፣
👉 አለም አቅፍ የትምህርት እድል አማካሪዎች
👉 ኢንኩቤተሮች
👉 የዲጂታል አገልግሎት አቅራቢዎች
👉 የትምህርት ቁሳቁስ አምራቾች እና አቅራቢዎች
👉 ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት እና
👉 ተያያዥነት ያላቸው።
ለመመዝገብ ይህችን ሊንክ ይጫኑ👇!
www.backtoschoolafrica.com
☎️ : +251 974 08 2036
+251 974 08 2037
በታላቁ አብርሆት ቤተ መፃህፍትና በቨርቹዋል መድረክ
ላይ ይካሄዳል።
ብዙዎች ተመዝግበዋል! እርሶስ?
ከነዚህ መሃል ከሆኑ አሁኑኑ ይመዝገቡ
👉 ትምህርት ቤቶች
👉 ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች
👉 የሶፍትዌር ገንቢዎች
👉 ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች
👉 ት/ቤት አስተዳደር ዲጂታል መፍትሔ አቅራቢዎች፣
👉 አለም አቅፍ የትምህርት እድል አማካሪዎች
👉 ኢንኩቤተሮች
👉 የዲጂታል አገልግሎት አቅራቢዎች
👉 የትምህርት ቁሳቁስ አምራቾች እና አቅራቢዎች
👉 ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት እና
👉 ተያያዥነት ያላቸው።
ለመመዝገብ ይህችን ሊንክ ይጫኑ👇!
www.backtoschoolafrica.com
☎️ : +251 974 08 2036
+251 974 08 2037
ማስታወቂያ!
በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ ባስመዘገባችሁት ውጤት መሠረት በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ምደባ ማግኘት የሚያስችል ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ከዚህ ቅደም የተቋም እና የመስክ ምርጫ ማካሄዳችሁ ይታወቃል።
ሆኖም ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ምደባ የሚያደርግ መሆኑን አውቃችሁ የሚከተሉትን ማስተካከያዎች እንድታደርጉ ሲል አሳስቧል።
1ኛ. የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የተማሪዎች አማካይ ውጤት አፈፃፀም፣ ወዘተ ከግንዛቤ በማስገባት የዩኒቨርሲቲ ምርጫችሁን እስከ መጋቢት 13/2014 ዓ.ም ድረስ በ Portal.neaea.gov.et ገብታችሁ እንድታስተካክሉ እየገለፀ ከምደባ በኋላ የሚቀርብ ምንም አይነት የምደባ ለውጥ የማያስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ ያሳውቃል።
2ኛ. በጤና እና ልዩ ልዩ ጉዳዮች ምደባ በልዩ ሁኔታ እንዲታይላችሁ የምታመለክቱ ተማሪዎች መረጃችሁን እስከ መጋቢት 11/2014 ዓ.ም ድረስ በ https://student.ethernet.edu.et/ በኩል እንድትልኩ እያሳሰበ በአካል የሚቀርብ ምንም ዓይነት ማስረጃ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ ባስመዘገባችሁት ውጤት መሠረት በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ምደባ ማግኘት የሚያስችል ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ከዚህ ቅደም የተቋም እና የመስክ ምርጫ ማካሄዳችሁ ይታወቃል።
ሆኖም ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ምደባ የሚያደርግ መሆኑን አውቃችሁ የሚከተሉትን ማስተካከያዎች እንድታደርጉ ሲል አሳስቧል።
1ኛ. የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የተማሪዎች አማካይ ውጤት አፈፃፀም፣ ወዘተ ከግንዛቤ በማስገባት የዩኒቨርሲቲ ምርጫችሁን እስከ መጋቢት 13/2014 ዓ.ም ድረስ በ Portal.neaea.gov.et ገብታችሁ እንድታስተካክሉ እየገለፀ ከምደባ በኋላ የሚቀርብ ምንም አይነት የምደባ ለውጥ የማያስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ ያሳውቃል።
2ኛ. በጤና እና ልዩ ልዩ ጉዳዮች ምደባ በልዩ ሁኔታ እንዲታይላችሁ የምታመለክቱ ተማሪዎች መረጃችሁን እስከ መጋቢት 11/2014 ዓ.ም ድረስ በ https://student.ethernet.edu.et/ በኩል እንድትልኩ እያሳሰበ በአካል የሚቀርብ ምንም ዓይነት ማስረጃ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
በሳዑዲ ዓረቢያ የሚገኙ ከ100 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ የተቋቋመው ብሄራዊ ኮሚቴ ወደ ሪያድ ሊጓዝ እንደሆነ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። ብሄራዊ ኮሚቴው ዜጎችን ለመመለስ የመጨረሻው ጫፍ ላይ መድረሱን እና ባሁኑ ወቅት ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እና በሪያድ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ፍልሰተኞችን የመመዝገብ እና የማጣራት ሥራ እየሠሩ እንደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል። ኮሚቴው ፍልሰተኞቹን ለመመለስ እና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችለውን የትግበራ መርሃ ግብር ቀደም ሲል ማዘጋጀቱ ይታወሳል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
እናት ፓርቲ ከትግራይ ክልል ተፈናቅለው ወደ አማራ ክልል የገቡትን ጨምሮ የመዋቅራዊ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል ያላቸው ተፈናቃዮችን ህዝቡ እንዲታደጋቸው ጥሪ አቀረበ!
ፓርቲው መጋቢት 7 ቀን 2014 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ” የመዋቅራዊ ጥቃትና ጦርነቱ ሰላባ የሆኑ” ያላቸው ”ተፈናቃይ ወገኖች ህዝቡ በአፋጣኝ ይድረስላቸው”ሲል ጠይቋል፡፡ፓርቲው”በሀገራችን ሞትን እየተለማመድን፣ የሞተው ሰው ቁጥርና የአሟሟቱ የዘግናኝነት መጠን ያነጋግር ካልሆነ እንጂ የጅምላ ፍጅትና ዕልቂት የሚስገርም አልሆነም፡፡” ሲል ወቅሷል፡፡
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የተከሰቱትን ዘግናኝ ወንጀሎችን በመግለጫው ያስታወሰው ፓርቲው ድርጊቶቹ”ዝም በመባላቸው ዛሬ ሰው ከነህይወቱ እያገላበጥን መጥበስ ላይ ተደርሷል” ሲል ኮንኗል፡፡ አክሎም ”ይህም ዝም ስለሚባል ነገ ምን እንደሚደረግ መገመት አያዳግትም፡፡” ብሏል፡፡
ፓርቲው በመግለጫው”በቅርቡ በመቶዎች የሚቆጠሩ መድረሻ ያጡ ምስኪን ኢትዮጵዊን አንገት ማስገቢያ ጎጆ አጥተው እንደ ኳስ ከቦታ ቦታ ሲላጉ እያየን ሃይ ባይ ስላጣን መቶሺዎች በመዋቅራዊ ጥቃት ሰበብ አማራ ክልል፣ ፍኖተ ሰላም አካባቢውን አጥልቅቀዋል፡፡” ሲል አመለክቷል፡፡
እናት ፓርቲ ” ትግራይ ክልል ውስጥ ያለው ሁኔታ” በህወሓት በፓርቲው አገላለፅ ትህነግ፣ አማካይነት ወደምድራዊ ሲዖል በመቀየሩ፣ ማህበረሰቡ እግሩ ወዳደረሰው በገፍ በመሰደድ በመጀመሩ አንዱ መዳረሻ ወደሆነው ቆቦና ሰቆጣ ሆኗል ሲል ገልፆል፡፡
ስለዚህም በመቶሺዎች የሚቆጠሩ በአማራ አፋር ክልል፣ አንዲሁም ከትግራይ ክልል እየገቡ ላሉት ” ተፈናቃዮች ” የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲድረስላቸውና እንዲታደጋቸው በመግለጫው ጠይቋል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
ፓርቲው መጋቢት 7 ቀን 2014 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ” የመዋቅራዊ ጥቃትና ጦርነቱ ሰላባ የሆኑ” ያላቸው ”ተፈናቃይ ወገኖች ህዝቡ በአፋጣኝ ይድረስላቸው”ሲል ጠይቋል፡፡ፓርቲው”በሀገራችን ሞትን እየተለማመድን፣ የሞተው ሰው ቁጥርና የአሟሟቱ የዘግናኝነት መጠን ያነጋግር ካልሆነ እንጂ የጅምላ ፍጅትና ዕልቂት የሚስገርም አልሆነም፡፡” ሲል ወቅሷል፡፡
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የተከሰቱትን ዘግናኝ ወንጀሎችን በመግለጫው ያስታወሰው ፓርቲው ድርጊቶቹ”ዝም በመባላቸው ዛሬ ሰው ከነህይወቱ እያገላበጥን መጥበስ ላይ ተደርሷል” ሲል ኮንኗል፡፡ አክሎም ”ይህም ዝም ስለሚባል ነገ ምን እንደሚደረግ መገመት አያዳግትም፡፡” ብሏል፡፡
ፓርቲው በመግለጫው”በቅርቡ በመቶዎች የሚቆጠሩ መድረሻ ያጡ ምስኪን ኢትዮጵዊን አንገት ማስገቢያ ጎጆ አጥተው እንደ ኳስ ከቦታ ቦታ ሲላጉ እያየን ሃይ ባይ ስላጣን መቶሺዎች በመዋቅራዊ ጥቃት ሰበብ አማራ ክልል፣ ፍኖተ ሰላም አካባቢውን አጥልቅቀዋል፡፡” ሲል አመለክቷል፡፡
እናት ፓርቲ ” ትግራይ ክልል ውስጥ ያለው ሁኔታ” በህወሓት በፓርቲው አገላለፅ ትህነግ፣ አማካይነት ወደምድራዊ ሲዖል በመቀየሩ፣ ማህበረሰቡ እግሩ ወዳደረሰው በገፍ በመሰደድ በመጀመሩ አንዱ መዳረሻ ወደሆነው ቆቦና ሰቆጣ ሆኗል ሲል ገልፆል፡፡
ስለዚህም በመቶሺዎች የሚቆጠሩ በአማራ አፋር ክልል፣ አንዲሁም ከትግራይ ክልል እየገቡ ላሉት ” ተፈናቃዮች ” የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲድረስላቸውና እንዲታደጋቸው በመግለጫው ጠይቋል፡፡
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
‘ኦብነግ’ ከ25 ዓመታት በኋላ 2ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ እያካሄደ ነው! በአሸባሪነት ተፈርጆ ለ25 ዓመታት ከሐገር ውጭ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በማካሄድ ላይ የነበረው፣ በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ምክርቤት 2 መቀመጫ ያለው፣ እኤአ በ1984 ዓ.ም. የተመሰረተው የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር /ኦብነግ/ ድርጅታዊ ጉባኤውን በጅግጅጋ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል። አዘጋጅ ኮሚቴው ጉባኤው ከመጋቢት 7 እስከ መጋቢት…
በትላንትናው ዕለት ሊካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት የኦብነግ ድርጅታዊ ጉባኤ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ!
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) በጅግጅጋ ከተማ ሊያካሂደው ቀጠሮ የያዘለትን ድርጅታዊ ጉባኤ ማራዘሙን አስታወቀ።የግንባሩ የድርጅት ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ እና የጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሁሴን ኑር ትላንት ምሽት በጽ/ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ግንባሩ እቅድ የያዘለትን 5ኛውን ድርጅታዊ ጉባኤ እንደማያካሂድ አሳውቀዋል።
አቶ ሁሴን በመግለጫቸው “ኦብነግ ጉባኤውን ያራዘመው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተወካዮች ልኮ ስብሰባውን ለመታደም ባለመቻሉ ነው” ብለዋል።የምርጫ ቦርድ ጥያቄ በኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ ተቀባይነት በማግኘቱ ጉባኤው መራዘሙን ተናግረዋል።አመራሮች እና አባላት በአካል ተገኝተው በድርጅታዊ እና ሐገራዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ቀጠሮ የተያዘለት የኦብነግ ጠቅላላ ድርጅታዊ ጉባኤ መቼ እንደሚካሄድ ወደፊት ይገለጻል ተብሏል።
[Addis Zeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) በጅግጅጋ ከተማ ሊያካሂደው ቀጠሮ የያዘለትን ድርጅታዊ ጉባኤ ማራዘሙን አስታወቀ።የግንባሩ የድርጅት ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ እና የጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሁሴን ኑር ትላንት ምሽት በጽ/ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ግንባሩ እቅድ የያዘለትን 5ኛውን ድርጅታዊ ጉባኤ እንደማያካሂድ አሳውቀዋል።
አቶ ሁሴን በመግለጫቸው “ኦብነግ ጉባኤውን ያራዘመው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተወካዮች ልኮ ስብሰባውን ለመታደም ባለመቻሉ ነው” ብለዋል።የምርጫ ቦርድ ጥያቄ በኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ ተቀባይነት በማግኘቱ ጉባኤው መራዘሙን ተናግረዋል።አመራሮች እና አባላት በአካል ተገኝተው በድርጅታዊ እና ሐገራዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ቀጠሮ የተያዘለት የኦብነግ ጠቅላላ ድርጅታዊ ጉባኤ መቼ እንደሚካሄድ ወደፊት ይገለጻል ተብሏል።
[Addis Zeybe]
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ፍ/ቤት ታስሬ እንድቀርብ ማዘዙ አግባብ አደለም ሲሉ አቤቱታ በጽሁፍ አቀረቡ!
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ፍ/ቤት ታስሬ እንድቀርብ ማዘዙ አግባብ አደለም ሲሉ አቤቱታቸውን ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በጽሁፍ አቀረቡ።የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ከዚህ በፊት እንዲቀርቡ መታዘዙ እንደማያውቁና መጥሪያ እንዳልደረሳቸው ገልጸው፤ መጥርያ ተረክቤ እንቢ ባላለኩበት ሁኔታ ታስሬ እንድቀርብ በፍ/ቤት መታዘዙን አግባብ አደለም ሲሉም አቤቱታቸውን አቅርበዋል።
በጥር 30 ቀን 2014 ታስሬ እንድቀርብ መታዘዙን ማህበራዊ ሚዲያ ነው የሰማሁት ሲሉ በጽሁፍ ለፍርድ ቤቱ በላኩት አቤቱታ አብራርተዋል።በደረሳቸው አገራዊ ጥሪ መሰረት ለአገር እና ለህዝብ ጥቅም እየሰሩ መሆናቸውን ተከትሎ ለሥራ በውጭ አገር እንደሚገኙ ጠቅሰው በማንኛውም ሰዓት ለመቅረብ ታዛዥ መሆናቸውን ገልጸዋል።ሆኖም ካላቸው የሥራ ሁኔታ አንጻር በአካል ለመገኘት እንደሚቸገሩ ገልጸው፤ ነገር ግን ምስክርነቱን ባሉበት ቦታ ሆነው በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ ጥያቄውኝ ማስተናገድ እንደሚችሉ ፍርድ ቤቱ በላኩት ምላሽ አብራርተዋል።
የእነ ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ጠበቃ ሀፍቶም ከሰተ በበኩላቸው፤ ሀይለማርያም ደሳለኝ መጥሪያ መላኩን አላውቅም ፈርሜ አልተቀበልኩም ማለታቸው እንደማይቀበለው ገልጿል።በተደጋጋሚ መጥሪያ እንዲደርሳቸው መታዘዙን ተከትሎ ለሮማንና ሀይለማርያም ፋውንዴሽን ድርጅት ጸሀፊ መሰጠቱንና ጸሀፊዋ በኢሜል ለሀይለማርያም እንደላከላቸው መግለጿንም ጠበቃ ሀፍቶም አብራርቷል።አገር ውስጥ መሆናቸውን በሚዲያ ከመመልከት ውጪ የሚኖሩበት አድራሻን እንደማያውቁና በቀድሞ ጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት በኩል ምላሽ ተሰቶ እንደነበር አስታዋሷል።
ሀይለ ማርያም እንደሚፈለጉ አውቀዋል ይህ በሆነበት ሁኔታ ትዛዙን አያውቁም ለማለት አይቻልም ሲል ምላሽ የሰጠው ጠበቃው፤ ነገር ግን በችሎት ለመቅረብ የሚቸገሩ ከሆነ በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ ባሉበት ሆነው ምስክርነታቸው ቢሰማ አንቃወምም ብሏል።ከሳሽ ዓቃቢህግ ሀይለማርያምም ሆኑ የቀድሞ የጀርመን አንባሳደር ፍስሀ አስገዶም ካውንስለር ካሳን ጨምሮ ሌሎችም ካላቸው ሥራ ጫና አኳያ ባሉበት ሆነው ምስክርነታቸው ቢሰማ እንደማይቃወም አስተያየት መስጠቱን ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ ከችሎት ዘግባለች።
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ፍ/ቤት ታስሬ እንድቀርብ ማዘዙ አግባብ አደለም ሲሉ አቤቱታቸውን ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በጽሁፍ አቀረቡ።የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ከዚህ በፊት እንዲቀርቡ መታዘዙ እንደማያውቁና መጥሪያ እንዳልደረሳቸው ገልጸው፤ መጥርያ ተረክቤ እንቢ ባላለኩበት ሁኔታ ታስሬ እንድቀርብ በፍ/ቤት መታዘዙን አግባብ አደለም ሲሉም አቤቱታቸውን አቅርበዋል።
በጥር 30 ቀን 2014 ታስሬ እንድቀርብ መታዘዙን ማህበራዊ ሚዲያ ነው የሰማሁት ሲሉ በጽሁፍ ለፍርድ ቤቱ በላኩት አቤቱታ አብራርተዋል።በደረሳቸው አገራዊ ጥሪ መሰረት ለአገር እና ለህዝብ ጥቅም እየሰሩ መሆናቸውን ተከትሎ ለሥራ በውጭ አገር እንደሚገኙ ጠቅሰው በማንኛውም ሰዓት ለመቅረብ ታዛዥ መሆናቸውን ገልጸዋል።ሆኖም ካላቸው የሥራ ሁኔታ አንጻር በአካል ለመገኘት እንደሚቸገሩ ገልጸው፤ ነገር ግን ምስክርነቱን ባሉበት ቦታ ሆነው በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ ጥያቄውኝ ማስተናገድ እንደሚችሉ ፍርድ ቤቱ በላኩት ምላሽ አብራርተዋል።
የእነ ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ጠበቃ ሀፍቶም ከሰተ በበኩላቸው፤ ሀይለማርያም ደሳለኝ መጥሪያ መላኩን አላውቅም ፈርሜ አልተቀበልኩም ማለታቸው እንደማይቀበለው ገልጿል።በተደጋጋሚ መጥሪያ እንዲደርሳቸው መታዘዙን ተከትሎ ለሮማንና ሀይለማርያም ፋውንዴሽን ድርጅት ጸሀፊ መሰጠቱንና ጸሀፊዋ በኢሜል ለሀይለማርያም እንደላከላቸው መግለጿንም ጠበቃ ሀፍቶም አብራርቷል።አገር ውስጥ መሆናቸውን በሚዲያ ከመመልከት ውጪ የሚኖሩበት አድራሻን እንደማያውቁና በቀድሞ ጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት በኩል ምላሽ ተሰቶ እንደነበር አስታዋሷል።
ሀይለ ማርያም እንደሚፈለጉ አውቀዋል ይህ በሆነበት ሁኔታ ትዛዙን አያውቁም ለማለት አይቻልም ሲል ምላሽ የሰጠው ጠበቃው፤ ነገር ግን በችሎት ለመቅረብ የሚቸገሩ ከሆነ በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ ባሉበት ሆነው ምስክርነታቸው ቢሰማ አንቃወምም ብሏል።ከሳሽ ዓቃቢህግ ሀይለማርያምም ሆኑ የቀድሞ የጀርመን አንባሳደር ፍስሀ አስገዶም ካውንስለር ካሳን ጨምሮ ሌሎችም ካላቸው ሥራ ጫና አኳያ ባሉበት ሆነው ምስክርነታቸው ቢሰማ እንደማይቃወም አስተያየት መስጠቱን ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ ከችሎት ዘግባለች።
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ የተሾሙ አምባሳደሮች የተመደቡባቸው ሀገራት ዝርዝር ይፋ አደረገ!
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው ሳምንታዊ መግለጫቸው ጥር 18 ቀን 2014 ዓ.ም ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ኢትዮጵያን በተለያዩ ሀገሮች ለሚወክሉ አምባሳደሮች የባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት እና የአምባሳደርነት ሹመት መስጠታቸውን አስታዉሰዉ ፤በዚህም መሰረት ፤
1. አምባሳደር ተፈራ ደርበው ---ጃፓን
2. አምባሳደር ደሴ ዳልኬ---ደቡብ ኮሪያ
3. አምባሳደር ዶ/ር ስለሺ በቀለ---አሜሪካ
4. አምባሳደር ባጫ ደበሌ__ኬንያ
5. አምባሳደር ሀሰን ኢብራሂም--ግብፅ
6. አምባሳደር ዳባ ደበሌ --ሩዋንዳ
7. አምባሳደር ጀማል በከር--ፖኪሲታን
8. አምባሳደር ፈይሰል አሊይ__ኳታር
9. አምባሳደር ኢሳያስ ጎታ---ሞሮኮ
10. አምባሳደር ፀጋአብ ክበበው--አውስትራሊያ
11. አምባሳደር ምህረተአብ ሙሉጌታ---ስዊዲን
12. አምባሳደር ፍቃዱ በየነ--ኤርትራ
ተቀማጭነታቸው በኢትዮጵያ ሆኖ በተለያዩ ሀገሮች የተሾሙ አምባሳደሮች፦
13. አምባሳደር ጣፋ ቱሉ--ብራዚል
14. አምባሳደር ዶ/ር ገነት ተሾመ--ኩባ
15. አምባሳደር ሽታዬ ምናለ-- ኮትዲቯር
16. እምባሳደር ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ-ኢንዶኔዥያ
17. አምባሳደር ረሻድ መሀመድ-- ዝምባብዌ
በቆንስል ጅነራልነት የተመደቡ:
18. አምባሳደር አንተነህ ታሪኩን -ገዳሪፍ
19. አምባሳደርአክሊሉ ከበደ--ዱባይ
20. አምባሳደር ሰይድ መሐመድ-ሀርጌሳ
21. አምባሳደር አወል ወግሪስ--ባህሬን
በምክትል የሚሲዮን መሪነት፦
22. አምባሳደር አሳየ አለማየሁ--ጋና
23. አምባሳደር ኃይላይ ብርሃነ--ጀርመን
24. አምባሳደር ብዙነሽ መሠረት--ህንድ
25. አምባሳደር ዮሴፍ ካሳዬ--ኒው ዮርክ
26. አምባሳደር ዘላለም ብርሃን--ዋሽንግተን
27. አምባሳደር ፍርቱና ዲባኮ-- ቤልጅየም
28. አምባሳደር ወርቃለማሁ ደሰታ --ኬንያ
29. አምባሳደር ውብሸት ደምሴ--እንግሊዝ
30. አምባሳደር ሙሉጌታ ከሊል--ፓኪስታን ተመድበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው ሳምንታዊ መግለጫቸው ጥር 18 ቀን 2014 ዓ.ም ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ኢትዮጵያን በተለያዩ ሀገሮች ለሚወክሉ አምባሳደሮች የባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት እና የአምባሳደርነት ሹመት መስጠታቸውን አስታዉሰዉ ፤በዚህም መሰረት ፤
1. አምባሳደር ተፈራ ደርበው ---ጃፓን
2. አምባሳደር ደሴ ዳልኬ---ደቡብ ኮሪያ
3. አምባሳደር ዶ/ር ስለሺ በቀለ---አሜሪካ
4. አምባሳደር ባጫ ደበሌ__ኬንያ
5. አምባሳደር ሀሰን ኢብራሂም--ግብፅ
6. አምባሳደር ዳባ ደበሌ --ሩዋንዳ
7. አምባሳደር ጀማል በከር--ፖኪሲታን
8. አምባሳደር ፈይሰል አሊይ__ኳታር
9. አምባሳደር ኢሳያስ ጎታ---ሞሮኮ
10. አምባሳደር ፀጋአብ ክበበው--አውስትራሊያ
11. አምባሳደር ምህረተአብ ሙሉጌታ---ስዊዲን
12. አምባሳደር ፍቃዱ በየነ--ኤርትራ
ተቀማጭነታቸው በኢትዮጵያ ሆኖ በተለያዩ ሀገሮች የተሾሙ አምባሳደሮች፦
13. አምባሳደር ጣፋ ቱሉ--ብራዚል
14. አምባሳደር ዶ/ር ገነት ተሾመ--ኩባ
15. አምባሳደር ሽታዬ ምናለ-- ኮትዲቯር
16. እምባሳደር ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ-ኢንዶኔዥያ
17. አምባሳደር ረሻድ መሀመድ-- ዝምባብዌ
በቆንስል ጅነራልነት የተመደቡ:
18. አምባሳደር አንተነህ ታሪኩን -ገዳሪፍ
19. አምባሳደርአክሊሉ ከበደ--ዱባይ
20. አምባሳደር ሰይድ መሐመድ-ሀርጌሳ
21. አምባሳደር አወል ወግሪስ--ባህሬን
በምክትል የሚሲዮን መሪነት፦
22. አምባሳደር አሳየ አለማየሁ--ጋና
23. አምባሳደር ኃይላይ ብርሃነ--ጀርመን
24. አምባሳደር ብዙነሽ መሠረት--ህንድ
25. አምባሳደር ዮሴፍ ካሳዬ--ኒው ዮርክ
26. አምባሳደር ዘላለም ብርሃን--ዋሽንግተን
27. አምባሳደር ፍርቱና ዲባኮ-- ቤልጅየም
28. አምባሳደር ወርቃለማሁ ደሰታ --ኬንያ
29. አምባሳደር ውብሸት ደምሴ--እንግሊዝ
30. አምባሳደር ሙሉጌታ ከሊል--ፓኪስታን ተመድበዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዲሲፕሊን ምክንያት 146 አመራሮችንና አባላትን ማሰናበቱን አስታወቀ!
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባለፉት ስድስት ወራት የተለያዩ የዲሲፕሊን ጥፋት የተገኘባቸውን 146 የፖሊስ አመራሮችንና አባሎችን በፖሊስ ማባረሩን ዛሬ መጋቢት 7 ቀን 2014 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀ፡፡
አመራሮቹና አባለቱ የተሰናበቱት በሰራዊቱ ህግና ደንብ መሰረት መሆኑን ያስታወቀው ፖሊስ ኮሚሽኑ፣ ይሄንን አይነት እርምጃ ሊወስድ የቻለው በስነምግባርና በአቅም ከተማዋን የሚመጥን የፖሊስ ሀይል ለማደራጀት መሆኑን ገልጿል፡፡
ፖሊስ ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም በተለያየ ደረጃ የፖሊስ አባል የነበሩና በአስተዳደር ችግሮች ሳቢያ ከሰራዊቱ ወጥተው የነበሩ ከ400 በላይ የቀድሞ አባላትን፣ በድጋሚ ወደ ሠራዊቱ መቀላቀሉን አስታውቋል፡፡ ወደ ስራ ገበታቸው የተመለሱት የቀድሞ የፖሊስ አባላት፣ በሰራዊቱ ውስጥ የነበረው አሰራር ቅሬታ ስላሳደረባቸው “መስራት አንፈልግም” በማለት ወጥተው የነበሩ መሆናቸውን የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ ተናግረዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባለፉት ስድስት ወራት የተለያዩ የዲሲፕሊን ጥፋት የተገኘባቸውን 146 የፖሊስ አመራሮችንና አባሎችን በፖሊስ ማባረሩን ዛሬ መጋቢት 7 ቀን 2014 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀ፡፡
አመራሮቹና አባለቱ የተሰናበቱት በሰራዊቱ ህግና ደንብ መሰረት መሆኑን ያስታወቀው ፖሊስ ኮሚሽኑ፣ ይሄንን አይነት እርምጃ ሊወስድ የቻለው በስነምግባርና በአቅም ከተማዋን የሚመጥን የፖሊስ ሀይል ለማደራጀት መሆኑን ገልጿል፡፡
ፖሊስ ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም በተለያየ ደረጃ የፖሊስ አባል የነበሩና በአስተዳደር ችግሮች ሳቢያ ከሰራዊቱ ወጥተው የነበሩ ከ400 በላይ የቀድሞ አባላትን፣ በድጋሚ ወደ ሠራዊቱ መቀላቀሉን አስታውቋል፡፡ ወደ ስራ ገበታቸው የተመለሱት የቀድሞ የፖሊስ አባላት፣ በሰራዊቱ ውስጥ የነበረው አሰራር ቅሬታ ስላሳደረባቸው “መስራት አንፈልግም” በማለት ወጥተው የነበሩ መሆናቸውን የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ ተናግረዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በትግራይ መቐለን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ከሁለት ዓመት በኃላ በከፊል ትምህርት መጀመሩ ተገለፀ።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለዶቼቬለ እንደገለፀው በመቐለ እና ሌሎች የትግራይ አካባቢዎች የቅድመ መደበኛ የህፃናት ትምህርት እና እስከ ስድስተኛ ክፍል ያሉ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ተመልሰዋል።የተማሪ ወላጆች ግን መቋጫ ካላገኘው ጦርነት ጋር ተያይዞ ጥቃቶች ሊፈፀሙ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳላቸው ገልፀዋል።ይህ በእንዲህ እንዳለ በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ ትምህርት ተቋማት ላይ ከፍተኛ ውድመት መድረሱ የትግራይ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል። ቢሮው በቅርቡ ይፋ ባደረገው መረጃ 88 በመቶ የሚሆኑ በትግራይ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች በተለያየ ደረጃ ውድመት የደረሰባቸው ሲሆን፤235 መምህራን መገደላቸውን አስታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለዶቼቬለ እንደገለፀው በመቐለ እና ሌሎች የትግራይ አካባቢዎች የቅድመ መደበኛ የህፃናት ትምህርት እና እስከ ስድስተኛ ክፍል ያሉ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ተመልሰዋል።የተማሪ ወላጆች ግን መቋጫ ካላገኘው ጦርነት ጋር ተያይዞ ጥቃቶች ሊፈፀሙ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳላቸው ገልፀዋል።ይህ በእንዲህ እንዳለ በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ ትምህርት ተቋማት ላይ ከፍተኛ ውድመት መድረሱ የትግራይ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል። ቢሮው በቅርቡ ይፋ ባደረገው መረጃ 88 በመቶ የሚሆኑ በትግራይ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች በተለያየ ደረጃ ውድመት የደረሰባቸው ሲሆን፤235 መምህራን መገደላቸውን አስታውቋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መንግስት የዓለም አቀፉን የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር መግለጫ ነቀፈ በተለይ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም «ሆን ብለው የተሳሳተ መረጃ እያሰራጩ»ነው በማለት የኢትዮጵያ መንግስት ወቅሷል።
የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ሀላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከጀኔቭ ስዊዘር ላንድ ትናትንት በሰጡት መግለጫ በትግራይ ከፍተኛ የህክምና ቁሳቁስ እጥረትና የጤና ቀውስ መኖሩን ገልፀዋል።ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ ዛሬ ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን እንደገለፁት ፤የዓለም የጤና ድርጅት «ህክምና ቁሳቁስ ወደ ትግራይ ክልል እንዳላደርስ በመንግስት ተከልክያለሁ»ማለቱ ከእውነት የራቀ ነው ብለዋል።
የህወሃት ታጣቂዎች መንገድ በመዝጋት የህክምና ቁሳቁስ እና ሌሎች እርዳታዎች ወደ ትግራይ እንዳይደርስ እያደረጉ ነው።ያሉት ሀላፊው።እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ መንግስትን ተወቃሽ ማድረግ ትክክል አለመሆኑን ገልፀዋል።
በተለይ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም «ሆን ብለው የተሳሳተ መረጃ እያሰራጩ»ነው በማለት የኢትዮጵያ መንግስት ወቅሷል።የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ ቀደምም የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር «የድርጀቱን መርሆችና እሴቶችን የጣሰ አካሄድ እየተከተሉ» ነው የሚል ቅሬታ ለድርጅቱ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ሀላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከጀኔቭ ስዊዘር ላንድ ትናትንት በሰጡት መግለጫ በትግራይ ከፍተኛ የህክምና ቁሳቁስ እጥረትና የጤና ቀውስ መኖሩን ገልፀዋል።ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ ዛሬ ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን እንደገለፁት ፤የዓለም የጤና ድርጅት «ህክምና ቁሳቁስ ወደ ትግራይ ክልል እንዳላደርስ በመንግስት ተከልክያለሁ»ማለቱ ከእውነት የራቀ ነው ብለዋል።
የህወሃት ታጣቂዎች መንገድ በመዝጋት የህክምና ቁሳቁስ እና ሌሎች እርዳታዎች ወደ ትግራይ እንዳይደርስ እያደረጉ ነው።ያሉት ሀላፊው።እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ መንግስትን ተወቃሽ ማድረግ ትክክል አለመሆኑን ገልፀዋል።
በተለይ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም «ሆን ብለው የተሳሳተ መረጃ እያሰራጩ»ነው በማለት የኢትዮጵያ መንግስት ወቅሷል።የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ ቀደምም የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር «የድርጀቱን መርሆችና እሴቶችን የጣሰ አካሄድ እየተከተሉ» ነው የሚል ቅሬታ ለድርጅቱ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በሳውዲ አረቢያ በእሥር እና በተለያየ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን መካከል ሰላሳ አምስት ሺህ ያህሉ ወደ አገራቸው ለመመለስ መመዝገባቸው ተገለፀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ እንዳስታወቀው 100 ሺህ ዜጎችን ከሳውዲ ለምምለስ በተያዘው ዕቅድ መሠረት በእሥር ላይ የሚገኙም ሆነ በውጪ ያሉት እንዲመለሱ ይደረጋል።የሚኒስቴሩ ቃል ዐቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው መግለጫቸው የዓለም ጤና ድርጅት በትግራይ ስላለው የጤና አገልግሎት ችግር መናገራቸው ተጠቅሶ ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ዳይሬክተሩ ችግሩ በአማራም፣በአፋርም መኖሩን ቢናገሩ ተገቢ ነበር የሚል መልስ ሰጥተዋል።ኢትዮጵያ አውዳሚ ጦርነት ውስጥ የገቡት ሩሲያ እና ዩክሬን ድጋፍ ለማሰባሰብ በሚያደርጉት ጥረት ገለልተኛ አቋም ስለመያዟ እና ሁለቱ አገሮች ልዩነታቸውን በሰላማዊ መንገድ ቢፈቱ ይሻላል፣ ለዓለምም የሚበጀው ይህ ነው በሚል አቋሟን በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ግልጽ ማድረጓ በመግለጫው ተጠቅሷል።
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ እንዳስታወቀው 100 ሺህ ዜጎችን ከሳውዲ ለምምለስ በተያዘው ዕቅድ መሠረት በእሥር ላይ የሚገኙም ሆነ በውጪ ያሉት እንዲመለሱ ይደረጋል።የሚኒስቴሩ ቃል ዐቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው መግለጫቸው የዓለም ጤና ድርጅት በትግራይ ስላለው የጤና አገልግሎት ችግር መናገራቸው ተጠቅሶ ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ዳይሬክተሩ ችግሩ በአማራም፣በአፋርም መኖሩን ቢናገሩ ተገቢ ነበር የሚል መልስ ሰጥተዋል።ኢትዮጵያ አውዳሚ ጦርነት ውስጥ የገቡት ሩሲያ እና ዩክሬን ድጋፍ ለማሰባሰብ በሚያደርጉት ጥረት ገለልተኛ አቋም ስለመያዟ እና ሁለቱ አገሮች ልዩነታቸውን በሰላማዊ መንገድ ቢፈቱ ይሻላል፣ ለዓለምም የሚበጀው ይህ ነው በሚል አቋሟን በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ግልጽ ማድረጓ በመግለጫው ተጠቅሷል።
@YeneTube @FikerAssefa