ከ100 በላይ ሰዎች ከሞሮኮ በዉሃ ዋና ወደ ስፔን የወደብ ከተማ ሲዉታ መግባታቸዉ ተሰማ
የስፔን መንግስት እንዳስታወቀዉ ከ100 በላይ የሆኑ ስደተኞች በአንድ ሌሊት ከሞሮኮ ወደ ስፔን ሲውታ አከባቢ በባህር ዳርቻ ተንሳፋፊ አካል በመጠቀም እና በዋና መግባታቸዉን ይፋ አድርጓል፡፡
የስፔን የመገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ከሆነ የሞሮኮ ድንበር ጠባቂዎች ይህ ሁኔታ ሲፈጠር በአጠገባቸው ቆመው ስደተኞቹ ራሳቸውን ለአደጋ ሲያጋልጡ እየተመለከቱ ነበር ሲሉ ዘግበዋል፡፡
አብዛኛዎቹ ስደተኞች የመጡት በሰሜናዊው የቤንዙ ዳርቻ አካባቢ ሲሆን የተወሰኑት በስተደቡብ በኩል ታራላል በተባለዉ የባህር ዳርቻ ነወ፡፡
በትላንትናዉ እለት ብቻ 5000 ያህል ስደተኞች ወደ ስፔን መግባታቸዉን ተከትሎ የስፔን መንግስት ወታደራዊ ሀይሉን ድንበሩን እንዲጠብቅ ማድረጓ ተሰምቷል፡፡
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa
የስፔን መንግስት እንዳስታወቀዉ ከ100 በላይ የሆኑ ስደተኞች በአንድ ሌሊት ከሞሮኮ ወደ ስፔን ሲውታ አከባቢ በባህር ዳርቻ ተንሳፋፊ አካል በመጠቀም እና በዋና መግባታቸዉን ይፋ አድርጓል፡፡
የስፔን የመገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ከሆነ የሞሮኮ ድንበር ጠባቂዎች ይህ ሁኔታ ሲፈጠር በአጠገባቸው ቆመው ስደተኞቹ ራሳቸውን ለአደጋ ሲያጋልጡ እየተመለከቱ ነበር ሲሉ ዘግበዋል፡፡
አብዛኛዎቹ ስደተኞች የመጡት በሰሜናዊው የቤንዙ ዳርቻ አካባቢ ሲሆን የተወሰኑት በስተደቡብ በኩል ታራላል በተባለዉ የባህር ዳርቻ ነወ፡፡
በትላንትናዉ እለት ብቻ 5000 ያህል ስደተኞች ወደ ስፔን መግባታቸዉን ተከትሎ የስፔን መንግስት ወታደራዊ ሀይሉን ድንበሩን እንዲጠብቅ ማድረጓ ተሰምቷል፡፡
#ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa