የሲዳማ ክልል የ8ኛ ክፍል ውጤት በሚቀጥለው ሳምንት መጨረሻ ይፋ ይደረጋል።
በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት፣ የ2012 ዓ.ም የ8ተኛ ክፍል የፈተና ውጤት በቅርቡ እንደሚሰጥ የሲዳማ ክልል ትምህርት ቢሮ ዛሬ ገልጿል።
በአሁኑ ወቅት ፈተናው ታርሞ የተጠናቀቀ ሲሆን እስከሚቀጥለው ሳምንት መጨረሻ ድረስ ውጤቱ ለተማሪዎች እንደሚሰጥ በክልሉ ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊና መማ/ማስ/ምዘና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታፈስ ገ/ማርያም አሳውቀዋል።
Via:- Affini
@Yenetube @Fikerassefa
በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት፣ የ2012 ዓ.ም የ8ተኛ ክፍል የፈተና ውጤት በቅርቡ እንደሚሰጥ የሲዳማ ክልል ትምህርት ቢሮ ዛሬ ገልጿል።
በአሁኑ ወቅት ፈተናው ታርሞ የተጠናቀቀ ሲሆን እስከሚቀጥለው ሳምንት መጨረሻ ድረስ ውጤቱ ለተማሪዎች እንደሚሰጥ በክልሉ ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊና መማ/ማስ/ምዘና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታፈስ ገ/ማርያም አሳውቀዋል።
Via:- Affini
@Yenetube @Fikerassefa
ትናንት ሁለት ከፍተኛ የመንግስታቱ ድርጅት ባለስልጣናት ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል
ትናንት ሁለት ከፍተኛ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ነበሩ፡፡
ባለስልጣናቱ ኢትዮጵያ የነበሩት በወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በተለይም ተጠናቋል በተባለው የህግ ማስከበር ዘመቻ እና ዘመቻውን ተከትሎ እየተደረጉ ባሉ ሰብዓዊ ድጋፎች ዙሪያ ከከፍተኛ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር ለመምከር ነው፡፡
ከሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልም ጋር መክረዋል፡፡
ባለስልጣናቱ የድርጅቱ የደህንነት ዋና ጸሀፊ ጊልስ ሚካድ እና የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ ናቸው፡፡
ወ/ሮ ሙፈሪያት ቀደም ሲል በተጠቀሱት በኢትዮጵያ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ጉዳዮች ዙሪያ ከሚ/ር ጊልስ ሚካድ ጋር ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበረሰብ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡
በትግራይ ክልል የተካሄደውን የህግ ማስከበር ዘመቻ ተከትሎ እየተከናወኑ ስላሉ የሰብዓዊ ድጋፍ እና የመልሶ ማቋቋም ተግባራት ጥልቅ ውይይት ማድረጋቸውን የገለጹም ሲሆን በቀጣይ የድጋፍና ትብብር መስኮች ላይ ተመካክረናል ብለዋል።
ሚኒስትሯ ከስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነሩ ፊሊፖ ግራንዲ እና ልዑካቸው ጋር በሰብዓዊ ዕርዳታና ስደተኞች ጉዳይ ዙርያ ውይይት ማድረጋቸውንም ነው የገለጹት፡፡
በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ባሉ እና አፋጣኝ ምላሽ በሚሹ ጉዳዮች ላይ በቀጣይ ይበልጥ በትብብር መስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ እንደተወያዩም ጽፈዋል፡፡
በቀጣይ በትብብር ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሰናልም ብለዋል ወ/ሮ ሙፈሪያት፡፡
Via Alian
@Yenetube @Fikerassefa
ትናንት ሁለት ከፍተኛ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ነበሩ፡፡
ባለስልጣናቱ ኢትዮጵያ የነበሩት በወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በተለይም ተጠናቋል በተባለው የህግ ማስከበር ዘመቻ እና ዘመቻውን ተከትሎ እየተደረጉ ባሉ ሰብዓዊ ድጋፎች ዙሪያ ከከፍተኛ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር ለመምከር ነው፡፡
ከሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልም ጋር መክረዋል፡፡
ባለስልጣናቱ የድርጅቱ የደህንነት ዋና ጸሀፊ ጊልስ ሚካድ እና የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ ናቸው፡፡
ወ/ሮ ሙፈሪያት ቀደም ሲል በተጠቀሱት በኢትዮጵያ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ጉዳዮች ዙሪያ ከሚ/ር ጊልስ ሚካድ ጋር ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበረሰብ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡
በትግራይ ክልል የተካሄደውን የህግ ማስከበር ዘመቻ ተከትሎ እየተከናወኑ ስላሉ የሰብዓዊ ድጋፍ እና የመልሶ ማቋቋም ተግባራት ጥልቅ ውይይት ማድረጋቸውን የገለጹም ሲሆን በቀጣይ የድጋፍና ትብብር መስኮች ላይ ተመካክረናል ብለዋል።
ሚኒስትሯ ከስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነሩ ፊሊፖ ግራንዲ እና ልዑካቸው ጋር በሰብዓዊ ዕርዳታና ስደተኞች ጉዳይ ዙርያ ውይይት ማድረጋቸውንም ነው የገለጹት፡፡
በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ባሉ እና አፋጣኝ ምላሽ በሚሹ ጉዳዮች ላይ በቀጣይ ይበልጥ በትብብር መስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ እንደተወያዩም ጽፈዋል፡፡
በቀጣይ በትብብር ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሰናልም ብለዋል ወ/ሮ ሙፈሪያት፡፡
Via Alian
@Yenetube @Fikerassefa
የደወንሌ ድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪ ማቆያ ተርሚናል ዛሬ ይመረቃል።
በሲቲ ዞን አይሻአ ወረዳ የተገነባው የደወንሌ ድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪ ማቆያ ተርሚናል ዛሬ ይመረቃል።
በትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የተመራው ከፍተኛ የፌዴራል መንግሥት የስራ ሀላፊዎችም ድሬደዋ ገብተዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
በሲቲ ዞን አይሻአ ወረዳ የተገነባው የደወንሌ ድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪ ማቆያ ተርሚናል ዛሬ ይመረቃል።
በትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የተመራው ከፍተኛ የፌዴራል መንግሥት የስራ ሀላፊዎችም ድሬደዋ ገብተዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
በአዳማ ከተማ ለእንግድነት ከወላጅ እናቱ ጋር የሄደ የ18 ወር ህፃን በጅብ ተበላ!
በአዳማ ከተማ መስተዳድር ዳቤ ክፍለ ከተማ ዳቤ ሹሉቄ ቀበሌ ልዩ ቦታው ቀጠና 9 ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ለእንግድነት ከወላጅ እናቱ ጋር የሄደ የ 18ወር ህፃን በጅብ ስለመበላቱ ብስራት ራዲዮ ሰምቷል።
በተጠቀሰው እለት ከምሽቱ 3ሰዓት ላይ አንዲት እናት የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ህፃን ልጇን በመታቀፍ አቶ ሚኒሊክ ታዬ ከተባሉ ግለሰብ ቤት ታቀናለች።
ጫካ አፋፍ ላይ ከሚገኘው መኖሪያ ቤት ደርሳም ቡና ተፈልቶላት ከቤተሰቡ ጋር በመጫወት ላይ ሳለች ፤ ከጫካው የወጣ ጅብ ህፃኗን ከእናት እቅፍ ፈልቅቆ በመውሰድ ይሰወራል።
የከተማዋ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ በተለይ ለብስራት ራዲዮ ሪፓርተር ሚኪያስ ፀጋዬ እንደተናገሩት ፤ በሁኔታው የተደናገጠው ቤተሰብ ጅቡን ተከታትለው ወደ ጫካ ቢገቡም ሊያገኙት የቻሉት ብቸኛ ነገር የህፃን ጨርቅ ብቻ ሁኗል።
ጉዳዩ ለአዳማ ከተማ ፖሊስ ሪፖርት የተደረገ ሲሆን የምርመራ ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛል ያሉት ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ፤ በቅርብ ግዜያት መሰል አደጋ በከተማዋ ሲፈጠር ይህ ለሶስተኛ ግዜ መሆኑንም አስታውሰዋል።
[ብስራት ራዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዳማ ከተማ መስተዳድር ዳቤ ክፍለ ከተማ ዳቤ ሹሉቄ ቀበሌ ልዩ ቦታው ቀጠና 9 ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ለእንግድነት ከወላጅ እናቱ ጋር የሄደ የ 18ወር ህፃን በጅብ ስለመበላቱ ብስራት ራዲዮ ሰምቷል።
በተጠቀሰው እለት ከምሽቱ 3ሰዓት ላይ አንዲት እናት የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ህፃን ልጇን በመታቀፍ አቶ ሚኒሊክ ታዬ ከተባሉ ግለሰብ ቤት ታቀናለች።
ጫካ አፋፍ ላይ ከሚገኘው መኖሪያ ቤት ደርሳም ቡና ተፈልቶላት ከቤተሰቡ ጋር በመጫወት ላይ ሳለች ፤ ከጫካው የወጣ ጅብ ህፃኗን ከእናት እቅፍ ፈልቅቆ በመውሰድ ይሰወራል።
የከተማዋ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ በተለይ ለብስራት ራዲዮ ሪፓርተር ሚኪያስ ፀጋዬ እንደተናገሩት ፤ በሁኔታው የተደናገጠው ቤተሰብ ጅቡን ተከታትለው ወደ ጫካ ቢገቡም ሊያገኙት የቻሉት ብቸኛ ነገር የህፃን ጨርቅ ብቻ ሁኗል።
ጉዳዩ ለአዳማ ከተማ ፖሊስ ሪፖርት የተደረገ ሲሆን የምርመራ ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛል ያሉት ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ፤ በቅርብ ግዜያት መሰል አደጋ በከተማዋ ሲፈጠር ይህ ለሶስተኛ ግዜ መሆኑንም አስታውሰዋል።
[ብስራት ራዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ ባካሄደው ስብሰባ ህገ ወጥ የመሬት ወረራ፤ ባለቤት አልባ ህንፃዎች፤ የኮንደሚኒየም ቤቶች፤ የቀበሌ መኖርያና ንግድ ቤቶችን አስመልክቶ በጥናት የተገኘው ግኝትቶች ላይ የውሳኔ ሃሳብ አስተላለፈ፡፡
የከተማው ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የከተማው አመራር በሪፎርሙ በገባው ቃል መሰረት ምንም እንኳ ቢዘገይም የነዋሪው ቅሬታ መነሻ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት እና በተጨባጭ ጥናት በመመርኮዝ ለማጣራት እና ለመለየት የተደረገውን ጥረት ያመሰገኑ ሲሆን ወደፊት መወሰድ አለበት ባሉት እርምጃ ላይ አፅንኦት ሰተው ተወያይተዋል፡፡በመሆኑም በጥናቱ የተገኙ 322 ባለቤት አልባ ህንጻዎች በግልፅ ጨረታ ተሸጠው ወደ መንግስት ካዝና ገቢ እንዲሆኑ፤ በጥናቱ የተገኘው ህገ-ወጥ መንገድ የተያዙ፤ ባዶ ሆነው የተገኙ 21,695 የኮንዶሚኒየም ቤቶችን በማስለቀቅ ለተጠቃሚዎች እንዲታደል፤ በዋናነት በ1997 ተመዝጋቢ የሆኑና በቋሚነት እየቆጠቡ ላሉ ነዋሪዎች በእጣ እንዲተላለፍ፤ የቀበሌ ቤቶችን አስመልክቶ በህገ-ወጦች የተያዙ የመኖርያ ቤቶች ግልፅ የሆነ መስፈርት ወቶላቸው ለደሆች፤ ለአቅመ ደካሞችና ለተለያየ ችግር ለተጋለጡ ነዋሪዎች እንዲሰጥ፤ የቀበሌ የንግድ ቤቶች በህገ-ወጥነት ከያዙት ሰዎች ተነጥቆ ለስራ አጥ ወጣቶች በእጣ እንሰጥ ሲሉ ወስነዋል፡፡ካቢኔው በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ በሰፊው የተወያየ ሲሆን ይህ ችግርና ስርዓት አልበኝነት 1997 ጀምሮ እየተንከባለለ የመጣ መሆኑን እና ወደፊት እንዳይደገም እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል፡፡
[Capital]
@YeneTube @FikerAssefa
የከተማው ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የከተማው አመራር በሪፎርሙ በገባው ቃል መሰረት ምንም እንኳ ቢዘገይም የነዋሪው ቅሬታ መነሻ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት እና በተጨባጭ ጥናት በመመርኮዝ ለማጣራት እና ለመለየት የተደረገውን ጥረት ያመሰገኑ ሲሆን ወደፊት መወሰድ አለበት ባሉት እርምጃ ላይ አፅንኦት ሰተው ተወያይተዋል፡፡በመሆኑም በጥናቱ የተገኙ 322 ባለቤት አልባ ህንጻዎች በግልፅ ጨረታ ተሸጠው ወደ መንግስት ካዝና ገቢ እንዲሆኑ፤ በጥናቱ የተገኘው ህገ-ወጥ መንገድ የተያዙ፤ ባዶ ሆነው የተገኙ 21,695 የኮንዶሚኒየም ቤቶችን በማስለቀቅ ለተጠቃሚዎች እንዲታደል፤ በዋናነት በ1997 ተመዝጋቢ የሆኑና በቋሚነት እየቆጠቡ ላሉ ነዋሪዎች በእጣ እንዲተላለፍ፤ የቀበሌ ቤቶችን አስመልክቶ በህገ-ወጦች የተያዙ የመኖርያ ቤቶች ግልፅ የሆነ መስፈርት ወቶላቸው ለደሆች፤ ለአቅመ ደካሞችና ለተለያየ ችግር ለተጋለጡ ነዋሪዎች እንዲሰጥ፤ የቀበሌ የንግድ ቤቶች በህገ-ወጥነት ከያዙት ሰዎች ተነጥቆ ለስራ አጥ ወጣቶች በእጣ እንሰጥ ሲሉ ወስነዋል፡፡ካቢኔው በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ በሰፊው የተወያየ ሲሆን ይህ ችግርና ስርዓት አልበኝነት 1997 ጀምሮ እየተንከባለለ የመጣ መሆኑን እና ወደፊት እንዳይደገም እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል፡፡
[Capital]
@YeneTube @FikerAssefa
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ በትግራይ ክልል የሚገኙ የኤርትራ ስደተኛ መጠለያ ጣቢያዎችን ጎበኙ፡፡
ኮሚሽነሩ በማይ ዐይኒ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የኤርትራውያን ስደተኞችን ነው የጎበኙት፡፡
በጉብኝቱ የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ተሳትፈዋል።
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ኮሚሽነሩ በማይ ዐይኒ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የኤርትራውያን ስደተኞችን ነው የጎበኙት፡፡
በጉብኝቱ የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ተሳትፈዋል።
[Al-ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በደቡብ ጎንደር ዞን ሰዴ ሙጃ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ24 ሰዎች ህይወት አለፈ!
መነሻውን ከባሕር ዳር ያደረገው የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ሰዴ ሙጃ ወረዳ ሲደርስ 200 ሜትር ከሚረዝም ገደል በመግባቱ የ24 ሰዎች ህይወት ማለፉን የደቡብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የመንገድ ትራፊክ ደኅንነት ዋና ክፍል ኃላፊ ኮማንደር ጋሻው አለኸኝ ተናግረዋል፡፡
በአደጋው ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች በደብረታቦርና በፈለገሕይወት ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ኮማንደር ጋሻው ለአብመድ በስልክ ገልፀዋል፡፡የአደጋው መንስዔ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ ኮማንደሩ አመላክተዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
መነሻውን ከባሕር ዳር ያደረገው የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ሰዴ ሙጃ ወረዳ ሲደርስ 200 ሜትር ከሚረዝም ገደል በመግባቱ የ24 ሰዎች ህይወት ማለፉን የደቡብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የመንገድ ትራፊክ ደኅንነት ዋና ክፍል ኃላፊ ኮማንደር ጋሻው አለኸኝ ተናግረዋል፡፡
በአደጋው ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች በደብረታቦርና በፈለገሕይወት ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ኮማንደር ጋሻው ለአብመድ በስልክ ገልፀዋል፡፡የአደጋው መንስዔ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ ኮማንደሩ አመላክተዋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ ለመምህራን ይከፈል የነበረውን የቤት አበል ከብር 850 ወደ ብር 3 ሺህ እንዲሻሻል ወሰነ!
የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ ለመምህራን ይከፈል የነበረውን የቤት አበል ከብር 850 ወደ ብር 3 ሺህ እንዲሻሻል መወሰኑ ተገለጸ፡፡
የከተማ መስተዳድሩ ካሁን በፊት በከተማው ትምህርት ቤቶች ለሚያስተምሩ መምህራን 5 ሺህ የመኖርያ ቤት ማቅረቡ ይታወሳል፡፡
ሆኖም ለሁሉም መምህራን በፍጥነት ቤት ማዘጋጀት ባለመቻሉ፤ ለሁሉም መምህራን 3 ሺህ ብር የቤት አበል ክፍያ እንዲከፈላቸው የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ዛሬ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
ካቢኔው በተጨማሪም የከተማ የቦታ ደረጃና የመሬት ሊዝ ዋጋን አስመልክቶ በጥናት የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ አፀደቀ፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያጠናው ይህ የመነሻ ሃሳብ ከአሁን በፊት የከተማ ቦታ ደረጃ 14 የነበረውን ወደ 18 ከፍ እንዲል፤ እንዲሁም የሊዝ መነሻ ዋጋ በ18ቱም የቦታ ደረጃዎች ተጠንቶ መቅረቡ ነው የተገለጸው፡፡
የጥናቱ ዋና አላማ በዝቅተኛ ሁኔታ ኑሯቸውን የሚመሩ ዜጎችን እንዳይጎዱ፤ ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት፤ ባለሃብቶች ወደ ኢንቨስትመንቱ እንዲገቡ ለማድረግ፤ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን እና ልማትን ለማፋጠን የሚረዳ መሆኑን ተገልጿል፡፡
ጥናቱ አጠቃላይ የከተማ አስተዳደሩ በተለያየ አግባብ የሚያወጣቸውን ወጪ መነሻ በማድረግ በሳይንሳዊ መንገድ እንዲጠና በመደረጉ ባለፉት ሁለት አመታት መሬት በምደባ ብቻ ይሠጥ የነበረውን አሁን ግን በምደባም በጨረታም ለመስጠት ያስችላልም ተብሎአል፡፡
ነባር ይዞታዎችና ሰነድ አልባ ቦታዎች ቀድሞ ባለው መመሪያ 11/2004 የሚስተናገዱ ይሆናሉ በማለት ካቢኔው መወሰኑን ከአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬተርያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ ለመምህራን ይከፈል የነበረውን የቤት አበል ከብር 850 ወደ ብር 3 ሺህ እንዲሻሻል መወሰኑ ተገለጸ፡፡
የከተማ መስተዳድሩ ካሁን በፊት በከተማው ትምህርት ቤቶች ለሚያስተምሩ መምህራን 5 ሺህ የመኖርያ ቤት ማቅረቡ ይታወሳል፡፡
ሆኖም ለሁሉም መምህራን በፍጥነት ቤት ማዘጋጀት ባለመቻሉ፤ ለሁሉም መምህራን 3 ሺህ ብር የቤት አበል ክፍያ እንዲከፈላቸው የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ዛሬ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
ካቢኔው በተጨማሪም የከተማ የቦታ ደረጃና የመሬት ሊዝ ዋጋን አስመልክቶ በጥናት የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ አፀደቀ፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያጠናው ይህ የመነሻ ሃሳብ ከአሁን በፊት የከተማ ቦታ ደረጃ 14 የነበረውን ወደ 18 ከፍ እንዲል፤ እንዲሁም የሊዝ መነሻ ዋጋ በ18ቱም የቦታ ደረጃዎች ተጠንቶ መቅረቡ ነው የተገለጸው፡፡
የጥናቱ ዋና አላማ በዝቅተኛ ሁኔታ ኑሯቸውን የሚመሩ ዜጎችን እንዳይጎዱ፤ ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት፤ ባለሃብቶች ወደ ኢንቨስትመንቱ እንዲገቡ ለማድረግ፤ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን እና ልማትን ለማፋጠን የሚረዳ መሆኑን ተገልጿል፡፡
ጥናቱ አጠቃላይ የከተማ አስተዳደሩ በተለያየ አግባብ የሚያወጣቸውን ወጪ መነሻ በማድረግ በሳይንሳዊ መንገድ እንዲጠና በመደረጉ ባለፉት ሁለት አመታት መሬት በምደባ ብቻ ይሠጥ የነበረውን አሁን ግን በምደባም በጨረታም ለመስጠት ያስችላልም ተብሎአል፡፡
ነባር ይዞታዎችና ሰነድ አልባ ቦታዎች ቀድሞ ባለው መመሪያ 11/2004 የሚስተናገዱ ይሆናሉ በማለት ካቢኔው መወሰኑን ከአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬተርያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በሱዳን ወረራ ኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች ከ226 ሚ.ብር በላይ ንብረት መዘረፋቸውን ተናገሩ!
የዛሬ 2 ወር ገደማ የሱዳን ጦር በሃይል ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ገብቶ የመሬት ወረራ ሲፈፅም ከ226 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት፤ መዘረፋቸውን የአካባቢው ባለሃብት አርሶ አደሮች ለአዲስ አድማስ የገለፁ ሲሆን መንግስት አስቸኳይ ድጋፍ አድርጎላቸው፣ ወደ ስራቸው መመለስ እንዲችሉ ጠይቀዋል፡፡
16 የሚደርሱ ባለሀብት አርሶ አደሮች በሱዳን ወታደሮች ወረራና ጥቃት እያንዳንዳቸው ከ2.5 ሚሊዮን እስከ 39 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት እንደተዘረፉ ተናግረዋል፡፡ህዳር 26 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ ስምንት ሰዓት ተኩል ላይ ባልጠበቅነው ሁኔታ ነው ጥቃት የተፈፀመብን የሚሉት ባለሃብት አርሶ አደሮቹ፤ ቋሚ ንብረታቸውን ጨምሮ በማሳ ላይ የነበረ የደረሱ የሰሊጥና የማሽላ ሰብልም መዘረፋቸውን ነው ለአዲስ አድማስ ያስረዱት፡፡
[Addis Admas]
@YeneTube @FikerAssefa
የዛሬ 2 ወር ገደማ የሱዳን ጦር በሃይል ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ገብቶ የመሬት ወረራ ሲፈፅም ከ226 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት፤ መዘረፋቸውን የአካባቢው ባለሃብት አርሶ አደሮች ለአዲስ አድማስ የገለፁ ሲሆን መንግስት አስቸኳይ ድጋፍ አድርጎላቸው፣ ወደ ስራቸው መመለስ እንዲችሉ ጠይቀዋል፡፡
16 የሚደርሱ ባለሀብት አርሶ አደሮች በሱዳን ወታደሮች ወረራና ጥቃት እያንዳንዳቸው ከ2.5 ሚሊዮን እስከ 39 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት እንደተዘረፉ ተናግረዋል፡፡ህዳር 26 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ ስምንት ሰዓት ተኩል ላይ ባልጠበቅነው ሁኔታ ነው ጥቃት የተፈፀመብን የሚሉት ባለሃብት አርሶ አደሮቹ፤ ቋሚ ንብረታቸውን ጨምሮ በማሳ ላይ የነበረ የደረሱ የሰሊጥና የማሽላ ሰብልም መዘረፋቸውን ነው ለአዲስ አድማስ ያስረዱት፡፡
[Addis Admas]
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ዕዳ ተረክቦ የሚያስተዳድር ኮርፖሬሽን ልታቋቁም ነው።
የኢትዮጵያ የምኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት "ከፍተኛ የዕዳ ጫና ያለባቸውን የመንግስት የልማት ድርጅቶች የዕዳ ጫና ለማቃለል የቀረበ የውሳኔ ሐሳብ እንዲሁም የዕዳ እና የሐብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን" ማቋቋሚያ የደንብ ረቂቅን አጽድቋል።የጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጽህፈት ቤት ይፋ ባደረገው መግለጫ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በነበሩባቸው እንከኖች "ከአገር ውስጥና ከውጭ አገር በብድር የወሰዱትን ገንዘብ መክፈል አልቻሉም" ብሏል። "ተለይተው የሚሰጡትን የልማት ድርጅቶች ዕዳዎች የሚያስተዳድር እንዲሁም በጥናት በተለዩ የኢንቨስትመንት መስኮች የሚሰማራ ብሎም ውጤታማ የዕዳ እና የሐብት አስተዳደር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ኮርፖሬሽን" እንዲቋቋም ውሳኔ መተላለፉንም የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።የኢትዮጵያ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታ እና አስተዳደር ኤጀንሲ ድረ-ገጽ እንደሚያሳየው አገሪቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ 21 የልማት ድርጅቶች አሏት። ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና የስኳር ኮርፖሬሽን ከእነዚህ መካከል ይጠቀሳሉ።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የምኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት "ከፍተኛ የዕዳ ጫና ያለባቸውን የመንግስት የልማት ድርጅቶች የዕዳ ጫና ለማቃለል የቀረበ የውሳኔ ሐሳብ እንዲሁም የዕዳ እና የሐብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን" ማቋቋሚያ የደንብ ረቂቅን አጽድቋል።የጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጽህፈት ቤት ይፋ ባደረገው መግለጫ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በነበሩባቸው እንከኖች "ከአገር ውስጥና ከውጭ አገር በብድር የወሰዱትን ገንዘብ መክፈል አልቻሉም" ብሏል። "ተለይተው የሚሰጡትን የልማት ድርጅቶች ዕዳዎች የሚያስተዳድር እንዲሁም በጥናት በተለዩ የኢንቨስትመንት መስኮች የሚሰማራ ብሎም ውጤታማ የዕዳ እና የሐብት አስተዳደር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል ኮርፖሬሽን" እንዲቋቋም ውሳኔ መተላለፉንም የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።የኢትዮጵያ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታ እና አስተዳደር ኤጀንሲ ድረ-ገጽ እንደሚያሳየው አገሪቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ 21 የልማት ድርጅቶች አሏት። ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና የስኳር ኮርፖሬሽን ከእነዚህ መካከል ይጠቀሳሉ።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የመቐለ ከተማን ነዋሪ ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያግዙ ከ400 በላይ ነባር የፖሊስ አባላት ወደ መደበኛ ሥራቸው መመለሳቸውን የከተማዋ ጊዜያዊ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በጽህፈት ቤቱ የወንጀል መከላከል ሃላፊ ኢንስፔክተር ሠለሞን ገብረመድህን ለኢዜአ እንደገለጹት ወደ ስራቸው የተመለሱት በተደረላቸው ጥሪ መሰረት ቀደም ሲል በከተማው ከነበሩት ከ800 በላይ የፖሊስ አባላት መካከል ነው።
ወንጀልን በመከላከል የከተማዋን ነዋሪ ህዝብ ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የፖሊስ አባላቱ መደበኛ ስራቸው መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት በክፍለ ከተማ ደረጃም የፖሊስ አባላትን የማደራጀት እየተከናወነ መሆኑን ኢንስፔክተር ሠለሞን አስረድተዋል።
ህብረተሰቡ ሠላምና ፀጥታውን በማስጠበቅ ተሳታፊ መሆን እንዳለበት ያመለከቱት ኢንስፔክተር ሠለሞን በቀጣይም በቀበሌ ደረጃ የኮሚኒቲ ፖሊስ የማደራጀት ስራ እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
በከተማ ደረጃ ወንጀሎችን የመከላከል ስራ መቀጠሉን ገልጸው በእስካሁኑ ሂደትም ልዩ ልዩ ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠሩ45 ግለሰቦች መያዛቸውንና ጉዳያቸው ተጠርቶ ወደ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡም አስታውቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በጽህፈት ቤቱ የወንጀል መከላከል ሃላፊ ኢንስፔክተር ሠለሞን ገብረመድህን ለኢዜአ እንደገለጹት ወደ ስራቸው የተመለሱት በተደረላቸው ጥሪ መሰረት ቀደም ሲል በከተማው ከነበሩት ከ800 በላይ የፖሊስ አባላት መካከል ነው።
ወንጀልን በመከላከል የከተማዋን ነዋሪ ህዝብ ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የፖሊስ አባላቱ መደበኛ ስራቸው መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት በክፍለ ከተማ ደረጃም የፖሊስ አባላትን የማደራጀት እየተከናወነ መሆኑን ኢንስፔክተር ሠለሞን አስረድተዋል።
ህብረተሰቡ ሠላምና ፀጥታውን በማስጠበቅ ተሳታፊ መሆን እንዳለበት ያመለከቱት ኢንስፔክተር ሠለሞን በቀጣይም በቀበሌ ደረጃ የኮሚኒቲ ፖሊስ የማደራጀት ስራ እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
በከተማ ደረጃ ወንጀሎችን የመከላከል ስራ መቀጠሉን ገልጸው በእስካሁኑ ሂደትም ልዩ ልዩ ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠሩ45 ግለሰቦች መያዛቸውንና ጉዳያቸው ተጠርቶ ወደ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡም አስታውቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የህዳሴው ግድብ ግንባታ በታቀደለት ጊዜና በሚፈለገው መንገድ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ!
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ እና የኢትዮጰያ ኤሌክትሪክ ቦርድ አባላት በትናንትናው ዕለት በስፍራው በመገኘት ግምገማ አድርገዋል። ከጉብኝቱ በኋላ ፣ የግድቡ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ እየተከናወነ እንደሆነና የግንባታ ሂደቱም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ገልፀዋል፡፡ሚንስትሩና የቦርድ አባላቱ የግንባታ ስራውን ከሚያከናውኑ ኮንትራክተሮች ፣ ከባለሙያዎችና አማካሪዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ ለግድቡ መጠናቀቅ መላው ኢትዮጵያውያን ከሃገር ውስጥና ውጪ እያደረጉት ያለው ድጋፍ ከምን ግዜውም በላይ ተጠናክሮ ቀጥሏልም ነው ያሉት።
@YeneTube @FikerAssefa
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ እና የኢትዮጰያ ኤሌክትሪክ ቦርድ አባላት በትናንትናው ዕለት በስፍራው በመገኘት ግምገማ አድርገዋል። ከጉብኝቱ በኋላ ፣ የግድቡ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ እየተከናወነ እንደሆነና የግንባታ ሂደቱም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ገልፀዋል፡፡ሚንስትሩና የቦርድ አባላቱ የግንባታ ስራውን ከሚያከናውኑ ኮንትራክተሮች ፣ ከባለሙያዎችና አማካሪዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ ለግድቡ መጠናቀቅ መላው ኢትዮጵያውያን ከሃገር ውስጥና ውጪ እያደረጉት ያለው ድጋፍ ከምን ግዜውም በላይ ተጠናክሮ ቀጥሏልም ነው ያሉት።
@YeneTube @FikerAssefa
የህዳሴው ግድብ ግንባታ በታቀደለት ጊዜና በሚፈለገው መንገድ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ!
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ እና የኢትዮጰያ ኤሌክትሪክ ቦርድ አባላት በትናንትናው ዕለት በስፍራው በመገኘት ግምገማ አድርገዋል። ከጉብኝቱ በኋላ ፣ የግድቡ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ እየተከናወነ እንደሆነና የግንባታ ሂደቱም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ገልፀዋል፡፡ሚንስትሩና የቦርድ አባላቱ የግንባታ ስራውን ከሚያከናውኑ ኮንትራክተሮች ፣ ከባለሙያዎችና አማካሪዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ ለግድቡ መጠናቀቅ መላው ኢትዮጵያውያን ከሃገር ውስጥና ውጪ እያደረጉት ያለው ድጋፍ ከምን ግዜውም በላይ ተጠናክሮ ቀጥሏልም ነው ያሉት።
@YeneTube @FikerAssefa
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ እና የኢትዮጰያ ኤሌክትሪክ ቦርድ አባላት በትናንትናው ዕለት በስፍራው በመገኘት ግምገማ አድርገዋል። ከጉብኝቱ በኋላ ፣ የግድቡ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ እየተከናወነ እንደሆነና የግንባታ ሂደቱም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ገልፀዋል፡፡ሚንስትሩና የቦርድ አባላቱ የግንባታ ስራውን ከሚያከናውኑ ኮንትራክተሮች ፣ ከባለሙያዎችና አማካሪዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ ለግድቡ መጠናቀቅ መላው ኢትዮጵያውያን ከሃገር ውስጥና ውጪ እያደረጉት ያለው ድጋፍ ከምን ግዜውም በላይ ተጠናክሮ ቀጥሏልም ነው ያሉት።
@YeneTube @FikerAssefa
የኮሮና ክትባት በመጪው ሚያዝያ ወር ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚገባ ተገለጸ!
ክትባቱ 20 ከመቶ ለሚሆኑ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች ይዳረሳል ተብሏል፡፡ የክትባት ስራውን የሚያስተባብር ግብረሃይል በብሄራዊ ደረጃ መቋቋሙንም የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ክትባቱ 20 ከመቶ ለሚሆኑ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች ይዳረሳል ተብሏል፡፡ የክትባት ስራውን የሚያስተባብር ግብረሃይል በብሄራዊ ደረጃ መቋቋሙንም የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የህወሃት ሊቀመንበር የሆኑት ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ከሁለት ወራት ዝምታ በኋላ በትናትናው ዕለት፣ ጥር 22፣ 2013 ዓ.ም በድምፂ ወያነ ትግራይ ፌስቡክ ገፅ በቀጥታ ለትግራይ ህዝብ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) በትግራይ ላይ የተከሰተውን ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ በተቋረጠው ድምፂ ወያነ ትግራይ የፌስቡክ ገፅ በቀጥታ ለ13 ደቂቃዎች በድምፅ ባስተላለፉት መልዕከት ክልሉ ላይ ደርሷል ስለተባሉ ውድመቶች፣ ቀጥሏል ስላሉት ትግል ሁኔታ እንዲሁም ለትግራይ ህዝብና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ጥሪ አቅርበዋል።"የትግራይ ሴቶች በተናጠልና በደቦ ይደፈራሉ። የትግራይ ሰዎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችና ነጻነቶች በከፋ መገለጫና አኳሃን ይጣሳሉ፣ ይገፈፋሉ። የትግራይ መንደሮችና ዓብያተ እምነቶች፣ የትግራይ ሰራዊት ይኑርበት አይኑርበት ሳይገዳቸው የቦምቦችና የመድፎ ዒላማ ይደረጋሉ። ውድና መተኪያ የሌላቸው ቅርሶችም ይወድማሉ፣ ይዘረፋሉ። በሚልዮን የሚቆጠር ህዝብ እንዳለ ከቀየው ወጥቶና ተፈናቅሎ የመከራ ኑሮ ይኖራል።" ብለዋል።
በትግራይ ክልል ከተከሰተው ቀውስ ጋር በተያያዘ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና የፌደራል ፖሊስ በበርካታ የህወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣታቸው ይፋ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው። ከነዚህም አመራሮች አንዱ የህወሃት ሊቀ መንበር ደብረ ፅዮን ሲሆኑ በአሁኑ ወቅት ያሉበት አይታወቅም።ለእስር ማዘዣው ዋነኛ ምክንያቶቹ በትግራይ ክልል በሚገኘው በአገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈፀም፣ የአገር ክህደት ወንጀል በመፈፀም፣ የመከላከያ ሠራዊትና የፖሊስ አባላት እንዲታገቱ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው ነው።
(BBC)
@YeneTube @FikerAssefa
ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) በትግራይ ላይ የተከሰተውን ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ በተቋረጠው ድምፂ ወያነ ትግራይ የፌስቡክ ገፅ በቀጥታ ለ13 ደቂቃዎች በድምፅ ባስተላለፉት መልዕከት ክልሉ ላይ ደርሷል ስለተባሉ ውድመቶች፣ ቀጥሏል ስላሉት ትግል ሁኔታ እንዲሁም ለትግራይ ህዝብና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ጥሪ አቅርበዋል።"የትግራይ ሴቶች በተናጠልና በደቦ ይደፈራሉ። የትግራይ ሰዎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችና ነጻነቶች በከፋ መገለጫና አኳሃን ይጣሳሉ፣ ይገፈፋሉ። የትግራይ መንደሮችና ዓብያተ እምነቶች፣ የትግራይ ሰራዊት ይኑርበት አይኑርበት ሳይገዳቸው የቦምቦችና የመድፎ ዒላማ ይደረጋሉ። ውድና መተኪያ የሌላቸው ቅርሶችም ይወድማሉ፣ ይዘረፋሉ። በሚልዮን የሚቆጠር ህዝብ እንዳለ ከቀየው ወጥቶና ተፈናቅሎ የመከራ ኑሮ ይኖራል።" ብለዋል።
በትግራይ ክልል ከተከሰተው ቀውስ ጋር በተያያዘ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና የፌደራል ፖሊስ በበርካታ የህወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣታቸው ይፋ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው። ከነዚህም አመራሮች አንዱ የህወሃት ሊቀ መንበር ደብረ ፅዮን ሲሆኑ በአሁኑ ወቅት ያሉበት አይታወቅም።ለእስር ማዘዣው ዋነኛ ምክንያቶቹ በትግራይ ክልል በሚገኘው በአገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈፀም፣ የአገር ክህደት ወንጀል በመፈፀም፣ የመከላከያ ሠራዊትና የፖሊስ አባላት እንዲታገቱ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው ነው።
(BBC)
@YeneTube @FikerAssefa
በጉለሌ ክፍለ ከተማ ጉለሌ እጽዋት ማዕከል ውስጥ የተነሣው የእሳት ቃጠሎ የከፋ ጉዳት ሳያስከትል እና ወደ ሌላ ቦታ ሳይስፋፋ በቁጥጥር ስር ዋለ።
ዛሬ ከቀኑ 7:00 ሰዓት አካባቢ በጉለሌ ክፍለ ከተማ በሚገኘው በጉለሌ እጽዋት ማዕከል ውስጥ ተነስቶ የነበረው እሣት በተደረገው ርብርብ እሳቱ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ እና ወደ ሌላ ቦታ ሳይስፋፋ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል ።
ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የእሣት አደጋው በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጸዋል።የተነሣውን እሳት ማጥፋት በርካታ የአዲስ አበባና የፌዴራል ፖሊስ አመራሮች እና አባላት ፣ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት እና የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ባለሙያዎች ፣ የመንገዶች ባለስልጣን፣ የአካባቢው አስተዳደር እና ህብረተሰቡ እሳቱን ለማጥፋት ከፍተኛ ርብርብ ማድረጋቸውን ወ/ሮ አዳነች ገልጸዋል።እሳት ውስጥ ገብታችሁ እሳት ላጠፋችሁ ሁሉም አካላት በከተማ አስተዳደሩ ስም ከልብ ላመሰግን እወዳለሁ ብለዋል።ለእሳቱ ምክንያት ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል ያሉት ወ/ሮ አዳነች ቀሪ ስራዎችን በልዩ ትኩረት የምናከውን ሲሆን መረጃዎችን በየወቅቱ ለህብረተሰቡ እናደርሳለን ብለዋል ።
Via Addis Ababa City PS
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ ከቀኑ 7:00 ሰዓት አካባቢ በጉለሌ ክፍለ ከተማ በሚገኘው በጉለሌ እጽዋት ማዕከል ውስጥ ተነስቶ የነበረው እሣት በተደረገው ርብርብ እሳቱ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ እና ወደ ሌላ ቦታ ሳይስፋፋ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል ።
ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የእሣት አደጋው በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጸዋል።የተነሣውን እሳት ማጥፋት በርካታ የአዲስ አበባና የፌዴራል ፖሊስ አመራሮች እና አባላት ፣ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት እና የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ባለሙያዎች ፣ የመንገዶች ባለስልጣን፣ የአካባቢው አስተዳደር እና ህብረተሰቡ እሳቱን ለማጥፋት ከፍተኛ ርብርብ ማድረጋቸውን ወ/ሮ አዳነች ገልጸዋል።እሳት ውስጥ ገብታችሁ እሳት ላጠፋችሁ ሁሉም አካላት በከተማ አስተዳደሩ ስም ከልብ ላመሰግን እወዳለሁ ብለዋል።ለእሳቱ ምክንያት ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል ያሉት ወ/ሮ አዳነች ቀሪ ስራዎችን በልዩ ትኩረት የምናከውን ሲሆን መረጃዎችን በየወቅቱ ለህብረተሰቡ እናደርሳለን ብለዋል ።
Via Addis Ababa City PS
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 629 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተያዙ፡፡
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 7,109 የላብራቶሪ ምርመራ 629 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡
ባለፋት 24 ሰዓታት የ2ሰዎች ሕይወት አልፏል፤አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 2,093 አድርሶታል።
በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 274 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 122,862 አድርሶታል፡፡
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 137,650 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 7,109 የላብራቶሪ ምርመራ 629 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡
ባለፋት 24 ሰዓታት የ2ሰዎች ሕይወት አልፏል፤አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 2,093 አድርሶታል።
በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 274 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 122,862 አድርሶታል፡፡
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 137,650 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
#CoupAlert
በማይናማሯ መሪ አንግ ሳን ሱ ኪ ላይ መፈንቅለ መንግሥት ተፈፀመ!
በቀድሞዋ በርማ በአሁኑ መጠሪያዋ ማይናማር የምትባለው ሀገር መሪ ዳው አንግ ሳን ሱ ኪ ላይ በመከላከያ ሰራዊቱ መፈንቅለ መንግስት እንደተፈፀመባቸው እየወጡ የሚገኙ ዘገባዎች ያሳያሉ። የሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን የተቋረጠ ሲሆን የኢንተርኔት እና የስልክ ግኑኝነት በተመሳሳይ ተቋርጠዋል። መከላከያ ሰራዊቱ በራሱ የቴሌቪዥን ጣቢያ እንዳስታወቀው ከሆነ በሀገሪቱ ለአንድ አመት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል። ይህንንም ተከትሎ ሁሉም ስልጣኖች በመከላከያ ሰራዊቱ እጅ እንደሚሆኑም ተገልጿል። በዚህ መግለጫ መሪዋና የሷ ሰዎች ከሁለት ወር በፊት የተደረገውን የምርጫ ውጤት በማጭበርበራቸው ከስልጣን እንዲነሱና እንዲታሰሩ ተደርገዋል በሚል ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
በማይናማሯ መሪ አንግ ሳን ሱ ኪ ላይ መፈንቅለ መንግሥት ተፈፀመ!
በቀድሞዋ በርማ በአሁኑ መጠሪያዋ ማይናማር የምትባለው ሀገር መሪ ዳው አንግ ሳን ሱ ኪ ላይ በመከላከያ ሰራዊቱ መፈንቅለ መንግስት እንደተፈፀመባቸው እየወጡ የሚገኙ ዘገባዎች ያሳያሉ። የሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን የተቋረጠ ሲሆን የኢንተርኔት እና የስልክ ግኑኝነት በተመሳሳይ ተቋርጠዋል። መከላከያ ሰራዊቱ በራሱ የቴሌቪዥን ጣቢያ እንዳስታወቀው ከሆነ በሀገሪቱ ለአንድ አመት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል። ይህንንም ተከትሎ ሁሉም ስልጣኖች በመከላከያ ሰራዊቱ እጅ እንደሚሆኑም ተገልጿል። በዚህ መግለጫ መሪዋና የሷ ሰዎች ከሁለት ወር በፊት የተደረገውን የምርጫ ውጤት በማጭበርበራቸው ከስልጣን እንዲነሱና እንዲታሰሩ ተደርገዋል በሚል ተገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
✅ ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ
✅ ከ3,200 በላይ ዕቃዎች
@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com
📞 0953707070
Dedicated online shopping platform
✅ ከ3,200 በላይ ዕቃዎች
@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com
📞 0953707070
Dedicated online shopping platform
Forwarded from YeneTube
🖼 ለጓደኛ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለሙሽሮች እና ለተመራቂዎች ለየት ያለ ስጦታ መስጠት ይፈልጋሉ?
#join
👇👇👇👇
@giftsoflovee
@giftsoflovee
👆👆👆👆
📱+251914839754
📱+251936871620
#ኣድራሻችን፡ 4 ኪሎ: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ
#join
👇👇👇👇
@giftsoflovee
@giftsoflovee
👆👆👆👆
📱+251914839754
📱+251936871620
#ኣድራሻችን፡ 4 ኪሎ: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ