YeneTube
የአውሎ ሚዲያ ጋዜጠኛ የሆነው በቃሉ አላምረው ዛሬ ከጠዋቱ 2 ሰዓት አካባቢ በሶስት ፖሊሶችና አንድ የፀጥታ ባለሙያ ተወስዶ እንደታሰረ አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል። @YeneTube @FikerAssefa
የአውሎ ሜዲያ አዘጋጅ ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ዛሬ ዋስትና አስይዞ ከእስር እንዲፈታ ፍርድ ቤት ቢወሰንለትም፣ ፖሊስ ይግበኝ እንደጠየቀበት ሜዲያው በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ዘግቧል፡፡ በይግባኙ የተነሳ ጋዜጠኛው ሳይፈታ ቀርቷል፡፡ ጋዜጠኛው 10 ሺህ ብር ዋስ አስይዞ እንዲፈታ ነበር ፍርድ ቤት ዛሬ ጧት የወሰነው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
የመከላከያ ሠራዊት በዛሬው ዕለት በትግራይ በምሥራቅና በምዕራብ ግንባሮች ወሳኝ ድሎችን ተቀዳጅቷል ተባለ።
በምሥራቁ ግንባር ራያ ሙሉ በሙሉ ነጻ ወጥቷል። ጨርጨር፣ ጉጉፍቶ መሖኒን ሠራዊቱ ነጻ አውጥቷል። በየቦታው የነበሩ ወሳኝ የኮንክሪት ምሽጐችንም አፍርሷል። ሠራዊቱ በአሁኑ ጊዜ ወደ መቀሌ በመገሥገሥ ላይ ነው። በምዕራብ ግንባር ደግሞ በአዲ ነብሪድና በአዲ ዳእሮ የሚገኙ ከባድ ምሽጎችን በማፍረስ ሽሬን ተቆጣጥሮ ወደ አክሱም በመገሥገሥ ላይ ይገኛል።
በውጊያው እጅግ ብዙ መሣሪያዎች ከመማረካቸውም በላይ ህወሓት ለክፉ ዓላማው ያሰለፋቸው የትግራይ ልዩ ኃይል አባላት በቁጥጥር ሥር ውለዋል።የመከላከያ ሠራዊቱ የህወሓት ጁንታን በሕግ ቁጥጥር ሥር ለማዋል እየገሠገሠ ሲሆን የጁንታው ኃይል የመከላከያ ሠራዊቱን ክንድ መቋቋም አቅቶት ወደኋላ እየሸሸ ነው።
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
በምሥራቁ ግንባር ራያ ሙሉ በሙሉ ነጻ ወጥቷል። ጨርጨር፣ ጉጉፍቶ መሖኒን ሠራዊቱ ነጻ አውጥቷል። በየቦታው የነበሩ ወሳኝ የኮንክሪት ምሽጐችንም አፍርሷል። ሠራዊቱ በአሁኑ ጊዜ ወደ መቀሌ በመገሥገሥ ላይ ነው። በምዕራብ ግንባር ደግሞ በአዲ ነብሪድና በአዲ ዳእሮ የሚገኙ ከባድ ምሽጎችን በማፍረስ ሽሬን ተቆጣጥሮ ወደ አክሱም በመገሥገሥ ላይ ይገኛል።
በውጊያው እጅግ ብዙ መሣሪያዎች ከመማረካቸውም በላይ ህወሓት ለክፉ ዓላማው ያሰለፋቸው የትግራይ ልዩ ኃይል አባላት በቁጥጥር ሥር ውለዋል።የመከላከያ ሠራዊቱ የህወሓት ጁንታን በሕግ ቁጥጥር ሥር ለማዋል እየገሠገሠ ሲሆን የጁንታው ኃይል የመከላከያ ሠራዊቱን ክንድ መቋቋም አቅቶት ወደኋላ እየሸሸ ነው።
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
<<"የኢትዮጵያ መንግሥት ከደቡብ ሱዳን የጦር ድጋፍ እንዲደረግለት በደብዳቤ ጠይቋል" ተብሎ የሀሰት ዜና ተሰራጭቷል። እንዲህ ያሉ የፈጠራ ዜናዎች፣ የሀገር ውስጥ ጉዳያችንን ቀጣናዊ ገጽታ ያለው አስመስሎ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማቅረብ በአጥፊዎቹ አካላት የሚደረግ ጥረት ነው። ሁሉም ሰው ይህን የመሰሉ የሀሰት ዜናዎችን ባለማጋራት፣ የተሳሳተ መረጃን ከማሰራጨት እንዲቆጠብ ጥሪ እናደርጋለን።>>
[የአስቸኳይ አዋጅ መረጃ አጣሪ]
@YeneTube @FikerAssefa
[የአስቸኳይ አዋጅ መረጃ አጣሪ]
@YeneTube @FikerAssefa
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ምኒስትር ማይክ ፖምፔዎ ህወሓት በኤርትራ ላይ የፈጸመውን ጥቃት አወገዙ።
ውጭ ጉዳይ ምኒስትሩ "ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ በኤርትራ ላይ የፈጸመውን ጥቃት እና ግጭቱን ዓለም አቀፋዊ ለማድረግ ያደረገውን ሙከራ አጥብቀን እናወግዛለን።ህወሓት እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ግጭቱን ለማብረድ፣ ሰላምን ለማስፈን እና የሰላማዊ ሰዎችን ደሕንነት ለመጠበቅ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ እናቀርባለን" ብለዋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
ውጭ ጉዳይ ምኒስትሩ "ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ በኤርትራ ላይ የፈጸመውን ጥቃት እና ግጭቱን ዓለም አቀፋዊ ለማድረግ ያደረገውን ሙከራ አጥብቀን እናወግዛለን።ህወሓት እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ግጭቱን ለማብረድ፣ ሰላምን ለማስፈን እና የሰላማዊ ሰዎችን ደሕንነት ለመጠበቅ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ እናቀርባለን" ብለዋል።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 339 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተያዙ፡፡
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 3,778 የላብራቶሪ ምርመራ 339 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ባለፋት 24 ሰዓታት የ7 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 1,588 አድርሶታል።በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 163 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 64,293 አድርሶታል፡፡በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 103,395 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 3,778 የላብራቶሪ ምርመራ 339 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡ባለፋት 24 ሰዓታት የ7 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 1,588 አድርሶታል።በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 163 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 64,293 አድርሶታል፡፡በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 103,395 ደርሷል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ሕወሐት ወደ መቀሌ የሚያስኬዱ አራት ድልድዮችን እያፈረሰ ነው ተባለ።
የመከላከያ ሠራዊት ወደፊት መገሥገሡ ያስጨነቀው 'ጁንታ'፣ በሁሉም አቅጣጫ ወደ መቀሌ በሚወስዱት መንገዶች ላይ የሚገኙ አራት ድልድዮችን ማፍረሱን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ አስታውቋል።የተማመነባቸው ከባድ ምሽጎቹ ፈራርሰው፣ በሽሬ መንገድ የደረሰበት ሽንፈት ያንገበገበው ጁንታ፣ በሽሬና በአክሱም መካከል የሚገኘውን አስፓልት በግሬደር ቆፍሮ ወደ ጉድጓድነት ቀይሮታል።የሕወሐት ጁንታው እስከዛሬ ከፈጸማቸው ወንጀሎች በተጨማሪ ባወደማቸው መሠረተ ልማቶች በቅርቡ ይጠይቅባቸዋልም ብሏል መረጃው።
@YeneTube @FikerAssefa
የመከላከያ ሠራዊት ወደፊት መገሥገሡ ያስጨነቀው 'ጁንታ'፣ በሁሉም አቅጣጫ ወደ መቀሌ በሚወስዱት መንገዶች ላይ የሚገኙ አራት ድልድዮችን ማፍረሱን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ አስታውቋል።የተማመነባቸው ከባድ ምሽጎቹ ፈራርሰው፣ በሽሬ መንገድ የደረሰበት ሽንፈት ያንገበገበው ጁንታ፣ በሽሬና በአክሱም መካከል የሚገኘውን አስፓልት በግሬደር ቆፍሮ ወደ ጉድጓድነት ቀይሮታል።የሕወሐት ጁንታው እስከዛሬ ከፈጸማቸው ወንጀሎች በተጨማሪ ባወደማቸው መሠረተ ልማቶች በቅርቡ ይጠይቅባቸዋልም ብሏል መረጃው።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
"ከ 27,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከትግራይ ወደ ሱዳን ገብተዋል" የተመድ ስደተኞች ኮሚሽን
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን በፌዴራልና በትግራይ ክልል መንግሥታት መካከል ተቀስቅሶ ለሁለት ሳምንታት ያህል እየተካሄደ ባለው ወጊያ ሳቢያ በቀን በአማካይ ከ4000 በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከኖቬምበር 10 ወዲህ የሱዳንን ድንበር እየተሻገሩ መሆኑ የሰብዓዊ ዕርዳታ ቀውስ ያሳሰበው መሆኑን ገልጧል።
የተመድ ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን ቃል አቀባይ የሆኑት ባባር ባሎች ሁነቱ የሰብዓዊ ቀውሱን ወደ ላቀ ደረጃ እያመራው መሆኑን ጠቁመው በኮሚሽኑ በኩል "የእርዳታው አስፈላጊነት በጨመረ ቁጥር ሰብዓዊ ዕገዛውን ከፍ እያደረገ" ያለ መሆኑን አስታውቀዋል።በጦርነቱም ሳቢያ የረድኤት ሠራተኞች ክልሉን ለቅቀው እየወጡ ይገኛሉ።
አንድ ዲፕሎማት አክለውም ከጦርነቱ በፊት በርካታ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች የእርዳታ ምግብ እየተደጎሙ ያሉ እንደነበር፣ በዚህ ሳምንት ውስጥ 600 ያህል አብዛኛውን የውጭ አገር ዜጎች በሁለት ኮንቮይ አዲስ አበባ የገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን በፌዴራልና በትግራይ ክልል መንግሥታት መካከል ተቀስቅሶ ለሁለት ሳምንታት ያህል እየተካሄደ ባለው ወጊያ ሳቢያ በቀን በአማካይ ከ4000 በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከኖቬምበር 10 ወዲህ የሱዳንን ድንበር እየተሻገሩ መሆኑ የሰብዓዊ ዕርዳታ ቀውስ ያሳሰበው መሆኑን ገልጧል።
የተመድ ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን ቃል አቀባይ የሆኑት ባባር ባሎች ሁነቱ የሰብዓዊ ቀውሱን ወደ ላቀ ደረጃ እያመራው መሆኑን ጠቁመው በኮሚሽኑ በኩል "የእርዳታው አስፈላጊነት በጨመረ ቁጥር ሰብዓዊ ዕገዛውን ከፍ እያደረገ" ያለ መሆኑን አስታውቀዋል።በጦርነቱም ሳቢያ የረድኤት ሠራተኞች ክልሉን ለቅቀው እየወጡ ይገኛሉ።
አንድ ዲፕሎማት አክለውም ከጦርነቱ በፊት በርካታ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች የእርዳታ ምግብ እየተደጎሙ ያሉ እንደነበር፣ በዚህ ሳምንት ውስጥ 600 ያህል አብዛኛውን የውጭ አገር ዜጎች በሁለት ኮንቮይ አዲስ አበባ የገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለው ህግን የማስከበር ሂደት ወንጀለኞችን ለህግ ከማቅረብ ያለፈ አላማ እንደሌለው መንግሥት አስታወቀ።
የጠቅላይ ሚንስቴር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው ሕወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መለየት የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር እና ሕገ ወጥ ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት በድጋሜ ያረጋግጣል:: ነገር ግን ይህ ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ በብሔር ወይም በሌላ ወገንተኝነት ላይ የተቃኘ ነው የሚለውን የተሳሳተ እሳቤ አጥብቆ ያወግዛል፡፡
በአሁኑ ወቅት በትግራይ የሚካሄደው ሕግ የማስከበር ሥራ በዋነኝነት ኢትዮጵያን በማተራመስ ላይ በተሠማሩ ሥርዓት አልበኞች፣ በተንኮልና በሤራ በተሞሉ የሕወሐት ቡድን አባላት ላይ ያነጣጠረ ስለመሆኑ ማንም ሰው ጥርጣሬ ሊገባው አይገባም፡፡
በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ ሳይቀር የከፋ በደል የሚፈጽመውን ይህን የሕወሐት ጁንታየወንጀል ሰንሰለት ለማስቆም የፌዴራሉ መንግሥት ቆርጦ ተነሥቷል፡፡በዚህ ሕግ የማስከበር ዘመቻ የትግራይ ሕዝብ የመጀመሪያው ተጠቃሚ ይሆናል፡፡ለኢትዮጵያ ያለን ራእይ በብዝኃነት የሚኮሩ ብሔር ብሔረሰቦች በአንድነት የሚኖሩባት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት ነው፡፡ የትግራይ ሕዝብ ሕዝባችን ነው። በዚህ ሕዝባችን ላይ ምንም ዓይነት ክፉ ነገር እንዲደርስ አንፈልግም። ይሄንን የሚያደርጉትንም አንታገሥም ሲል ጽህፈት ቤቱ ገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
የጠቅላይ ሚንስቴር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው ሕወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መለየት የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር እና ሕገ ወጥ ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት በድጋሜ ያረጋግጣል:: ነገር ግን ይህ ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ በብሔር ወይም በሌላ ወገንተኝነት ላይ የተቃኘ ነው የሚለውን የተሳሳተ እሳቤ አጥብቆ ያወግዛል፡፡
በአሁኑ ወቅት በትግራይ የሚካሄደው ሕግ የማስከበር ሥራ በዋነኝነት ኢትዮጵያን በማተራመስ ላይ በተሠማሩ ሥርዓት አልበኞች፣ በተንኮልና በሤራ በተሞሉ የሕወሐት ቡድን አባላት ላይ ያነጣጠረ ስለመሆኑ ማንም ሰው ጥርጣሬ ሊገባው አይገባም፡፡
በትግራይ ክልል ሕዝብ ላይ ሳይቀር የከፋ በደል የሚፈጽመውን ይህን የሕወሐት ጁንታየወንጀል ሰንሰለት ለማስቆም የፌዴራሉ መንግሥት ቆርጦ ተነሥቷል፡፡በዚህ ሕግ የማስከበር ዘመቻ የትግራይ ሕዝብ የመጀመሪያው ተጠቃሚ ይሆናል፡፡ለኢትዮጵያ ያለን ራእይ በብዝኃነት የሚኮሩ ብሔር ብሔረሰቦች በአንድነት የሚኖሩባት የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት ነው፡፡ የትግራይ ሕዝብ ሕዝባችን ነው። በዚህ ሕዝባችን ላይ ምንም ዓይነት ክፉ ነገር እንዲደርስ አንፈልግም። ይሄንን የሚያደርጉትንም አንታገሥም ሲል ጽህፈት ቤቱ ገልጿል።
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ቀደም ሲል የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በግል ለመውሰድ በሚቀርባችሁ ትምህርት ቤቶች ተመዝግባችሁ የነበራችሁ ተፈታኞች ቀደም ሲል ተመዝግባችሁበት የነበረዉ ትምህርት ቤት የሚገኝበት ክፍለ ከተማ በመሄድ በአስቸካይ እንድትመዘገቡ እያሳሰበ ለምዝገባ በምትሄዱበት ጊዜ ከዚህ በፊት ስትመዘገቡ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ በመያዝ እና አዲስ መመዝገብ የምትፈልጉ ተፈታኞች ደግሞ 260 ብር በመክፈል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡
[የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ]
@YeneTube @FikerAssefa
[የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ የሚገኙ የአልኮል ፋብሪካዎች ባጋጠማቸው የሞላሰስ እጥረት ምክንያት ሥራቸውን ለመቀጠል እንቅፋት ስለሆነባቸው ምርት ለማቆም መገደዳቸውን አስታወቁ።ልዩ አዲስ የአልኮል መጠጦች ኢንዱስትሪ እና መስከረም አልኮል እና ለስላሳ መጠጥ ፋብሪካ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ እንዲሁም ብሔራዊ የአልኮል እና የአረቄ ፋብሪካ ደግሞ በግማሽ በአልኮል እና በሞላሰስ እጥረት ምክንያት ምርት ለማቆም እየተገደዱ እንደሆነ አስታውቀዋል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የልዩ ዕድል ሎተሪ በወቅታዊ የአገሪቱ ሁኔታ ምክንያት የመውጫ ቀኑ ህዳር 30/2013 ድረስ ተራዘመ፡፡
በርካቶች በጉጉት የሚጠብቁትና በ1ኛ ዕጣ 20 ሚሊዮን ብር፣ በ2ኛ ዕጣ 10 ሚሊዮን ብር፣ በ3ኛ ዕጣ 5 ሚሊዮን ብር፣ በ4ኛ ዕጣ 3 ሚሊዮን ብር እና ሌሎችም በርካታ አጓጊ ሽልማቶችን ይዞ ገበያ ላይ የቆየው ልዩ ዕድል ሎተሪ የመውጫ ቀኑ ህዳር 10/2013 ዓ.ም ቢሆንም አገሪቱ በአጋጣማት ወቅታዊ ችግር የመውጫ ቀኑ ህዳር 30/2013 ዓ.ም ድረስ ተራዝሟል፡፡
[የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር]
@YeneTube @FikerAssefa
በርካቶች በጉጉት የሚጠብቁትና በ1ኛ ዕጣ 20 ሚሊዮን ብር፣ በ2ኛ ዕጣ 10 ሚሊዮን ብር፣ በ3ኛ ዕጣ 5 ሚሊዮን ብር፣ በ4ኛ ዕጣ 3 ሚሊዮን ብር እና ሌሎችም በርካታ አጓጊ ሽልማቶችን ይዞ ገበያ ላይ የቆየው ልዩ ዕድል ሎተሪ የመውጫ ቀኑ ህዳር 10/2013 ዓ.ም ቢሆንም አገሪቱ በአጋጣማት ወቅታዊ ችግር የመውጫ ቀኑ ህዳር 30/2013 ዓ.ም ድረስ ተራዝሟል፡፡
[የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን የመከላከያ ሰራዊት በማንኛውም አካል ጥቃት ሊደርስበት አይገባም አለ!
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ፅህፈት ቤት በኢትዮጵያ በወቅቱ በተከሰተው ግጭትና በንፁሀን ዜጎች ላይ እየተከሰተ ባለው ዘርን ያማከለ ጥቃት ዙርያ ጋዜጣዊ መግለጫ ያወጣ ሲሆን ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ ላይ በጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም የተከፈተውን ጥቃት እንዲሁም በማይካድራና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ህይወታቸውን ዘርን ባማከለ ጥቃት ምክንያት ባጡ ኢትዮጵያውያን የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።
Via @AddisZeybe
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ፅህፈት ቤት በኢትዮጵያ በወቅቱ በተከሰተው ግጭትና በንፁሀን ዜጎች ላይ እየተከሰተ ባለው ዘርን ያማከለ ጥቃት ዙርያ ጋዜጣዊ መግለጫ ያወጣ ሲሆን ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ ላይ በጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም የተከፈተውን ጥቃት እንዲሁም በማይካድራና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ህይወታቸውን ዘርን ባማከለ ጥቃት ምክንያት ባጡ ኢትዮጵያውያን የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።
Via @AddisZeybe
@YeneTube @FikerAssefa
የገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን በመጀመሪያ ሩብ አመት የ4 ወር አፈፃፀም 107 ቢሊየን ብር ከሀገር ውስጥ ታክስ፣ ከውጭ ንግድ ቀረጥና ታክስ እና ከሎተሪ ሽያጭ ሰበሰበ።በአጠቃላይ አፈፃፀሙ ከእቅዱ 103 በመቶ ሲሆን ከባለፈው እመት ተመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 19 በመቶ ወይም 17 ቢሊየን ብር ብልጫ አሳይቷል።
[ካፒታል]
@YeneTube @FikerAssefa
[ካፒታል]
@YeneTube @FikerAssefa
በደቡብ ክልል ሰገን ህዝቦች ዞን በአሌ እና በኮንሶ በተነሳው ግጭት ብዙዎች መሞታቸውንና በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸው ተገለጸ።
ካለፈው አርብ እለት ጀምሮ በደቡብ ክልል በአሊ አካባቢ የተቀሰቀሰው ግጭት ለቀናት መዝለቁ ነው የተሰማው፡፡ኢትዮ ኤፍ ኤም ከአካባቢው ነዋረዎች ሰማው እንዳለው አብዛኛው ነዋሪዎችና የመንግስት ሰራተኛ በሳውላ በኩል መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው መሰደዳቸውን ተሰምቷል፡፡ከዚህ ጥቃት በተአምር ነው የተረፍኩት ያለችን አንድ የአካባቢው ነዋሪ “እንዲህ አይነት ችግሮች በአካባቢው ላይ ከወረዳና ከዞን ጥያቄ ጋር በተገናኘ የተለመደ እየሆነ ቢመጣም አሁን ግን ጥቃትና ግድያውን ፈጸመዋል የሚባሉት የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ናቸው” ስትል ግምቷን ተናግራለች፡፡
በአርባ ምንጭ ባለው የነጭ ሳር ፖርክ አቅራቢያ ባለው የአባያ ሀይቅ አካባቢ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ምሽግ እንዳላቸው እና ከዚህ ፓርክ እየወጡ እያጠቋቸው እንደሆኑ ተፈናቃዮቹ ተናግረዋል፡፡ከቅርብ ቀናት በፊትም መንግስት ባደረገው መጠነ ሰፊ ዘመቻ የጦር መሳሪዎች መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡እኛም ቢሆን በአካባቢያችን ላይ የምናያቸውን ፀጉረ ልውጥ ሰዎችን ለአካባቢው ፖሊስ ጠቁመናል ነው ያሉት፡፡ይሁን አንጂ አሁን ላይ ጥቃቱን በሚያደርሱት ታጣቂዎች ላይ የጸጥታ ሀይሉ እርምጃ እየወሰደ አለመሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ምላሽ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው አንድ የደቡብ ክልል መንግስት ስማቸውና ድምጻቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው በተጠቀሱት አካባቢዎች ጥቃት መፈጸሙን ተናግረዋል።በዚህ ጥቃት ምክንያትም ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ዜጎች በዚህ ጥቃት ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን እና ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን ተናግረዋል።ከትላንት ጅምሮም የደቡብ ክልል መንግስት የጸጥታ ተቋማት አመራሮች ወደ ቦታው አምርተው በቀጣይ ስለሚወሰዱ እርምጃዎች በመምከር ላይ መሆናቸውንም ሃላፊው ገልጸዋል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ካለፈው አርብ እለት ጀምሮ በደቡብ ክልል በአሊ አካባቢ የተቀሰቀሰው ግጭት ለቀናት መዝለቁ ነው የተሰማው፡፡ኢትዮ ኤፍ ኤም ከአካባቢው ነዋረዎች ሰማው እንዳለው አብዛኛው ነዋሪዎችና የመንግስት ሰራተኛ በሳውላ በኩል መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው መሰደዳቸውን ተሰምቷል፡፡ከዚህ ጥቃት በተአምር ነው የተረፍኩት ያለችን አንድ የአካባቢው ነዋሪ “እንዲህ አይነት ችግሮች በአካባቢው ላይ ከወረዳና ከዞን ጥያቄ ጋር በተገናኘ የተለመደ እየሆነ ቢመጣም አሁን ግን ጥቃትና ግድያውን ፈጸመዋል የሚባሉት የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ናቸው” ስትል ግምቷን ተናግራለች፡፡
በአርባ ምንጭ ባለው የነጭ ሳር ፖርክ አቅራቢያ ባለው የአባያ ሀይቅ አካባቢ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ምሽግ እንዳላቸው እና ከዚህ ፓርክ እየወጡ እያጠቋቸው እንደሆኑ ተፈናቃዮቹ ተናግረዋል፡፡ከቅርብ ቀናት በፊትም መንግስት ባደረገው መጠነ ሰፊ ዘመቻ የጦር መሳሪዎች መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡እኛም ቢሆን በአካባቢያችን ላይ የምናያቸውን ፀጉረ ልውጥ ሰዎችን ለአካባቢው ፖሊስ ጠቁመናል ነው ያሉት፡፡ይሁን አንጂ አሁን ላይ ጥቃቱን በሚያደርሱት ታጣቂዎች ላይ የጸጥታ ሀይሉ እርምጃ እየወሰደ አለመሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ምላሽ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው አንድ የደቡብ ክልል መንግስት ስማቸውና ድምጻቸው እንዳይገለጽ ጠይቀው በተጠቀሱት አካባቢዎች ጥቃት መፈጸሙን ተናግረዋል።በዚህ ጥቃት ምክንያትም ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ዜጎች በዚህ ጥቃት ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን እና ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን ተናግረዋል።ከትላንት ጅምሮም የደቡብ ክልል መንግስት የጸጥታ ተቋማት አመራሮች ወደ ቦታው አምርተው በቀጣይ ስለሚወሰዱ እርምጃዎች በመምከር ላይ መሆናቸውንም ሃላፊው ገልጸዋል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
የጦር ሀይሎች ጠ/አዛዥ ጀነራል ብርሀኑ ጁላ ፣ ከደቂቃዎች በሁዋላ በውቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ይሰጣሉ። @YeneTube @FikerAssefa
የጦር ሀይሎች ጠ/ኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሀኑ ጁላ ፣ ሠራዊቱ በሁሉም ግንባሮች ድልን እየተጎናፀፈ እንደሚገኝ ተናገሩ።
'ጁንታው' እያንዳንዳቸው 2ሺ 500 የሰው ሀይል የያዙ 11 ብርጌድ ልዩ ሀይል፣ 14 ብርጌድ የዞን ታጣቂ እና አንድ ብርጌድ ሚሊሻ ቢገነባም ፣ አሁን ነፍስ አውጭኝ ላይ ይገኛል ብለዋል ።ጀግናው ሠራዊታችን በምዕራብ ትግራይ ከዳንሻ - ባዕከር ፣ አዲጎሹ ፣ አዲ ሀገራይ ፣ አዲጉዞምን ሰብሮ ትናንት ሽሬን መቆጣጠሩን አረጋግጠዋል።በደቡቡ ግንባርም ከዋጃ ጀምሮ አላማጣ ፣ ኮረምን ይዞ ወደፊት ቀጥሏል።በምስራቁ ግንባር ፣ ጨርጨር ፣ መሆኔ ፣ ራያ ቆቦና ሌሎች ቦታዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል። 'ጁንታውን' ለህግ ለማቅረብም ግስጋሴውን ቀጥሏል ።
ነጻ በወጣው አካባቢ የሚገኘው ህብረተሰብ ለሠራዊታችን ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ጀነራል ብርሀኑ አስታውሰው ፣ ህዝቡ ሠራዊታችንን ከሁዋላው እንዲመታ ቢያስታጥቁትም ፣ ምንም ሳይተኩሱ 200 መትረየስና ክላሽ አዲኮኮብ እና ሽሬ ላይ ለሠራዊታችን እስረክቧል ብለዋል።'ጁንታው' ኮማንድ ፖስቱን እና ትኳሾቹን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቢያደርግም ሠራዊታችን ነጥሎ ለመምታት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል ብለዋል ።በአሁኑ ሰዓት 'ጁንታው' ኢትዮጵያን ወደ ጦርነት ለማስገባትና ለመበታተን ያቀደው እንደከሸፈበትና በመከበቡ ነፍስ አውጭኝ ላይ ይገኛልም ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
'ጁንታው' እያንዳንዳቸው 2ሺ 500 የሰው ሀይል የያዙ 11 ብርጌድ ልዩ ሀይል፣ 14 ብርጌድ የዞን ታጣቂ እና አንድ ብርጌድ ሚሊሻ ቢገነባም ፣ አሁን ነፍስ አውጭኝ ላይ ይገኛል ብለዋል ።ጀግናው ሠራዊታችን በምዕራብ ትግራይ ከዳንሻ - ባዕከር ፣ አዲጎሹ ፣ አዲ ሀገራይ ፣ አዲጉዞምን ሰብሮ ትናንት ሽሬን መቆጣጠሩን አረጋግጠዋል።በደቡቡ ግንባርም ከዋጃ ጀምሮ አላማጣ ፣ ኮረምን ይዞ ወደፊት ቀጥሏል።በምስራቁ ግንባር ፣ ጨርጨር ፣ መሆኔ ፣ ራያ ቆቦና ሌሎች ቦታዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል። 'ጁንታውን' ለህግ ለማቅረብም ግስጋሴውን ቀጥሏል ።
ነጻ በወጣው አካባቢ የሚገኘው ህብረተሰብ ለሠራዊታችን ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ጀነራል ብርሀኑ አስታውሰው ፣ ህዝቡ ሠራዊታችንን ከሁዋላው እንዲመታ ቢያስታጥቁትም ፣ ምንም ሳይተኩሱ 200 መትረየስና ክላሽ አዲኮኮብ እና ሽሬ ላይ ለሠራዊታችን እስረክቧል ብለዋል።'ጁንታው' ኮማንድ ፖስቱን እና ትኳሾቹን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቢያደርግም ሠራዊታችን ነጥሎ ለመምታት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል ብለዋል ።በአሁኑ ሰዓት 'ጁንታው' ኢትዮጵያን ወደ ጦርነት ለማስገባትና ለመበታተን ያቀደው እንደከሸፈበትና በመከበቡ ነፍስ አውጭኝ ላይ ይገኛልም ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
በምዕራብ ወለጋ ዞን በ142 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ፡፡
በምዕራብ ወለጋ ዞን በቅርቡ በተደረገው ኦፕሬሽን በ142 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ እንደተወሰዳባቸው፣48 ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉና፣ 64 ደግሞ በህብረተሰቡ ውስጥ ከተበታተኑ በኋላ መያዛቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ አስታውቀዋል፡፡
ለኦነግ ሸኔ አባላት የሎጂስቲክስና ስልጠና ሲሰጡ የነበሩ 1 ሽህ 341 ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለዋል ተብሏል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 104 የጽንፈኛው የህወሃት ቡድን አባላት መሆናቸው ተገልጿል፡፡በምዕራብና በደቡብ ኦሮሚያ አካባቢዎች አንፃራዊ ሰላም እንደሰፈነ ኮሚሽነሩ መግለፃቸውን ኢብኮ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
በምዕራብ ወለጋ ዞን በቅርቡ በተደረገው ኦፕሬሽን በ142 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ እንደተወሰዳባቸው፣48 ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉና፣ 64 ደግሞ በህብረተሰቡ ውስጥ ከተበታተኑ በኋላ መያዛቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ አስታውቀዋል፡፡
ለኦነግ ሸኔ አባላት የሎጂስቲክስና ስልጠና ሲሰጡ የነበሩ 1 ሽህ 341 ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለዋል ተብሏል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 104 የጽንፈኛው የህወሃት ቡድን አባላት መሆናቸው ተገልጿል፡፡በምዕራብና በደቡብ ኦሮሚያ አካባቢዎች አንፃራዊ ሰላም እንደሰፈነ ኮሚሽነሩ መግለፃቸውን ኢብኮ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ ደመቀ መኮንን ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ!
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሺሰኬዲ ጋር ተወያዩ።ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከፕሬዚዳንቱ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ምንጭ: ኢቢሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሺሰኬዲ ጋር ተወያዩ።ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከፕሬዚዳንቱ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ምንጭ: ኢቢሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ የኤርትራ ከፍተኛ ሹማምንት ግብፅ እንደነበሩ ተሰምቷል፡፡
የኤርትራ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ እና የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አማካሪ የማነ ገብረአብ ናቸው ዛሬ ካይሮ የታዩት፡፡በሁለቱ ሹማምንት የተመራው ልዑክ ከግብፅ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሽኩሪ ጋር መወያየቱን የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገፃቸው ላይ ፅፏል፡፡የኤርትራዊያን ባለስልጣናት የካይሮ ጉዞ ሁለቱ አገራት በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጉት መደበኛ ምክክር አካል ነው ያሉት አቶ የማነ ገብረመስቀል፣ ባለሥልጣናቱ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ድርድር እና በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይም ሐሳብ መለዋወጣቸውን ጽፈዋል፡፡
[Sheger FM]
@YeneTube @FikerAssefa
የኤርትራ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ እና የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አማካሪ የማነ ገብረአብ ናቸው ዛሬ ካይሮ የታዩት፡፡በሁለቱ ሹማምንት የተመራው ልዑክ ከግብፅ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሽኩሪ ጋር መወያየቱን የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገፃቸው ላይ ፅፏል፡፡የኤርትራዊያን ባለስልጣናት የካይሮ ጉዞ ሁለቱ አገራት በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጉት መደበኛ ምክክር አካል ነው ያሉት አቶ የማነ ገብረመስቀል፣ ባለሥልጣናቱ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ድርድር እና በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይም ሐሳብ መለዋወጣቸውን ጽፈዋል፡፡
[Sheger FM]
@YeneTube @FikerAssefa
የአገር ክህደት ወንጀል በፈጸሙ 76 ጄነራል መኮንኖች፣ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች እና የበታች ሹማምንቶች ላይ የመያዣ ትዕዛዝ ወጣ፡፡
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa