YeneTube
116K subscribers
31.6K photos
485 videos
79 files
3.91K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት በሃገራችን ወቅታዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ውይይት በማድረግ ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ።

ምክር ቤቱ በሃገራችን የተቃጡ፣ የከሸፉ እና ጉዳት ያደረሱ የብሔራዊ ደህንነት ስጋቶችን በዝርዝር ዳስሷል።በአሁኑ ወቅት ያሉ ወቅታዊ የደህንነት ጉዳዮች ላይም በዝርዝር የተመለከተ ሲሆን በቀጣይ ስጋቶቹን በተቀናጀ መልኩ መግታት የሚቻልበት አግባብ ላይ ተወያይቷል።በዚህም የሃገርን ሉዓላዊነት፣ የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅና የህግ የበላይነትን ለማስከበር መንግስት ቁርጠኝነት እንደሚሰራ በመግለፅ ይህን እውን ለማድረግም መከላከያን ጨምሮ ሁሉም የደህንነትና ጸጥታ ተቋማት እስካሁን እያደረጉት ያለውን ጥረትና መስዋዕትነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ምክር ቤቱ አረጋግጧል።

#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
በባሕር ዳር ከተማ ትናንት ማታ በረዶ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ በንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ፡፡

በባሕር ዳር ከተማ ትናንት ጳጉሜን 3/2012 ዓ.ም ማታ የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ በንብረታቸው ላይ ጉዳት ማድረሱን አብመድ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች አስተያዬት ሰጥተዋል፡፡አደጋው በተለይም በጣና ክፍለ ከተማ ባታ ቀበሌ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ነው ነዋሪዎች የተናገሩት፡፡በረዶ እና አውሎ ንፋስ ቀላቅሎ ለ1፡00 ያክል የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ የነዋሪዎቹን ቤቶች አጥለቅልቋል፤ የቤት ቁሳቁስ ላይም ጉዳት ማድረሱ ተመልክቷል፡፡የጉዳቱን መጠንና በቀጣይ መሠራት ያለባቸውን ጉዳዮች በተመለከተ ከከተማ አስተዳደሩ መረጃ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡

[AMMA]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለቤቶች ግንባታ ተበድሮ ያልመለሰው ዕዳ 50 ቢሊዮን ብር መድረሱ ታወቀ!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላለፉት 15 ዓመታት ለገነባቸው የኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ ከባንክ ተበድሮ ያልመለሰው ዕዳ 50 ቢሊዮን ብር መድረሱ ታወቀ።ሪፖርተር ከከተማው አስተዳደር ምንጮቹ ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ ከተጀመረበት 1997 ዓ.ም. አንስቶ እስከ ዘንድሮ ድረስ የተገነቡ ቤቶች የፋይናንስ ምንጭ የባንክ ብድር ነው። በዚህ መሠረት አስተዳደሩ የተለያዩ የብድር ሥልቶችን ተጠቅሞ ለኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባው ከወሰደው ብድር ውስጥ 50 ቢሊዮን ብር የተወዘፈ ዕዳ እንዳለበት ለማወቅ ተችሏል።

አስተዳደሩ ከተጠቀማቸው የብድር ሥልቶች መካከል የረዥም ጊዜ ቀጥታ ብድርና የመንግሥት የዕዳ ሰነድን በዋስትና በማስያዝ የተገኙ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።አስተዳደሩ ካለበት ብድር ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚይዘው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተገኘ መሆኑንም ምንጮች ገልጸዋል። አስተዳደሩ ያለበት የዕዳ መጠን ከፍተኛ በመሆኑም፣ ለአዲስ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ የሚሆን ብድር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማግኘት አልቻለም።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ የጀመረው በ1997 ዓ.ም. ሲሆን፣ ከዚህ ወቅት አንስቶ በነበሩት 15 ዓመታት ተገንብተው ለተጠቃሚዎች የተላለፉት አጠቃላይ ቤቶች ብዛት 276 ሺሕ ናቸው።

በአሁኑ ወቅት በግንባታ ላይ የሚገኙ ቤቶች ሲጨመሩ ደግሞ የቤቶቹ ብዛት 300 ሺሕ ይደርሳል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሆነው በቅርቡ የተሾሙት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ባለፈው ሳምንት ከኢቲቪ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ ከተጀመረበት ወቅት አንስቶ ቤቶቹን ለማግኘት የተመዘገቡ ነዋሪዎች ቁጥር አንድ ሚሊዮን እንደሆነ ገልጸዋል።ተመዝጋቢዎቹን ለማጥራት በ2005 ዓ.ም. በተደረገ ዳግም ምዝገባ ቤት ያገኙት ተመዝጋቢዎች ቁጥር ተቀንሶ፣ አሁን የአዲስ ከበባ ነዋሪ መሆኑ ተረጋግጦ በቤት ፈላጊነት መዝገብ ውስጥ የሚገኝ ቤት ፈላጊ ብዛት 650 ሺሕ መሆኑን አስረድተዋል።

ባለፉት 15 ዓመታት ተገንብተው ለተጠቃሚዎች ከተላለፉት 276 ሺሕ ቤቶች ውስጥ፣ 176 ሺሕ የሚሆኑት ለተመዘገቡ ቤት ፈላጊዎች የተላለፉ መሆናቸውንም ገልጸዋል።የተቀሩት ቤቶች በመንግሥት ውሳኔ ለተለያዩ አካላት እንደተላለፉ ምክትል ከንቲባዋ የተናገሩ ሲሆን፣ ይህም ማለት 94 ሺሕ ቤቶች ያለ ዕጣ በመንግሥት ውሳኔ እንደተላለፉ ያስገነዝባል።በመንግሥት ውሳኔ ቤቶቹን እንዲያገኙ የተደረጉት በኃላፊነት ላይ ያሉ የከተማ አስተዳደሩና ሌሎች የመንግሥት ሠራተኞች፣ መምህራን፣ የጤና ባለሙያዎችና የልማት ተነሺዎችና መሬታቸውን የለቀቁ አርሶ አደሮች መሆናቸውን ምክትል ከንቲባዋ ገልጸዋል።

የኮንዶሚኒየም ቤቶችን ለማግኘች የተመዘገቡ ነዋሪዎች ቤቱን ለማግኘት ቀድመው የመቆጠብ ግዴታ ያለባቸው ቢሆንም፣ የቤቶቹ ግንባታ የሚካሄደው በተቆጠበው ገንዘብ እንደሆነ ተደርጎ የሚነገረው የተሳሳተ እንደሆነና ግንባታው በባንክ ብድር ሲካሄድ እንደቆየም ምክትል ከንቲባዋ ገልጸዋል። ነገር ግን ቤቶቹ ከተላለፉ በኋላ የባንክ ዕዳው ቤቶቹ ለተላለፈላቸው ተጠቃሚዎቹ እንደሚዘዋወር ገልጸዋል።በአሁኑ ወቅት በ20/80 እና በ40/60 የቤቶች ፕሮግራም ቤት ለማግኘት ተመዝግበው እየተጠባበቁ የሚገኙ ነዋሪዎች ብዛት 650 ሺሕ መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ውስጥ በትክልል የሚጠበቅባቸውን የባንክ ቁጠባ እየፈጸሙ የሚገኙት 200 ሺሕ ገደማ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።

በ1997 ዓ.ም. ተመዝግበው እስካሁን ቤት ያልደረሳቸው ነዋሪዎች ቁጥር 45 ሺሕ እንደሆነ፣ ከዚህ ውስጥ የቁጠባ ግዴታቸውን የተወጡት 18 ሺሕ እንደሆኑም ገልጸዋል።ለእነዚህም በአሁኑ ወቅት በግንባታ ሒደት ላይ ከሚገኙትና በቅርቡ ዕጣ ከሚወጣባቸው 23 ሺሕ ቤቶች መካከል ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው አስታውቀዋል።የተቀሩት 630 ሺሕ የሚሆኑ ቤት ፈላጊዎች ለማስተናገድ የተለያዩ የግንባታ አማራጮችን በመከተል፣ በተቻለ ፍጥነት ለመመለስ ጥረት እንደሚደረግም አስረድተዋል።ከእነዚህ አማራጮች መካከልም ቅድሚያ የሚሰጠው በሁለቱም የቤቶች ግንባታ ከተመዘገቡት ውስጥ፣ አቅም ያላቸውን ከባንክ ጋር በማገናኘትና ከሊዝ ነፃ መሬት በማቅረብ፣ እንዲሁም ከተቋራጮች ጋር በማቀናጀት በማኅበር ተደራጅተው በራሳቸው እንዲገነቡ ማድረግ ይገኝበታል።

[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ በ2013 በጀት ዓመት በየወሩ 470 ሺህ ሰዎችን የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ለማድረግ መታቀዱን የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ኢንስቲትዩቱ ዛሬ በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው በቀጣዩ ዓመት በየወሩ በአማካኝ 470 ሺህ ሰዎችን የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ለማድረግ እቅድ ተይዟል።እስካሁን በተደረገው የግንዛቤ ፈጠራ ስራ 40 ሚሊዮን ህዝብ ስለ ኮሮና ቫይረስ ምንነት፣መተላለፊያ መንገዶች እና መደረግ ስላለባቸው የጥንቃቄ እርምጃዎች ትምህር መሰጠቱ ተገልጿል።

ቫይረሱ ወደ ኢትዮጵያ ከገባበት ጊዜ አንስቶም 1 ቢሊዮን የሚደርሱ የሕክምና ቁሳቁሶች ለክልሎች መሰራጨታቸውም በመግለጫው ላይ ተገልጿል።

ሕብረተሰቡ፣አምራቾች እና የተለያዩ ተቋማት ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ብር ድጋፍ አድርገው ይሄው ድጋፍ ለሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳድሮች መሰራጨቱ ተጠቁሟል።በተጨማሪም 217 ሚሊዮን የላብራቶሪ ግብዓት እና ከ19 ሚሊዮን በላይ ልዩ ልዩ መድሃኒቶች ለሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳድሮች መሰራጨታቸውን ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።

[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመደበኛነት ወደ ናይጄሪያ መብረር ጀመረ!

በመጥፎ እና በጥሩ ጊዜያት ሁልጊዜ ከደንበኞቻችን ጋር ነን ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወረርሽኙ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ የተራራቁ ቤተሰቦችን ሳገናኝ ነበር ያለ ሲሆን አሁንም በመደበኛነት ወደ ናይጄሪያ የመንገደኞች በረራ ማድረግ መጀመሩን አስታውቋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት ሶስት የክረምት ወራት ብቻ ከ130 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች በጎርፍ አደጋ ምክንያት ከመኖሪያ ቀያቸው የመፈናቀል አደጋ እንደደረሰባቸው የብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።ከሰኔ ወር መጀመሪያ እስከ ነሀሴ ወር አጋማሽ ባለው ወቅት በሁሉም የአገሪቷ አካባቢዎች ከ130 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች በጎርፍ አደጋ ምክንያት መፈናቀላቸውን የብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አልማዝ ደምሴ ገልፀዋል።

[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
ተማሪዎች ከሚደረስባቸው የስነ ልቦና ጉዳት እንዲላቀቁ ትምህርት ለመጀመር የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ምክረ ሃሳብ ቀረበ።

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት ቤት በመዘጋቱ ቤታቸው የዋሉ ተማሪዎች ለተለያዩ ጉዳቶች እየተጋለጡ መሆናቸው ይታወቃል። ተማሪዎች ያለ እድሜ ጋብቻ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ጉልበት ብዝበዛና ይህንን ተከትሎ በሚመጣ የስነ ልቦና ችግር እየተጋለጡ መሆናቸውን ጥናቶች አሳይተዋል።እነዚህን ችግሮች ለማስወገድና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማድረግ የትምህርት ሚኒስቴር ኮሮናን በመከላከል ትምህርት መጀመር የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እያጠና ይገኛል።በተደረጉ የዳሰሳ ጥናቶች ተማሪዎች የትምህርት መጀመርን በጉጉት እየጠበቁ መሆናቸውን ለመረዳት የተቻለ ሲሆን።

በሌላ በኩል ወላጆች የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ እየተስፋፋ ባለበት በአሁኑ ወቅት ልጆቻቸው ትምህርት ቤት ሲሄዱ ለኮሮና ቫይረስ ሊጋለጡ ይችላሉ የሚለው ከፍተኛ ስጋት እንዳለባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡እነዚህን ተቃራኒ ሃሳቦች ከግምት ውስጥ በማስገባት ትምህርት ሚኒስቴር እንደ አካባቢዎቹ ወቅታዊ የኮሮና ስርጭት ሁኔታ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ በደረጃ መክፈት የሚያስችሉ መንገዶችን እየገመገመ ይገኛል።ትምህርት ሚኒስቴር እያካሄደ ባለው ጥናት ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት በአንድ ክፍል ውስጥ ከ 20 እስከ 25 ተማሪዎችን ማስተማር፣ የንፅህና መጠበቂያ ለትምህርት ቤቶች ማቅረብ፣ ተጨማሪ ትምህርት ቤቶችን መገንባት የሚሉ አማራጮች ቀርበዋል።ጥናቱ ሲጠናቀቅ በሚቀርበው ተጨማሪ ምክረ ሃሳብ መሰረት አስፈላጊው ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ትምህርት ለመጀመር ጥረት ይደረጋል።

[MoE]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግስት ሆስፒታሎች የኩላሊት እጥበት ለሚያደርጉ ህሙማን የአንድ ዓመት ወጪ ለመሸፈን ቃል ገባ!

ለ2013 ዓ.ም የሚሆን ስጦታ በሚል በመንግስት ሆስፒታሎች የኩላሊት እጥበት ለሚያደርጉ ህሙማን በሙሉ የአንድ ዓመት ወጪ እንደሚሸፍን የከተማ አስተዳደሩ ቃል ገብቷል፡፡ዛሬ እየተከበረ የሚገኘውን የምስጋና ቀን ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በዘውዲቱ ሆስፒታል የሚገኙ የጤና ባለሙያዎችን ጎብኝተዋል፡፡ምክትል ከንቲባዋ በጉብኝታቸው ወቅት ቃል እንደገቡት በከተማዋ በመንግስት ሆስፒታሎች የሚገኙ የኩላሊት እጥበት የሚያደርጉ ሁሉም ህሙማን የአንድ አመት የህክምና ወጪያቸው በከተማ አስተዳደሩ የሚሸፈን ይሆናል፡፡ ይህም በገንዘብ ሲሰላም ከ 12 ሚሊየን ብር በላይ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡

[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግስት ሆስፒታሎች የኩላሊት እጥበት ለሚያደርጉ ህሙማን የአንድ ዓመት ወጪ ለመሸፈን ቃል ገባ! ለ2013 ዓ.ም የሚሆን ስጦታ በሚል በመንግስት ሆስፒታሎች የኩላሊት እጥበት ለሚያደርጉ ህሙማን በሙሉ የአንድ ዓመት ወጪ እንደሚሸፍን የከተማ አስተዳደሩ ቃል ገብቷል፡፡ዛሬ እየተከበረ የሚገኘውን የምስጋና ቀን ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ…
በአገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን ወደ 312 የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች በኮረና ቫይረስ መያዛቸውን እና አሁን ላይ የተወሰኑት አገግመው 56 የሚሆኑ ክትትል እያደረጉ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡ይህንንም ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በነበራቸው የምስጋና ቀን ጉብኝት ህይወታቸውን መስዋዕት አድርገው እያደረጉ ላለው ሁሉ ከልብ ምስጋና እናዳላቸው ገልጸዋል፡፡ ለበዓል መዋያ 2 በሬዎችን እና 5 በጎችንም በስጦታ አቅርበዋል፡፡በቀጣይ የጤና ባለሞያዎች የሚያነሷቸውን ችግሮች በከተማ አስተዳደሩ ውይይት ተደርጎበት በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ምላሽ ለመስጠት ቃል ገብተዋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዮት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ አድርገው ሾመዋል።

#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
ዶናልድ ትራምፕ ለኖቤል ሽልማት ታጩ!

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እና እስራኤል የሰላም ስምምነት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ለኖቤል የሰላም ሽልማት ታጩ።ትራምፕ የታጩት ለስምምነቱ ስኬት ቁልፍ ሚናን ተጫውተዋል በሚል ባሞካሿቸው የኖርዌይ ምክር ቤት አባል ክሪስቲያን ታይብሪንግ ነው፡፡በሃገራቱ መካከል ሰላምን ለማውረድ ከየትኛውም እጩ በላይ ትራምፕ ሰርቷል ሲሉም ነው ታይብሪንግ ለፎክስ ኒውስ የተናገሩት፡፡በሽልማቱ ህግ መሰረት የምክር ቤት አባል የሆነ የትኛውም ሰው ለዓለም ሰላም መጠበቅ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል ያለውን ሰው እጩ አድርጎ ለማቅረብ ይችላል፡፡“ታሪካዊ” በሚል የሚጠቀሰውን ስምምነት በማርሽ ቀያሪነት የጠቀሱት ታይብሪንግ ሌሎች የመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት ሊከተሉት የሚችሉት እንደሆነም ለሽልማት ተቋሙ በጻፉት የእጩ መጠቆሚያ ደብዳቤ ገልጸዋል፡፡

[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ለጃዋር መሐመድ የሳተላይት መሳሪያ በመግጠም የተከሰሱ ባለሙያ ዋስትና ተፈቀደላቸው!

በአቶ ጃዋር መሐመድ መኖሪያ ቤት ህገ ወጥ የሳተላይት መሳሪያ በመግጠም የተከሰሱት አቶ ሚሻ አደም ዋስትና ተፈቀደላቸው። ተከሳሹ የ20 ሺህ ብር ዋስትና በማስያዝ በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ዛሬ ውሳኔ የሰጠው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው።የአቶ ሚሻን ክስ እየተመለከተ የሚገኘው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 20ኛ ወንጀል ችሎት ለዛሬ ረቡዕ ጳጉሜ 4፤ 2012 ቀጠሮ የሰጠው የተከሳሹ ጠበቆች ባቀረቡት ዋስትና ላይ ውሳኔ ለመስጠት ነበር።

[Ethiopia Insider]
@YeneTube @FikerAssefa
አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለ551 ታራሚዎች ይቅርታ ተደረገላቸው!

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የ2013 ዓ.ም አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ በፌዴራል፣ በክልልና በመከላከያ ወታደራዊ ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ 551 የፌዴራል ታራሚዎች በተለያዩ መስፈርቶች መነሻነት ይቅርታ ማድረጉን አሰታውቋል፡፡መጪውን የ2013 ዓ.ም አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ ከፌዴራል ማራሚያ ቤቶች ለ398፣ ከመከላከያ ወታደራዊ ማረሚያ ቤት ለ129፣ ከኦሮሚያ ክልል ለ18 እና ከአማራ ክልል ለ6 የፌዴራል ታራሚዎች የይቅርታ ቦርድ የቀረበውን ማስረጃ መርምሮ ይቅርታ እንዲደረግ ለኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ባቀረበው የውሳኔ ሀሳብ መሰረት የውሳኔው በመጽደቁ ታራሚዎቹ የይቅርታው ታጠቃሚ መሆናቸውን ከጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
ባንኮች ከሚሰጡት አመታዊ ብድር 5% የሚሆነውን በተንቀሳቃሽ ንብረት ለሚሰጥ የብድር አይነት እንዲውል ብሄራዊ ባንክ በመመሪያ አዘዘ።

በከፍተኛ ለውጥ እያለፈ ያለው ብሄራዊ ባንክ ባለፈው ሁለት አመታት 47 መመሪያዎችን ማውጣቱን አስታወቀ።የብሄራዊ ባንክ ገዥ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ከወጡት መመሪያዎች አብዛኞቹ አዳዲስ ናቸው።የተቀሩት ደግሞ የቀደሙትን ማሻሻያ ነው።

[Capital]
@YeneTube @FikerAssefa
ወደ ዩንቨርስቲ መግቢያ ቀን እንደተቆረጠ የሚሰራጨው ዜና ሀሰት እንደሆነ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር አስታወቀ!

በኮቪድ 19 ወረርሸኝ ምክንያት የገጽ ለገጽ ትምህርት መቋረጡና ለበለጠ ጥንቃቄ ሲባል ተማሪዎች በልዩ ዝግጅት ወደቤተሰቦቻቸው መሸኛታቸው ይታወሳል።ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተቋረጠውን ትምህርት ለማስቀጠል የሚያስችሉ የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችን እያደረገ መሆኑን ቀደም ተብሎ መገለፁ ይታወቃል።ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ዩኒቨርስቲዎች የሚከፈቱበት ቀን እንደተቆረጠ ሆኖ በተለያዩ አካላት የሚወጣው መረጃ የተሳሳተ እንደሆነና የተቋረጠው ትምህርት ሊቀጥል የሚችለው ከሚመለከተው የመንግስት አካል ትምህርት ማስቀጠል የሚያስችል መረጃ ሲገኝ ብቻ እንደሆነ እና መረጃውም የሚሰጠው በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በኩል ብቻ መሆኑን እንድታውቁ ተብላቿል።

[MoSHE]
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሚያ ኒውስ ኔትዎርክ (ኦ.ኤን.ኤን.) ጋዜጠኞችና ሠራተኞች ዛሬ ለፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

እሁድ ከሰዓት የዓዲስ ዓመት የመዝናኛ ፕሮግራም በመሥራት ላይ ሳሉ በአከባቢው ከሚገኙ 26 ሰዎች ጋር ወደ ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደው እንደነበር ጣቢያው ዐሳውቋል፡፡በጋዜጠኛ ደሱ ዱላ መዝገብ ስር ዛሬ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡ 22 ሰዎች ከሸማቂው የኦነግ ሸኔ ኃይል ጋር ትሰራላችሁ በሚል ተጠርጥረው መከሰሳቸውንም ጠበቃቸው አቶ ቱሊ ባይሳ ለዶይቼ ቨሌ ተናግረዋል፡፡ዛሬ በዋለው ችሎት ላይ በአካል መቅረብ ያልቻለው አንደኛው ተጠርጣሪ ሙዚቀኛ ጋሮማ ሁንዴ በህመም ምክኒያት በ10 ሺህ ብር ዋስትና ሲለቀቅ፤ ቀሪዎቹ 21 ሰዎች ለነገ ጠዋት ሌላ ቀጠሮ መሰጠቱንም አቶ ቱሊ አክለው ተናግረዋል፡፡የኦ.ኤን.ኤን ዳይሬክተር አቶ ሶርሳ ደበላ ለዶይቼ ቨሌ እንደተናገሩት አስቀድመው ትናንት አራት ሰዎች መለቀቃቸውን ገልጸው የጋዜጠኞቹ ቡድን ለቀጣይ አዲስ ዓመት ክብረ በዓል የመዝናኛ ፕሮግራም በማሰናዳት ላይ ሳሉ ድንገት ወደ ፖሊስ ጣቢያው መወሰዳቸውን ከጋዜጠኛ ደሱ ዱላ መረዳታቸውን ገልጸዋል፡፡

[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በገበታ ለአገር የእራት ፕሮግራም 3 የ VVIP መግቢያ ለመግዛት መወሰኑን አስታወቀ።በዚህም መሰረት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ ለሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ለእያንዳንዳቸው የ 10 ሚሊየን ብር ለመደገፍ መድን ሰጭው ወስኗል።

[Capital]
@YeneTube @FikerAssefa
በመተከል ዞን ወንበራና ቡለን ወረዳዎች የተከሰተውን የፀጥታ ችግር የማረጋጋት ስራ እየተሰራ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ኮማንደር አምሳሉ ኢረና እንዳሉት ከሰሞኑም በመተከል ዞን ቡለንና ወንበራ ወረዳ በሚገኙ አንዳንድ ቀበሌዎች ላይ "የጥፋት ተልእኮ በተሰጣቸው ኃይሎች" የተከሰተው የፀጥታ ችግር የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች፣ የፌደራል ፖሊስና የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጋር በቦታው ተገኝቶ የህግ የበላይነትን የማስፈንና የማረጋጋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡የፀጥታ ኃይሎች እየሰሩት ባለው ስራ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ምክትል ኮሚሽነሩ በወንበራ ወረዳ መልካን ቀበሌ በጥፋት ኃይሎች 26 ንጹሃን ዜጎች መታገታቸውን አስታውቀዋል፡፡

በተመሳሳይ በቡለን ወረዳ ኤፓር ቀበሌ ላይ የጥፋት ቡድኑ በንፁኃን ዜጎች ላይ ጥቃት ማድረሱን ያስታወቁት ምክትል ኮሚሽነሩ በፀጥታ ችግሩ የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል መሆኑን በአካባቢው የኔት ወርክ ችግር ያለ በመሆኑ ትክክለኛ አሁናዊ መረጃ ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ እንደሌላቸው ጠቁመዋል፡፡የደረሰውን ጉዳት ትክክለኛ መረጃ በማጣራት ኮሚሽኑ በቀጣይ ለህብረተሰቡ የሚያሳውቅ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡የአካባቢውን ሰላምና የህዝቡን ደህንነት ለማስከበር የጸጥታ አካሉ ከሚያደርገው ጥረት ጎን ህብረተሰቡም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣም ምክትል ኮሚሽነር ኮማንደር አምሳሉ ኢረና ጥሪ አቅርበዋል፡፡

[የክልሉ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት]
@YeneTube @FikerAssefa