Forwarded from Teklu Tilahun - ተክሉ ጥላሁን
#መከረኞች
#እምዩ
ዘመን የማይሽራቸው መጽሐፍት በገበያ ላይ!!
#መከረኞች በአንድ ፊቱ የህብረተሰብ ታሪክ፣ በሌላ ፊቱ ፍልስፍና፣ በሶስተኛ መልኩ የጥበብ ስራ፣ ከዚህም ውጪ በብዙ አንጻር ሊተረጎም የሚችል ‹‹ዘላለማዊ›› ተብለው ከሚጠሩ ስነ-ፅሁፎች የሚመደብ፡፡
#እምዩ #የእናት_ፍቅርና_መስዋዕትነት ከባድ ፈተና ውስጥ የሚገባበት… እጅግ መሳጭ ታሪክ የያዘ ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር መጽሐፍ!!!
#የመጽሐፍ_ቅርስ_ካስፈለገዎት
#መከረኞችና_እምዩ_መጽሐፍት_አሉልዎት፡፡
በየመፅሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኟቸዋል፡፡
ይቀላቀሉን 👉 http://tttttt.me/teklutilahun
#እምዩ
ዘመን የማይሽራቸው መጽሐፍት በገበያ ላይ!!
#መከረኞች በአንድ ፊቱ የህብረተሰብ ታሪክ፣ በሌላ ፊቱ ፍልስፍና፣ በሶስተኛ መልኩ የጥበብ ስራ፣ ከዚህም ውጪ በብዙ አንጻር ሊተረጎም የሚችል ‹‹ዘላለማዊ›› ተብለው ከሚጠሩ ስነ-ፅሁፎች የሚመደብ፡፡
#እምዩ #የእናት_ፍቅርና_መስዋዕትነት ከባድ ፈተና ውስጥ የሚገባበት… እጅግ መሳጭ ታሪክ የያዘ ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር መጽሐፍ!!!
#የመጽሐፍ_ቅርስ_ካስፈለገዎት
#መከረኞችና_እምዩ_መጽሐፍት_አሉልዎት፡፡
በየመፅሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኟቸዋል፡፡
ይቀላቀሉን 👉 http://tttttt.me/teklutilahun
Forwarded from YeneTube
N A T C O M P U T E R S ®
ናት ኮ ም ፒ ው ተ ር ስ ®
HP Envy X-360 (convertable touch screen)
Intel®core i7 8TH GENERATION
🟢Storage : 1Tb
🟨ram : 16GB DDR4
🟥 status: New
⚫battery: 5hrs
🔘Inch : 15.6" FULL HD Slim CONVERTABLE TOUCH SCREEN
💵 price: 37500 ብር
አድራሻ : - ቦሌ መድሐኒያለም Morningstar Mall 1ኛ ፎቅ ከAngla Burger ፊት ለ ፊት
🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥
N AT C O M P U T E R S ®
ናት ኮ ም ፒ ው ተ ር ስ ®
ይደውሉ
☎️+251911522626 /+251953120011
📌join @natcomputers1
📩 @natyendex ለአጭር መልክት
ናት ኮ ም ፒ ው ተ ር ስ ®
HP Envy X-360 (convertable touch screen)
Intel®core i7 8TH GENERATION
🟢Storage : 1Tb
🟨ram : 16GB DDR4
🟥 status: New
⚫battery: 5hrs
🔘Inch : 15.6" FULL HD Slim CONVERTABLE TOUCH SCREEN
💵 price: 37500 ብር
አድራሻ : - ቦሌ መድሐኒያለም Morningstar Mall 1ኛ ፎቅ ከAngla Burger ፊት ለ ፊት
🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥
N AT C O M P U T E R S ®
ናት ኮ ም ፒ ው ተ ር ስ ®
ይደውሉ
☎️+251911522626 /+251953120011
📌join @natcomputers1
📩 @natyendex ለአጭር መልክት
YeneTube
ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋርን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ እስከ መስከረም 8 2013 ዓ.ም ክስ እንዲመሰርት ብይን ሰጠ! የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቶ ጃዋር መሃመድና በቀለ ገርባን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ እስከ መስከረም 8 2013 ዓ.ም ክስ እንዲመሰርት ብይን ሰጠ።ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋር መሃመድና…
በትናንትናው ችሎት ላይ አቶ ጃዋር ምስጋና ማቅረብ እንደሚፈልጉና ለመንግሥትም መልዕክት እንዳላቸው የተናገሩ ሲሆን፣ ለዳኞችና ለፖሊስ ምስጋና አቅርበዋል።
የመናገር መብታቸው እንደተጠበቀላቸውና ፖሊሶችም ጥሩ እንክብካቤ እያደረጉላቸው እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል።"ይኹን እንጂ ይህ እንክብካቤ ለታዋቂ ሰዎች ብቻ ሳይሆን፤ ለሁሉም ሰዎች መሆን እንዳለበት በማንሳት በሌሎች ስፍራዎች ደንብ ልብስ የለበሱት ፖሊሶች "ሰዎችን እየገደሉ ነው" በማለት ተናግረዋል።አክለውም " እኛ የፖለቲካ ታሳሪዎች ነን፤ ገድለን፣ ሰርቀን ወይንም ዘርፈን አይደለም እዚህ የተገኘነው፤ የታሰርነው ለኦሮሞ ሕዝብ ስለታገልን ነው" ያሉት አቶ ጃዋር፣ የፍትህ አካላትም፣ ፍትህ ከፖለቲካ ሥልጣንና ከፖለቲካ ድርጅት በላይ እንዲሆን እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል አቶ በቀለ ገርባ "በእስካሁኑ ቆይታ ለፍርድ ቤቱ፣ ለአቃቢያነ ሕግ እና ለፖሊሶች ክብር አለን" ብለዋል።"የፖለቲካ ሰዎች ተመርጠው የዋስ መብት የማያሰጥ አንቀጽ እየተፈለገባቸው እየተከሰሱ ነው" ያሉት አቶ በቀለ መንግሥት ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር መወያየት እንዳለበት ተናግረዋል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የመናገር መብታቸው እንደተጠበቀላቸውና ፖሊሶችም ጥሩ እንክብካቤ እያደረጉላቸው እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል።"ይኹን እንጂ ይህ እንክብካቤ ለታዋቂ ሰዎች ብቻ ሳይሆን፤ ለሁሉም ሰዎች መሆን እንዳለበት በማንሳት በሌሎች ስፍራዎች ደንብ ልብስ የለበሱት ፖሊሶች "ሰዎችን እየገደሉ ነው" በማለት ተናግረዋል።አክለውም " እኛ የፖለቲካ ታሳሪዎች ነን፤ ገድለን፣ ሰርቀን ወይንም ዘርፈን አይደለም እዚህ የተገኘነው፤ የታሰርነው ለኦሮሞ ሕዝብ ስለታገልን ነው" ያሉት አቶ ጃዋር፣ የፍትህ አካላትም፣ ፍትህ ከፖለቲካ ሥልጣንና ከፖለቲካ ድርጅት በላይ እንዲሆን እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል አቶ በቀለ ገርባ "በእስካሁኑ ቆይታ ለፍርድ ቤቱ፣ ለአቃቢያነ ሕግ እና ለፖሊሶች ክብር አለን" ብለዋል።"የፖለቲካ ሰዎች ተመርጠው የዋስ መብት የማያሰጥ አንቀጽ እየተፈለገባቸው እየተከሰሱ ነው" ያሉት አቶ በቀለ መንግሥት ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር መወያየት እንዳለበት ተናግረዋል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በክፍል ውስጥ የተማሪዎችን ቁጥር በመመጠንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ትምህርት ለማስጀመር ጥናት ተደርጓል - አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ
ለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ሊያጋልጥ በማይችልና ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ የመማር ማስተማር ሂደቱን በአዲሱ ዓመት ለማስጀመር ጥናት መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እንዳለው በአንድ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎችን ቁጥር በመመጠንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ትምህርት ማስጀመር በሚቻልበት መንገድ ላይ ጥናት ተደርጓል።የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ የ2013 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ መጀመሩን አመልክተዋል።
ኮሮናቫይረስ በፖለቲካ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፍ በሳደረው ጫና ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጭ እንዲሆኑ መደረጉንም አስታውሰዋል።
አቶ ሚሊዮን እንዳሉት ትምህርት መቋረጡ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመግታት አስተዋፅኦ ቢኖረውም በተማሪዎች በተለይም ከህጻናት እድገት አንጻር ከፍተኛ ጫና አሳድሯል።በተለይ ህጻናት ትምህርት ዝግ ሆኖ ቤት በመዋላቸው ለአስገድዶ መደፈርና ያለዕድሜ ጋብቻ መዳረጋቸውን ሚኒስቴር ዴኤታው ገልጸዋል።በኢትዮጵያ ባሉ ከ42 ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ከ700 ሺህ በላይ መምህራንና ከ26 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ይገኛሉ።
“ወቅቱ ኮሮናቫይረስ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ያለበት በመሆኑ ትምህርት ቤቶች መከፈታቸው ህብረተሰቡን እያነጋገረ ነው” ያሉት አቶ ሚሊዮን፣ ወረርሽኙ የሚቆምበት ጊዜ ባለመታወቁ ትምህርት እንደሚጀመርና ይህም የጤና ጥበቃ የሚያስቀምጠውን መስፈርት ተግባራዊ በማድረግ እንደሚከናወን ገልጸዋል።ባለፈው የመማር ማስተማር ሂደት በአማካይ ከ60 እስከ 80 ተማሪዎች በአንድ ክፍል ውስጥ ይማሩ የነበረበት ሁኔታ እንደነበር አቶ ሚሊዮን አስታውሰዋል።
በቀጣይ ትምህርት ሲከፈት በቅድመ መደበኛ 14 በመቶ የሚሆኑትን ትምህርት ቤቶች ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ብቻ በአንድ ክፍል እንዲያስተምሩና አንድ ተማሪ በአንድ ዴስክ ብቻ እንዲቀመጥ ለማድረግ መታቀዱን አስረድተዋል።አቶ ሚሊዮን እንዳሉት ቀሪዎቹ 80 በመቶ ተማሪዎች በፈረቃ እንዲማሩና 6 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርት ቤት በመገንባትና አማራጭ ማህበራዊ ተቋማትን በመጠቀም ለማስተማር ታቅዷል።
በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 24 በመቶ ወይም ከ20 እስከ 25 ተማሪዎች በአንድ ከፍል ውስጥ እንዲማሩ፣ 56 በመቶ በፈረቃ እንዲሁም 20 በመቶ ተጨማሪ ክፍል በመገንባት እንዲማሩ ተወስኗል።በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 19 በመቶ ተማሪዎች ወይም ከ20 እስከ 25 የሚሆኑት በአንድ ክፍል ውስጥ እንዲማሩ እንዲሁም 50 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ በፈረቃ የሚማሩ ይሆናል።
ሌሎች 31 በመቶ ተጨማሪ ክፍሎችን በመገንባትና አማራጭ ማህበራዊ ተቋማትን በመጠቀም ለማስተማር መታቀዱንም አመልክተዋል።በሽታን በመከላከል የትምህርት ተቋማትን ስራ ለማስጀመር ተቋማቱን ማስፋት እንደሚገባም አቶ ሚሊዮን ተናግረዋል።
ኦሮሚያ ክልል ሃብት በማሰባሰብ 30 ሺህ አዳዲስ ክፍሎችን መገንባቱን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ “አማራ ክልልም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ያለውን የክፍል እጥረት ችግር ለመቅረፍ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው” ብለዋል።
ተማሪዎች በተረጋጋ ሁኔታ እንዲማሩ የቀደመው የመማር ማስተማር ስልት በአዲስ መልክ እንደሚሆን ጠቁመው፣ ይህም የቡድን ስራን ጨምሮ የተማሪዎችን አካላዊ ንክኪን ሊያስቀር በሚችል መልኩ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።አቶ ሚሊዮን እንዳሉት የትምህርት ቤቶች አከፋፈት ጥናቱን መሰረት ያደረገ ይሆናል።ትምህርት ቤቶች በተመሳሳይ ወቀት አንድ ላይ ሊከፈቱ እንደማይችሉና ደረጃ በደረጃ የመክፈት ሂደት እንደሚኖር ገልጸው፣ አጀማመሩ ከክልል ክልልና ከዞን ዞን ሊለያይ እንደሚችል አመልክተዋል።
ይህንን ተከትሎ አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ጭማሪ እየጠየቁ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን በሚያደርጉ ተቋማት ላይ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶችን እስከመዝጋት የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስድ አመልክተዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ሊያጋልጥ በማይችልና ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ የመማር ማስተማር ሂደቱን በአዲሱ ዓመት ለማስጀመር ጥናት መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እንዳለው በአንድ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎችን ቁጥር በመመጠንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ትምህርት ማስጀመር በሚቻልበት መንገድ ላይ ጥናት ተደርጓል።የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ የ2013 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ መጀመሩን አመልክተዋል።
ኮሮናቫይረስ በፖለቲካ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፍ በሳደረው ጫና ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጭ እንዲሆኑ መደረጉንም አስታውሰዋል።
አቶ ሚሊዮን እንዳሉት ትምህርት መቋረጡ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመግታት አስተዋፅኦ ቢኖረውም በተማሪዎች በተለይም ከህጻናት እድገት አንጻር ከፍተኛ ጫና አሳድሯል።በተለይ ህጻናት ትምህርት ዝግ ሆኖ ቤት በመዋላቸው ለአስገድዶ መደፈርና ያለዕድሜ ጋብቻ መዳረጋቸውን ሚኒስቴር ዴኤታው ገልጸዋል።በኢትዮጵያ ባሉ ከ42 ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ከ700 ሺህ በላይ መምህራንና ከ26 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ይገኛሉ።
“ወቅቱ ኮሮናቫይረስ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ያለበት በመሆኑ ትምህርት ቤቶች መከፈታቸው ህብረተሰቡን እያነጋገረ ነው” ያሉት አቶ ሚሊዮን፣ ወረርሽኙ የሚቆምበት ጊዜ ባለመታወቁ ትምህርት እንደሚጀመርና ይህም የጤና ጥበቃ የሚያስቀምጠውን መስፈርት ተግባራዊ በማድረግ እንደሚከናወን ገልጸዋል።ባለፈው የመማር ማስተማር ሂደት በአማካይ ከ60 እስከ 80 ተማሪዎች በአንድ ክፍል ውስጥ ይማሩ የነበረበት ሁኔታ እንደነበር አቶ ሚሊዮን አስታውሰዋል።
በቀጣይ ትምህርት ሲከፈት በቅድመ መደበኛ 14 በመቶ የሚሆኑትን ትምህርት ቤቶች ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ብቻ በአንድ ክፍል እንዲያስተምሩና አንድ ተማሪ በአንድ ዴስክ ብቻ እንዲቀመጥ ለማድረግ መታቀዱን አስረድተዋል።አቶ ሚሊዮን እንዳሉት ቀሪዎቹ 80 በመቶ ተማሪዎች በፈረቃ እንዲማሩና 6 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርት ቤት በመገንባትና አማራጭ ማህበራዊ ተቋማትን በመጠቀም ለማስተማር ታቅዷል።
በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 24 በመቶ ወይም ከ20 እስከ 25 ተማሪዎች በአንድ ከፍል ውስጥ እንዲማሩ፣ 56 በመቶ በፈረቃ እንዲሁም 20 በመቶ ተጨማሪ ክፍል በመገንባት እንዲማሩ ተወስኗል።በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 19 በመቶ ተማሪዎች ወይም ከ20 እስከ 25 የሚሆኑት በአንድ ክፍል ውስጥ እንዲማሩ እንዲሁም 50 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ በፈረቃ የሚማሩ ይሆናል።
ሌሎች 31 በመቶ ተጨማሪ ክፍሎችን በመገንባትና አማራጭ ማህበራዊ ተቋማትን በመጠቀም ለማስተማር መታቀዱንም አመልክተዋል።በሽታን በመከላከል የትምህርት ተቋማትን ስራ ለማስጀመር ተቋማቱን ማስፋት እንደሚገባም አቶ ሚሊዮን ተናግረዋል።
ኦሮሚያ ክልል ሃብት በማሰባሰብ 30 ሺህ አዳዲስ ክፍሎችን መገንባቱን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ “አማራ ክልልም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ያለውን የክፍል እጥረት ችግር ለመቅረፍ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው” ብለዋል።
ተማሪዎች በተረጋጋ ሁኔታ እንዲማሩ የቀደመው የመማር ማስተማር ስልት በአዲስ መልክ እንደሚሆን ጠቁመው፣ ይህም የቡድን ስራን ጨምሮ የተማሪዎችን አካላዊ ንክኪን ሊያስቀር በሚችል መልኩ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።አቶ ሚሊዮን እንዳሉት የትምህርት ቤቶች አከፋፈት ጥናቱን መሰረት ያደረገ ይሆናል።ትምህርት ቤቶች በተመሳሳይ ወቀት አንድ ላይ ሊከፈቱ እንደማይችሉና ደረጃ በደረጃ የመክፈት ሂደት እንደሚኖር ገልጸው፣ አጀማመሩ ከክልል ክልልና ከዞን ዞን ሊለያይ እንደሚችል አመልክተዋል።
ይህንን ተከትሎ አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ጭማሪ እየጠየቁ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን በሚያደርጉ ተቋማት ላይ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶችን እስከመዝጋት የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስድ አመልክተዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
በጠገዴ ወረዳ ሰው አግቶ ገንዘብ በተቀበለ ግለሠብ ላይ የሦሮቃ ንዑስ ወረዳ ፍ/ቤት የቅጣት ውሳኔ አስተላለፈ።
ግንቦት 19/2012 ዓ/ም ተጠርጣሪ ሙቀት አለማየሁ የማይ አጋም ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን በየነ ጥላሁን በሥራ ላይ እያለ 6 ሽህ ብር መክፈል አለብህ በማለት ለአራት ቀናት አግቶት ቆይቷል። የታገተው ግለሠብ ቤተሠቦችን ግንቦት 22/2012 ዓ/ም 6ሽህ ብር ከፍለው ከታገተበት አስለቅቀውታል። ተጠርጣሪው ገንዘቡን እንደተቀበለ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 አካባቢ ነዋሪነቱን አድርጓል። ፖሊስ ግለሠቡን በመከታተሉና ከማህበረሰቡ በደረሰ ጥቆማ በጎንደር ከተማ ነሀሴ 12/2012 ዓ/ም ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውላል።
የሶ/ን/ወረዳ ፖሊስ ተጠርጣሪውን ነሀሴ 25/2012 ዓ/ም ወንጀሉን ወደ ፈፀመበት ሶሮቃ ንዑስ ወረዳ በመውሰድ ምርመራውን ጀምሯል።ተከሳሹም ክዶ ተከራክሯል የሶ/ን/ወረዳ ዓ/ ህግ የተላለፈውን የኢፌድሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 586/1/ እና 590 ንዑስ ቁጥር "ሐ 2" በመጥቀስ በመተላለፍ የህግ ማስረጃወችን አሠምቷል።
ክሱን የተመለከተው የሶ/ን/ወረዳ/ፍ/ቤት ተከሳሹን ጥፋተኛ በማለት እሡንም ሆነ ሌሎችን ያስተምራል በማለት ናሀሴ 27/2012 ዓ/ ም በወለው የወንጀል ችሎት በ8 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ዓ/ህግ ተከሳሹ በጦር መሳሪያ ይዞ ወንጀሉን የፈፀመ በመሆኑ ቅጣቱን አንሷል ሲል ይግባኝ ጠይቋል ። መረጃውን ያደረሰን የሶሮቃ ንዑሥ ወረዳ ዓቃቢ ህግ ጽ/ቤትን ጠቅሶ የጠገዴ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ግንቦት 19/2012 ዓ/ም ተጠርጣሪ ሙቀት አለማየሁ የማይ አጋም ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን በየነ ጥላሁን በሥራ ላይ እያለ 6 ሽህ ብር መክፈል አለብህ በማለት ለአራት ቀናት አግቶት ቆይቷል። የታገተው ግለሠብ ቤተሠቦችን ግንቦት 22/2012 ዓ/ም 6ሽህ ብር ከፍለው ከታገተበት አስለቅቀውታል። ተጠርጣሪው ገንዘቡን እንደተቀበለ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 አካባቢ ነዋሪነቱን አድርጓል። ፖሊስ ግለሠቡን በመከታተሉና ከማህበረሰቡ በደረሰ ጥቆማ በጎንደር ከተማ ነሀሴ 12/2012 ዓ/ም ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውላል።
የሶ/ን/ወረዳ ፖሊስ ተጠርጣሪውን ነሀሴ 25/2012 ዓ/ም ወንጀሉን ወደ ፈፀመበት ሶሮቃ ንዑስ ወረዳ በመውሰድ ምርመራውን ጀምሯል።ተከሳሹም ክዶ ተከራክሯል የሶ/ን/ወረዳ ዓ/ ህግ የተላለፈውን የኢፌድሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 586/1/ እና 590 ንዑስ ቁጥር "ሐ 2" በመጥቀስ በመተላለፍ የህግ ማስረጃወችን አሠምቷል።
ክሱን የተመለከተው የሶ/ን/ወረዳ/ፍ/ቤት ተከሳሹን ጥፋተኛ በማለት እሡንም ሆነ ሌሎችን ያስተምራል በማለት ናሀሴ 27/2012 ዓ/ ም በወለው የወንጀል ችሎት በ8 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ዓ/ህግ ተከሳሹ በጦር መሳሪያ ይዞ ወንጀሉን የፈፀመ በመሆኑ ቅጣቱን አንሷል ሲል ይግባኝ ጠይቋል ። መረጃውን ያደረሰን የሶሮቃ ንዑሥ ወረዳ ዓቃቢ ህግ ጽ/ቤትን ጠቅሶ የጠገዴ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ዓለም ለሚቀጥለው ወረርሽኝ በአግባቡ መዘጋጀት አለባት- የአለም ጤና ድርጅት
የአለም ጤና ድርጅት ኃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በትናንትናው እለት ሀገራትን በህብረተሰብ ጤና ላይ አተኩረው እንዲሰሩ በጠየቁበት ወቅት፣ ዓለም ለሚቀጥለው ወረርሽኝ በሚገባ መዘጋጅት እንዳለባት ተናግረዋል፡፡እስካሁን ሮይተርስ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ በሽታ በፈረንጆቹ 2019 በቻይና ከተገኘበት ጊዜ ጀምሮ አዘጋጀሁት ባለው መረጃ መሰረት ከ27 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሲሆን 888 326 ሰዎችደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ዶክተር ቴድሮስ ይሄ የመጨረሻው ወረርሽኝ አይደለም ብለዋል፡፡ “ታሪክ እንደሚያስተምረን ወረርሽኞች የሚኖሩ ናቸው፤ስለሆነም ዓለም ከአሁን በላይ መዘጋጀት” እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
የአለም ጤና ድርጅት ኃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በትናንትናው እለት ሀገራትን በህብረተሰብ ጤና ላይ አተኩረው እንዲሰሩ በጠየቁበት ወቅት፣ ዓለም ለሚቀጥለው ወረርሽኝ በሚገባ መዘጋጅት እንዳለባት ተናግረዋል፡፡እስካሁን ሮይተርስ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ በሽታ በፈረንጆቹ 2019 በቻይና ከተገኘበት ጊዜ ጀምሮ አዘጋጀሁት ባለው መረጃ መሰረት ከ27 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሲሆን 888 326 ሰዎችደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ዶክተር ቴድሮስ ይሄ የመጨረሻው ወረርሽኝ አይደለም ብለዋል፡፡ “ታሪክ እንደሚያስተምረን ወረርሽኞች የሚኖሩ ናቸው፤ስለሆነም ዓለም ከአሁን በላይ መዘጋጀት” እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮውን ወደ ትግራይ ክልል አዘዋወረ!
በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ባለቤትነት ስር የሚተዳደረውና በርካታ የልማት ድርጅቶችን አቅፎ በያዘው የትግራይ መልሶ ማቋቋም (ኤፈርት) ተብሎ በሚጠራው ድርጅቶች ውስጥ አንዱ የሆነው ሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮውን ወደ መቐለ ማዘዋወሩ ተገለፀ።
አዲስ ማለዳ ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው የኮንስትራክሽን ድርጅቱ ቦሌ ሸዋ ዳቦ አፍሪካ ጎዳና አካባቢ ባስገነባው የራሱ ህንፃ አገልግሎት ይሰጥ የነበረ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ወደ ትግራይ ክልል ማዘዋወሩ ተገልጿል።
በሱር ኮንስትራክሽን ውስጥ ከሚሰሩ ሰራተኞች መሃል ለአዲስ ማለዳ የተናገሩት እንዳሉት ኮቪድ 19 ከገባ ከጥቂት ቀናት በኋላ ዋና መስሪያ ቤቱ ወደ መቐለ መዛወሩን የተናገሩ ሲሆን በዚህም አዲስ አበባ የሚገኙ ሰራተኞች ፈቃድ እንደሰጠና ለዚህም ምክንያቱ ኮቪድ 19 ኢትዮጵያ መግባቱ መሆኑ እንደተገለፀላቸው ተናግረዋል።
ድርጅቱ ይህን ይበል እንጂ ከቀናት በኋላ በአዲስ አበባ ለሚገኙ ሰራተኞች የተገለፀው ፈቃደኛ ሆነው ትግራይ ክልል መቀሌ ገብተው መስራት ከፈለጉ እንደሚችሉ እና ካልሆነ ግን በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን እንደለቀቁ እንደሚወሰድ እንደተነገራቸው አዲስ ማለዳ ከምንጮቿ አረጋግጣለች።ከዚህ ጉዳይ ጋር ጋዜጣው ያነጋገራቸው የሱር ኮንስትራክሽን ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ታደሰ የማነ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት ከሆነ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ተሰማርቶ ያለው ሱር ኮንትራክሽን ከዚህ ቀደም የነበረውን ዋናውን ቢሮ አለመልቀቁን እና ቅሬታውም ከእውነት የራቀ ነው በማለት ተናግረዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ እንደሚሉት ከዚህ ቀደም የሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮ የሚገኝበት ደምበል አካባቢ ከሜጋ ህንፃ ጎን እንደሆነ እና አሁንም እዛው እንዳለ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።ታደሰ ጨምረውም አሁን ደምበል አካባቢ የሚገኘው ቢሯቸው አገልግሎት እየሰጠ ያልሆነበት ምክንትን ሲጠቅሱ፤ በትግራይ ክልል ከ30 በላይ ፕሮጀክቶች በመጀመራቸው እና ሱር ኮንስትራክሽንም ለስራው ቅርብ መሆን ስላለበት አንዳንድ ዋና ዋና የስራ ኃላፊዎች ወደዛው መቅረብ ስላለባቸው መሆኑን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
ነገር ግን ይላሉ በፕሮጀክቱ ላይ ለመሳተፍ ምን ያህል ሰራተኞች እንደሄዱ በቁጥር እንደማያውቁ እና አዲስ አበባ ከሚገኘው ዋናው ቢሮም ምንም አይነት ሰራተኛ በእረፍት ላይ አይገኝም ሲሉ አስተባብለዋል።ሱር ኮንስትራክሽን በኤፈርት ስር ከሚገኙ ወደ 14 የሚጠጉ ድርጅቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከሦስት ሺሕ በላይ ቋሚ እና ከሰባት ሺሕ በላይ ደግሞ ቀን ሰራተኞችን በስሩ ሚያስተዳደር ግዙፍ ኩባንያ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
ከ20 ዓመታት በፊት በ108 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተመሰረተው ሱር ኮንስትራክሽን በሕወሓት ባለቤትነት በሚመራው ኤፈርት ኩባንያዎች አንዱ አካል እንደሆነም ይታወቃል።ሱር ኮንስትራክሽን በአገር ውስጥ ካሉ ኮንስትራክሽኖች ደረጃ አንድ ግንባታ ድርጅት ሲሆን፤ ሀይድሮፓወር ፕሮጀክቶች እና የመኖሪያ ቤት ግንነባታዎችም ላይ በስፋት እንደሚሳተፍም ይታወቃል።ከተሳተፈባቸው ፕሮጀክቶችም መካከል በከፍተኛ ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የዛሬማ ሜይዴይ ግድብ አንዱ ሲሆን በአገር በቀል ድርጅቶች ይህን የሚያክል ከፍተኛ በጀት ያላቸውን ፕሮጀክቶች በዋና ተቋራጭነት በመሳተፍ ሱር ቀዳሚው ድርጅት ነው።በተመሳሳይም በመቐለ ከተማ መኖሪያ መንደርም በመገንባት ስራ ላይም ተሰመራርቷል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ባለቤትነት ስር የሚተዳደረውና በርካታ የልማት ድርጅቶችን አቅፎ በያዘው የትግራይ መልሶ ማቋቋም (ኤፈርት) ተብሎ በሚጠራው ድርጅቶች ውስጥ አንዱ የሆነው ሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮውን ወደ መቐለ ማዘዋወሩ ተገለፀ።
አዲስ ማለዳ ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው የኮንስትራክሽን ድርጅቱ ቦሌ ሸዋ ዳቦ አፍሪካ ጎዳና አካባቢ ባስገነባው የራሱ ህንፃ አገልግሎት ይሰጥ የነበረ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ወደ ትግራይ ክልል ማዘዋወሩ ተገልጿል።
በሱር ኮንስትራክሽን ውስጥ ከሚሰሩ ሰራተኞች መሃል ለአዲስ ማለዳ የተናገሩት እንዳሉት ኮቪድ 19 ከገባ ከጥቂት ቀናት በኋላ ዋና መስሪያ ቤቱ ወደ መቐለ መዛወሩን የተናገሩ ሲሆን በዚህም አዲስ አበባ የሚገኙ ሰራተኞች ፈቃድ እንደሰጠና ለዚህም ምክንያቱ ኮቪድ 19 ኢትዮጵያ መግባቱ መሆኑ እንደተገለፀላቸው ተናግረዋል።
ድርጅቱ ይህን ይበል እንጂ ከቀናት በኋላ በአዲስ አበባ ለሚገኙ ሰራተኞች የተገለፀው ፈቃደኛ ሆነው ትግራይ ክልል መቀሌ ገብተው መስራት ከፈለጉ እንደሚችሉ እና ካልሆነ ግን በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን እንደለቀቁ እንደሚወሰድ እንደተነገራቸው አዲስ ማለዳ ከምንጮቿ አረጋግጣለች።ከዚህ ጉዳይ ጋር ጋዜጣው ያነጋገራቸው የሱር ኮንስትራክሽን ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ታደሰ የማነ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት ከሆነ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ተሰማርቶ ያለው ሱር ኮንትራክሽን ከዚህ ቀደም የነበረውን ዋናውን ቢሮ አለመልቀቁን እና ቅሬታውም ከእውነት የራቀ ነው በማለት ተናግረዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ እንደሚሉት ከዚህ ቀደም የሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮ የሚገኝበት ደምበል አካባቢ ከሜጋ ህንፃ ጎን እንደሆነ እና አሁንም እዛው እንዳለ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።ታደሰ ጨምረውም አሁን ደምበል አካባቢ የሚገኘው ቢሯቸው አገልግሎት እየሰጠ ያልሆነበት ምክንትን ሲጠቅሱ፤ በትግራይ ክልል ከ30 በላይ ፕሮጀክቶች በመጀመራቸው እና ሱር ኮንስትራክሽንም ለስራው ቅርብ መሆን ስላለበት አንዳንድ ዋና ዋና የስራ ኃላፊዎች ወደዛው መቅረብ ስላለባቸው መሆኑን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
ነገር ግን ይላሉ በፕሮጀክቱ ላይ ለመሳተፍ ምን ያህል ሰራተኞች እንደሄዱ በቁጥር እንደማያውቁ እና አዲስ አበባ ከሚገኘው ዋናው ቢሮም ምንም አይነት ሰራተኛ በእረፍት ላይ አይገኝም ሲሉ አስተባብለዋል።ሱር ኮንስትራክሽን በኤፈርት ስር ከሚገኙ ወደ 14 የሚጠጉ ድርጅቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከሦስት ሺሕ በላይ ቋሚ እና ከሰባት ሺሕ በላይ ደግሞ ቀን ሰራተኞችን በስሩ ሚያስተዳደር ግዙፍ ኩባንያ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
ከ20 ዓመታት በፊት በ108 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተመሰረተው ሱር ኮንስትራክሽን በሕወሓት ባለቤትነት በሚመራው ኤፈርት ኩባንያዎች አንዱ አካል እንደሆነም ይታወቃል።ሱር ኮንስትራክሽን በአገር ውስጥ ካሉ ኮንስትራክሽኖች ደረጃ አንድ ግንባታ ድርጅት ሲሆን፤ ሀይድሮፓወር ፕሮጀክቶች እና የመኖሪያ ቤት ግንነባታዎችም ላይ በስፋት እንደሚሳተፍም ይታወቃል።ከተሳተፈባቸው ፕሮጀክቶችም መካከል በከፍተኛ ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የዛሬማ ሜይዴይ ግድብ አንዱ ሲሆን በአገር በቀል ድርጅቶች ይህን የሚያክል ከፍተኛ በጀት ያላቸውን ፕሮጀክቶች በዋና ተቋራጭነት በመሳተፍ ሱር ቀዳሚው ድርጅት ነው።በተመሳሳይም በመቐለ ከተማ መኖሪያ መንደርም በመገንባት ስራ ላይም ተሰመራርቷል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
ኮሮና ቫይረስ በአውሮፓ በድጋሚ እያንሰራራ መሆኑ ተገለጸ!
ስፔን በምዕራብ አውሮፓ ግማሽ ሚሊዮን የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎችን በመመዝገብ የመጀመሪያዋ አገር ሆናለች፡፡በሀገሪቱ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ከ525 ሺ የበለጠ ሲሆን ይህም የሆነው ትምህርት ቤቶች እንደገና ከመከፈታቸው ጋር በተያያዘ ቫይረሱ ለሁለተኛ ጊዜ በማገርሸት ላይ በመሆኑ ነው፡፡
በሌሎች የአውሮፓ ሀገራትም በተመሳሳይ ቫይረሱ በድጋሚ በማንሰራራት ላይ ይገኛል፡፡ ፈረንሳይ በየቀኑ የተጠቂዎች ቁጥር “አሳሳቢ” በሆነ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን ያሳወቀች ሲሆን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እለት ተእለት በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በአማካይ ከ 5,000 በላይ መድረሱን ይፋ አድርጋለች፡፡
የተጠቂዎች ቁጥር እየጨመረባት ባለችው በሌላኛዋ አውሮፓዊት ሀገር ዩናይትድ ኪንግደም የአገር ውስጥ የቫይረሱ ስርጭት በአብዛኛው ከወጣቶች የተያያዘ ስለመሆኑ ዘ ናሺናል ዘግቧል፡፡በመላው ዓለም እስካሁን የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከ 27.4 ሚሊዮን በላይየደረሰ ሲሆን ከ 896,000 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸው አልፎ ከ 19 ሚሊዮን የሚበልጡት አገግመዋል፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ስፔን በምዕራብ አውሮፓ ግማሽ ሚሊዮን የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎችን በመመዝገብ የመጀመሪያዋ አገር ሆናለች፡፡በሀገሪቱ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ከ525 ሺ የበለጠ ሲሆን ይህም የሆነው ትምህርት ቤቶች እንደገና ከመከፈታቸው ጋር በተያያዘ ቫይረሱ ለሁለተኛ ጊዜ በማገርሸት ላይ በመሆኑ ነው፡፡
በሌሎች የአውሮፓ ሀገራትም በተመሳሳይ ቫይረሱ በድጋሚ በማንሰራራት ላይ ይገኛል፡፡ ፈረንሳይ በየቀኑ የተጠቂዎች ቁጥር “አሳሳቢ” በሆነ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን ያሳወቀች ሲሆን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እለት ተእለት በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በአማካይ ከ 5,000 በላይ መድረሱን ይፋ አድርጋለች፡፡
የተጠቂዎች ቁጥር እየጨመረባት ባለችው በሌላኛዋ አውሮፓዊት ሀገር ዩናይትድ ኪንግደም የአገር ውስጥ የቫይረሱ ስርጭት በአብዛኛው ከወጣቶች የተያያዘ ስለመሆኑ ዘ ናሺናል ዘግቧል፡፡በመላው ዓለም እስካሁን የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከ 27.4 ሚሊዮን በላይየደረሰ ሲሆን ከ 896,000 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸው አልፎ ከ 19 ሚሊዮን የሚበልጡት አገግመዋል፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች በበዓሉ ዋዜማ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳይጠቀሙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳሰበ!
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2013 ዓ.ም ዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚኖረው የኃይል ፍልጎት ለማሟላት የቅድመ ጥንቃቄ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በበአሉ ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን የኃይል መዋዠቅንና መቆራረጥ ለመቀነስ የድንጋይና እህል ወፍጮ፣ የፕላስቲክ፣ የጨርቃ ጨርቅ፣ የብረታ ብረት፣ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ የኬሚካልና ሌሎች ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ከጳጉሜ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከንጋቱ 12፡00 ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 4፡00 ድረስ ከግሪድ የሚያገኙትን የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳይጠቀሙ የተለመደ ትብብራቸውን አንዲሰጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳስቧል።
በዋዜማና በበዓሉ ቀን የኤሌክትሪክ ኃይል ሳይቆራረጥና ሳይዋዥቅ ለማቅረብ እንዲሁም ችግሩ ከተከሰተም በተገቢው መንገድ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑንንም ነው ተቋሙ የገለፀው፡፡በተደጋጋሚ ጊዜ የኃይል መቆራረጥ የሚስተዋልባቸውን አካባቢዎች በመለየት በመካከለኛና በዝቅተኛ መስመሮች ላይ ጭነት የማመጣጠንና የቅድመ መከላከል ጥገና ስራዎች በመሰራት ላይ መሆኑንንም አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ በመሆን ከኃይል ማመንጫ ጀምሮ እስከ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና ትራንስፎርመሮች ብልሽቶች ሲያጋጥሙ በአፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውም ተገልጿል፡፡
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2013 ዓ.ም ዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚኖረው የኃይል ፍልጎት ለማሟላት የቅድመ ጥንቃቄ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በበአሉ ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን የኃይል መዋዠቅንና መቆራረጥ ለመቀነስ የድንጋይና እህል ወፍጮ፣ የፕላስቲክ፣ የጨርቃ ጨርቅ፣ የብረታ ብረት፣ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ የኬሚካልና ሌሎች ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ከጳጉሜ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከንጋቱ 12፡00 ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 4፡00 ድረስ ከግሪድ የሚያገኙትን የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳይጠቀሙ የተለመደ ትብብራቸውን አንዲሰጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳስቧል።
በዋዜማና በበዓሉ ቀን የኤሌክትሪክ ኃይል ሳይቆራረጥና ሳይዋዥቅ ለማቅረብ እንዲሁም ችግሩ ከተከሰተም በተገቢው መንገድ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑንንም ነው ተቋሙ የገለፀው፡፡በተደጋጋሚ ጊዜ የኃይል መቆራረጥ የሚስተዋልባቸውን አካባቢዎች በመለየት በመካከለኛና በዝቅተኛ መስመሮች ላይ ጭነት የማመጣጠንና የቅድመ መከላከል ጥገና ስራዎች በመሰራት ላይ መሆኑንንም አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ በመሆን ከኃይል ማመንጫ ጀምሮ እስከ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና ትራንስፎርመሮች ብልሽቶች ሲያጋጥሙ በአፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውም ተገልጿል፡፡
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአምስት ቋንቋዎች የተሰናዳ የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት መተግበሩን አስታወቀ!
በኢትዮጵያውያን የተሠራና ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛል የተባለና ‹‹ጉዞ ጐ›› የተባለ በአምስት ቋንቋዎችና በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የተሠራ የኤሌክሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት መተግበሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ፡፡
ጉዞ ጐ የተሰኘው የበረራ ትኬት ሽያጭ ማከናወኛ ሶፍትዌር በአማርኛ፣ በኦሮሚኛ፣ በትግሪኛ፣ በሶማሊኛና እንግሊዝኛ ወይም እንዲተገበር ያደረገው ሶልጌት ትራቭል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው ስምምነት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ በረራ ካላቸው አሥር አየር መንገዶች ጋር የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ዘዴውን በመተግበር፣ በባንኩ በኩል የአየር ትኬት ሽያጭ በኦንላይን መጀመሩን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. የስምምነት ሰነድ በመፈጸም ትግበራውን ይፋ አድርገዋል፡፡
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ዮሐንስ ሚሊዮን፣ አዲስ የተተገበረውን የኦንላይን ኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ዘዴን በሚመለከት እንደገለጹት፣ የክፍያ ሥርዓትን ከማዘመን አንፃር ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡ ሶልጌት ትራቭል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያበለፀገው ጉዞ ጐ ዲጂታላይዝ የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መተግበሪያ፣ የአየር በረራ ትኬቶችን የመቁረጥና ለደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት የሚያገኙበት አሠራር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያውያን የተሠራና ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛል የተባለና ‹‹ጉዞ ጐ›› የተባለ በአምስት ቋንቋዎችና በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የተሠራ የኤሌክሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት መተግበሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ፡፡
ጉዞ ጐ የተሰኘው የበረራ ትኬት ሽያጭ ማከናወኛ ሶፍትዌር በአማርኛ፣ በኦሮሚኛ፣ በትግሪኛ፣ በሶማሊኛና እንግሊዝኛ ወይም እንዲተገበር ያደረገው ሶልጌት ትራቭል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው ስምምነት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ በረራ ካላቸው አሥር አየር መንገዶች ጋር የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ዘዴውን በመተግበር፣ በባንኩ በኩል የአየር ትኬት ሽያጭ በኦንላይን መጀመሩን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. የስምምነት ሰነድ በመፈጸም ትግበራውን ይፋ አድርገዋል፡፡
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ዮሐንስ ሚሊዮን፣ አዲስ የተተገበረውን የኦንላይን ኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ዘዴን በሚመለከት እንደገለጹት፣ የክፍያ ሥርዓትን ከማዘመን አንፃር ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡ ሶልጌት ትራቭል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያበለፀገው ጉዞ ጐ ዲጂታላይዝ የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መተግበሪያ፣ የአየር በረራ ትኬቶችን የመቁረጥና ለደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት የሚያገኙበት አሠራር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ለ1 ሺህ 29 የአየር ኃይል መኮንኖች የማእረግ እድገት ሰጠ!
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ለ1 ሺህ 29 የአየር ኃይል መኮንኖች የማእረግ እድገት ሰጠ።
የማእረግ እድገቱኑን የሰጡት የአየር ኃይሉ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ይልማ መርዳሳ በስነ-ስርአቱ ላይ እንደተናገሩት የማእረግ እድገቱ ለተጨማሪ ኃላፊነት የሚጋብዝ በመሆኑ መኮንኖቹ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን ለስኬት ማብቃት እንዳለባቸው አሳስበዋል።በእለቱ የአየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮችን ሀብት ማስመዝገብ፣ የተቋሙ የድህረ ገፅ ምርቃት እና የአብራሪዎች ትጥቅ ትውውቅ ተደርጓል።በዝግጅቱ ላይ ሰራዊቱ “ለገበታ ለሀገር” ፕሮጀክቶችም የአንድ ወር ሙሉ ደሞዛቸውን እንደሚሰጡ ተገልጿል።
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ለ1 ሺህ 29 የአየር ኃይል መኮንኖች የማእረግ እድገት ሰጠ።
የማእረግ እድገቱኑን የሰጡት የአየር ኃይሉ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ይልማ መርዳሳ በስነ-ስርአቱ ላይ እንደተናገሩት የማእረግ እድገቱ ለተጨማሪ ኃላፊነት የሚጋብዝ በመሆኑ መኮንኖቹ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን ለስኬት ማብቃት እንዳለባቸው አሳስበዋል።በእለቱ የአየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮችን ሀብት ማስመዝገብ፣ የተቋሙ የድህረ ገፅ ምርቃት እና የአብራሪዎች ትጥቅ ትውውቅ ተደርጓል።በዝግጅቱ ላይ ሰራዊቱ “ለገበታ ለሀገር” ፕሮጀክቶችም የአንድ ወር ሙሉ ደሞዛቸውን እንደሚሰጡ ተገልጿል።
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፖሊስ በአሥራት ጋዜጠኞች ላይ ያቀረበውን የይግባኝ ጥያቄ ውድቅ አደረገ።
የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ይግባኝ የወንጀል ችሎት ፖሊስ በአሥራት ጋዜጠኞች ላይ ያቀረበውን የይግባኝ ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።ፖሊስ የአሥራት ጋዜጠኞች በዋስትና ከእስር ቢፈቱ መረጃ ያጠፉብኛል ቢልም ፍርድ ቤቱ ይግባኙን አልተቀበለውም።ፖሊስ ከአራቱ የአሥራት ጋዜጠኞች መካከል በበላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብርና ምስጋናው ከፈለኝ ላይ ይግባኝ ጠይቆ የነበር ሲሆን በዋነኛነት ከኢመድኤ / INSA፣ ከሆስፒታል እና ከብሮድካስት ባለስልጣን መረጃ እንደሚያመጣ ጠቅሶ ከእስር ከወጡ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስለሆኑ መረጃ ያጠፉብኛል ብሏል ማለቱን አስራት ሚዲያ በፌስ ቡክ ገጹ ይፋ አደርጓል።
ይሁንና ፍርድ ቤቱ መረጃ ይመጣባቸዋል ከሚባሉት ተቋማት መረጃ ማጥፋት ሆነ ማዛባት እንደማይቻል ገልፆ የእስር ፍርድ ቤቱ በተደጋጋሚ ፖሊስ መረጃ እንዲታቀርብ ቀጠሮ ከሰጠ በኋላ ጋዜጠኞቹ በዋስትና እንዲለቀቁ ማድረጉ ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብሎታል።የአሥራት ጋዜጠኞች በአራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋስትና እንዲወጡ ከተወሰነላቸው በኋላ እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር የከፈሉ ሲሆን ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ በእስር እንዳቆያቸው ጠበቃቸው መግለፃቸው ይታወቃል።
[ኢትዮ ኤፍ ኤም]
@YeneTube @FikerAssefa
የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ይግባኝ የወንጀል ችሎት ፖሊስ በአሥራት ጋዜጠኞች ላይ ያቀረበውን የይግባኝ ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።ፖሊስ የአሥራት ጋዜጠኞች በዋስትና ከእስር ቢፈቱ መረጃ ያጠፉብኛል ቢልም ፍርድ ቤቱ ይግባኙን አልተቀበለውም።ፖሊስ ከአራቱ የአሥራት ጋዜጠኞች መካከል በበላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብርና ምስጋናው ከፈለኝ ላይ ይግባኝ ጠይቆ የነበር ሲሆን በዋነኛነት ከኢመድኤ / INSA፣ ከሆስፒታል እና ከብሮድካስት ባለስልጣን መረጃ እንደሚያመጣ ጠቅሶ ከእስር ከወጡ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስለሆኑ መረጃ ያጠፉብኛል ብሏል ማለቱን አስራት ሚዲያ በፌስ ቡክ ገጹ ይፋ አደርጓል።
ይሁንና ፍርድ ቤቱ መረጃ ይመጣባቸዋል ከሚባሉት ተቋማት መረጃ ማጥፋት ሆነ ማዛባት እንደማይቻል ገልፆ የእስር ፍርድ ቤቱ በተደጋጋሚ ፖሊስ መረጃ እንዲታቀርብ ቀጠሮ ከሰጠ በኋላ ጋዜጠኞቹ በዋስትና እንዲለቀቁ ማድረጉ ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብሎታል።የአሥራት ጋዜጠኞች በአራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋስትና እንዲወጡ ከተወሰነላቸው በኋላ እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር የከፈሉ ሲሆን ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ በእስር እንዳቆያቸው ጠበቃቸው መግለፃቸው ይታወቃል።
[ኢትዮ ኤፍ ኤም]
@YeneTube @FikerAssefa
የድምጽ ብክለትን ለመቆጣጠር የምሽት የቁጥጥር ሥራ ሊጀመር ነው!
በተለያዩ ሆቴሎች፣ መጠጥ ቤቶች እና ምግብ ቤቶች ፣በመንገድ ላይ፣ በልብስ መሸጫ (ቡቲክ) እና በተለያዩ ቦታዎች ላይ የሚስተዋለውን የድምጽ ብክለት ለመቆጣጠር ከዚህ በፊት ይተገበር ያልነበረው የምሽት የቁጥጥር ስራ ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ ለመጀመር ማቀዱን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ለአዲሰ ማለዳ አስታወቀ።የቁጥጥር ስራው ቅዳሜ እና እሁድን በመጨመር ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ተግባዊ እንደሚሆንም ኮሚሽኑ አስታውቋል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በተለያዩ ሆቴሎች፣ መጠጥ ቤቶች እና ምግብ ቤቶች ፣በመንገድ ላይ፣ በልብስ መሸጫ (ቡቲክ) እና በተለያዩ ቦታዎች ላይ የሚስተዋለውን የድምጽ ብክለት ለመቆጣጠር ከዚህ በፊት ይተገበር ያልነበረው የምሽት የቁጥጥር ስራ ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ ለመጀመር ማቀዱን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ለአዲሰ ማለዳ አስታወቀ።የቁጥጥር ስራው ቅዳሜ እና እሁድን በመጨመር ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ተግባዊ እንደሚሆንም ኮሚሽኑ አስታውቋል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር ወረዳ ሚስቱን የገደለው ተከሳሽ የሞት ፍርድ ተፈረደበት።
የዞኑ ኮሙንኬሽን እንዳስታወቀው ድርጊቱ ፈፃሚ አቶ በሀሩ ወንድም አገኝ ጉባሞ በጉራጌ ዞን እኖር ኤነረ ወረዳ የባረዋ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን ለባለቤቱ እንደሚገድላት በተደጋጋሚ እየዛተባት ነበር።በእለተ ሀሙስ በቀን 24/07/2012 በግምት ከንጋቱ 12:00 ሟች አፀደ ዘመድአገኝ በባለቤቷ እንደዛተባትም በአሰቃቂ ሁኔታ በዱላ ጭንቅላቷንና ማጅራቷን ደብድቦ ከገደላት በኋላ ወንዝ ላይ ጥሏት መሄዱ ተገልጿል።ይህንን አሰቃቂ ድርጊት የሚገልፅ የምርመራ መዝገብ የደረሰው የጉራጌ ዞን ዐቃቤ ህግ መምሪያ የልዩ ልዩ የወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ የምርመራ መዝገቡ በአግባቡ በመመርመር በተከሳሹ ግለሰብ ላይ የኢ ፌ ዲ ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 539 (1)(ሀ )ላይ የከባድ የሰው ግድያ ወንጀል ክስ መስርቶበታል።
ክሱ የደረሰው የወልቂጤ አካባቢ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን ሲያከራክር ቆይቶ በቀን 02/13/2012 ዓም በዋለው ችሎት የተከሳሹ ድርጊት እጅግ አደገኛና ነውረኛ መሆኑን ከግምት ውስጥ አስገብቷል።በተጨማሪም ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ከዚህ ቀደም በ1999 ዓም በሀዋሳ ከተማ የቀድሞ ባለቤቱ በተመሳሳይ ሁኔታ ገድሎ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት ከሁለት አመት በፊት በይቅርታ ተለቆ መውጣቱን በቅጣት ማክበጃነት ይዟል።በመሆኑም ሰው መግደል ልማድ አድርጎ የያዘ በመሆኑ: ከዚህ በኋላ እስራት ያስተምረዋል ተብሎ ስለማይታሰብና የኢ ፌ ዲ ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 117 መስፈርቶች ሙሉ በሙሉ የሚያሟላ በመሆኑ በአጠቃላይ ሌላው የህብረተሰብ ክፍል ሊያስተምር ይችላል ያለውን የሞት ቅጣት ውሳኔ ወስኖበታል ተብሏል።
[ኢትዮ ኤፍ ኤም]
@YeneTube @FikerAssefa
የዞኑ ኮሙንኬሽን እንዳስታወቀው ድርጊቱ ፈፃሚ አቶ በሀሩ ወንድም አገኝ ጉባሞ በጉራጌ ዞን እኖር ኤነረ ወረዳ የባረዋ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን ለባለቤቱ እንደሚገድላት በተደጋጋሚ እየዛተባት ነበር።በእለተ ሀሙስ በቀን 24/07/2012 በግምት ከንጋቱ 12:00 ሟች አፀደ ዘመድአገኝ በባለቤቷ እንደዛተባትም በአሰቃቂ ሁኔታ በዱላ ጭንቅላቷንና ማጅራቷን ደብድቦ ከገደላት በኋላ ወንዝ ላይ ጥሏት መሄዱ ተገልጿል።ይህንን አሰቃቂ ድርጊት የሚገልፅ የምርመራ መዝገብ የደረሰው የጉራጌ ዞን ዐቃቤ ህግ መምሪያ የልዩ ልዩ የወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ የምርመራ መዝገቡ በአግባቡ በመመርመር በተከሳሹ ግለሰብ ላይ የኢ ፌ ዲ ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 539 (1)(ሀ )ላይ የከባድ የሰው ግድያ ወንጀል ክስ መስርቶበታል።
ክሱ የደረሰው የወልቂጤ አካባቢ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን ሲያከራክር ቆይቶ በቀን 02/13/2012 ዓም በዋለው ችሎት የተከሳሹ ድርጊት እጅግ አደገኛና ነውረኛ መሆኑን ከግምት ውስጥ አስገብቷል።በተጨማሪም ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ከዚህ ቀደም በ1999 ዓም በሀዋሳ ከተማ የቀድሞ ባለቤቱ በተመሳሳይ ሁኔታ ገድሎ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት ከሁለት አመት በፊት በይቅርታ ተለቆ መውጣቱን በቅጣት ማክበጃነት ይዟል።በመሆኑም ሰው መግደል ልማድ አድርጎ የያዘ በመሆኑ: ከዚህ በኋላ እስራት ያስተምረዋል ተብሎ ስለማይታሰብና የኢ ፌ ዲ ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 117 መስፈርቶች ሙሉ በሙሉ የሚያሟላ በመሆኑ በአጠቃላይ ሌላው የህብረተሰብ ክፍል ሊያስተምር ይችላል ያለውን የሞት ቅጣት ውሳኔ ወስኖበታል ተብሏል።
[ኢትዮ ኤፍ ኤም]
@YeneTube @FikerAssefa
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መርሃ-ግብሮች ያስተማራቸውን ከ 1000 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ።
በ1999 ዓ.ም የተመሰረተውና የሁለተኛ ትውልድ ዩኒቨርስቲ የሆነው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መርሃግብሮች ያስተማራቸውን 1 ሺህ 79 ተማሪዎችን ዛሬው ዕለት ለ12 ኛ ጊዜ ባካሄደው የምረቃ ስነስርዓት አስመርቋል። የምረቃ-ስነስርዓቱም በኮቪድ-19 ወረረሽኝ ምክንያት በበይነ-መረብ በሚተፈላለፍ የቀጥታ ስርጭት ተካሂዷል፡፡ዩኒቨርሲቲው በድህረ ምረቃና በቅድመ ምረቃ በመደበኛ፣ በሳምንቱ መጨረሻ እና በክረምት መርሀግብር በማሰልጠን በዛሬው ዕለት ካስመርቃቸው 1 ሺህ 79 ዕጩ ምሩቃን 493ቱ ሴቶች ሲሆኑ ከኒዚህም ውስጥ 51ዱ በተለያዩ የትህርት መስኮች በድህረ ምረቃ ዕጩ ምሩቃን ናቸው፡፡
[የወላይታ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት]
@YeneTube @FikerAssefa
በ1999 ዓ.ም የተመሰረተውና የሁለተኛ ትውልድ ዩኒቨርስቲ የሆነው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መርሃግብሮች ያስተማራቸውን 1 ሺህ 79 ተማሪዎችን ዛሬው ዕለት ለ12 ኛ ጊዜ ባካሄደው የምረቃ ስነስርዓት አስመርቋል። የምረቃ-ስነስርዓቱም በኮቪድ-19 ወረረሽኝ ምክንያት በበይነ-መረብ በሚተፈላለፍ የቀጥታ ስርጭት ተካሂዷል፡፡ዩኒቨርሲቲው በድህረ ምረቃና በቅድመ ምረቃ በመደበኛ፣ በሳምንቱ መጨረሻ እና በክረምት መርሀግብር በማሰልጠን በዛሬው ዕለት ካስመርቃቸው 1 ሺህ 79 ዕጩ ምሩቃን 493ቱ ሴቶች ሲሆኑ ከኒዚህም ውስጥ 51ዱ በተለያዩ የትህርት መስኮች በድህረ ምረቃ ዕጩ ምሩቃን ናቸው፡፡
[የወላይታ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት]
@YeneTube @FikerAssefa
በወልቃይት እና ራያ አካባቢ ደርሷል የተባለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ምርመራ ሊካሔድበት ነው!
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በወልቃይት እና ራያ አካባቢ በሕወሓት እየደረሰ ነው የተባለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሊመረምር መሆኑን ለአዲስ ማለዳ አስታወቀ።በኢትዮጵያ ኮቪድ-19 መከሰቱን ምክንያት በማድረግ 6ኛው አገራዊ ምርጫ መራዘሙን ተከትሎ በገዥው ፓርቲ ብልጽግና እና በህወሓት መካከል የተፈጠረው የፖለቲካ ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ ትግራይ ክልል ምርጫውን በክልል ደረጃ ምርጫ ለማካሄድ ጫፍ ደርሷል ይሄኑ መነሻ በማድረግ በአማራ ክልልና በትግራይ ክልል አዋሳኝ በወልቃይትና በራያ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎች ህወሓት የግድ ትምርጣላችሁ በማለት ለእስር፣ድብደባ እና ለአፈና ተዳርገናል ሲሉ አቤቱታቸውን አቅርበዋል።
ተጨማሪ👇👇👇
https://telegra.ph/-09-08-449
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በወልቃይት እና ራያ አካባቢ በሕወሓት እየደረሰ ነው የተባለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሊመረምር መሆኑን ለአዲስ ማለዳ አስታወቀ።በኢትዮጵያ ኮቪድ-19 መከሰቱን ምክንያት በማድረግ 6ኛው አገራዊ ምርጫ መራዘሙን ተከትሎ በገዥው ፓርቲ ብልጽግና እና በህወሓት መካከል የተፈጠረው የፖለቲካ ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ ትግራይ ክልል ምርጫውን በክልል ደረጃ ምርጫ ለማካሄድ ጫፍ ደርሷል ይሄኑ መነሻ በማድረግ በአማራ ክልልና በትግራይ ክልል አዋሳኝ በወልቃይትና በራያ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎች ህወሓት የግድ ትምርጣላችሁ በማለት ለእስር፣ድብደባ እና ለአፈና ተዳርገናል ሲሉ አቤቱታቸውን አቅርበዋል።
ተጨማሪ👇👇👇
https://telegra.ph/-09-08-449
የትግራይ ክልል ምርጫውን ለመታዘብ የጠየቀ አንድ ተቋምን ማገዱ ተገለጠ!
«ሰብ ሕድሪ ሲቪል ማሕበረሰብ ትግራይ» የተባለ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀስ ነፃ ተቋም በትግራይ ምርጫ ለመታዘብ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ እንደተደረገበት ገለፀ፡፡
ሰብ ሕድሪ ሲቪል ማሕበረሰብ ትግራይ ያወጣው መግለጫ እንደሚያመለክተው ተቋሙ «ታሪካዊ» ባለው የትግራይ ምርጫ በታዛቢነት ለመሳተፍ 300 ገደማ አባላቱን ለታዛቢነት አዘጋጅቶ ነበር። ቢሆንም የትግራይ ምርጫ ኮምሽን ከሦስተኛ ወገን በቀረበለት ቅሬታ ከታዛቢነት እንዳገደው ዐስታውቋል፡፡ሰብ ሕድሪ ሲቪል ማሕበረሰብ ትግራይ በትግራይ ምርጫ ኮምሽን የተላለፈውን የእግድ ውሳኔ «ተገቢነት የሌለው» ብሎታል፡፡
የትግራይ ምርጫ ኮምሽን በበኩሉ ሲቪል ተቋሙ በምርጫው ከሚወዳደር ፓርቲ ቅሬታ ስለቀረበበት ነገ ይካኼዳል በተባለው ምርጫ ተሳታፊ እንዳይኾን መወሰኑን ገልጧል፡፡ሰብ ሕድሪ ሲቪል ማሕበረሰብ ትግራይ ሰኔ 2010 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን፤ በትግራይ «ዴሞክራታይዜሽን» እና ክብሮች ዙርያ የሚሠራ መሆኑን ይገልጻል፡፡
ይኽ በእንዲህ እንዳለ፦ የትግራይ ምርጫ ኮሚሽን ለ61 የሀገር ውስጥ ተቋማት ምርጫውን እንዲታዘቡ ፍቃድ መስጠቱን ዐስታውቋል፡፡
በትናንትናው እለት አራት ጋዜጠኞችን ጨምሮ የትግራይ ክልል ምርጫን ለመከታተል ወደ መቀሌ በአየር ሊጓዙ የነበሩ ዐሥራ ኹለት ሰዎች በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንደታገዱ ተነግሯል። ከታገዱት መካከል የሀገር ውስጥ እና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች እንደሚገኙበትም ተዘግቧል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
«ሰብ ሕድሪ ሲቪል ማሕበረሰብ ትግራይ» የተባለ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀስ ነፃ ተቋም በትግራይ ምርጫ ለመታዘብ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ እንደተደረገበት ገለፀ፡፡
ሰብ ሕድሪ ሲቪል ማሕበረሰብ ትግራይ ያወጣው መግለጫ እንደሚያመለክተው ተቋሙ «ታሪካዊ» ባለው የትግራይ ምርጫ በታዛቢነት ለመሳተፍ 300 ገደማ አባላቱን ለታዛቢነት አዘጋጅቶ ነበር። ቢሆንም የትግራይ ምርጫ ኮምሽን ከሦስተኛ ወገን በቀረበለት ቅሬታ ከታዛቢነት እንዳገደው ዐስታውቋል፡፡ሰብ ሕድሪ ሲቪል ማሕበረሰብ ትግራይ በትግራይ ምርጫ ኮምሽን የተላለፈውን የእግድ ውሳኔ «ተገቢነት የሌለው» ብሎታል፡፡
የትግራይ ምርጫ ኮምሽን በበኩሉ ሲቪል ተቋሙ በምርጫው ከሚወዳደር ፓርቲ ቅሬታ ስለቀረበበት ነገ ይካኼዳል በተባለው ምርጫ ተሳታፊ እንዳይኾን መወሰኑን ገልጧል፡፡ሰብ ሕድሪ ሲቪል ማሕበረሰብ ትግራይ ሰኔ 2010 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን፤ በትግራይ «ዴሞክራታይዜሽን» እና ክብሮች ዙርያ የሚሠራ መሆኑን ይገልጻል፡፡
ይኽ በእንዲህ እንዳለ፦ የትግራይ ምርጫ ኮሚሽን ለ61 የሀገር ውስጥ ተቋማት ምርጫውን እንዲታዘቡ ፍቃድ መስጠቱን ዐስታውቋል፡፡
በትናንትናው እለት አራት ጋዜጠኞችን ጨምሮ የትግራይ ክልል ምርጫን ለመከታተል ወደ መቀሌ በአየር ሊጓዙ የነበሩ ዐሥራ ኹለት ሰዎች በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንደታገዱ ተነግሯል። ከታገዱት መካከል የሀገር ውስጥ እና የውጭ መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች እንደሚገኙበትም ተዘግቧል።
[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
ብሄራዊ ባንክ ለ15 ተከታታይ አመታት ያልተንቀሳቀሱ ሂሳቦችን ወደ መንግስት እንዲገባ የሚያደርገውን የብሄራዊ ባንክ የባንክ ስራ አዎጅ ማስፈጸሚያ መመሪያ አወጣ!
በመመሪያው መሰረት ከ12 አመት በፊት የወጣውን የባንክ ስራ አዋጅ አንቀፅ 52 ማስፈፀሚያ የሚሆነው መመሪያ በባንኮች ለተከታታይ 15 አመት ያልተንቀሳቀሱ ከ5 ብር ጀምሮ ያሉ ሂሳቦች ወደ ብሄራዊ ባንክ መግባት አለባቸው፡፡ሆኖም ብሄራዊ ባንክ ቢደረግለትም ባለንብረቱ ወይም ህጋዊ ወራሽ ከመጣ ብሄራዊ ባንክ በማንኛውም ጊዜ ወለድን ሳይጨምር ገንዘቡን ይመልሳል፡፡
[Capital]
@YeneTube @FikerAssefa
በመመሪያው መሰረት ከ12 አመት በፊት የወጣውን የባንክ ስራ አዋጅ አንቀፅ 52 ማስፈፀሚያ የሚሆነው መመሪያ በባንኮች ለተከታታይ 15 አመት ያልተንቀሳቀሱ ከ5 ብር ጀምሮ ያሉ ሂሳቦች ወደ ብሄራዊ ባንክ መግባት አለባቸው፡፡ሆኖም ብሄራዊ ባንክ ቢደረግለትም ባለንብረቱ ወይም ህጋዊ ወራሽ ከመጣ ብሄራዊ ባንክ በማንኛውም ጊዜ ወለድን ሳይጨምር ገንዘቡን ይመልሳል፡፡
[Capital]
@YeneTube @FikerAssefa
የትምህርት ቤት ክፍያ ላይ አላስፈላጊ ጭማሪ ያሚደረጉ ትምህርት ቤቶች ላይ እስከ መዝጋት የሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድ ትምህርት ሚኒስቴር አስጠነቀቀ፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር ከተማሪ ወላጆች የሚመጡ ተደጋጋሚ ቅሬታዎችን መሰረት በማድረግ ነው እርምጃ እንደሚወሰድ ይፋ ያደረገው፡፡የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሚሊዮን ማቲዎስ ከቀጣይ አመት ትምህርት ጋር በተያያዘ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ሚኒስትር ዴኤታው የግል ትምህርት ቤቶች ቀድመው ሲሰሩበት ከነበረው የአከፋፈል ስርዓት ውጪ ምንም አይነት ጭማሪ ማድረግ እንማይችሉ አስስበዋል፡፡
ቀድመው ከሚሰሩበት አሰራር ውጭ ተጨማሪ ክፍያ በሚያስከፍሉ ትምህርት ቤቶች ላይ ትምህርት ቤቶቹን እስከ መዝጋት የሚደርስ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችልም ትምህር ሚኒስቴር አስጠንቅቋል፡፡በቀጣይ ትምህርት ሲከፈት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ትምህርት ቤቶች በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20 እስከ 25 ተማሪ ብቻ ለማስተማር የሚያስችላቸውን ዝግጅት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
‹‹የግል ትምህርት ቤቶች ይህንን ለማድረግ አይቸገሩም ወይ?›› ተብለው ከጋዜጠኞች ጥያቄ የተነሳላቸው ሚኒስትር ዴኤታው ሚሊየን ማቲዮስ ቀጣዩ የትምህርት ስርዓት ወደ አዲስ አሰራር የሚሸጋገርበት በመሆኑ ራሳቸውን ለዚህ ዝግጁ ማድረግ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት፡፡የመንግስት ትምህርት ቤቶችም ተመራጭ እንዲሆኑ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ተብራርቷል::ትምህርት ሲጀመር የሚኖረው የትምህርት አሰጣጥ ሂደትም በአንድ ከፍል የሚማሩ የተማሪዎችን ቁጥር የሚወስን ይሆናል፡፡
[MoE]
@YeneTube @FikerAssefa
ትምህርት ሚኒስቴር ከተማሪ ወላጆች የሚመጡ ተደጋጋሚ ቅሬታዎችን መሰረት በማድረግ ነው እርምጃ እንደሚወሰድ ይፋ ያደረገው፡፡የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሚሊዮን ማቲዎስ ከቀጣይ አመት ትምህርት ጋር በተያያዘ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ሚኒስትር ዴኤታው የግል ትምህርት ቤቶች ቀድመው ሲሰሩበት ከነበረው የአከፋፈል ስርዓት ውጪ ምንም አይነት ጭማሪ ማድረግ እንማይችሉ አስስበዋል፡፡
ቀድመው ከሚሰሩበት አሰራር ውጭ ተጨማሪ ክፍያ በሚያስከፍሉ ትምህርት ቤቶች ላይ ትምህርት ቤቶቹን እስከ መዝጋት የሚደርስ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችልም ትምህር ሚኒስቴር አስጠንቅቋል፡፡በቀጣይ ትምህርት ሲከፈት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ትምህርት ቤቶች በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20 እስከ 25 ተማሪ ብቻ ለማስተማር የሚያስችላቸውን ዝግጅት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
‹‹የግል ትምህርት ቤቶች ይህንን ለማድረግ አይቸገሩም ወይ?›› ተብለው ከጋዜጠኞች ጥያቄ የተነሳላቸው ሚኒስትር ዴኤታው ሚሊየን ማቲዮስ ቀጣዩ የትምህርት ስርዓት ወደ አዲስ አሰራር የሚሸጋገርበት በመሆኑ ራሳቸውን ለዚህ ዝግጁ ማድረግ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት፡፡የመንግስት ትምህርት ቤቶችም ተመራጭ እንዲሆኑ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ተብራርቷል::ትምህርት ሲጀመር የሚኖረው የትምህርት አሰጣጥ ሂደትም በአንድ ከፍል የሚማሩ የተማሪዎችን ቁጥር የሚወስን ይሆናል፡፡
[MoE]
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም ባንክ ለ4 የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት አዲስ ዳይሬክተር ሾመ!
የዓለም ባንክ አቶ ኬት ሃንሰንን የኬንያ፣ ርዋንዳ፣ ሶማሊያ እና ኡጋንዳ ዳይሬክተር አድርጎ ሾመ፡፡ልማትን የተመለከቱ የ30 ዓመታት ልምድ ያላቸው ሃንሰን የ13 ቢሊዬን ዶላር ዋጋ ያላቸው እና በ4ቱ የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት የተሚተገበሩ 100 ፕሮጄክቶችን ይመራሉ ተብሏል፡፡ትኩረታቸው በኮሮና ወረርሽኝ ላይ አድርገው ሃገራቱ የጀመሩትን የዘላቂ ልማት ጉዞ እንደሚደግፉም ነው የተገለጸው፡፡ከአሁን ቀደም አፍሪካን ጨምሮ ደቡብ አሜሪካን በመሳሰሉ የተለያዩ ክፍለ አህጉራት በተለያዩ ኃላፊነቶች ያገለገሉት ሃንሰን የባንኩ የሰብዓዊ ልማቶች ምክትል ዳይሬክተር ሆነው ያገለገሉም ሲሆን ዋና ስራ አስፈጻሚውን ያማክሩም እንደነበር የህይወትና የስራ ልምድ ማስረጃዎቻቸው ያሳያሉ፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም ባንክ አቶ ኬት ሃንሰንን የኬንያ፣ ርዋንዳ፣ ሶማሊያ እና ኡጋንዳ ዳይሬክተር አድርጎ ሾመ፡፡ልማትን የተመለከቱ የ30 ዓመታት ልምድ ያላቸው ሃንሰን የ13 ቢሊዬን ዶላር ዋጋ ያላቸው እና በ4ቱ የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት የተሚተገበሩ 100 ፕሮጄክቶችን ይመራሉ ተብሏል፡፡ትኩረታቸው በኮሮና ወረርሽኝ ላይ አድርገው ሃገራቱ የጀመሩትን የዘላቂ ልማት ጉዞ እንደሚደግፉም ነው የተገለጸው፡፡ከአሁን ቀደም አፍሪካን ጨምሮ ደቡብ አሜሪካን በመሳሰሉ የተለያዩ ክፍለ አህጉራት በተለያዩ ኃላፊነቶች ያገለገሉት ሃንሰን የባንኩ የሰብዓዊ ልማቶች ምክትል ዳይሬክተር ሆነው ያገለገሉም ሲሆን ዋና ስራ አስፈጻሚውን ያማክሩም እንደነበር የህይወትና የስራ ልምድ ማስረጃዎቻቸው ያሳያሉ፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa