በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የከተማችን ዜጎች ለ 10 ወራት የሚቆይ የገንዘብ ድጋፍ ሊደረግላቸው መሆኑን ተሰማ!
በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነታቸው ያደረጉ 350ሺህ የሚጠጉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎች በአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ወርሃዊ ድጋፍ ሊደረግላቸው መሆኑ ከሃላፊው ተሰምቷል።
የአዲስ አበባ ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደዳስታወቀው በኮሮና ቫይረስ መከሰት ምክንያት በአስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ 350 ሺህ ያህል ዜጎች ድጋፍ ሊያደርግ እንደሆነ ተነግሯል።
ድጋፉ ለሚቀጥሉት አስር ወራት የሚቆይ ሲሆን በየወሩ የአንድ ሺህ ብር ድጋፍ ያገኛሉ ብሏል፡፡የምግብ ዋስትና ጽ/ ቤት የህብረተሰብ ተሳትፎ እና አደረጃጀት የቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ረዳ እንደተናገሩት ለዚህ መርሀ ግብር ማስፈጸሚያ የሚሆን 1 ቢሊየን 51ሚሊየን ብር ከአለም ባንክ በኩል መገኘቱን ተናግረዋል፡፡
በ350ሺህ ዜጎች ተጠቃሚ ካደርጋል በተባለለት በዚህ መርሃ ግብር እስከ አሁን በሁሉም ክፍለ ከተሞች ደረጃ 290ሺህ ያህል ዜጎች ተለይተዋል ብለዋል፡፡ቀሪዎቹን 60 ሺህ የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚ ዜጎች የመለየቱ ስራ ደግሞ በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ አቶ ብርሀኑ ተናግረዋል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነታቸው ያደረጉ 350ሺህ የሚጠጉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎች በአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ወርሃዊ ድጋፍ ሊደረግላቸው መሆኑ ከሃላፊው ተሰምቷል።
የአዲስ አበባ ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደዳስታወቀው በኮሮና ቫይረስ መከሰት ምክንያት በአስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ 350 ሺህ ያህል ዜጎች ድጋፍ ሊያደርግ እንደሆነ ተነግሯል።
ድጋፉ ለሚቀጥሉት አስር ወራት የሚቆይ ሲሆን በየወሩ የአንድ ሺህ ብር ድጋፍ ያገኛሉ ብሏል፡፡የምግብ ዋስትና ጽ/ ቤት የህብረተሰብ ተሳትፎ እና አደረጃጀት የቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ረዳ እንደተናገሩት ለዚህ መርሀ ግብር ማስፈጸሚያ የሚሆን 1 ቢሊየን 51ሚሊየን ብር ከአለም ባንክ በኩል መገኘቱን ተናግረዋል፡፡
በ350ሺህ ዜጎች ተጠቃሚ ካደርጋል በተባለለት በዚህ መርሃ ግብር እስከ አሁን በሁሉም ክፍለ ከተሞች ደረጃ 290ሺህ ያህል ዜጎች ተለይተዋል ብለዋል፡፡ቀሪዎቹን 60 ሺህ የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚ ዜጎች የመለየቱ ስራ ደግሞ በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ አቶ ብርሀኑ ተናግረዋል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የግድቡ ግንባታ እንዲቆም ኢትዮጲያ አልተፈራረመችም ሲሉ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ!
የታላቁ የኢትዮጲያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲቆም ኢትዮጲያ የተፈራረመችው ምንም ነገር የለም ሲሉ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል።አምባሳደር ዲና በዛሬው እለት ሳምንታዊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ ማብራሪያ በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።
የግድቡ ግንባታ እስከቀጠለ ድረስ የማመንጨት ሂደት ላይ ይደርሳል ሲሉ ተናግረዋል። እ.ኤ.አ በ2015 በሱዳን መዲና ካርቱም ላይ የተፈረመው የሶስትዮሽ ስምምነት የግድቡ ግንባታ እንዲቆም የተደረሰበት አይደለም ሲሉ አስታውሰዋል።
አሁን ላይ የህግና የቴክኒክ ጉዳይ ላይ እየተሰራ ይገኛል ድርድሩ እንዲቆም ኢትዮጵያ አላደረገች፤ በኢትዮጵያ በኩል ያለው አቋም በቀሩት ልዩነቶች ላይ መወያያት ነው ሲሉ ገልፀዋል።የተገደበው ውሃ የግድቡን ተርባይን ሲመታ ወደ ታች ይወርዳል፤ እንዲሁም ቀደም ሲል በትነት ይባክን የነበረው በመገደቡ ጥቅሙ ለጋራችን ነው ሲሉ አምባሳደር ዲና መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።
የታላቁ የኢትዮጲያ የህዳሴ ግድብ በተለይ ለሱዳን የተለየ ጥቅም አለው፤ ግብፅ እና ሱዳን በርካሽ ዋጋ ኃይል መጠቀም ይችላሉ ሲሉ አክለዋል።የሚያዋጣን በናይል ወንዝ ላይ አብረን ማደግ ነው መናቆሩ አይጠቅም በተፋሰሱ በጋራ መጠቀም እንችላለን ወዳጆቻችን ይህንኑ እንዲያስተላልፉ ነው የምንፈልገው ሲሉም ጨምረው ተናግረዋል።
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
የታላቁ የኢትዮጲያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲቆም ኢትዮጲያ የተፈራረመችው ምንም ነገር የለም ሲሉ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል።አምባሳደር ዲና በዛሬው እለት ሳምንታዊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ ማብራሪያ በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።
የግድቡ ግንባታ እስከቀጠለ ድረስ የማመንጨት ሂደት ላይ ይደርሳል ሲሉ ተናግረዋል። እ.ኤ.አ በ2015 በሱዳን መዲና ካርቱም ላይ የተፈረመው የሶስትዮሽ ስምምነት የግድቡ ግንባታ እንዲቆም የተደረሰበት አይደለም ሲሉ አስታውሰዋል።
አሁን ላይ የህግና የቴክኒክ ጉዳይ ላይ እየተሰራ ይገኛል ድርድሩ እንዲቆም ኢትዮጵያ አላደረገች፤ በኢትዮጵያ በኩል ያለው አቋም በቀሩት ልዩነቶች ላይ መወያያት ነው ሲሉ ገልፀዋል።የተገደበው ውሃ የግድቡን ተርባይን ሲመታ ወደ ታች ይወርዳል፤ እንዲሁም ቀደም ሲል በትነት ይባክን የነበረው በመገደቡ ጥቅሙ ለጋራችን ነው ሲሉ አምባሳደር ዲና መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።
የታላቁ የኢትዮጲያ የህዳሴ ግድብ በተለይ ለሱዳን የተለየ ጥቅም አለው፤ ግብፅ እና ሱዳን በርካሽ ዋጋ ኃይል መጠቀም ይችላሉ ሲሉ አክለዋል።የሚያዋጣን በናይል ወንዝ ላይ አብረን ማደግ ነው መናቆሩ አይጠቅም በተፋሰሱ በጋራ መጠቀም እንችላለን ወዳጆቻችን ይህንኑ እንዲያስተላልፉ ነው የምንፈልገው ሲሉም ጨምረው ተናግረዋል።
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
ራሺያ በዩክሬን ላይ የቀጥታ ጦርነት መክፈቷ ከተሰማ በኋላ ለደህንነታቸው የሰጉ የኪየቭ ነዋሪዎች ከተማዋን ለቀው እየሸሹ ይገኛሉ።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
በልደታ ክ/ከተማ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ 4 አመራሮችና ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ!
በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ 4 አመራሮችና ባለሙያዎች በአዲስ አበባ ፓሊስ መምሪያና በማህበርሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ዋሉ።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ከአዲሱ የአመራር ምደባ በፊት የመሬት ልማት ማኔጅመንት ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የመሬት ልማት ማኔጅመንት ፋይናንስ አስተዳደር ፑል ጽ/ቤት ሀላፊ እንዲሁም በፑሉ የግዥ ቡድን መሪና የግዥ ባለሙያ መሆናቸው ተገልጿል።
አስተዳደሩ የደረሰበትን በየጊዜው ለህዝቡ እንደሚያሳውቅ እንዲሁም ሙስናና ብልሹ አሰራርንም በቁርጠኝነት እንደሚታገል መግለፁን ከልደታ ክ/ከ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
[AMN]
@YeneTube @FikerAssefa
በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ 4 አመራሮችና ባለሙያዎች በአዲስ አበባ ፓሊስ መምሪያና በማህበርሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ዋሉ።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ከአዲሱ የአመራር ምደባ በፊት የመሬት ልማት ማኔጅመንት ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የመሬት ልማት ማኔጅመንት ፋይናንስ አስተዳደር ፑል ጽ/ቤት ሀላፊ እንዲሁም በፑሉ የግዥ ቡድን መሪና የግዥ ባለሙያ መሆናቸው ተገልጿል።
አስተዳደሩ የደረሰበትን በየጊዜው ለህዝቡ እንደሚያሳውቅ እንዲሁም ሙስናና ብልሹ አሰራርንም በቁርጠኝነት እንደሚታገል መግለፁን ከልደታ ክ/ከ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
[AMN]
@YeneTube @FikerAssefa
የሩሲያን ወታደራዊ ጥቃት ተከትሎ ኪዬቭ ከሞስኮ ጋር የነበራትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በይፋ ማቋረጧን አስታወቀች።
ይህ የተገለጸው የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮሎደሚየር ዜሌኒስኪ በሰጡት መግለጫ ነው።
ፕሬዝደንቱ በዚህ መግለጫቸው ፍላጎት ያላቸውን የዩክሬን ዜጎች በሙሉ መንግሥታቸው እንደሚያስታጥቅ ተናግረዋል።
ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ፍጥጫ ውስጥ መግባቷን ተከትሎ ለሲቪል ዜጎቿ መሠረታዊ ወታደራዊ ስልጠና ስትሰጥ ቆይታለች።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ይህ የተገለጸው የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮሎደሚየር ዜሌኒስኪ በሰጡት መግለጫ ነው።
ፕሬዝደንቱ በዚህ መግለጫቸው ፍላጎት ያላቸውን የዩክሬን ዜጎች በሙሉ መንግሥታቸው እንደሚያስታጥቅ ተናግረዋል።
ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ፍጥጫ ውስጥ መግባቷን ተከትሎ ለሲቪል ዜጎቿ መሠረታዊ ወታደራዊ ስልጠና ስትሰጥ ቆይታለች።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት በእንግሊዝኛ ምህጻሩ ኔቶ ዛሬ ሐሙስ ካደረገው አስቸኳይ ስብሰባ በኋላ ዩክሬን እና ሩሲያ በሚዋሰኑበት ምሥራቃዊ ግዛት የምድር፣ የባህር እና የአየር ኃይሉን ለማጠናከር መወሰኑን አስታወቀ።
የኔቶ አምባሳደሮች ባወጡት መግለጫ "በጥምረቱ ምሥራቃዊ ክፍል ተጨማሪ የምድር፣ የአየር እና የባህር መከላከያ ኃይል ልናሰማራ ነው" ብለዋል። የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ የንስ ስቶልተንበርግ በምሥራቃዊ አውሮፓ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን የመከላከያ ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ መወሰኑን ለጋዜጠኞች አረጋግጠዋል።
የድርጅቱ አባላት የሆኑት የምስራቅ አዉሮጳ ሐገራት ኢስቶኒያ፣ ላቲቪያ፣ ሉቱኒያ እና ፖላንድ የሰሜን የግዛት አንድነት፣ የፖለቲካ ነጻነት ወይም ጸጥታ አደጋ ውስጥ ሲወድቅ ሌላ ስብስባ እንዲጠራ ጠይቀዋል። ለግጭቱ ቅርበት ካላቸው አገራት አንዷ የሆነችው ሉቱኒያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደንግጋለች።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የኔቶ አምባሳደሮች ባወጡት መግለጫ "በጥምረቱ ምሥራቃዊ ክፍል ተጨማሪ የምድር፣ የአየር እና የባህር መከላከያ ኃይል ልናሰማራ ነው" ብለዋል። የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ የንስ ስቶልተንበርግ በምሥራቃዊ አውሮፓ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን የመከላከያ ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ መወሰኑን ለጋዜጠኞች አረጋግጠዋል።
የድርጅቱ አባላት የሆኑት የምስራቅ አዉሮጳ ሐገራት ኢስቶኒያ፣ ላቲቪያ፣ ሉቱኒያ እና ፖላንድ የሰሜን የግዛት አንድነት፣ የፖለቲካ ነጻነት ወይም ጸጥታ አደጋ ውስጥ ሲወድቅ ሌላ ስብስባ እንዲጠራ ጠይቀዋል። ለግጭቱ ቅርበት ካላቸው አገራት አንዷ የሆነችው ሉቱኒያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደንግጋለች።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በቼርኖቤል ኒውክሌር ጣቢያ አቅራቢያ ጦርነት መቀስቀሱን ተናገሩ!
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት በትዊተር ገጻቸው ላይ “የሩሲያ ወረራ ሃይሎች የቼርኖቤል የኒውክሌር ሃይል ማመንጫ ጣቢያን ለመያዝ እየሞከሩ ነው” ሲሉ ለጥፈዋል።
ዘለንስኪ ወታደሮቹ ተቋሙን እየተከላከሉ መሆናቸውን እና የተጠረጠረውን ጥቃት ለስዊድን ጠ/ሚ እንዳሳወቁ ተናግሯል። ፕሬዚዳንቱ አክለውም “ይህ በመላው አውሮፓ ላይ የታወጀ የጦርነት ነው” ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት በትዊተር ገጻቸው ላይ “የሩሲያ ወረራ ሃይሎች የቼርኖቤል የኒውክሌር ሃይል ማመንጫ ጣቢያን ለመያዝ እየሞከሩ ነው” ሲሉ ለጥፈዋል።
ዘለንስኪ ወታደሮቹ ተቋሙን እየተከላከሉ መሆናቸውን እና የተጠረጠረውን ጥቃት ለስዊድን ጠ/ሚ እንዳሳወቁ ተናግሯል። ፕሬዚዳንቱ አክለውም “ይህ በመላው አውሮፓ ላይ የታወጀ የጦርነት ነው” ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል የገላን ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በተራራ ኔትዎርክ የበይነ መረብ ብዙኀን መገናኛ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ታምራት ነገራ ላይ ዛሬ የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንደፈቀደ ተራራ ኔትዎርክ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ዘግቧል።
የዛሬው ችሎት ቀጠሮ የፖሊስን የምርመራ ውጤት ለመስማት ቢሆንም፣ ፖሊስ ግን የተጠርጣሪውን ስልክ እና ኮምፒውተሮች ለመበርበር ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል በማለቱ ነው የጠየቀው ጊዜ የተፈቀደለት። የጋዜጠኛው ጠበቃ የፖሊስ የሽብር ክስ በሕጉ መሠረት ወደ ክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት መዛወር እንዳለበት ያቀረቡትን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጓል።
✍Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
የዛሬው ችሎት ቀጠሮ የፖሊስን የምርመራ ውጤት ለመስማት ቢሆንም፣ ፖሊስ ግን የተጠርጣሪውን ስልክ እና ኮምፒውተሮች ለመበርበር ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል በማለቱ ነው የጠየቀው ጊዜ የተፈቀደለት። የጋዜጠኛው ጠበቃ የፖሊስ የሽብር ክስ በሕጉ መሠረት ወደ ክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት መዛወር እንዳለበት ያቀረቡትን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጓል።
✍Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
የሩሲያ ወታደሮች ወደ ዋና ከተማ ኪዬቭ ተቃርበዋል ተባለ!
የሩሲያ አየር ወለዶች ከዩክሬን መዲና ኪዬቭ በ30 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ይገኛሉ።ከረፋድ ጀምሮ የሩሲያ አየር ወለዶች የዩክሬንን አንቶኖቭ ጦር ካምፕን በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ የዩክሬን ብሔራዊ ዘብ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ መጀመሩን አስታውቋል።በምድር፣ በአየርና በባሕር ሐሙስ ጠዋት በዩክሬን ላይ ጥቃት የከፈተችው ሩሲያ ከፍተኛ ውግዘት እየገጠማት ቢሆንም ዘመቻዋን ቀጥላለች።
የሩሲያ ጦር በተለያዩ አቅጣጫዎች ጥቃት የከፈተ ሲሆን ብረተ ለበስ ሜካናይዝድ ጦር ፈጣን ግስጋሴ እያደረገ ነው።በዚህም ከደቡብ አቅጣጫ በቤላሩስ ድንበር በኩል እንዲሁም በሰሜን ከክሬሚያ አቅጣጫ ወደ ዩክሬን አምርቷል።በኪዬቭ የሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ ፖል አደምስ ሩሲያ በቀጣይ ምን ልታደርግ እንደምትችል ግልጽ አይደለም ብሏል።
ምናልባት የአየር ኃይሉን ጦር ካምፕ የተቆጣጠሩት አየር ወለዶች ባሉበት ሆነው ሜካናይዝድ ጦሩን ሊጠብቁ እንደሚችሉ አመልክቷል።አልያም አየር ወለዶቹ የያዙትን የአየር ኃይል ካምፕ በኪዬቭ ላይ የአየር ጥቃት ለመክፈት ይጠቀሙበት ይሆናል ብሏል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የሩሲያ አየር ወለዶች ከዩክሬን መዲና ኪዬቭ በ30 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ይገኛሉ።ከረፋድ ጀምሮ የሩሲያ አየር ወለዶች የዩክሬንን አንቶኖቭ ጦር ካምፕን በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ የዩክሬን ብሔራዊ ዘብ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ መጀመሩን አስታውቋል።በምድር፣ በአየርና በባሕር ሐሙስ ጠዋት በዩክሬን ላይ ጥቃት የከፈተችው ሩሲያ ከፍተኛ ውግዘት እየገጠማት ቢሆንም ዘመቻዋን ቀጥላለች።
የሩሲያ ጦር በተለያዩ አቅጣጫዎች ጥቃት የከፈተ ሲሆን ብረተ ለበስ ሜካናይዝድ ጦር ፈጣን ግስጋሴ እያደረገ ነው።በዚህም ከደቡብ አቅጣጫ በቤላሩስ ድንበር በኩል እንዲሁም በሰሜን ከክሬሚያ አቅጣጫ ወደ ዩክሬን አምርቷል።በኪዬቭ የሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ ፖል አደምስ ሩሲያ በቀጣይ ምን ልታደርግ እንደምትችል ግልጽ አይደለም ብሏል።
ምናልባት የአየር ኃይሉን ጦር ካምፕ የተቆጣጠሩት አየር ወለዶች ባሉበት ሆነው ሜካናይዝድ ጦሩን ሊጠብቁ እንደሚችሉ አመልክቷል።አልያም አየር ወለዶቹ የያዙትን የአየር ኃይል ካምፕ በኪዬቭ ላይ የአየር ጥቃት ለመክፈት ይጠቀሙበት ይሆናል ብሏል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
አስደሳች ዜና 12ኛ ክፍል ለጨረሳቹ እና በመማር ላይ ላላቹ!!!
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
ማራኪ አማካሪ በ ካናዳ 🇨🇦 አሜሪካ 🇺🇸 እና ፖላንድ 🇵🇱 የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የምትችሉበትን ዕድል አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
እርሶም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ዛሬዉኑ ያለ ቅድመ ክፍያ ይመዝገቡ!
በቡድን ለሚመዘገቡ ቅናሽ አዘጋጅተናል
የተማሪዎቻችንን ምስክርነት ለመመልከት የ ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ
@marakiconsultancy
አድራሻ: ቦሌ ሸዋ ዳቦ ጌቱ የንግድ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102
ስልክ: 0960612222
0118345171
ለበለጠ መረጃ @marakiapplication
የሻረግ_ቅመማ_ቅመም
#YesharegSpices
የተለያዩ ቅመማ ቅመሞችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ሲፈልጉ የሻረግ ቅመማ ቅመም ብለው ይጠይቁ
🔔 አዲስ አበባ በሚገኙ ሱፐር ማርኬቶች ያገኙናል
☎️ +251 911 66 47 75
+251 911 87 28 27
🔴 የሻረግ ቅመማ ቅመም
ምርጥ ጣዕም❗️
#YesharegSpices
የተለያዩ ቅመማ ቅመሞችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ሲፈልጉ የሻረግ ቅመማ ቅመም ብለው ይጠይቁ
🔔 አዲስ አበባ በሚገኙ ሱፐር ማርኬቶች ያገኙናል
☎️ +251 911 66 47 75
+251 911 87 28 27
🔴 የሻረግ ቅመማ ቅመም
ምርጥ ጣዕም❗️
https://youtu.be/sG0S6CNbmvw
Check out and subscribe to our youtube channel to get recommendations on amazing movies and tvshows.
የፊልሞች እና የቲቪ ምርጫዎችን ለማግኘት የዩቲዩብ ቻናላችንን ይመልከቱ እና ሰብስክራይብ ያድርጉ።
https://youtu.be/5O1i0ZvTYMgb
Check out and subscribe to our youtube channel to get recommendations on amazing movies and tvshows.
የፊልሞች እና የቲቪ ምርጫዎችን ለማግኘት የዩቲዩብ ቻናላችንን ይመልከቱ እና ሰብስክራይብ ያድርጉ።
https://youtu.be/5O1i0ZvTYMgb
ለ 12 ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ውጤት በመለቀቁ እያልን !
ወደ ውጭ ሀገሮች ሄዳችሁ Scholarship መማር ለምትፈልጉ ተማሪዎች በሙሉ ወደ 👇👇👇👇
👉🇨🇦 ካናዳ
👉🇺🇸 አሜሪካ
👉🇦🇺 አውስትራሊያ
👉🇪🇺 አውሮፓ
👉🇬🇧 እንግሊዝ
ሌሎችም ሀገሮች ላይም apply ማድረግ ለምትፈልጉ ምዝገባ የጀመርን መሆኑን እየገለጽን
ለመመዝገብ 📞☎️
@Sabinavisa
@Sabinavisa2
0936363639
0936363680
ወደ ውጭ ሀገሮች ሄዳችሁ Scholarship መማር ለምትፈልጉ ተማሪዎች በሙሉ ወደ 👇👇👇👇
👉🇨🇦 ካናዳ
👉🇺🇸 አሜሪካ
👉🇦🇺 አውስትራሊያ
👉🇪🇺 አውሮፓ
👉🇬🇧 እንግሊዝ
ሌሎችም ሀገሮች ላይም apply ማድረግ ለምትፈልጉ ምዝገባ የጀመርን መሆኑን እየገለጽን
ለመመዝገብ 📞☎️
@Sabinavisa
@Sabinavisa2
0936363639
0936363680
በእሳት አደጋ የአንድ ቤተሰብ ልጆች የሆኑ ወንድም እና እህት ህይወታቸዉ አለፈ!
በትላንትናዉ እለት ከቀኑ ዘጠኝ ሰአት ከሀያ ደቂቃ ላይ አራብሳ ኮንደሚኒየም ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ የስድስት አመት እድሜ ያለው ህጻን ህይወቱ ሲያልፍ እድሜዋ 10 አመት የሆነች የሟች እህት በጭስ የመታፈን አደጋ ደርሶባት ወደ ሆስፒታል ገብታ ነበር፡፡ሆኖም በተደረገላት የህክምና ድጋፍ መትረፍ ሳትችል ህይወቷ አልፏል፡፡
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አራብሳ ኮንደሚኒየም ብሎክ ሰላሳ አራት 2ኛ ፎቅ ላይ አደጋው መድረሱን ገልፀዋል።አደጋው ሲደርስ በጋራ መኖሪያ ቤት ውስጥ የምትኖር የ18 አመት እድሜ ያላት የቤት ውስጥ ሰራተኛ ከ5ኛ ፎቅ ላይ ዘላ ራሷን ለማዳን ባደረገችዉ ሙከራ ከባድ ጉዳት እንደረሰባት ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡
በእሳት አደጋዉ 50 ሺህ ብር የተገመተ ንብረት ሲወድም የእሳት አደጋ ሰራተኞች ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ተዛምቶ ከዚህ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ እሳቱን መቆጣጠር ችለዋል። በኮንዶሚኒየም ቤቶች አልፎ አልፎም ቢሆን አደጋ እያጋጠመ በመሆኑና የአደጋዉ ምክንያትም በአብዛኛዉ ኤሌክትሪክ በመሆኑ በኤሌክትሪክ አጠቃቀም ወቅት ተገቢዉ ጥንቃቄ እንዲረግና የኤሌክትሪክ መስመሮቻችን በባለሞያ ማስፈተሽ እንደሚያስፈልግ አቶ ንጋቱ አሳስበዋል፡፡የትላንትናዉ የእሳት አደጋ በኤሌክትሪክ ምክንያት የተነሳ እንደሆነ ገልፀዋል።
የኮንደሚኒየም ቤቶች የአደጋ ጊዜ ማምለጫ ደረጃዎችም ሊታሰብበት የሚገባው ጉዳይ እንደሆነም ኮሚሽኑ አስታውቋል።
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
በትላንትናዉ እለት ከቀኑ ዘጠኝ ሰአት ከሀያ ደቂቃ ላይ አራብሳ ኮንደሚኒየም ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ የስድስት አመት እድሜ ያለው ህጻን ህይወቱ ሲያልፍ እድሜዋ 10 አመት የሆነች የሟች እህት በጭስ የመታፈን አደጋ ደርሶባት ወደ ሆስፒታል ገብታ ነበር፡፡ሆኖም በተደረገላት የህክምና ድጋፍ መትረፍ ሳትችል ህይወቷ አልፏል፡፡
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አራብሳ ኮንደሚኒየም ብሎክ ሰላሳ አራት 2ኛ ፎቅ ላይ አደጋው መድረሱን ገልፀዋል።አደጋው ሲደርስ በጋራ መኖሪያ ቤት ውስጥ የምትኖር የ18 አመት እድሜ ያላት የቤት ውስጥ ሰራተኛ ከ5ኛ ፎቅ ላይ ዘላ ራሷን ለማዳን ባደረገችዉ ሙከራ ከባድ ጉዳት እንደረሰባት ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡
በእሳት አደጋዉ 50 ሺህ ብር የተገመተ ንብረት ሲወድም የእሳት አደጋ ሰራተኞች ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ተዛምቶ ከዚህ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ እሳቱን መቆጣጠር ችለዋል። በኮንዶሚኒየም ቤቶች አልፎ አልፎም ቢሆን አደጋ እያጋጠመ በመሆኑና የአደጋዉ ምክንያትም በአብዛኛዉ ኤሌክትሪክ በመሆኑ በኤሌክትሪክ አጠቃቀም ወቅት ተገቢዉ ጥንቃቄ እንዲረግና የኤሌክትሪክ መስመሮቻችን በባለሞያ ማስፈተሽ እንደሚያስፈልግ አቶ ንጋቱ አሳስበዋል፡፡የትላንትናዉ የእሳት አደጋ በኤሌክትሪክ ምክንያት የተነሳ እንደሆነ ገልፀዋል።
የኮንደሚኒየም ቤቶች የአደጋ ጊዜ ማምለጫ ደረጃዎችም ሊታሰብበት የሚገባው ጉዳይ እንደሆነም ኮሚሽኑ አስታውቋል።
[ዳጉ ጆርናል]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ በ196 ሚሊየን ብር ወጪ ዘመናዊውን ዲጂታል የነዋሪነት መታወቂያ የክፍለ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሰሩት ለማስቻል 150 ማተሚያ ማሽኖችን ገዝቶ ለክፍለ ከተሞች ማከፋፈሉን ለዋዜማ ተናግሯል፡፡ ከዚህ ቀደም ዘመናዊ መታወቂያው በኤጀንሲው በኩል ብቻ የሚሰጥ የነበረ ሲሆን መታወቂያውን ለማግኘት ሁለት ወር ለሚጠጋ ጊዜ መጠበቅ ያስፈልግ ነበር።
[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
[Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢንዶኔዥያ ሱማትራ አቅራቢያ በ6.2 በሬክተር ስኬል በተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ 2 ሰዎች ሞቱ!
በኢንዶኔዥያ ዛሬ በተከሰተ በከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ 2 ሰዎች ሲሞቱ 20 ሰዎች ላይ አካላዊ ጉዳት አስከትሏል።ከኮረብታ ቡኪቲንግጊ ከተማ 66 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኙ ህንፃዎችን አፈራርሷል።እንደ ሀገሪቱ ባለሥልጣናቱ ገለጻ የመሬት መንሸራተት መከሰቱንና በጎረቤት ማሌዢያ እና ሲንጋፖርም ተፅዕኖዎች ማሳደሩን ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በኢንዶኔዥያ ዛሬ በተከሰተ በከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ 2 ሰዎች ሲሞቱ 20 ሰዎች ላይ አካላዊ ጉዳት አስከትሏል።ከኮረብታ ቡኪቲንግጊ ከተማ 66 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኙ ህንፃዎችን አፈራርሷል።እንደ ሀገሪቱ ባለሥልጣናቱ ገለጻ የመሬት መንሸራተት መከሰቱንና በጎረቤት ማሌዢያ እና ሲንጋፖርም ተፅዕኖዎች ማሳደሩን ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
“በሳዑዲ ዓረቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ዜጎችን በአጭር ጊዜ ለመመለስ እየተሠራ ነው” - አምባሳደር ሌንጮ ባቲ
በሳዑዲ ዓረቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን በአጭር ጊዜ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ከሀገሪቱ መንግሥት ጋር በቅርበት እየተሠራ መሆኑን በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።
በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሌንጮ ባቲ፣ በተለያየ ምክንያት በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ ገብተው ለእስር እና ለእንግልት የተዳረጉ ኢትዮጵያውያንን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ጋር በቅርበት እየሠራ ነው ብለዋል።
ከሳዑዲ የሚመለሱ ዜጎችን በተመለከተ ከተመለሱ በኋላ ችግር ላይ እንዳይወድቁ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የሚመራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ከክልሎች ጋር ወደ ሥራ መግባቱንም ተናግረዋል።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
በሳዑዲ ዓረቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን በአጭር ጊዜ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ከሀገሪቱ መንግሥት ጋር በቅርበት እየተሠራ መሆኑን በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።
በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሌንጮ ባቲ፣ በተለያየ ምክንያት በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ ገብተው ለእስር እና ለእንግልት የተዳረጉ ኢትዮጵያውያንን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ጋር በቅርበት እየሠራ ነው ብለዋል።
ከሳዑዲ የሚመለሱ ዜጎችን በተመለከተ ከተመለሱ በኋላ ችግር ላይ እንዳይወድቁ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የሚመራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ከክልሎች ጋር ወደ ሥራ መግባቱንም ተናግረዋል።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
ሩሲያ በፈፀመችው ጥቃት በዋና ከተማዋ በኪየቭ የሟቾች ቁጥር 137 ሲደርስ 316 ወታደሮች እና ሲቪሎች መቁሰላቸውም ታውቋል፡፡
የዩክሬን ታጣቂ ሃይሎች በ3 DPR ሰፈሮች ላይ ከባድ መሳሪያ መተኮሳቸው የተነገረ ሲሆን በዚህም 2 ሰዎች ሲሞቱ 12 ያክሉ ደግሞ ቆስለዋል ሲሉ የDPR አካባቢ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
የዩክሬን ሃይሎች በሮስቶቭ ክልል ሚሎሮቮ የሚገኘውን ወታደራዊ አየር ማረፊያ ቶቺካ በተሰኘው ሚሳኤል መምታታቸውን ያልተረጋገጠ ዘገባዎች አመላክተዋል ሲል RT ኒውስ ዘግቧል፡፡
የዩክሬን ሃይሎች ከኪየቭ 70 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ያለውን ቁልፍ ድልድይ ማፈንዳታቸውንም ዘገባው አክሏል፡፡
በሁሉም የኪየቭ አካባቢዎችም በአንድ ሌሊት በርካታ ፍንዳታዎች ተዘግበዋል።
አውሮፕላንም ከህንጻ ጋር መጋጨቱና የቪታሊ ከንቲባን ጨምሮ ሶስት ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል፡፡
ይህ ሁሉ እየሆነ ባለበት የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በቼርኖቤል በዋና ከተማዋ በኪየቭ እንደሚቆዩ አስታውቀዋል፡፡
ከ100,000 በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል ሲል የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ ማስታወቁን የሩሲያው አርቲ የዜና ወኪል ዘግቧል።
Via Ethio FM
@Yenetube @Fikerassefa
የዩክሬን ታጣቂ ሃይሎች በ3 DPR ሰፈሮች ላይ ከባድ መሳሪያ መተኮሳቸው የተነገረ ሲሆን በዚህም 2 ሰዎች ሲሞቱ 12 ያክሉ ደግሞ ቆስለዋል ሲሉ የDPR አካባቢ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
የዩክሬን ሃይሎች በሮስቶቭ ክልል ሚሎሮቮ የሚገኘውን ወታደራዊ አየር ማረፊያ ቶቺካ በተሰኘው ሚሳኤል መምታታቸውን ያልተረጋገጠ ዘገባዎች አመላክተዋል ሲል RT ኒውስ ዘግቧል፡፡
የዩክሬን ሃይሎች ከኪየቭ 70 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ያለውን ቁልፍ ድልድይ ማፈንዳታቸውንም ዘገባው አክሏል፡፡
በሁሉም የኪየቭ አካባቢዎችም በአንድ ሌሊት በርካታ ፍንዳታዎች ተዘግበዋል።
አውሮፕላንም ከህንጻ ጋር መጋጨቱና የቪታሊ ከንቲባን ጨምሮ ሶስት ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል፡፡
ይህ ሁሉ እየሆነ ባለበት የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በቼርኖቤል በዋና ከተማዋ በኪየቭ እንደሚቆዩ አስታውቀዋል፡፡
ከ100,000 በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል ሲል የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ ማስታወቁን የሩሲያው አርቲ የዜና ወኪል ዘግቧል።
Via Ethio FM
@Yenetube @Fikerassefa
👍1
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ዐቢይ ጾምን በማስመልከት ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ!
ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የዐቢይ ጾም መግባትን አስመልክተው ዛሬ የካቲት 18/2014 ዓ.ም ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አሁን ላይ ልባችን እንደሚመስክርብን ያለንበት ጊዜ ጥል ያየለበት ጭካኔ ስር የሰደደብት እንደሆነ አይካድም በዚህ ምክንያት የብዙ ልጆቻችን ሕይወት ተቀጠፎአል ተመስቃቅሏል ጥላቻ ቦታ ካገኝ ውጤቱ ክዚህ ሌላ ሊሆን አይችልምና ይህን ሁሉ አስከትሎብናል።
በዙም ወርኃ ጾም ንሥሐ መግባት አልበን ስንል የከረምነበትን የጥላቻ ሕሊና ከስር መሰረቱ ነቅለን በመጣል ፤ፍቅርንና ሰላምን በመሻት ወደ እግዚአብሔር መቀረብ አለብን ሲሉ ቅዱስ ፓትርያርኩ ተናግረዋል።
በመዋዕለ ጾሙ ስለሐገርና ሰለ ቤተክርስቲያናን አንድነት፤ ስለህዝባችን ዘላቂ ፍቅርና ስምምነት አጥብቀን እንድንጸልይ እንዲሁም በግጭትና በድርቁ ለትጎዱ ወገኖቻችን ካለን በማካፈል ምዕመኑ የችግሩ ተካፋይ እንዲሆን ቤተክርስቲያን መለዕክቷን አስተላልፋለች።
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa
ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የዐቢይ ጾም መግባትን አስመልክተው ዛሬ የካቲት 18/2014 ዓ.ም ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አሁን ላይ ልባችን እንደሚመስክርብን ያለንበት ጊዜ ጥል ያየለበት ጭካኔ ስር የሰደደብት እንደሆነ አይካድም በዚህ ምክንያት የብዙ ልጆቻችን ሕይወት ተቀጠፎአል ተመስቃቅሏል ጥላቻ ቦታ ካገኝ ውጤቱ ክዚህ ሌላ ሊሆን አይችልምና ይህን ሁሉ አስከትሎብናል።
በዙም ወርኃ ጾም ንሥሐ መግባት አልበን ስንል የከረምነበትን የጥላቻ ሕሊና ከስር መሰረቱ ነቅለን በመጣል ፤ፍቅርንና ሰላምን በመሻት ወደ እግዚአብሔር መቀረብ አለብን ሲሉ ቅዱስ ፓትርያርኩ ተናግረዋል።
በመዋዕለ ጾሙ ስለሐገርና ሰለ ቤተክርስቲያናን አንድነት፤ ስለህዝባችን ዘላቂ ፍቅርና ስምምነት አጥብቀን እንድንጸልይ እንዲሁም በግጭትና በድርቁ ለትጎዱ ወገኖቻችን ካለን በማካፈል ምዕመኑ የችግሩ ተካፋይ እንዲሆን ቤተክርስቲያን መለዕክቷን አስተላልፋለች።
[Asham]
@YeneTube @FikerAssefa