በየመን የአልቃይዳ መሪ በቁጥጥር ስር ውሏል ተባለ!
የተባሩት መንግስታት ድርጅት በየመን የአልቃይዳ መሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታወቀ፡፡የድርጅቱ የክትትል ቡድን ትናንት ሃሙስ ለጸጥታው ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት ካሊድ ባታርፊ በቁጥጥር ስር ከዋለ መቆየቱን ጠቁሟል፡፡ባታርፊ ከዓመት በፊት ነበር የሽብር ቡድኑን እንዲመራ የተመረጠው እንደ አረብ ኒውስ ዘገባ፡፡ምክትሉ ሰዓድ አቲፍ አል-አውላቂ አል ማህራህ ግዛት ውስጥ በምትገኘው ጋይዳ ከተማ ተካሂዶ በነበረው ዘመቻ መገደሉንም ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በኦሳማ ቢን ላደን እና አጋሮቹ መመስረቱ የሚነገርለት አልቃይዳ የጸጥታው ምክር ቤትን ጨምሮ በአሜሪካ እና በሌሎችም ሃገራት በሽብርተኝነት መፈረጁ የሚታወስ ነው፡፡ቢንላደን አሜሪካ በባራክ ኦባማ የስልጣን ዘመን ባካሄደችው ዘመቻ በፓኪስታን አቦታባድ መገደሉም አይዘነጋም፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
የተባሩት መንግስታት ድርጅት በየመን የአልቃይዳ መሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታወቀ፡፡የድርጅቱ የክትትል ቡድን ትናንት ሃሙስ ለጸጥታው ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት ካሊድ ባታርፊ በቁጥጥር ስር ከዋለ መቆየቱን ጠቁሟል፡፡ባታርፊ ከዓመት በፊት ነበር የሽብር ቡድኑን እንዲመራ የተመረጠው እንደ አረብ ኒውስ ዘገባ፡፡ምክትሉ ሰዓድ አቲፍ አል-አውላቂ አል ማህራህ ግዛት ውስጥ በምትገኘው ጋይዳ ከተማ ተካሂዶ በነበረው ዘመቻ መገደሉንም ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በኦሳማ ቢን ላደን እና አጋሮቹ መመስረቱ የሚነገርለት አልቃይዳ የጸጥታው ምክር ቤትን ጨምሮ በአሜሪካ እና በሌሎችም ሃገራት በሽብርተኝነት መፈረጁ የሚታወስ ነው፡፡ቢንላደን አሜሪካ በባራክ ኦባማ የስልጣን ዘመን ባካሄደችው ዘመቻ በፓኪስታን አቦታባድ መገደሉም አይዘነጋም፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያየ የትምህርት ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 5 ሺህ 117 ተማሪዎች ነገ ያስመርቃል፡፡
ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ በልዩ ልዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 5 ሺህ 117 ተማሪዎች ነገ ቅዳሜ ጥር 29/2013 ዓ.ም በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ፣ በስፔሻሊቲ እና ፖስት ግራጁዬት ዲፕሎማ ያስመርቃል፡፡በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ትምህርት ለማስቀጠል የ2012 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን ብቻ ጠርቶ በ15 አካዳሚክ ክፍሎች ማካካሻ ትምህርት ሲሰጥ እንደቆየ ነው የዩቨርሲቲው የኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮምዩኒኬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውዱ እምሩ (ዶክተር) የተናገሩት፡፡
[AMMA]
@YeneTube @FikerAssefa
ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ በልዩ ልዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 5 ሺህ 117 ተማሪዎች ነገ ቅዳሜ ጥር 29/2013 ዓ.ም በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ፣ በስፔሻሊቲ እና ፖስት ግራጁዬት ዲፕሎማ ያስመርቃል፡፡በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ትምህርት ለማስቀጠል የ2012 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን ብቻ ጠርቶ በ15 አካዳሚክ ክፍሎች ማካካሻ ትምህርት ሲሰጥ እንደቆየ ነው የዩቨርሲቲው የኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮምዩኒኬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውዱ እምሩ (ዶክተር) የተናገሩት፡፡
[AMMA]
@YeneTube @FikerAssefa
የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው የሚሳተፉበት አሰራር መዘጋጀቱን ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ገለጹ፡፡
የተፈናቀሉ ዜጎች በ6ኛው አገራዊ ምርጫ የሚሳተፉበት አሰራር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ገለጸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ”ይጠይቁ” በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የማህበራዊ ሚዲያ የተሳትፎ መድረክ ለቀረቡ ጥያቄዎች በቦርዱ የፌስቡክ ገጽ በቀጥታ ምላሽ ሰጥተዋል።
የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው በምን አይነት መልኩ ይሳተፋሉ? በሚል ከተሳታፊ ለተነሳው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው ላይ የሚሳተፉበትን ሁኔታ ቦርዱ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል። ዜጎቹ ባሉበት ቦታ ሆነው የሚመዘገቡበትና ከመጡበት አካባቢ በሚኖሩ ሰዎች ምርጫውን የሚያደርጉበት ሁኔታ መመቻቸቱን አመልክተዋል።
ምርጫ ቦርድ የተፈናቀሉት ዜጎች የሰጡትን ድምጽ ከመጡበት አካባቢ ሰዎች ከሚሰጡት ድምጽ ጋር የሚደመርበት የውጤት ማስላት ዘዴ ማዘጋጀቱን ተናግረዋል። በአዲስ መልክ ዜጎች የተፈናቀሉባቸው ቦታዎች በመኖራቸው የወቅቱን መረጃዎች ማወቅ እንደሚያስፈልግም ገልፀዋል። ለዚህ ደግሞ የሰላም ሚኒስቴርና የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይ.ኦ.ኤም) የሚያወጧቸውን መረጃዎች መሰረት በማድረግ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የተፈናቀሉ ዜጎች ባሉባቸው አካባቢዎች ለመራጮች ትምህርት ለመስጠት፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ምልመላና ሌሎች በተጓዳኝ የሚከናወኑ ስራዎች የሚመሩበት እቅድ መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።
[Arts TV]
@Yenetube @FikerAssefa
የተፈናቀሉ ዜጎች በ6ኛው አገራዊ ምርጫ የሚሳተፉበት አሰራር መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ገለጸዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ”ይጠይቁ” በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የማህበራዊ ሚዲያ የተሳትፎ መድረክ ለቀረቡ ጥያቄዎች በቦርዱ የፌስቡክ ገጽ በቀጥታ ምላሽ ሰጥተዋል።
የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው በምን አይነት መልኩ ይሳተፋሉ? በሚል ከተሳታፊ ለተነሳው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ የተፈናቀሉ ዜጎች በምርጫው ላይ የሚሳተፉበትን ሁኔታ ቦርዱ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል። ዜጎቹ ባሉበት ቦታ ሆነው የሚመዘገቡበትና ከመጡበት አካባቢ በሚኖሩ ሰዎች ምርጫውን የሚያደርጉበት ሁኔታ መመቻቸቱን አመልክተዋል።
ምርጫ ቦርድ የተፈናቀሉት ዜጎች የሰጡትን ድምጽ ከመጡበት አካባቢ ሰዎች ከሚሰጡት ድምጽ ጋር የሚደመርበት የውጤት ማስላት ዘዴ ማዘጋጀቱን ተናግረዋል። በአዲስ መልክ ዜጎች የተፈናቀሉባቸው ቦታዎች በመኖራቸው የወቅቱን መረጃዎች ማወቅ እንደሚያስፈልግም ገልፀዋል። ለዚህ ደግሞ የሰላም ሚኒስቴርና የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይ.ኦ.ኤም) የሚያወጧቸውን መረጃዎች መሰረት በማድረግ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። የተፈናቀሉ ዜጎች ባሉባቸው አካባቢዎች ለመራጮች ትምህርት ለመስጠት፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ምልመላና ሌሎች በተጓዳኝ የሚከናወኑ ስራዎች የሚመሩበት እቅድ መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።
[Arts TV]
@Yenetube @FikerAssefa
ስልሳ ስምንት ዜጎች ከሊባኖስ ቤይሩት ወደ አገራቸው ተመለሱ።
ዛሬ ጥር 28 ቀን 2013 ዓ.ም ስልሳ ስምንት ኢትዮጵያዊያን ከሊባኖስ ቤይሩት በፍሪደም ፈንድ እና አጋር ኢትዮጵያ በተባሉ አገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅቶች አማካኝነት ወደ አገራቸው ተመልሰዋል።
ወደ አገራቸው የተመለሱ ዜጎችን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይረክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ለተመላሾቹ አቀባበል ማድረጋቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ ጥር 28 ቀን 2013 ዓ.ም ስልሳ ስምንት ኢትዮጵያዊያን ከሊባኖስ ቤይሩት በፍሪደም ፈንድ እና አጋር ኢትዮጵያ በተባሉ አገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅቶች አማካኝነት ወደ አገራቸው ተመልሰዋል።
ወደ አገራቸው የተመለሱ ዜጎችን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይረክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ለተመላሾቹ አቀባበል ማድረጋቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
አምቦ ከተማ ተማሪዎች ሰልፍ ወጥተዋል!
አምቦ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ ተማሪዎች፤ ፍትህ ለሀጫሉ፣ የታሰሩ ፖለቲከኞች ይፈቱ፣ እና ሌሎች መፈከሮችን በማሰማት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን የአዲስ ዘይቤ መረጃ ያመለክታል። ሆኖም ሰልፉ ብዙም ሳይቆይ ተማሪዎቹ በፖሊስ ሀይሎች እንደተበተኑ እና አንዳዶችም እንደታፈሱ ከአይን እማኛችን ለማረጋገጥ ተችሏል።አዲስ ዘይቤ አምቦ ያለውን የፖሊስ ቢሮ ለማነጋገር ሙከራ ያደረገ ቢሆንም "ስብሰባ ላይ ነን አሁን ማናገር አንችልም" የሚል ምላሽ አግኝቻለው ብላለች።
@YeneTube @FikerAssefa
አምቦ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ ተማሪዎች፤ ፍትህ ለሀጫሉ፣ የታሰሩ ፖለቲከኞች ይፈቱ፣ እና ሌሎች መፈከሮችን በማሰማት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን የአዲስ ዘይቤ መረጃ ያመለክታል። ሆኖም ሰልፉ ብዙም ሳይቆይ ተማሪዎቹ በፖሊስ ሀይሎች እንደተበተኑ እና አንዳዶችም እንደታፈሱ ከአይን እማኛችን ለማረጋገጥ ተችሏል።አዲስ ዘይቤ አምቦ ያለውን የፖሊስ ቢሮ ለማነጋገር ሙከራ ያደረገ ቢሆንም "ስብሰባ ላይ ነን አሁን ማናገር አንችልም" የሚል ምላሽ አግኝቻለው ብላለች።
@YeneTube @FikerAssefa
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 78 ነጥብ 3 በመቶ ደረሰ!
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 78 ነጥብ 3 መድረሱን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ።ሚኒስቴሩ ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወናቸውን ተግባራትንና የህዳሴ ግድቡን የግንባታ ሂደት በተመለከተ መግለጫ የሰጡት የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንደገለጹት፤ የግድቡ ግንባታ የሲቪል ስራዎች አፈጻጸም 91 በመቶ ደርሷል።አጠቃላይ የግድቡ ግንባታ አፈጻጸም ደግሞ 78 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን አመልክተዋል።በቀጣይ ወራት የግድቡን ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት ለማሳካት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።ግድቡ ለተፋሰሱ አገሮች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት ኢንጂነር ስለሺ፤ “የግድቡ ግንባታ ሰኔ ወር ላይ ከነበረበት አፈጻጸም የ4 ነጥብ 05 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል” ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 78 ነጥብ 3 መድረሱን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ።ሚኒስቴሩ ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወናቸውን ተግባራትንና የህዳሴ ግድቡን የግንባታ ሂደት በተመለከተ መግለጫ የሰጡት የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንደገለጹት፤ የግድቡ ግንባታ የሲቪል ስራዎች አፈጻጸም 91 በመቶ ደርሷል።አጠቃላይ የግድቡ ግንባታ አፈጻጸም ደግሞ 78 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን አመልክተዋል።በቀጣይ ወራት የግድቡን ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት ለማሳካት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።ግድቡ ለተፋሰሱ አገሮች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት ኢንጂነር ስለሺ፤ “የግድቡ ግንባታ ሰኔ ወር ላይ ከነበረበት አፈጻጸም የ4 ነጥብ 05 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል” ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ዋልያ ለችግረኛ ወገኖች የተገነቡ ባለ ሰባት ብሎክ 53 ቤቶችን ለባለቤቶቹ አስረከበ
በአዲስ አበባ ከተማ ጎልተው ከሚታዩ ችግሮች አንዱ እና ዋነኛው ደረጃውን የጠበቀ መኖርያ ቤት ችግር ነው፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በልደታ ክፍለ ከተማ ከረዩ ሰፈር በተባለው አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች ግድግዳው እና ጣሪያው ከቆርቆሮ በተሠራ ቤት ላለፉት 40 ዓመታት ኖረዋል፡፡ መኖሪያ ቤታቸው ብቻ ሳይሆን ኩሽና እና መጸዳጃ ቤታቸውም ከቆርቆሮ ተሠርቶ ለረጅም ዘመን በማገልገሉ በአሳዛኝ ሁኔታ ላይ ይገኝ ነበር፡፡
ሃይንከን ኢትዮጵያ/ዋልያ ቢራ ይህን ችግር በመረዳት እነዚህን ባለሰባት ብሎክ 53 ቤቶች፣ ኩሽና እና መጸዳጃ ቤቶችን ሙሉ በሙሉ በማፍረስ ደረጃውን በጠበቀ የብሎኬት ቤት ተክቶታል፡፡ ግንባታው በሁለት ወራት የተጠናቀቀ ሲሆን፤ 8.4 ሚሊዮን ብር ወጥቶበታል።
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ ጎልተው ከሚታዩ ችግሮች አንዱ እና ዋነኛው ደረጃውን የጠበቀ መኖርያ ቤት ችግር ነው፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በልደታ ክፍለ ከተማ ከረዩ ሰፈር በተባለው አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች ግድግዳው እና ጣሪያው ከቆርቆሮ በተሠራ ቤት ላለፉት 40 ዓመታት ኖረዋል፡፡ መኖሪያ ቤታቸው ብቻ ሳይሆን ኩሽና እና መጸዳጃ ቤታቸውም ከቆርቆሮ ተሠርቶ ለረጅም ዘመን በማገልገሉ በአሳዛኝ ሁኔታ ላይ ይገኝ ነበር፡፡
ሃይንከን ኢትዮጵያ/ዋልያ ቢራ ይህን ችግር በመረዳት እነዚህን ባለሰባት ብሎክ 53 ቤቶች፣ ኩሽና እና መጸዳጃ ቤቶችን ሙሉ በሙሉ በማፍረስ ደረጃውን በጠበቀ የብሎኬት ቤት ተክቶታል፡፡ ግንባታው በሁለት ወራት የተጠናቀቀ ሲሆን፤ 8.4 ሚሊዮን ብር ወጥቶበታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋዜጣዊ መግለጫ በረሃብ አድማ ላይ የሚገኙ እስረኞች ሁኔታ ላይ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ/ኮሚሽኑ) ይህ መግለጫ እስከተዘጋጀበት ጊዜ ድረስ የረሃብ አድማ ላይ የሚገኙት በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የተከሰሱ እስረኞች እና ሌሎች እስረኞችንም ሁኔታ ተመልክቷል። ኮሚሽኑ ጥር 25 ቀን 2013 ዓ.ም. በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እና በቂሊንጦ ጊዜያዊ ማቆያ በመገኘት እስረኞቹን የጎበኘ ሲሆን፣ ከእነ አቶ ጃዋር መሐመድ በተጨማሪም፣ የኮሎኔል ገመቹ አያና እና የአቶ ጥላሁን ያሚ አያያዝ ላይ ክትትል አድርጓል። በክትትሉም ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት እና ከቂሊንጦ ጊዜያዊ ማቆያ ቤት አስተዳደሮች እንዲሁም ከእስረኞቹ ጋር ተነጋግሯል።
ኢሰመኮ ጥር 25 ቀን 2013 ዓ.ም. በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በተገኘበት ወቅት፣ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ሀምዛ አዳነ (ቦረና) እና አቶ ሸምሰዲን ጣሃ ከጥር 19 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በረሃብ አድማ ላይ ነበሩ። የረሃብ አድማው ዓላማ “መንግስት በሕዝብ እና በፓርቲያቸው ላይ እያደረሰ ያለውን አፈና እና የመብት ጥሰት ለመቃወም፣ የኮሎኔል ገመቹ አያናን አላግባብ የሆነ አያያዝ እና እንግልት እንዲቆም ለመጠየቅ እና የችሎት ሂደታቸውን ለመከታተል ወደ ፍርድ ቤት በሚመጡ እና እነሱን ለመጠየቅ ወደ ማረሚያ ቤት በሚመጡ ሰዎች ላይ የሚፈጸም እስር እና ወከባ እንዲቆም ለመጠየቅ” መሆኑን እስረኞቹ ለኢሰመኮ ገልጸዋል።
የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አስተዳደር በበኩሉ ለረሃብ አድማው በምክንያትነት የተጠቀሱ አብዛኛዎቹ ጉዳዮች ማረሚያ ቤቱን የማይመለከቱ መሆኑንና እስረኞችን ለመጠየቅ የሚመጡ ሰዎች ላይ ወከባ እንደማይፈጽም ገልጿል። አስተዳደሩ አክሎም የረሃብ አድማው በእስረኞቹ ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል፣ በተለይም ከመካከላቸው ሁለቱ የጤና ችግር ስላለባቸው በቋሚነት መድኃኒት የሚወስዱ በመሆኑ ቅርብ የህክምና ክትትል እንደሚደረግላቸው አስረድቷል። ኢሰመኮ በቦታው በነበረበት ወቅት የተባለው ህክምና ክትትል እንደሚደረግ በምልከታ ለማረጋገጥ ችሏል።
በሌላ በኩል፣ በማረሚያ ቤት ውስጥ ተቀርጾ በማኅበራዊ ሚዲያ ከተሰራጨ ቪዲዮ ፊልም ጋር በተያያዘ ደኅንነታቸው አደጋ ላይ ወድቋል የተባሉትን ኮሎኔል ገመቹ አያና እና የአቶ ጥላሁን ያሚ ደኅንነትና አያያዝ ሁኔታ ኮሚሽኑ አጣርቷል። ሁለቱም ታሳሪዎች በደኅንነት ላይ እንደሚገኙና አካላዊ ጥቃት እንዳልደረሰባቸው አረጋግጧል። ሆኖም ግን ኮሎኔል ገመቹ አያና ከዚህ በፊት ከነበረበት የእስር ክፍል (ዞን) እንዲወጣ ተደርጎ ‹‹ለደህንነቱ ምቹ ወዳልሆነ የእስር ክፍል (ዞን) እንዲዛወር መደረጉን›› እና ከዚህም በፊት በተደጋጋሚ ከቦታ ቦታ በመዘዋወሩ የደረሰበትን እንግልት በሚመለከት ቅሬታውን ለኮሚሽኑ አስረድቷል። የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር በበኩሉ በልዩ ልዩ ምክንያቶች የእስረኞች ክፍል (ዞን) ዝውውር ሊደረግ የሚችል መሆኑን ገልጾ፤ ኮሎኔል ገመቹ የተዛወሩበት የእስር ክፍል (ዞን) ሌሎች እስረኞችም የሚገኙበት መሆኑን ይገልጻል። ኮሚሽኑም በጉብኝቱ ወቅት የማረሚያ ቤቱን ደንብ በመተላለፍ ምክንያት ወደዚህ የእስር ክፍል (ዞን) መምጣቱን የገለጸ አንድ ታሳሪ መኖሩን ኢሰመኮ ተመልክቷል፡፡
ኢሰመኮ ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ለማረሚያ ቤቱ አስተዳደር የሰጠውን ምክረ ሃሳብ ተከትሎ፣ አስተዳደሩ እስረኛውን ወደ ሌላ ዞን ለማዛወር በዝግጅት ላይ የነበረ ቢሆንም፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥር 26 ቀን 2013 ዓ.ም. በዋለው ችሎት እስረኛው ከቂሊንጦ እስር ቤት ወደ ቃሊቲ እስር ቤት መዛወሩ አግባብ አለመሆኑን ጠቅሶ ወደ ቂሊንጦ እንዲመለስ ትዕዛዝ ሰጥቷል። በዚህም መሰረት፣ ከጥር 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ እስረኛው በቂሊንጦ ጊዜያዊ ማረፊያ ቤት የሚገኝ መሆኑን ኢሰመኮ እስረኛውን በመጎብኘት አረጋግጧል።
በተመሳሳይ መልኩ፣ ኢሰመኮ በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ተጠርጥሮ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኘውን የአቶ ጥላሁን ያሚን ደኅንነትና አያያዝ አጣርቷል። እስረኛው በሙሉ ደኅንነት የሚገኝ ሲሆን በማሕበራዊ ሚዲያ የተሰራጨውን ቪዲዬ ተከትሎ ከማቆያ ቤቱ ቅጥር ግቢ እንዳይወጣ ከመደረጉ በስተቀር በቂሊንጦ ጊዜያዊ ማቆያ እያለ ድብደባም ሆነ ሌላ አይነት የመብት ጥሰት ያልተፈጸመበት መሆኑን አስረድቶ፣ ነገር ግን ከዚህ ቀደም በፖሊስ ጣቢያ በምርመራ ወቅት የነበረውን ተገቢ ያልሆነ አያያዝ በተመለከተ ለኢሰመኮ ቅሬታውን አስረድቷል ።
በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በረሃብ አድማ ላይ የሚገኙ እስረኞችን አስመልክቶ፣ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ “የእስረኞቹ ጤንነትና ሕይወት የከፋ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ የቅርብ ክትትል ማድረግ እንደሚያስፈልግ፣ ለታሳሪዎች ምክንያታዊ የሆኑ ጥያቄዎች ተገቢውን አፋጣኝ ምላሽ መስጠትና የእስረኞችን ጠያቂዎች በማረሚያ ቤቱም ሆነ በፍርድ ቤቶች በአግባቡ ማስተናገድ ይገባል›› በማለት ገልጸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ/ኮሚሽኑ) ይህ መግለጫ እስከተዘጋጀበት ጊዜ ድረስ የረሃብ አድማ ላይ የሚገኙት በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የተከሰሱ እስረኞች እና ሌሎች እስረኞችንም ሁኔታ ተመልክቷል። ኮሚሽኑ ጥር 25 ቀን 2013 ዓ.ም. በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እና በቂሊንጦ ጊዜያዊ ማቆያ በመገኘት እስረኞቹን የጎበኘ ሲሆን፣ ከእነ አቶ ጃዋር መሐመድ በተጨማሪም፣ የኮሎኔል ገመቹ አያና እና የአቶ ጥላሁን ያሚ አያያዝ ላይ ክትትል አድርጓል። በክትትሉም ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት እና ከቂሊንጦ ጊዜያዊ ማቆያ ቤት አስተዳደሮች እንዲሁም ከእስረኞቹ ጋር ተነጋግሯል።
ኢሰመኮ ጥር 25 ቀን 2013 ዓ.ም. በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በተገኘበት ወቅት፣ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ሀምዛ አዳነ (ቦረና) እና አቶ ሸምሰዲን ጣሃ ከጥር 19 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በረሃብ አድማ ላይ ነበሩ። የረሃብ አድማው ዓላማ “መንግስት በሕዝብ እና በፓርቲያቸው ላይ እያደረሰ ያለውን አፈና እና የመብት ጥሰት ለመቃወም፣ የኮሎኔል ገመቹ አያናን አላግባብ የሆነ አያያዝ እና እንግልት እንዲቆም ለመጠየቅ እና የችሎት ሂደታቸውን ለመከታተል ወደ ፍርድ ቤት በሚመጡ እና እነሱን ለመጠየቅ ወደ ማረሚያ ቤት በሚመጡ ሰዎች ላይ የሚፈጸም እስር እና ወከባ እንዲቆም ለመጠየቅ” መሆኑን እስረኞቹ ለኢሰመኮ ገልጸዋል።
የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አስተዳደር በበኩሉ ለረሃብ አድማው በምክንያትነት የተጠቀሱ አብዛኛዎቹ ጉዳዮች ማረሚያ ቤቱን የማይመለከቱ መሆኑንና እስረኞችን ለመጠየቅ የሚመጡ ሰዎች ላይ ወከባ እንደማይፈጽም ገልጿል። አስተዳደሩ አክሎም የረሃብ አድማው በእስረኞቹ ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል፣ በተለይም ከመካከላቸው ሁለቱ የጤና ችግር ስላለባቸው በቋሚነት መድኃኒት የሚወስዱ በመሆኑ ቅርብ የህክምና ክትትል እንደሚደረግላቸው አስረድቷል። ኢሰመኮ በቦታው በነበረበት ወቅት የተባለው ህክምና ክትትል እንደሚደረግ በምልከታ ለማረጋገጥ ችሏል።
በሌላ በኩል፣ በማረሚያ ቤት ውስጥ ተቀርጾ በማኅበራዊ ሚዲያ ከተሰራጨ ቪዲዮ ፊልም ጋር በተያያዘ ደኅንነታቸው አደጋ ላይ ወድቋል የተባሉትን ኮሎኔል ገመቹ አያና እና የአቶ ጥላሁን ያሚ ደኅንነትና አያያዝ ሁኔታ ኮሚሽኑ አጣርቷል። ሁለቱም ታሳሪዎች በደኅንነት ላይ እንደሚገኙና አካላዊ ጥቃት እንዳልደረሰባቸው አረጋግጧል። ሆኖም ግን ኮሎኔል ገመቹ አያና ከዚህ በፊት ከነበረበት የእስር ክፍል (ዞን) እንዲወጣ ተደርጎ ‹‹ለደህንነቱ ምቹ ወዳልሆነ የእስር ክፍል (ዞን) እንዲዛወር መደረጉን›› እና ከዚህም በፊት በተደጋጋሚ ከቦታ ቦታ በመዘዋወሩ የደረሰበትን እንግልት በሚመለከት ቅሬታውን ለኮሚሽኑ አስረድቷል። የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር በበኩሉ በልዩ ልዩ ምክንያቶች የእስረኞች ክፍል (ዞን) ዝውውር ሊደረግ የሚችል መሆኑን ገልጾ፤ ኮሎኔል ገመቹ የተዛወሩበት የእስር ክፍል (ዞን) ሌሎች እስረኞችም የሚገኙበት መሆኑን ይገልጻል። ኮሚሽኑም በጉብኝቱ ወቅት የማረሚያ ቤቱን ደንብ በመተላለፍ ምክንያት ወደዚህ የእስር ክፍል (ዞን) መምጣቱን የገለጸ አንድ ታሳሪ መኖሩን ኢሰመኮ ተመልክቷል፡፡
ኢሰመኮ ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ለማረሚያ ቤቱ አስተዳደር የሰጠውን ምክረ ሃሳብ ተከትሎ፣ አስተዳደሩ እስረኛውን ወደ ሌላ ዞን ለማዛወር በዝግጅት ላይ የነበረ ቢሆንም፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥር 26 ቀን 2013 ዓ.ም. በዋለው ችሎት እስረኛው ከቂሊንጦ እስር ቤት ወደ ቃሊቲ እስር ቤት መዛወሩ አግባብ አለመሆኑን ጠቅሶ ወደ ቂሊንጦ እንዲመለስ ትዕዛዝ ሰጥቷል። በዚህም መሰረት፣ ከጥር 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ እስረኛው በቂሊንጦ ጊዜያዊ ማረፊያ ቤት የሚገኝ መሆኑን ኢሰመኮ እስረኛውን በመጎብኘት አረጋግጧል።
በተመሳሳይ መልኩ፣ ኢሰመኮ በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ተጠርጥሮ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኘውን የአቶ ጥላሁን ያሚን ደኅንነትና አያያዝ አጣርቷል። እስረኛው በሙሉ ደኅንነት የሚገኝ ሲሆን በማሕበራዊ ሚዲያ የተሰራጨውን ቪዲዬ ተከትሎ ከማቆያ ቤቱ ቅጥር ግቢ እንዳይወጣ ከመደረጉ በስተቀር በቂሊንጦ ጊዜያዊ ማቆያ እያለ ድብደባም ሆነ ሌላ አይነት የመብት ጥሰት ያልተፈጸመበት መሆኑን አስረድቶ፣ ነገር ግን ከዚህ ቀደም በፖሊስ ጣቢያ በምርመራ ወቅት የነበረውን ተገቢ ያልሆነ አያያዝ በተመለከተ ለኢሰመኮ ቅሬታውን አስረድቷል ።
በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በረሃብ አድማ ላይ የሚገኙ እስረኞችን አስመልክቶ፣ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ “የእስረኞቹ ጤንነትና ሕይወት የከፋ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ የቅርብ ክትትል ማድረግ እንደሚያስፈልግ፣ ለታሳሪዎች ምክንያታዊ የሆኑ ጥያቄዎች ተገቢውን አፋጣኝ ምላሽ መስጠትና የእስረኞችን ጠያቂዎች በማረሚያ ቤቱም ሆነ በፍርድ ቤቶች በአግባቡ ማስተናገድ ይገባል›› በማለት ገልጸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ከቀበሌ እስከ ዞን ያለውን አደረጃጀት ለውጥ ማምጣት በሚችል መንገድ ማደራጀት ተጀምሯል - ሌተናል ጄኔራል አስራት ዴኔሮ
በመተከል ዞን የግብረ ሃይሉ መሪ ሌተናል ጄኔራል አስራት ዴኔሮ ከቀበሌ እስከ ዞን ያለውን አደረጃጀት ለውጥ ማምጣት በሚችል መንገድ ማደራጀት ጀምረናል ብለዋል።
"ተፈናቃዮች ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሲመለሱ አስተማማኝ ሠላም እንዲሰፍን የአካባቢውን ህዝብ የሚመስል የሚሊሻ አደረጃጀት ተፈጥሯል፤ ወደ 10 ሺህ የሚጠጉ የሚሊሻ አባላትም ከዛሬ ጀምሮ የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ይወስዳሉ" ብለዋል፡፡
ሽፍታው የሚንቀሳቀስባቸውና የጸጥታ ስጋት ያለባቸው 32 ቀበሌዎች በሚቀጥሉት 15 ቀናት ሙሉ በሙሉ ከሽፍታው እንቅስቃሴ ነጻ እንዲሆኑ አመራሩ ታች ድረስ ወርዶ መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ስዩም መስፍን ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ከመመለሳቸው በፊት የአካባቢው ሠላም አስተማማኝ መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባም አመልክተዋል፡፡
ተፈናቃዮች በሚቋቋሙበት ጊዜ የሚፈጠረውን ውዝግብ ለመፍታት አስቀድሞ ትክክለኛ ቁጥራቸውን መለየት እንደሚገባ ገልጸው፣ ለዚህ ደግሞ የሠላም ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ጋር ይሰራል ብለዋል።
በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ በልጅጌም ተፈናቃዮችን ለመመለስ ማወያየት፣ የዕርቀ ሠላም ስራና ሌሎችም ቅድመ ሁኔታዎች እንደሚሟሉና ያ ሳይሆን የመመለሱ ስራ እንደማይሰራ አረጋግጠዋል።
ምንጭ፡- ኢዜአ
@YeneTube @FikerAssefa
በመተከል ዞን የግብረ ሃይሉ መሪ ሌተናል ጄኔራል አስራት ዴኔሮ ከቀበሌ እስከ ዞን ያለውን አደረጃጀት ለውጥ ማምጣት በሚችል መንገድ ማደራጀት ጀምረናል ብለዋል።
"ተፈናቃዮች ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሲመለሱ አስተማማኝ ሠላም እንዲሰፍን የአካባቢውን ህዝብ የሚመስል የሚሊሻ አደረጃጀት ተፈጥሯል፤ ወደ 10 ሺህ የሚጠጉ የሚሊሻ አባላትም ከዛሬ ጀምሮ የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ይወስዳሉ" ብለዋል፡፡
ሽፍታው የሚንቀሳቀስባቸውና የጸጥታ ስጋት ያለባቸው 32 ቀበሌዎች በሚቀጥሉት 15 ቀናት ሙሉ በሙሉ ከሽፍታው እንቅስቃሴ ነጻ እንዲሆኑ አመራሩ ታች ድረስ ወርዶ መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ስዩም መስፍን ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ከመመለሳቸው በፊት የአካባቢው ሠላም አስተማማኝ መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባም አመልክተዋል፡፡
ተፈናቃዮች በሚቋቋሙበት ጊዜ የሚፈጠረውን ውዝግብ ለመፍታት አስቀድሞ ትክክለኛ ቁጥራቸውን መለየት እንደሚገባ ገልጸው፣ ለዚህ ደግሞ የሠላም ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ጋር ይሰራል ብለዋል።
በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ በልጅጌም ተፈናቃዮችን ለመመለስ ማወያየት፣ የዕርቀ ሠላም ስራና ሌሎችም ቅድመ ሁኔታዎች እንደሚሟሉና ያ ሳይሆን የመመለሱ ስራ እንደማይሰራ አረጋግጠዋል።
ምንጭ፡- ኢዜአ
@YeneTube @FikerAssefa
የጡረታ መዋጮ የማይከፍሉ የግል ድርጅቶች የንግድ ፍቃዳቸው እንዳይታደስ የሚያደርግ አሠራር ተዘረጋ!
የጡረታ መዋጮ የማይከፍሉ የግል ድርጅቶች የንግድ ፍቃዳቸው እንዳይታደስ የሚያደርግ የጋራ አሠራር መዘርጋቱን የግል ድርጅቶች ማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ አስታወቀ።አብዛኞቹ የግል ድርጅቶች የሠራተኞቻቸውን የጡረታ መዋጮ በአግባቡ እየከፈሉ ቢሆንም፣ አንዳንዶች ጊዜውን ጠብቀው ያለመክፈል፣ የተወሰኑት ደግሞ ከእነጭራሹ እንደማይከፍሉ ሁኔታ መኖሩን ኤጀንሲው ገልጿል።
የኤጂንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ገመቹ ወዩማ፣ ከጡረታ መዋጮ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ ድርጅቶች ላይ የሚስተዋለውን መዘግየት እና ለመክፈል አለመፈለግ ችግሮች ለመፍታት በአካል ጭምር በመሄድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ሲሠራ መቆየቱን ተናግረዋል። በመሆኑም በተለያዩ ምክንያቶች የጡረታ መዋጮ የማይከፍሉ ድርጅቶች እንዲከፍሉ እና ሓላፊነታቸውን እንዲወጡ ለማድረግ ኤጀንሲው ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር ቅንጅታዊ አሠራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል።
በዚሁ መሠረት የጡረታ መዋጮ የማይከፍሉ የግል ድርጅቶች በዓመቱ መጨረሻ የንግድ ፈቃድ እድሳት እንዳይደረግላቸው የሚያደርግ አሠራር ተዘርግቷል ነው ያሉት።ኤጀንሲው በበጀት ዓመቱ አጋማሽ ከግል ድርጅት ሠራተኞች የጡረታ መዋጮ ክፍያ 5 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን የገለጹት አቶ ገመቹ፣ ገቢው በስድስት ወራት ለመሰብሰብ ከታቀደው 106 በመቶ መሆኑንም መናገራቸውንም ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
የጡረታ መዋጮ የማይከፍሉ የግል ድርጅቶች የንግድ ፍቃዳቸው እንዳይታደስ የሚያደርግ የጋራ አሠራር መዘርጋቱን የግል ድርጅቶች ማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ አስታወቀ።አብዛኞቹ የግል ድርጅቶች የሠራተኞቻቸውን የጡረታ መዋጮ በአግባቡ እየከፈሉ ቢሆንም፣ አንዳንዶች ጊዜውን ጠብቀው ያለመክፈል፣ የተወሰኑት ደግሞ ከእነጭራሹ እንደማይከፍሉ ሁኔታ መኖሩን ኤጀንሲው ገልጿል።
የኤጂንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ገመቹ ወዩማ፣ ከጡረታ መዋጮ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ ድርጅቶች ላይ የሚስተዋለውን መዘግየት እና ለመክፈል አለመፈለግ ችግሮች ለመፍታት በአካል ጭምር በመሄድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ሲሠራ መቆየቱን ተናግረዋል። በመሆኑም በተለያዩ ምክንያቶች የጡረታ መዋጮ የማይከፍሉ ድርጅቶች እንዲከፍሉ እና ሓላፊነታቸውን እንዲወጡ ለማድረግ ኤጀንሲው ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር ቅንጅታዊ አሠራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል።
በዚሁ መሠረት የጡረታ መዋጮ የማይከፍሉ የግል ድርጅቶች በዓመቱ መጨረሻ የንግድ ፈቃድ እድሳት እንዳይደረግላቸው የሚያደርግ አሠራር ተዘርግቷል ነው ያሉት።ኤጀንሲው በበጀት ዓመቱ አጋማሽ ከግል ድርጅት ሠራተኞች የጡረታ መዋጮ ክፍያ 5 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን የገለጹት አቶ ገመቹ፣ ገቢው በስድስት ወራት ለመሰብሰብ ከታቀደው 106 በመቶ መሆኑንም መናገራቸውንም ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦቱ ላይ ያለው እክል እንዳልተቃለለ፣ ነገር ግን ወደ ክልሉ የሚገባው ዕርዳታ በየጊዜው እየጨመረ እንደሄደ የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ በፌስቡክ ገጹ ባሰራጨው መግለጫ አስታውቋል። ዕርዳታ በእጅጉ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ግን ዛሬም ተደራሽ አልሆኑም- ብሏል ቢሮው። በርካታ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርቶች እንደሚቀርቡ የጠቀሰው ቢሮው፣ ሆኖም ምዕራባዊ፣ ማዕከላዊ፣ ምሥራቃዊ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ደቡባዊ እና ደቡብ ምሥራቃዊ ትግራይ ተደራሽ ስላልሆኑ ሪፖርቶቹን ማረጋገጥ እንዳልተቻለ አክሎ ገልጧል።
✍Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
✍Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
🖼 ለጓደኛ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለሙሽሮች እና ለተመራቂዎች ለየት ያለ ስጦታ መስጠት ይፈልጋሉ?
#join
👇👇👇👇
@giftsoflovee
@giftsoflovee
👆👆👆👆
📱+251914839754
📱+251936871620
#ኣድራሻችን፡ 4 ኪሎ: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ
#join
👇👇👇👇
@giftsoflovee
@giftsoflovee
👆👆👆👆
📱+251914839754
📱+251936871620
#ኣድራሻችን፡ 4 ኪሎ: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ
‹‹ኤርትራ ወታደሮቿን ከትግራይ በአስቸኳይ ታስወጣ›› በሚል የወጣውን የዩናይትድ ስቴትስ መግለጫ አስመራ አግባብነት የሌለው ስትል ውድቅ አደረገች፡፡
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረመስቀል በቲውተር ገፃቸው ባሰፈሩት አጭር ምላሽ በኤርትራ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ያወጣውን መግለጫ ሀሰተኛና ተንሳፋፊ ወይም ማስረጃ ያልቀረበበት ክስ ብለውታል፡፡በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን በቲውተር ገፃቸው ያሰፈሩት በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ‹‹የተወሰኑ አገራት መንግሥት ስለመኖራቸው ማረጋገጫ ሳይሰጥ የኤርትራ ወታደሮች ከትግራይ ክልል እንዲወጡ ሲጠይቁ እየተመለከትን ነው›› ብለዋል፡፡‹‹ግን ለምን ወረራ የፈፀመውና የኢትዮጵያን ሉኣላዊ ድንበር የያዘውን የሱዳን ኃይል እንዲወጣ ጥያቄ አያቀርቡም?›› ሲሉም አገራቱን ተችዋል፡፡
ዩናይትድ ስቴትስ አርብ ባወጣችው መግለጫ ‹‹በትግራይ ክልል የኤርትራ ወታደሮች እንዳሉ የሚያሳይ ተጨባጭ መረጃ አለኝ›› በማለት በአስቸኳይ እንዲወጡ መጠየቋ ይታወሳል፡፡‹‹ወታደሮቹ የሰብኣዊ መብት ጥሰትንም እየፈፀሙ ነው›› በማለት በአስቸኳይ እንዲወጡ መጠየቋን በኤርትራ የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ማሳወቁም አይዘነጋም።የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግሥታት ግን በትግራይ ክልል የኤርትራ ወታደሮች ተሳትፎ አለ የሚለውን ሪፖርት አይቀበሉትም።
✍አሐዱ
@YeneTube @FikerAssefa
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረመስቀል በቲውተር ገፃቸው ባሰፈሩት አጭር ምላሽ በኤርትራ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ያወጣውን መግለጫ ሀሰተኛና ተንሳፋፊ ወይም ማስረጃ ያልቀረበበት ክስ ብለውታል፡፡በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን በቲውተር ገፃቸው ያሰፈሩት በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ‹‹የተወሰኑ አገራት መንግሥት ስለመኖራቸው ማረጋገጫ ሳይሰጥ የኤርትራ ወታደሮች ከትግራይ ክልል እንዲወጡ ሲጠይቁ እየተመለከትን ነው›› ብለዋል፡፡‹‹ግን ለምን ወረራ የፈፀመውና የኢትዮጵያን ሉኣላዊ ድንበር የያዘውን የሱዳን ኃይል እንዲወጣ ጥያቄ አያቀርቡም?›› ሲሉም አገራቱን ተችዋል፡፡
ዩናይትድ ስቴትስ አርብ ባወጣችው መግለጫ ‹‹በትግራይ ክልል የኤርትራ ወታደሮች እንዳሉ የሚያሳይ ተጨባጭ መረጃ አለኝ›› በማለት በአስቸኳይ እንዲወጡ መጠየቋ ይታወሳል፡፡‹‹ወታደሮቹ የሰብኣዊ መብት ጥሰትንም እየፈፀሙ ነው›› በማለት በአስቸኳይ እንዲወጡ መጠየቋን በኤርትራ የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ማሳወቁም አይዘነጋም።የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግሥታት ግን በትግራይ ክልል የኤርትራ ወታደሮች ተሳትፎ አለ የሚለውን ሪፖርት አይቀበሉትም።
✍አሐዱ
@YeneTube @FikerAssefa
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ነው!
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ እና በተከታታይ ፕሮግራም ያስተማራቸውን 5 ሺህ 310 ተማሪዎች እያስመረቀ ነው፡፡
በመጀመሪያ ዲግሪ 2ሺህ 963 ወንድ እና 2ሺህ 115 ሴት ተማሪዎችን እነዲሁም 214 ወንድ እና 18 ሴት ተማሪዎችን በድህረ ምረቃ ፕሮግራም ነው እያስመቀ ያለው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ እና በተከታታይ ፕሮግራም ያስተማራቸውን 5 ሺህ 310 ተማሪዎች እያስመረቀ ነው፡፡
በመጀመሪያ ዲግሪ 2ሺህ 963 ወንድ እና 2ሺህ 115 ሴት ተማሪዎችን እነዲሁም 214 ወንድ እና 18 ሴት ተማሪዎችን በድህረ ምረቃ ፕሮግራም ነው እያስመቀ ያለው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የዲ.አር.ኮንጎ ፕሬዝደንት ትናንት ምሽት አዲስ አበባ ገብተዋል!
የዲሞክራቲክ ሪፓሊክ ኮንጎ ፕሬዝደንት ፌሊክስ አንቶየን ትሺስኬዲ ትናንት ጥር 28 ቀን 2013 ዓ.ም ምሽት ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ፕሬዝደንቱ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ፕሬዝደንት ትሺስኬዲ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበርነትን ከደቡብ አፍሪካው ፕሬዝደንት ሲሪል ራማፎሳ ይቀበላሉ፡፡የሕዳሴ ግድቡ ድርድርም በእርሳቸው መሪነት የሚቀጥል ይሆናል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
የዲሞክራቲክ ሪፓሊክ ኮንጎ ፕሬዝደንት ፌሊክስ አንቶየን ትሺስኬዲ ትናንት ጥር 28 ቀን 2013 ዓ.ም ምሽት ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ፕሬዝደንቱ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ፕሬዝደንት ትሺስኬዲ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበርነትን ከደቡብ አፍሪካው ፕሬዝደንት ሲሪል ራማፎሳ ይቀበላሉ፡፡የሕዳሴ ግድቡ ድርድርም በእርሳቸው መሪነት የሚቀጥል ይሆናል፡፡
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ 2‚785 ተማሪዎችን አስመረቀ!
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 785 ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡
በምረቃ ስነ ስርአት ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር የደህንነት ጉዳዮች አማካሪ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ጨምሮ ሌሎች የክልል እና የፌዴራል ከፍተና የስራ ሀላፊዎች እና የኃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 785 ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡
በምረቃ ስነ ስርአት ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር የደህንነት ጉዳዮች አማካሪ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ጨምሮ ሌሎች የክልል እና የፌዴራል ከፍተና የስራ ሀላፊዎች እና የኃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
336 ኢትዮጵያዊያን ከሳዑዲ ዓረብያ ሪያድ ከተማ በትናንትናው ዕለት ወደ አገራቸው መመለሳቸውን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይረክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ለተመላሾቹ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቆንስላ ጉዳዮች ዳይረክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ለተመላሾቹ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ በ30 ሄክታር መሬት የተገነባው ፊቤላ እንዱስትሪያል ኮምፕሌክስ በነገው ዕለት ይመረቃል፡፡
ሰባት ከፋብሪካዎች የያዘ ፊቤላ እንዱስትሪያል ኮምፕሌክስ በቀን 1ሺህ 500 ቶን የምግብ ዘይት የሚያመርት ሲሆን፣ የሀገሪቱን 60 በመቶ የዘይት ፍላጎት የሚሸፍንና ለዘይት ይወጣ ከነበረው 30 በመቶ ወጪውን የሚያስቀር እንደሆነ ባለሃብቱና የቢኬጂ ቦርድ ሊቀመንበሩ አቶ በላይነህ ክንዴ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ፊቤላ እንዱስትሪያል ኮምፕሌክስ ከዘይት ፍብሪካው በተጨማሪ በቀን 200 ቶን ሰሊጥ ማቀነባበር የሚችል ፋብሪካ፣ በቀን 96 ቶን ሳሙና የሚያመርት ፋብሪካ፣ የአትክልትና ማርጋሪት ማምረቻ፣ የፕላስቲክና ጠርሙስ እንዲሁም የካርቶን ፍብሪካዎችን በውስጡ እንደሚያመርት ተናግረዋል።የዘይት ፍብሪካው ምርት የጥራት ደረጃው ተፈትሾ ለገበያ እንዲቀርብ ፍቃድ በማግኘቱ ከሰኞ ጀምሮ ለሸማቹ እንደሚደርስም ተገልጿል።
[Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
ሰባት ከፋብሪካዎች የያዘ ፊቤላ እንዱስትሪያል ኮምፕሌክስ በቀን 1ሺህ 500 ቶን የምግብ ዘይት የሚያመርት ሲሆን፣ የሀገሪቱን 60 በመቶ የዘይት ፍላጎት የሚሸፍንና ለዘይት ይወጣ ከነበረው 30 በመቶ ወጪውን የሚያስቀር እንደሆነ ባለሃብቱና የቢኬጂ ቦርድ ሊቀመንበሩ አቶ በላይነህ ክንዴ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ፊቤላ እንዱስትሪያል ኮምፕሌክስ ከዘይት ፍብሪካው በተጨማሪ በቀን 200 ቶን ሰሊጥ ማቀነባበር የሚችል ፋብሪካ፣ በቀን 96 ቶን ሳሙና የሚያመርት ፋብሪካ፣ የአትክልትና ማርጋሪት ማምረቻ፣ የፕላስቲክና ጠርሙስ እንዲሁም የካርቶን ፍብሪካዎችን በውስጡ እንደሚያመርት ተናግረዋል።የዘይት ፍብሪካው ምርት የጥራት ደረጃው ተፈትሾ ለገበያ እንዲቀርብ ፍቃድ በማግኘቱ ከሰኞ ጀምሮ ለሸማቹ እንደሚደርስም ተገልጿል።
[Walta]
@YeneTube @FikerAssefa
በሰላም ሚኒስትር የተመራ ልዑክ በትግራይ ክልል የሰብአዊ ድጋፍ ስርጭት ያለበትን ሁኔታ ለመመልከት መቐለ ገባ!
በሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል እና በዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቤስሊ የተመራ የልዑካን ቡድን በትግራይ ክልል የሰብአዊ ድጋፍ ስርጭት ያለበትን ሁኔታ ለመመልከት መቐለ ገብቷል።
እንደ ኢዘአ ዘገባ የልዑክ ቡድኑ አባላት በትግራይ ክልል በሚኖራቸው ቆይታ በመቐለ እና በአካባቢው እንዲሁም በኩሃ ያለውን የሰብአዊ ድጋፍ ስርጭት ሁኔታን ተዘዋውረው ይጎበኛሉ።
በተጨማሪም በትግራይ ክልል እየተሰጠ ባለው የሰብአዊ ድጋፍ ዙሪያ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እና ከብሔራዊ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል።
[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa
በሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል እና በዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቤስሊ የተመራ የልዑካን ቡድን በትግራይ ክልል የሰብአዊ ድጋፍ ስርጭት ያለበትን ሁኔታ ለመመልከት መቐለ ገብቷል።
እንደ ኢዘአ ዘገባ የልዑክ ቡድኑ አባላት በትግራይ ክልል በሚኖራቸው ቆይታ በመቐለ እና በአካባቢው እንዲሁም በኩሃ ያለውን የሰብአዊ ድጋፍ ስርጭት ሁኔታን ተዘዋውረው ይጎበኛሉ።
በተጨማሪም በትግራይ ክልል እየተሰጠ ባለው የሰብአዊ ድጋፍ ዙሪያ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እና ከብሔራዊ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሥራ ኃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩም ይጠበቃል።
[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa