በአማራ ክልል ለሰላም መስፈን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጠ!
በአማራ ክልል ለሰላም መስፈን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና የመስጠት ስነስርአት በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።በስነስርአቱ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተገኝተዋል።መድረኩ ሁሉም አካል ለሰላም መስፈንና ለህግ የበላይነት መረጋገጥ ቅድሚያ ሰጥቶ እንዲሰራ ለማሳሰብ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ለሰላም መስፈን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና የመስጠት ስነስርአት በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።በስነስርአቱ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተገኝተዋል።መድረኩ ሁሉም አካል ለሰላም መስፈንና ለህግ የበላይነት መረጋገጥ ቅድሚያ ሰጥቶ እንዲሰራ ለማሳሰብ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa
የአሥራት ጋዜጠኞች በዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ወሰነ!
አራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአሥራት ጋዜጠኞች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔ ማስተላለፉን አስራት ሚዲያ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል።ፖሊስ በተደጋጋሚ መረጃ አቀርባለሁ በሚል ቀጠሮ እንዲሰጠው ቢጠይቅም በተሰጠው ቆጠሮ አለኝ ያለውን መረጃ ማቅረብ አልቻለም።በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብር፣ ምስጋናው ከፈለኝ እና ዮናታን ሙሉጌታ በእያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል።
@YeneTube @FikerAssefa
አራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአሥራት ጋዜጠኞች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔ ማስተላለፉን አስራት ሚዲያ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል።ፖሊስ በተደጋጋሚ መረጃ አቀርባለሁ በሚል ቀጠሮ እንዲሰጠው ቢጠይቅም በተሰጠው ቆጠሮ አለኝ ያለውን መረጃ ማቅረብ አልቻለም።በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብር፣ ምስጋናው ከፈለኝ እና ዮናታን ሙሉጌታ በእያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል።
@YeneTube @FikerAssefa
አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ!
በእንቦጭ አረም በመዘጋቱ አገልግሎት ለጊዜው አቋርጦ የነበረው የአዋሽ II የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡የእንቦጭ አረሙ የውሃ መቀየሻ ግድብ ላይ በመተኛቱ የተነሳ የውሃ መቀበያው (water intake) አገልግሎቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡አረሙን ከወንጂ ስኳር ፋብሪካ በተገኘ ኤክስካቫተር የማንሳት ሥራ ሲከናወን ቆይቶ የውሃ መቀበያው በመከፈቱ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከአርብ ነሐሴ 29 ጀምሮ ዳግም ኃይል ማምረት ጀምሯል፡፡32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ1966 ዓ.ም ነበር፡፡
[EEPCo]
@YeneTube @FikerAssefa
በእንቦጭ አረም በመዘጋቱ አገልግሎት ለጊዜው አቋርጦ የነበረው የአዋሽ II የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡የእንቦጭ አረሙ የውሃ መቀየሻ ግድብ ላይ በመተኛቱ የተነሳ የውሃ መቀበያው (water intake) አገልግሎቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡አረሙን ከወንጂ ስኳር ፋብሪካ በተገኘ ኤክስካቫተር የማንሳት ሥራ ሲከናወን ቆይቶ የውሃ መቀበያው በመከፈቱ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከአርብ ነሐሴ 29 ጀምሮ ዳግም ኃይል ማምረት ጀምሯል፡፡32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ1966 ዓ.ም ነበር፡፡
[EEPCo]
@YeneTube @FikerAssefa
የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ለአንድ ቀን ይፋዊ ስራ ጉብኝት ዛሬ ረፋድ አስመራ መግባታቸውን የኤርትራ የመረጃ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል አስታውቀዋል፡፡
አል ቡርሃን እና ልዑካቸው አስመራ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የኤርትራ ባለስልጣናት አቀባበል እንዳደረጉላቸውም ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት፡፡
መሪዎቹ በሁለትዮሽ እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩም ገልጸዋል፡፡ባሳለፍነው ወርሃ ሃምሌ ከፍተኛ የኤርትራ የመከላከያ ኃላፊዎች ወደ ካርቱም አቅንተው ከምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሃምዳን ደገሎ (ሄሜቲ) ጋር መምከራቸው ይታወሳል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
አል ቡርሃን እና ልዑካቸው አስመራ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የኤርትራ ባለስልጣናት አቀባበል እንዳደረጉላቸውም ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት፡፡
መሪዎቹ በሁለትዮሽ እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩም ገልጸዋል፡፡ባሳለፍነው ወርሃ ሃምሌ ከፍተኛ የኤርትራ የመከላከያ ኃላፊዎች ወደ ካርቱም አቅንተው ከምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሃምዳን ደገሎ (ሄሜቲ) ጋር መምከራቸው ይታወሳል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ የኮሮና ቫይረስ መከሰትን ተከትሎ በወጣው የትራንስፖርት አገልግሎት ታሪፍና የመጫን አቅም መመሪያ ላይ ማሻሻያ ተደረገ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ባለስልጣን ማሻሻያውን አስመልክቶ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቷል።በመግለጫውም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሚኒባስ፣ የአንበሳ አውቶብስ፣ ሸገር እና ሀይገር ባሶች በወንበራቸው ልክ እንዲጭኑ ተወስኗል።የሚኒባስ ታክሲዎች ከኋላ ባለው መቀመጫ ከ2 ሰው በላይ መጫን አይችሉም ብሏል ቢሮው በመግለጫው።
እንዲሁም ባለ ሶስት እና ባለ አራት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪዎች እስከ ሹፌሩ 3 ሰው መጫን እንደሚችሉም ነው የተገለፀው።
ቀላል ባቡር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መመሪያ በ25 በመቶ የመጫን አቅም ብቻ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው አሁን ላይ ወደ 75 በመቶ ክፍ እንዲል መደረጉንም አስታውቋል።
ከታሪፍ ጋር በተያያዘም በእጥፍ ሲከፈል የነበረው ቀርቶ መጠነኛ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ባለስልጣኑ አስታውቋል።
በዚህም መሰረት የሚኒባስ ታክሲ ታሪፍ እንደሚከተለው ማስተካከያ ተደርጎበታል።
👉እስከ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 1 ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን ላይ 2 ብር
👉ከ2 ነጥብ 6 እስከ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 3 ብር የነበረው አሁን 4 ብር
👉ከ5 ነጥብ 1 እስከ 7 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 4 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 6 ብር
👉ከ7 ነጥብ 6 እስከ 10 ኪሎ ሜትር በፊት 6 ብር የበረው አሁን 8 ብር
👉ከ10 ነጥብ 1 እስከ 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር 7 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 10 ብር
👉ከ12 ነጥብ 6 እስከ 15 ኪሎ ሜትር በፊት 9 ብር የነበረው አሁን 12 ብር
👉ከ15 ነጥብ 1 እስከ 17 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 10 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 13 ብር
👉ከ17 ነጥብ 6 እስከ 20 ኪሎ ሜትር በፊት 12 ብር የነበረው አሁን 15 ብር
👉ከ20 ነጥብ 1 እስከ 22 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 13 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 17 ብር
👉ከ22 ነጥብ 6 እስከ 25 ኪሎ ሜትር በፊት 15 ብር የነበረው አሁን 19 ብር
👉ከ25 ነጥብ 1 እስከ እስከ 27 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 16 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 20 ብር
👉ከ27 ነጥብ 6 እስከ 30 ኪሎ ሜትር በፊት 18 የነበረው አሁን 22 ብር ሆኖ ማሻሻያ መደረጉንም የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ባለስልጣን በመግለጫው አመላክቷል።
ከተፈቀደው ሰው በላይ መጫን ከ1 ሺህ ብር ጀምሮ ከታሪፍ በላይ ማስከፈል 1 ሺህ 500 ብር ጀምሮ እንደሚያስቀጣም ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ይህንን ለመቆጣጠር ከትራፊክ ፖሊስ በዘለለ የፖሊስና የፀጥታ አካላት መሰማራታቸው የተገለፀ ሲሆን፥ ህብረተሰቡ ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ እና ትርፍ የሚጭኑትን ለመጠቆም የሚጠቁምበት የስክል ቁጥር በቅርቡ ይፋ ይሆናል ብሏል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ባለስልጣን ማሻሻያውን አስመልክቶ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቷል።በመግለጫውም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሚኒባስ፣ የአንበሳ አውቶብስ፣ ሸገር እና ሀይገር ባሶች በወንበራቸው ልክ እንዲጭኑ ተወስኗል።የሚኒባስ ታክሲዎች ከኋላ ባለው መቀመጫ ከ2 ሰው በላይ መጫን አይችሉም ብሏል ቢሮው በመግለጫው።
እንዲሁም ባለ ሶስት እና ባለ አራት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪዎች እስከ ሹፌሩ 3 ሰው መጫን እንደሚችሉም ነው የተገለፀው።
ቀላል ባቡር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መመሪያ በ25 በመቶ የመጫን አቅም ብቻ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው አሁን ላይ ወደ 75 በመቶ ክፍ እንዲል መደረጉንም አስታውቋል።
ከታሪፍ ጋር በተያያዘም በእጥፍ ሲከፈል የነበረው ቀርቶ መጠነኛ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ባለስልጣኑ አስታውቋል።
በዚህም መሰረት የሚኒባስ ታክሲ ታሪፍ እንደሚከተለው ማስተካከያ ተደርጎበታል።
👉እስከ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 1 ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን ላይ 2 ብር
👉ከ2 ነጥብ 6 እስከ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 3 ብር የነበረው አሁን 4 ብር
👉ከ5 ነጥብ 1 እስከ 7 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 4 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 6 ብር
👉ከ7 ነጥብ 6 እስከ 10 ኪሎ ሜትር በፊት 6 ብር የበረው አሁን 8 ብር
👉ከ10 ነጥብ 1 እስከ 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር 7 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 10 ብር
👉ከ12 ነጥብ 6 እስከ 15 ኪሎ ሜትር በፊት 9 ብር የነበረው አሁን 12 ብር
👉ከ15 ነጥብ 1 እስከ 17 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 10 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 13 ብር
👉ከ17 ነጥብ 6 እስከ 20 ኪሎ ሜትር በፊት 12 ብር የነበረው አሁን 15 ብር
👉ከ20 ነጥብ 1 እስከ 22 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 13 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 17 ብር
👉ከ22 ነጥብ 6 እስከ 25 ኪሎ ሜትር በፊት 15 ብር የነበረው አሁን 19 ብር
👉ከ25 ነጥብ 1 እስከ እስከ 27 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 16 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 20 ብር
👉ከ27 ነጥብ 6 እስከ 30 ኪሎ ሜትር በፊት 18 የነበረው አሁን 22 ብር ሆኖ ማሻሻያ መደረጉንም የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ባለስልጣን በመግለጫው አመላክቷል።
ከተፈቀደው ሰው በላይ መጫን ከ1 ሺህ ብር ጀምሮ ከታሪፍ በላይ ማስከፈል 1 ሺህ 500 ብር ጀምሮ እንደሚያስቀጣም ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ይህንን ለመቆጣጠር ከትራፊክ ፖሊስ በዘለለ የፖሊስና የፀጥታ አካላት መሰማራታቸው የተገለፀ ሲሆን፥ ህብረተሰቡ ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ እና ትርፍ የሚጭኑትን ለመጠቆም የሚጠቁምበት የስክል ቁጥር በቅርቡ ይፋ ይሆናል ብሏል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ለብሉምበርግ፣ ኒውዮርክ ታይምስ እና ቪኦኤ እንግሊዘኛ የሚፅፈው ፍሪላንስ ጋዜጠኛ ሳይመን ማርክስ እና ሌሎች አስር ገደማ ሰዎች ወደ መቐለ ለመሄድ ቦሌ አየር ማረፊያ ቢገኙም በፀጥታ አካላት እንዳይጓዙ እንደታገዱ የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል።ሳይመን ወደ መቐለ ሊጓዝ የነበረው ምርጫውን ለመዘገብ እንደነበር መረጃው ያመለክታል።
Via Elias Meseret
@YeneTube @FikerAssefa
Via Elias Meseret
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
በአማራ ክልል ለሰላም መስፈን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጠ! በአማራ ክልል ለሰላም መስፈን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና የመስጠት ስነስርአት በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።በስነስርአቱ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተገኝተዋል።መድረኩ…
የአማራ ክልልን ሰላም በማስከበር የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የፖሊስ አካላት የማዕረግ ሽልማት ከተለያዩ የፌዴራልና የክልል የስራ ኃላፊዎች በተገኙ ተከናውኗል።
ማዕረግ የተሰጣቸው!
አምስት የምክትል ኮሚሽነርነት
አስራ ሶስት የረዳት ኮሚሽነርነት
ሁለት የኮማንደርነት
ሶስት የምክትል ኮማንደርነት
አንድ የዋና ኢንስፔክተርነት
ሁለት የረዳት ኢንስፔክተርነት ማዕረግ ሽልማት ተሰጥቷል።
[አማራ ፓሊስ ኮሚሽን]
@YeneTube @FikerAssefa
ማዕረግ የተሰጣቸው!
አምስት የምክትል ኮሚሽነርነት
አስራ ሶስት የረዳት ኮሚሽነርነት
ሁለት የኮማንደርነት
ሶስት የምክትል ኮማንደርነት
አንድ የዋና ኢንስፔክተርነት
ሁለት የረዳት ኢንስፔክተርነት ማዕረግ ሽልማት ተሰጥቷል።
[አማራ ፓሊስ ኮሚሽን]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የቤት መኪኖች በወንበር ልክ መጫን እንደሚችሉ አስታወቀ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ የኮሮና ቫይረስ መከሰትን ተከትሎ በወጣው የትራንስፖርት አገልግሎት ታሪፍና የመጫን አቅም መመሪያ ላይ በተደረገው ማሻሻያ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሚኒባስ፣ የአንበሳ አውቶብስ፣ ሸገር እና ሀይገር ባሶች በወንበራቸው ልክ እንዲጭኑ መወሰኑ ይታወቃል፡፡የቤት መኪኖችን እንዲሁም የሜትር ታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ተሸርካሪዎችን በሚመለከት ግን በማሻሻያው ላይ የተጠቀሰ ነገር ባመኖሩ ኢትዮ ኤፍ ኤም በዚሁ ጉዳይ ላይ ቢሮውን ጠይቋል፡፡
የቢሮው የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ አቶ አረጋዊ ማሩ እንዳሉት የቤት መኪኖች እንዲሁም የሜትር ታክሲ አገልግሎት ሰጪዎችም በወንበር ልክ እንዲጭኑ መወሰኑን ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ቀደም የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመቀነስ በሚል የቤት መኪኖች ከሹፌሩ ውጪ መጫን ከሚችሉት የሰው ቁጥር በግማሽ ቀንሰው ይጭኑ እንደነበር ይታወሳል፡፡እንዲሁም ባለ ሶስት እና ባለ አራት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪዎች እስከ ሹፌሩ 3 ሰው መጫን እንደሚችሉም ተነግሯል።ቀላል ባቡር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መመሪያ በ25 በመቶ የመጫን አቅም ብቻ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው አሁን ላይ ወደ 75 በመቶ ከፍ እንዲል መደረጉንም አስታውቋል።
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ የኮሮና ቫይረስ መከሰትን ተከትሎ በወጣው የትራንስፖርት አገልግሎት ታሪፍና የመጫን አቅም መመሪያ ላይ በተደረገው ማሻሻያ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሚኒባስ፣ የአንበሳ አውቶብስ፣ ሸገር እና ሀይገር ባሶች በወንበራቸው ልክ እንዲጭኑ መወሰኑ ይታወቃል፡፡የቤት መኪኖችን እንዲሁም የሜትር ታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ተሸርካሪዎችን በሚመለከት ግን በማሻሻያው ላይ የተጠቀሰ ነገር ባመኖሩ ኢትዮ ኤፍ ኤም በዚሁ ጉዳይ ላይ ቢሮውን ጠይቋል፡፡
የቢሮው የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ አቶ አረጋዊ ማሩ እንዳሉት የቤት መኪኖች እንዲሁም የሜትር ታክሲ አገልግሎት ሰጪዎችም በወንበር ልክ እንዲጭኑ መወሰኑን ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ቀደም የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመቀነስ በሚል የቤት መኪኖች ከሹፌሩ ውጪ መጫን ከሚችሉት የሰው ቁጥር በግማሽ ቀንሰው ይጭኑ እንደነበር ይታወሳል፡፡እንዲሁም ባለ ሶስት እና ባለ አራት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪዎች እስከ ሹፌሩ 3 ሰው መጫን እንደሚችሉም ተነግሯል።ቀላል ባቡር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መመሪያ በ25 በመቶ የመጫን አቅም ብቻ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው አሁን ላይ ወደ 75 በመቶ ከፍ እንዲል መደረጉንም አስታውቋል።
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
ለብሉምበርግ፣ ኒውዮርክ ታይምስ እና ቪኦኤ እንግሊዘኛ የሚፅፈው ፍሪላንስ ጋዜጠኛ ሳይመን ማርክስ እና ሌሎች አስር ገደማ ሰዎች ወደ መቐለ ለመሄድ ቦሌ አየር ማረፊያ ቢገኙም በፀጥታ አካላት እንዳይጓዙ እንደታገዱ የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል።ሳይመን ወደ መቐለ ሊጓዝ የነበረው ምርጫውን ለመዘገብ እንደነበር መረጃው ያመለክታል። Via Elias Meseret @YeneTube @FikerAssefa
#Update
ከምርጫው ጋር ለተያያዘ ሥራ በአውሮፕላን ሊጓዙ የነበሩት ጋዜጠኞች ቁጥራቸው ከ10 በላይ እንደሆነም የተነገረ ሲሆን፤ በበረራ መርሃ ግብራቸው መሰረት ወደ አውሮፕላን ከገቡ በኋላ ከአውሮፕላኑ እንዲወርዱ መደረጉ ተገልጿል።
ከጋዜጠኞቹ መካከል አንዱ የሆነው ለብሉምበርግና ለአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ የሚሰራው ሳይመን ማርክስ "የተወሰንን ሰዎችን መታወቂያ ካርድ ከተመለከቱ በኋላ ተሳፍረንበት ከነበረው አውሮፕላን ተገደን እንድንወርድ ተደርገናል" በማለት ለቢቢሲ ተናግሯል።
ዛሬ ረፋድ ላይ ወደ መቀለ ሊጓዝ በነበረው አውሮፕላን ውስጥ ሰላሳ የሚደርሱ መንገደኞች የነበሩ ሲሆን የአውሮፕላን ማረፊያው የደኅንነት ሠራተኞች የተሳፋሪዎቹን መታወቂያ ከተመለከቱ በኋላ ተጓዦቹ እንዲወርዱ ማደረጋቸውን አንድ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ተሳፋሪ ገልጸዋል።ቢቢሲ ያናገራቸው አንድ ተጓዥ እንዳሉት ደግሞ የጸጥታ ሠራተኞቹ የመንገደኞቹ ሞባይል እና ላፕቶፕ ሲቀበሉ መመልከታቸውን ተናግረው በረራውም ሳይሰረዝ እንዳልቀረ ገልጸዋል።ወደ መቀለ እንዳይጓዙ ከተደረጉ ተሳፋሪዎች መካከል የዓለም አቀፉ የቀውስ ጉዳዮች አጥኚ ተቋም የኢትዮጵያ ተመራማሪ የሆነው ዊሊያም ዳቪሰንም እንዳለበት ቢቢሲ አረጋግጧል።
ሮይተርስ ወደ መቀሌ ለማምራት በዝግጅት ላይ የነበረው አውሮፕላን ውስጥ የነበሩ መንገደኞች ነገሩኝ ብሎ እንደዘገበው ከሆነ አራት ጋዜጠኞችን ጨምሮ 12 የሚሆኑ ሰዎች ወደ መቀሌ በረራ ለማድረግ ከተዘጋጀው አውሮፕላን ውስጥ እንዲወርዱ ተደርገዋል።የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን ተከትሎ አንዳንድ የመገናኛ ብዙሃንና ጋዜጠኞች በትግራይ የሚካሄደውን ምርጫ እንዳንዘግብ ጫና እየደረሰብን ነው ያሉ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዳይሬክተር ጌታቸው ደንቁ (ዶ/ር) ለድምጸ ወያኔ እንዲህ አይነት ነገር እንደሌለ ባለፈው ቅዳሜ ተናግረው ነበር።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ከምርጫው ጋር ለተያያዘ ሥራ በአውሮፕላን ሊጓዙ የነበሩት ጋዜጠኞች ቁጥራቸው ከ10 በላይ እንደሆነም የተነገረ ሲሆን፤ በበረራ መርሃ ግብራቸው መሰረት ወደ አውሮፕላን ከገቡ በኋላ ከአውሮፕላኑ እንዲወርዱ መደረጉ ተገልጿል።
ከጋዜጠኞቹ መካከል አንዱ የሆነው ለብሉምበርግና ለአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ የሚሰራው ሳይመን ማርክስ "የተወሰንን ሰዎችን መታወቂያ ካርድ ከተመለከቱ በኋላ ተሳፍረንበት ከነበረው አውሮፕላን ተገደን እንድንወርድ ተደርገናል" በማለት ለቢቢሲ ተናግሯል።
ዛሬ ረፋድ ላይ ወደ መቀለ ሊጓዝ በነበረው አውሮፕላን ውስጥ ሰላሳ የሚደርሱ መንገደኞች የነበሩ ሲሆን የአውሮፕላን ማረፊያው የደኅንነት ሠራተኞች የተሳፋሪዎቹን መታወቂያ ከተመለከቱ በኋላ ተጓዦቹ እንዲወርዱ ማደረጋቸውን አንድ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ተሳፋሪ ገልጸዋል።ቢቢሲ ያናገራቸው አንድ ተጓዥ እንዳሉት ደግሞ የጸጥታ ሠራተኞቹ የመንገደኞቹ ሞባይል እና ላፕቶፕ ሲቀበሉ መመልከታቸውን ተናግረው በረራውም ሳይሰረዝ እንዳልቀረ ገልጸዋል።ወደ መቀለ እንዳይጓዙ ከተደረጉ ተሳፋሪዎች መካከል የዓለም አቀፉ የቀውስ ጉዳዮች አጥኚ ተቋም የኢትዮጵያ ተመራማሪ የሆነው ዊሊያም ዳቪሰንም እንዳለበት ቢቢሲ አረጋግጧል።
ሮይተርስ ወደ መቀሌ ለማምራት በዝግጅት ላይ የነበረው አውሮፕላን ውስጥ የነበሩ መንገደኞች ነገሩኝ ብሎ እንደዘገበው ከሆነ አራት ጋዜጠኞችን ጨምሮ 12 የሚሆኑ ሰዎች ወደ መቀሌ በረራ ለማድረግ ከተዘጋጀው አውሮፕላን ውስጥ እንዲወርዱ ተደርገዋል።የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን ተከትሎ አንዳንድ የመገናኛ ብዙሃንና ጋዜጠኞች በትግራይ የሚካሄደውን ምርጫ እንዳንዘግብ ጫና እየደረሰብን ነው ያሉ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዳይሬክተር ጌታቸው ደንቁ (ዶ/ር) ለድምጸ ወያኔ እንዲህ አይነት ነገር እንደሌለ ባለፈው ቅዳሜ ተናግረው ነበር።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
መንግሥት በንፁሃን ዜጎች ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ወንጀል የሚዘክር ቋሚ መታሰቢያ እንዲያቆም አብን ጠየቀ።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አብን በአገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል።ንቅናቄው በመግለጫው እንዳስታወቀው የአገሪቱ የዲሞክራሲ እና የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሰ መምጣቱንም አስታውቋል።በአጠቃላይ አብን በጥናቴ አረጋግጫቸዋለሁ መንግስትም በቀጣይ የማስተካከያ እርምጃዎችን ሊወስድባቸው ይገባል ያላቸውን ጉዳዮች በዝርዝር አስቀምጧል።
በኦሮሚያ ክልል የተደረገው "የዘር ማጥፋት" ተገቢውን ትኩረት ያለማግኘቱና ችግሩን በአጭር ጊዜም ይሁን በዘለቄታ ለመፍታት የሚታየው ዳተኝነት ፓርቲውን ክፉኛ እንደሚያሳስበውም ገልጿል። በመሆኑም
ሀ) የተፈፀመው ወንጀል "የዘር ማጥፋት" መሆኑ ታምኖበት በስሙ እንዲጠራና ለተፈፀመው ወንጀልም ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠየቅ፤
ለ) መንግሥት የተፈፀመውን "የዘር ፍጅት" የሚያጣራና የሚመረምር ልዩ የምርመራ ኮሚሽንና አቃቤ ሕግ ጽ/ቤት እንዲያቋቁምና ወንጀለኞች የሚዳኙበት ልዩ ችሎት እንዲሰይም፤
ሐ) መንግሥት በንፁሃን ዜጎች ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ወንጀል የሚዘክር ቋሚ መታሰቢያ እንዲያቆም፤
መ) ችግሩን በዘለቄታ ለመፍታት በክልሉ በሚኖሩ የተለያዩ ማህበረሰቦችና ህዝቦች መካከል የእርቅና የመግባባት ስራዎች እንዲጀመሩ እንዲሁም የኦሮሚያ ክልልም በክልሉ ለሚኖሩ ኦሮሞ ያልሆኑ ማህበረሰቦችና ህዝቦች ሰብአዊና ህገ መንግሥታዊ መብቶቻቸው የሚከበሩበት ዋስትና እንዲሰጥ ንቅናቄው ጠይቋል።
Via Ethio FM
ሙሉ መግለጫው 👇👇👇
https://telegra.ph/-09-07-523
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አብን በአገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል።ንቅናቄው በመግለጫው እንዳስታወቀው የአገሪቱ የዲሞክራሲ እና የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሰ መምጣቱንም አስታውቋል።በአጠቃላይ አብን በጥናቴ አረጋግጫቸዋለሁ መንግስትም በቀጣይ የማስተካከያ እርምጃዎችን ሊወስድባቸው ይገባል ያላቸውን ጉዳዮች በዝርዝር አስቀምጧል።
በኦሮሚያ ክልል የተደረገው "የዘር ማጥፋት" ተገቢውን ትኩረት ያለማግኘቱና ችግሩን በአጭር ጊዜም ይሁን በዘለቄታ ለመፍታት የሚታየው ዳተኝነት ፓርቲውን ክፉኛ እንደሚያሳስበውም ገልጿል። በመሆኑም
ሀ) የተፈፀመው ወንጀል "የዘር ማጥፋት" መሆኑ ታምኖበት በስሙ እንዲጠራና ለተፈፀመው ወንጀልም ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠየቅ፤
ለ) መንግሥት የተፈፀመውን "የዘር ፍጅት" የሚያጣራና የሚመረምር ልዩ የምርመራ ኮሚሽንና አቃቤ ሕግ ጽ/ቤት እንዲያቋቁምና ወንጀለኞች የሚዳኙበት ልዩ ችሎት እንዲሰይም፤
ሐ) መንግሥት በንፁሃን ዜጎች ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ወንጀል የሚዘክር ቋሚ መታሰቢያ እንዲያቆም፤
መ) ችግሩን በዘለቄታ ለመፍታት በክልሉ በሚኖሩ የተለያዩ ማህበረሰቦችና ህዝቦች መካከል የእርቅና የመግባባት ስራዎች እንዲጀመሩ እንዲሁም የኦሮሚያ ክልልም በክልሉ ለሚኖሩ ኦሮሞ ያልሆኑ ማህበረሰቦችና ህዝቦች ሰብአዊና ህገ መንግሥታዊ መብቶቻቸው የሚከበሩበት ዋስትና እንዲሰጥ ንቅናቄው ጠይቋል።
Via Ethio FM
ሙሉ መግለጫው 👇👇👇
https://telegra.ph/-09-07-523
ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋርን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ እስከ መስከረም 8 2013 ዓ.ም ክስ እንዲመሰርት ብይን ሰጠ!
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቶ ጃዋር መሃመድና በቀለ ገርባን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ እስከ መስከረም 8 2013 ዓ.ም ክስ እንዲመሰርት ብይን ሰጠ።ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋር መሃመድና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ ከጳጉሜ 2 እስከ ጳጉሜ 5 2012 ዓ.ም የተሰሙ የምስክር ቃል ተገልብጦ ወስዶ እስከ መስከረም 8 ቀን 2013 ዓ.ም ክስ አንዲመሰርት ነው ብይን የሰጠው።
በተጨማሪም ፍርድ ቤቱ ሌሎች ከ11ኛ እስከ 14ኛ ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ደግሞ በ5 ቀን ውስጥ ክስ እንዲመሰርትባቸውም ትእዛዝ ሰጥቷል።ፍርድ ቤቱ በዛሬ ውሎው ተጠርጣሪዎቹ ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ትእዛዝ ሳይሰጥ፤ ተጠርጣሪዎቹ በማረፊያ ቤት አንዲቆዩ በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 93 መሰረት ትእዛዝ ሰጥቷል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቶ ጃዋር መሃመድና በቀለ ገርባን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ እስከ መስከረም 8 2013 ዓ.ም ክስ እንዲመሰርት ብይን ሰጠ።ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋር መሃመድና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ ከጳጉሜ 2 እስከ ጳጉሜ 5 2012 ዓ.ም የተሰሙ የምስክር ቃል ተገልብጦ ወስዶ እስከ መስከረም 8 ቀን 2013 ዓ.ም ክስ አንዲመሰርት ነው ብይን የሰጠው።
በተጨማሪም ፍርድ ቤቱ ሌሎች ከ11ኛ እስከ 14ኛ ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ደግሞ በ5 ቀን ውስጥ ክስ እንዲመሰርትባቸውም ትእዛዝ ሰጥቷል።ፍርድ ቤቱ በዛሬ ውሎው ተጠርጣሪዎቹ ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ትእዛዝ ሳይሰጥ፤ ተጠርጣሪዎቹ በማረፊያ ቤት አንዲቆዩ በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 93 መሰረት ትእዛዝ ሰጥቷል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ማስክ ሳያደርግ ታክሲ ውስጥ የተገኘ ሰው 500 ብር እንደሚቀጣ ተገለፀ!
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ የኮሮና ቫይረስ መከሰትን ተከትሎ በወጣው የትራንስፖርት አገልግሎት መመሪያ ላይ ተሳፋሪዎች ማስክ ሳያደርጉ ትራንሰፖርት መጠቀም እንደማይችሉ ቢከለክልም ባላደረጉት ላይ ያስቀመጠው የቅጣት መጠን አለመኖሩ ይታወሳል፡፡በመመሪያው ላይ ዛሬ በተደረገው ማሻሻያም የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ወይም ማስክ በማያደርጉ ተሳፋሪዎች ላይ የ500 ብር ቅጣት መጣሉን የቢሮው የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ አቶ አረጋዊ ማሩ ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ማስክ ያላደረጉ ተሳፋሪዎችን የጫነ አሽከርካሪና ረዳት ላይም እያንዳንዳቸው 1 ሺ ብር እንዲቀጡ መወሰኑን አቶ አረጋዊ ተናግረዋል፡፡ከዚህ ቀደም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የተጣለው የምሽት 2 ሰዓት ገደብ ከተነሳ የቆየ ቢሆንም አሁንም ተሳፋሪዎች እንዲሁም አሽርካሪዎች ላይ ብዥታ ተፈጥሯል፡፡ይህንንም ተከትሎ ትራንስፖርት ሰጪዎች ላይ ተጥሎ የነበረው የሰዓት ገደብ ከተነሳ መቆየቱን እና ይህ ብዥታ ሊኖር እንደማይገባ አክለው ተናግረዋል፣ ዘገባው የኢትዮ ኤፍ ኤም ነው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ የኮሮና ቫይረስ መከሰትን ተከትሎ በወጣው የትራንስፖርት አገልግሎት መመሪያ ላይ ተሳፋሪዎች ማስክ ሳያደርጉ ትራንሰፖርት መጠቀም እንደማይችሉ ቢከለክልም ባላደረጉት ላይ ያስቀመጠው የቅጣት መጠን አለመኖሩ ይታወሳል፡፡በመመሪያው ላይ ዛሬ በተደረገው ማሻሻያም የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ወይም ማስክ በማያደርጉ ተሳፋሪዎች ላይ የ500 ብር ቅጣት መጣሉን የቢሮው የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ አቶ አረጋዊ ማሩ ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ማስክ ያላደረጉ ተሳፋሪዎችን የጫነ አሽከርካሪና ረዳት ላይም እያንዳንዳቸው 1 ሺ ብር እንዲቀጡ መወሰኑን አቶ አረጋዊ ተናግረዋል፡፡ከዚህ ቀደም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የተጣለው የምሽት 2 ሰዓት ገደብ ከተነሳ የቆየ ቢሆንም አሁንም ተሳፋሪዎች እንዲሁም አሽርካሪዎች ላይ ብዥታ ተፈጥሯል፡፡ይህንንም ተከትሎ ትራንስፖርት ሰጪዎች ላይ ተጥሎ የነበረው የሰዓት ገደብ ከተነሳ መቆየቱን እና ይህ ብዥታ ሊኖር እንደማይገባ አክለው ተናግረዋል፣ ዘገባው የኢትዮ ኤፍ ኤም ነው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
የፌዴሬሽን ምክር ቤት በትግራይ ክልል ምርጫ ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ ህገ-ወጥ እና የክልሉ ህዝብም ሆነ መንግስት የማይቀበለው መሆኑን የትግራይ ክልል አስታወቀ፡፡
የትግራይ ክልል የመንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊያ ካሳ ለአሀዱ እንዳስታወቁት የክልሉ መንግስት እያካሄደ ያለው ምርጫ የህዝብ ውሳኔ የታከለበት እና ህገ-መንግስታዊ ስርዓትን የተከተለ ነው ብለዋል፡፡የምርጫው ባለቤት የትግራይ ህዝብ ነው ያሉት ወይዘሮ ሊያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ያስተላለፈው ውሳኔ የትግራይን ህዝብ ያስቆጣ እና ኢ-ህገ-መንግስታዊ ነው ብለውታል፡፡የፌዴሬሽን ምክር ቤት አገሪቱን የሚበታትን እንጅ ለህዝብ የሚጠቅም ውሳኔ ወስኗል ብለው እንደማያምኑም ነው ወይዘሮ ሊያ ያስታወቁት፡፡
[አሐዱ ሬዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ክልል የመንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊያ ካሳ ለአሀዱ እንዳስታወቁት የክልሉ መንግስት እያካሄደ ያለው ምርጫ የህዝብ ውሳኔ የታከለበት እና ህገ-መንግስታዊ ስርዓትን የተከተለ ነው ብለዋል፡፡የምርጫው ባለቤት የትግራይ ህዝብ ነው ያሉት ወይዘሮ ሊያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ያስተላለፈው ውሳኔ የትግራይን ህዝብ ያስቆጣ እና ኢ-ህገ-መንግስታዊ ነው ብለውታል፡፡የፌዴሬሽን ምክር ቤት አገሪቱን የሚበታትን እንጅ ለህዝብ የሚጠቅም ውሳኔ ወስኗል ብለው እንደማያምኑም ነው ወይዘሮ ሊያ ያስታወቁት፡፡
[አሐዱ ሬዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
የማስጠንቀቂያ መልክቶች ሰሚ ባለማግኘታቸው የሰው ህይወት እየጠፋና ንብረት እየወደመ ነው ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
በተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶች ሊከሰቱባቸው የሚችሉ ቦታዎችን በመለየት ግጭቶች ተከስተው በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ቀድመን በተደጋጋሚ ብናሳውቅም በመንግስት በኩል ትኩረት እየተሰጠው አይደለም ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ገልጿል፡፡
ኮሚሽኑ ከመንግስትም ሆነ ከህብረተሰቡ ሳይወግን የሚሰራ እንደመሆኑ መረጃዎችን አጥንቶ በሚያሳውቅበት ወቅት በመንግስት በኩል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጊዜያዊ አስተባባሪ አቶ በለጠ ይልማ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
ከሶስት ሳምንታት በፊት በወላይታ ሶዶና በዞኑ ባሉ አንዳንድ ከተሞች ተከስተው የነበሩ ግጭቶችን ለመገምገም ኮሚሽኑ በቦታው በመገኘት ከመንግስት አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ሙሉ መረጃዎችን አሰባስቦ ጨርሷል፡፡ሙሉ ሪፖርቱን በሚቀጥሉት 3 ቀናት ውስጥ እንደሚያሳውቁ አቶ በለጠ አስታውቀዋል፡፡
[አሐዱ ሬዲዮ 94.3]
@YeneTube @FikerAssefa
በተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶች ሊከሰቱባቸው የሚችሉ ቦታዎችን በመለየት ግጭቶች ተከስተው በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ቀድመን በተደጋጋሚ ብናሳውቅም በመንግስት በኩል ትኩረት እየተሰጠው አይደለም ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ገልጿል፡፡
ኮሚሽኑ ከመንግስትም ሆነ ከህብረተሰቡ ሳይወግን የሚሰራ እንደመሆኑ መረጃዎችን አጥንቶ በሚያሳውቅበት ወቅት በመንግስት በኩል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጊዜያዊ አስተባባሪ አቶ በለጠ ይልማ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
ከሶስት ሳምንታት በፊት በወላይታ ሶዶና በዞኑ ባሉ አንዳንድ ከተሞች ተከስተው የነበሩ ግጭቶችን ለመገምገም ኮሚሽኑ በቦታው በመገኘት ከመንግስት አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ሙሉ መረጃዎችን አሰባስቦ ጨርሷል፡፡ሙሉ ሪፖርቱን በሚቀጥሉት 3 ቀናት ውስጥ እንደሚያሳውቁ አቶ በለጠ አስታውቀዋል፡፡
[አሐዱ ሬዲዮ 94.3]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የጋዜጠኞች የጉዞ ክልከላን በተመለከተ “መረጃ አልነበረኝም” አለ
ከነገ በስቲያ በትግራይ የሚካሄደውን ምርጫን ለመዘገብ፤ ዛሬ ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበሩ ጋዜጠኞች ከአውሮፕላን ጣቢያ እንዲመለሱ መደረጉን በተመለከተ ቅድሚያ መረጃ እንዳልነበረው እና ጉዳዩን እንደሚያጣራ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጸ። የጉዞ እገዳ የተደረገባቸው ጋዜጠኞች መታወቂያቸው፣ የተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው፣ ላፕቶፖቻቸው፣ ካሜራዎች እና ሌሎች የስራ ዕቃዎቻቸው መወሰዳቸውን በጸጥታ ኃይሎች እንደተወሰዱባቸው ተናግረዋል።
ጋዜጠኞቹ እና ሌሎች መንገደኞች ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበረው ዛሬ ከቀኑ አምስት ሰዓት ላይ ነበር። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ መንገደኛ እንደተናገሩት የአየር ማረፊያ የጸጥታ ሰዎች ከወትሮው በተለየ ለውጭ ሀገር ዜጎች ጥያቄ ሲያቀርቡ ነበር። በኢትዮጵያ የኒው ዮርክ ታይምስ ዘጋቢ የሆነው ሳይመን ማርክስ በተለይ በርካታ ጥያቄዎች ሲቀርቡለት እንደነበር ማየታቸውን ተናግረዋል።
Via Ethiopia insider
@YeneTube @FikerAssefa
ከነገ በስቲያ በትግራይ የሚካሄደውን ምርጫን ለመዘገብ፤ ዛሬ ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበሩ ጋዜጠኞች ከአውሮፕላን ጣቢያ እንዲመለሱ መደረጉን በተመለከተ ቅድሚያ መረጃ እንዳልነበረው እና ጉዳዩን እንደሚያጣራ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጸ። የጉዞ እገዳ የተደረገባቸው ጋዜጠኞች መታወቂያቸው፣ የተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው፣ ላፕቶፖቻቸው፣ ካሜራዎች እና ሌሎች የስራ ዕቃዎቻቸው መወሰዳቸውን በጸጥታ ኃይሎች እንደተወሰዱባቸው ተናግረዋል።
ጋዜጠኞቹ እና ሌሎች መንገደኞች ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበረው ዛሬ ከቀኑ አምስት ሰዓት ላይ ነበር። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ መንገደኛ እንደተናገሩት የአየር ማረፊያ የጸጥታ ሰዎች ከወትሮው በተለየ ለውጭ ሀገር ዜጎች ጥያቄ ሲያቀርቡ ነበር። በኢትዮጵያ የኒው ዮርክ ታይምስ ዘጋቢ የሆነው ሳይመን ማርክስ በተለይ በርካታ ጥያቄዎች ሲቀርቡለት እንደነበር ማየታቸውን ተናግረዋል።
Via Ethiopia insider
@YeneTube @FikerAssefa
በድርድርና ሽምግልና የሚለቀቅ ተጠርጣሪ አይኖርም- ጠ/ዐቃቤ ህግ
በድርድርና ሽምግልና የሚለቀቅ ተጠርጣሪ አይኖርም ሲል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታወቀ።ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ፍቃዱ ጸጋ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ በመግለጫቸው ወንጀልን በሽምግልና የምንፈታበት ህግም ስልጣንም የለንም ነው ያሉት።በአደባባይ ሰው የገደሉና ውድመት እንዲፈጠር ያደረጉ ተጠርጣሪዎች ሳንመረምር አናስርም የሚል የለም ማስረጃውን መዝኖ ለህግ የማቅረብ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
በመግለጫቸው የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን በመፈጸምና ግድያውን ተከትሎ በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ ተብሎ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ክስ እንደሚመሰረት አስታውቀዋል።
በሰጡት መግለጫ ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ቀጥታ ተሳትፎ የነበራቸውንና አብራው በነበረችው ግለሰብ ፣ በእነ አቶ ጃዋር መሀመድ መዝገብና በእነ አቶ እስክንድር ነጋ መዝገብ ላይ እስከ ፊታችን ሀሙስ ድረስ ክስ እንደሚመሰረት ገልፀዋል።በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ያሉት በአብዛኞቹ ላይ ምርመራው ተጠናቋል ተብሏል።አቶ ፍቃዱ ጸጋ በመግለጫው ላይ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ያለውን አቅም ተጠቅሞ ጥፋተኞችን ለፍትህ የማቅረብ ሂደት በሻለ ሁኔታ ተፈጻሚ እየሆነ ነው ብለዋል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በድርድርና ሽምግልና የሚለቀቅ ተጠርጣሪ አይኖርም ሲል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታወቀ።ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ፍቃዱ ጸጋ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ በመግለጫቸው ወንጀልን በሽምግልና የምንፈታበት ህግም ስልጣንም የለንም ነው ያሉት።በአደባባይ ሰው የገደሉና ውድመት እንዲፈጠር ያደረጉ ተጠርጣሪዎች ሳንመረምር አናስርም የሚል የለም ማስረጃውን መዝኖ ለህግ የማቅረብ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
በመግለጫቸው የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን በመፈጸምና ግድያውን ተከትሎ በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ ተብሎ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ክስ እንደሚመሰረት አስታውቀዋል።
በሰጡት መግለጫ ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ቀጥታ ተሳትፎ የነበራቸውንና አብራው በነበረችው ግለሰብ ፣ በእነ አቶ ጃዋር መሀመድ መዝገብና በእነ አቶ እስክንድር ነጋ መዝገብ ላይ እስከ ፊታችን ሀሙስ ድረስ ክስ እንደሚመሰረት ገልፀዋል።በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ያሉት በአብዛኞቹ ላይ ምርመራው ተጠናቋል ተብሏል።አቶ ፍቃዱ ጸጋ በመግለጫው ላይ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ያለውን አቅም ተጠቅሞ ጥፋተኞችን ለፍትህ የማቅረብ ሂደት በሻለ ሁኔታ ተፈጻሚ እየሆነ ነው ብለዋል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮ ቴሌኮም 5 በመቶ ድርሻ ለበርካታ ዜጎች በአክሲዮን እንደሚሸጥ ሪፖርተር ዘግቧል፡፡ ለግል ኩባንያዎች የአገልግሎት ፍቃድ የመስጠቱ ሂደት፣ ከመስከረም እስከ የካቲት ይከናወናል፡፡ ለግል ኩባንያዎች 40 በመቶ ድርሻ የሚሸጥላቸው ሲሆን፣ መንግሥት እና ሕዝቡ 60 በመቶ ድርሻ ይኖራቸዋል፡፡ ይህ የተገለጸው የኩባንያው ከፊል ሽያጭ ሂደት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ባሉበት ዛሬ በተገመገመበት ስብሰባ ላይ ነው፡፡
[Reporter & Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
[Reporter & Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 976 ሰዎች በኮሮና ሲያዙ የ15 ሰዎች ህይወት አለፈ!
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 19,449 የላቦራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 976 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
309 ሰዎች ሲያገግሙ 15 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።
እስካሁን በአጠቃላይ 59,648 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 21,789 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን የ933 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 19,449 የላቦራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 976 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
309 ሰዎች ሲያገግሙ 15 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።
እስካሁን በአጠቃላይ 59,648 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 21,789 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን የ933 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ትምህርት ሚኒስቴር የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የሚያስችሉ ሁኔታዎችን እያጤንኩ ነው አለ፡፡
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሚሊዮን ማቲዎስ የ2013 አ.ም.የትምህርት ሂደትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ከትምህርት ቤቶች አከፋፈት ጋር ተያይዞ ባሉ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ መከሰቱን ተከትሎ ከ42 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ይማሩ የነበሩ ከ26 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነዋል፡፡የ2013 ዓመት ትምህርትን ለመጀመር የሚስችሉ ሁኔታዎችን ለመቃኘት የጥናት ቡደን ተቋቁሞ ጥናት እያደረገ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡በጥናቱ መሰረት ትምህርት ቤቶች በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ለማስተማር የሚያስችል አቅም ስለመኖርና አለመኖራቸው ልየታ እየተካሄድ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የተማሪዎችን ርቀት ለማስጠበቅ በአንድ ወንበር አንድ ተማሪ እንዲቀመጥ የሚደረግ ሲሆን በፈረቃ ትምህርት መስጠት፣ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች መገንባት፣ የማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ለማስተማሪያነት መጠቀም እንደ አማራጭ ጥቅም ላይ እንደሚውሉ ተገልጧል፡፡ይህንን ታሳቢ በማድረግ አንዳንድ ክልሎች አስቀድመው ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን የገነቡ ቢሆንም ሁሉም ክልሎች በየትምህርት ቤቱ ተጨማሪ ክፍሎችን እንዲገነቡ እየተደረገ ነው።በትምህርት ቤቶች ውስጥ ውሃ እንዲኖር ማድረግ፣ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘርና ማስክ የማቅረብ ስራዎችም እንደሚሰሩ ተነስቷል፡፡የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ያለበት ሁኔታ እየተገመገመ ደረጃ በደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት የሚያስችሉ ሁኔታዎች እየተጤኑ ነው ያሉት ሚስትር ዴኤታው ሚሊዮን ማቲዎስ ለስኬቱ ወላጆችና ባለድርሻ አካላት ከመንግስት ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል፡፡
[MoE]
@YeneTube @FikerAssefa
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሚሊዮን ማቲዎስ የ2013 አ.ም.የትምህርት ሂደትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ከትምህርት ቤቶች አከፋፈት ጋር ተያይዞ ባሉ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ መከሰቱን ተከትሎ ከ42 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ይማሩ የነበሩ ከ26 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነዋል፡፡የ2013 ዓመት ትምህርትን ለመጀመር የሚስችሉ ሁኔታዎችን ለመቃኘት የጥናት ቡደን ተቋቁሞ ጥናት እያደረገ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡በጥናቱ መሰረት ትምህርት ቤቶች በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ለማስተማር የሚያስችል አቅም ስለመኖርና አለመኖራቸው ልየታ እየተካሄድ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የተማሪዎችን ርቀት ለማስጠበቅ በአንድ ወንበር አንድ ተማሪ እንዲቀመጥ የሚደረግ ሲሆን በፈረቃ ትምህርት መስጠት፣ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች መገንባት፣ የማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ለማስተማሪያነት መጠቀም እንደ አማራጭ ጥቅም ላይ እንደሚውሉ ተገልጧል፡፡ይህንን ታሳቢ በማድረግ አንዳንድ ክልሎች አስቀድመው ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን የገነቡ ቢሆንም ሁሉም ክልሎች በየትምህርት ቤቱ ተጨማሪ ክፍሎችን እንዲገነቡ እየተደረገ ነው።በትምህርት ቤቶች ውስጥ ውሃ እንዲኖር ማድረግ፣ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘርና ማስክ የማቅረብ ስራዎችም እንደሚሰሩ ተነስቷል፡፡የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ያለበት ሁኔታ እየተገመገመ ደረጃ በደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት የሚያስችሉ ሁኔታዎች እየተጤኑ ነው ያሉት ሚስትር ዴኤታው ሚሊዮን ማቲዎስ ለስኬቱ ወላጆችና ባለድርሻ አካላት ከመንግስት ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል፡፡
[MoE]
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from Teklu Tilahun - ተክሉ ጥላሁን
#ትንቢተ_ፍጻሜ
#3ኛ_ዕትም_በገበያ_ላይ
እያንዳንዷን ቀን በጥንቃቄ እና በብልሀት መኖርን መዘንጋት የለብንም፡፡ እኛ የመጨረሻዎቹ የሰው ልጅ ፍጥረቶች መሆናችንን ተገንዝበን ይህችን ዓለም ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እንደምንሰናበታት ባወቅን ጊዜ በእያንዳንዷ ቀናችን ጠንቃቃና ዝግጁ መሆን እንዳለብን መካሪ አያሻንም፡፡ ለሞት ከሚያበቁ በሽታዎች በርን ዘግቶ ማምለጥ፣ ከድንገተኛ መቅሰፍት እና ከወቅታዊ ወረርሽኝ ራስን በመሰወር የመጨረሻዋን ምድራዊ ሕይወት ኑሮ ጨርሶ ወደ ዘላለማዊ ቤታችን ጠቅልሎ ለመሄድ መጠንቀቅ የብልሆች ስራ ነው፡፡ ይህን እያሰባችሁ መኖር እንዳለባችሁ ለማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡
#ሲልቪያ_ብራውን
#END_of_DAYS መጽሐፍ
#ትንቢተ_ፍጻሜ በሚል በአማርኛ ተተርጉሞ በገበያ ላይ ውሏል፡፡
*
በክርስትና፣ በእስልምና፣ በጆሆቫ፣ በራስ ተፈሪያኖች… በሁሉም ኃይማኖቶች ስለዓለም ፍጻሜ የተነበየ መጽሐፍ፡፡
#ኢትዮጵያ_እና_የንጉሶች_ንጉስ_የሆኑት_አጼ_ኃይለስላሴም_በዚህ_መጽሐፍ_ውስጥ_ተጠቅሰዋል፡፡ ከትንቢተ ፍጻሜው ጋር ምን ያገናኛቸው ይሆን?
#እውን እንደሚባለው ዓለም ፍጻሜዋ አሁን ይሆን? #ወይስ_ስንት_ዘመን_ትቆይ_ይሆን?
ተርጓሚ ራሴላስ ጋሻነህ
የመጽሐፈ ሔኖክ ኢትዮጵያዊና የስኬት ፍልስፍና መጽሐፍት ተርጓሚ
👉 ይቀላቀሉን http://tttttt.me/teklutilahun
#3ኛ_ዕትም_በገበያ_ላይ
እያንዳንዷን ቀን በጥንቃቄ እና በብልሀት መኖርን መዘንጋት የለብንም፡፡ እኛ የመጨረሻዎቹ የሰው ልጅ ፍጥረቶች መሆናችንን ተገንዝበን ይህችን ዓለም ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እንደምንሰናበታት ባወቅን ጊዜ በእያንዳንዷ ቀናችን ጠንቃቃና ዝግጁ መሆን እንዳለብን መካሪ አያሻንም፡፡ ለሞት ከሚያበቁ በሽታዎች በርን ዘግቶ ማምለጥ፣ ከድንገተኛ መቅሰፍት እና ከወቅታዊ ወረርሽኝ ራስን በመሰወር የመጨረሻዋን ምድራዊ ሕይወት ኑሮ ጨርሶ ወደ ዘላለማዊ ቤታችን ጠቅልሎ ለመሄድ መጠንቀቅ የብልሆች ስራ ነው፡፡ ይህን እያሰባችሁ መኖር እንዳለባችሁ ለማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡
#ሲልቪያ_ብራውን
#END_of_DAYS መጽሐፍ
#ትንቢተ_ፍጻሜ በሚል በአማርኛ ተተርጉሞ በገበያ ላይ ውሏል፡፡
*
በክርስትና፣ በእስልምና፣ በጆሆቫ፣ በራስ ተፈሪያኖች… በሁሉም ኃይማኖቶች ስለዓለም ፍጻሜ የተነበየ መጽሐፍ፡፡
#ኢትዮጵያ_እና_የንጉሶች_ንጉስ_የሆኑት_አጼ_ኃይለስላሴም_በዚህ_መጽሐፍ_ውስጥ_ተጠቅሰዋል፡፡ ከትንቢተ ፍጻሜው ጋር ምን ያገናኛቸው ይሆን?
#እውን እንደሚባለው ዓለም ፍጻሜዋ አሁን ይሆን? #ወይስ_ስንት_ዘመን_ትቆይ_ይሆን?
ተርጓሚ ራሴላስ ጋሻነህ
የመጽሐፈ ሔኖክ ኢትዮጵያዊና የስኬት ፍልስፍና መጽሐፍት ተርጓሚ
👉 ይቀላቀሉን http://tttttt.me/teklutilahun