የፌዴሬሽን ምክር ቤት በትግራይ ክልል ምርጫ ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ ህገ-ወጥ እና የክልሉ ህዝብም ሆነ መንግስት የማይቀበለው መሆኑን የትግራይ ክልል አስታወቀ፡፡
የትግራይ ክልል የመንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊያ ካሳ ለአሀዱ እንዳስታወቁት የክልሉ መንግስት እያካሄደ ያለው ምርጫ የህዝብ ውሳኔ የታከለበት እና ህገ-መንግስታዊ ስርዓትን የተከተለ ነው ብለዋል፡፡የምርጫው ባለቤት የትግራይ ህዝብ ነው ያሉት ወይዘሮ ሊያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ያስተላለፈው ውሳኔ የትግራይን ህዝብ ያስቆጣ እና ኢ-ህገ-መንግስታዊ ነው ብለውታል፡፡የፌዴሬሽን ምክር ቤት አገሪቱን የሚበታትን እንጅ ለህዝብ የሚጠቅም ውሳኔ ወስኗል ብለው እንደማያምኑም ነው ወይዘሮ ሊያ ያስታወቁት፡፡
[አሐዱ ሬዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ክልል የመንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊያ ካሳ ለአሀዱ እንዳስታወቁት የክልሉ መንግስት እያካሄደ ያለው ምርጫ የህዝብ ውሳኔ የታከለበት እና ህገ-መንግስታዊ ስርዓትን የተከተለ ነው ብለዋል፡፡የምርጫው ባለቤት የትግራይ ህዝብ ነው ያሉት ወይዘሮ ሊያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ያስተላለፈው ውሳኔ የትግራይን ህዝብ ያስቆጣ እና ኢ-ህገ-መንግስታዊ ነው ብለውታል፡፡የፌዴሬሽን ምክር ቤት አገሪቱን የሚበታትን እንጅ ለህዝብ የሚጠቅም ውሳኔ ወስኗል ብለው እንደማያምኑም ነው ወይዘሮ ሊያ ያስታወቁት፡፡
[አሐዱ ሬዲዮ]
@YeneTube @FikerAssefa
የማስጠንቀቂያ መልክቶች ሰሚ ባለማግኘታቸው የሰው ህይወት እየጠፋና ንብረት እየወደመ ነው ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
በተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶች ሊከሰቱባቸው የሚችሉ ቦታዎችን በመለየት ግጭቶች ተከስተው በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ቀድመን በተደጋጋሚ ብናሳውቅም በመንግስት በኩል ትኩረት እየተሰጠው አይደለም ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ገልጿል፡፡
ኮሚሽኑ ከመንግስትም ሆነ ከህብረተሰቡ ሳይወግን የሚሰራ እንደመሆኑ መረጃዎችን አጥንቶ በሚያሳውቅበት ወቅት በመንግስት በኩል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጊዜያዊ አስተባባሪ አቶ በለጠ ይልማ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
ከሶስት ሳምንታት በፊት በወላይታ ሶዶና በዞኑ ባሉ አንዳንድ ከተሞች ተከስተው የነበሩ ግጭቶችን ለመገምገም ኮሚሽኑ በቦታው በመገኘት ከመንግስት አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ሙሉ መረጃዎችን አሰባስቦ ጨርሷል፡፡ሙሉ ሪፖርቱን በሚቀጥሉት 3 ቀናት ውስጥ እንደሚያሳውቁ አቶ በለጠ አስታውቀዋል፡፡
[አሐዱ ሬዲዮ 94.3]
@YeneTube @FikerAssefa
በተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶች ሊከሰቱባቸው የሚችሉ ቦታዎችን በመለየት ግጭቶች ተከስተው በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ቀድመን በተደጋጋሚ ብናሳውቅም በመንግስት በኩል ትኩረት እየተሰጠው አይደለም ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ገልጿል፡፡
ኮሚሽኑ ከመንግስትም ሆነ ከህብረተሰቡ ሳይወግን የሚሰራ እንደመሆኑ መረጃዎችን አጥንቶ በሚያሳውቅበት ወቅት በመንግስት በኩል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ጊዜያዊ አስተባባሪ አቶ በለጠ ይልማ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
ከሶስት ሳምንታት በፊት በወላይታ ሶዶና በዞኑ ባሉ አንዳንድ ከተሞች ተከስተው የነበሩ ግጭቶችን ለመገምገም ኮሚሽኑ በቦታው በመገኘት ከመንግስት አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ሙሉ መረጃዎችን አሰባስቦ ጨርሷል፡፡ሙሉ ሪፖርቱን በሚቀጥሉት 3 ቀናት ውስጥ እንደሚያሳውቁ አቶ በለጠ አስታውቀዋል፡፡
[አሐዱ ሬዲዮ 94.3]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የጋዜጠኞች የጉዞ ክልከላን በተመለከተ “መረጃ አልነበረኝም” አለ
ከነገ በስቲያ በትግራይ የሚካሄደውን ምርጫን ለመዘገብ፤ ዛሬ ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበሩ ጋዜጠኞች ከአውሮፕላን ጣቢያ እንዲመለሱ መደረጉን በተመለከተ ቅድሚያ መረጃ እንዳልነበረው እና ጉዳዩን እንደሚያጣራ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጸ። የጉዞ እገዳ የተደረገባቸው ጋዜጠኞች መታወቂያቸው፣ የተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው፣ ላፕቶፖቻቸው፣ ካሜራዎች እና ሌሎች የስራ ዕቃዎቻቸው መወሰዳቸውን በጸጥታ ኃይሎች እንደተወሰዱባቸው ተናግረዋል።
ጋዜጠኞቹ እና ሌሎች መንገደኞች ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበረው ዛሬ ከቀኑ አምስት ሰዓት ላይ ነበር። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ መንገደኛ እንደተናገሩት የአየር ማረፊያ የጸጥታ ሰዎች ከወትሮው በተለየ ለውጭ ሀገር ዜጎች ጥያቄ ሲያቀርቡ ነበር። በኢትዮጵያ የኒው ዮርክ ታይምስ ዘጋቢ የሆነው ሳይመን ማርክስ በተለይ በርካታ ጥያቄዎች ሲቀርቡለት እንደነበር ማየታቸውን ተናግረዋል።
Via Ethiopia insider
@YeneTube @FikerAssefa
ከነገ በስቲያ በትግራይ የሚካሄደውን ምርጫን ለመዘገብ፤ ዛሬ ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበሩ ጋዜጠኞች ከአውሮፕላን ጣቢያ እንዲመለሱ መደረጉን በተመለከተ ቅድሚያ መረጃ እንዳልነበረው እና ጉዳዩን እንደሚያጣራ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጸ። የጉዞ እገዳ የተደረገባቸው ጋዜጠኞች መታወቂያቸው፣ የተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው፣ ላፕቶፖቻቸው፣ ካሜራዎች እና ሌሎች የስራ ዕቃዎቻቸው መወሰዳቸውን በጸጥታ ኃይሎች እንደተወሰዱባቸው ተናግረዋል።
ጋዜጠኞቹ እና ሌሎች መንገደኞች ወደ መቀሌ ሊጓዙ የነበረው ዛሬ ከቀኑ አምስት ሰዓት ላይ ነበር። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ መንገደኛ እንደተናገሩት የአየር ማረፊያ የጸጥታ ሰዎች ከወትሮው በተለየ ለውጭ ሀገር ዜጎች ጥያቄ ሲያቀርቡ ነበር። በኢትዮጵያ የኒው ዮርክ ታይምስ ዘጋቢ የሆነው ሳይመን ማርክስ በተለይ በርካታ ጥያቄዎች ሲቀርቡለት እንደነበር ማየታቸውን ተናግረዋል።
Via Ethiopia insider
@YeneTube @FikerAssefa
በድርድርና ሽምግልና የሚለቀቅ ተጠርጣሪ አይኖርም- ጠ/ዐቃቤ ህግ
በድርድርና ሽምግልና የሚለቀቅ ተጠርጣሪ አይኖርም ሲል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታወቀ።ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ፍቃዱ ጸጋ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ በመግለጫቸው ወንጀልን በሽምግልና የምንፈታበት ህግም ስልጣንም የለንም ነው ያሉት።በአደባባይ ሰው የገደሉና ውድመት እንዲፈጠር ያደረጉ ተጠርጣሪዎች ሳንመረምር አናስርም የሚል የለም ማስረጃውን መዝኖ ለህግ የማቅረብ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
በመግለጫቸው የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን በመፈጸምና ግድያውን ተከትሎ በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ ተብሎ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ክስ እንደሚመሰረት አስታውቀዋል።
በሰጡት መግለጫ ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ቀጥታ ተሳትፎ የነበራቸውንና አብራው በነበረችው ግለሰብ ፣ በእነ አቶ ጃዋር መሀመድ መዝገብና በእነ አቶ እስክንድር ነጋ መዝገብ ላይ እስከ ፊታችን ሀሙስ ድረስ ክስ እንደሚመሰረት ገልፀዋል።በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ያሉት በአብዛኞቹ ላይ ምርመራው ተጠናቋል ተብሏል።አቶ ፍቃዱ ጸጋ በመግለጫው ላይ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ያለውን አቅም ተጠቅሞ ጥፋተኞችን ለፍትህ የማቅረብ ሂደት በሻለ ሁኔታ ተፈጻሚ እየሆነ ነው ብለዋል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በድርድርና ሽምግልና የሚለቀቅ ተጠርጣሪ አይኖርም ሲል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታወቀ።ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ፍቃዱ ጸጋ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ በመግለጫቸው ወንጀልን በሽምግልና የምንፈታበት ህግም ስልጣንም የለንም ነው ያሉት።በአደባባይ ሰው የገደሉና ውድመት እንዲፈጠር ያደረጉ ተጠርጣሪዎች ሳንመረምር አናስርም የሚል የለም ማስረጃውን መዝኖ ለህግ የማቅረብ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
በመግለጫቸው የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን በመፈጸምና ግድያውን ተከትሎ በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ ተብሎ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ክስ እንደሚመሰረት አስታውቀዋል።
በሰጡት መግለጫ ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ቀጥታ ተሳትፎ የነበራቸውንና አብራው በነበረችው ግለሰብ ፣ በእነ አቶ ጃዋር መሀመድ መዝገብና በእነ አቶ እስክንድር ነጋ መዝገብ ላይ እስከ ፊታችን ሀሙስ ድረስ ክስ እንደሚመሰረት ገልፀዋል።በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ያሉት በአብዛኞቹ ላይ ምርመራው ተጠናቋል ተብሏል።አቶ ፍቃዱ ጸጋ በመግለጫው ላይ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ያለውን አቅም ተጠቅሞ ጥፋተኞችን ለፍትህ የማቅረብ ሂደት በሻለ ሁኔታ ተፈጻሚ እየሆነ ነው ብለዋል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮ ቴሌኮም 5 በመቶ ድርሻ ለበርካታ ዜጎች በአክሲዮን እንደሚሸጥ ሪፖርተር ዘግቧል፡፡ ለግል ኩባንያዎች የአገልግሎት ፍቃድ የመስጠቱ ሂደት፣ ከመስከረም እስከ የካቲት ይከናወናል፡፡ ለግል ኩባንያዎች 40 በመቶ ድርሻ የሚሸጥላቸው ሲሆን፣ መንግሥት እና ሕዝቡ 60 በመቶ ድርሻ ይኖራቸዋል፡፡ ይህ የተገለጸው የኩባንያው ከፊል ሽያጭ ሂደት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ባሉበት ዛሬ በተገመገመበት ስብሰባ ላይ ነው፡፡
[Reporter & Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
[Reporter & Wazema]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 976 ሰዎች በኮሮና ሲያዙ የ15 ሰዎች ህይወት አለፈ!
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 19,449 የላቦራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 976 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
309 ሰዎች ሲያገግሙ 15 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።
እስካሁን በአጠቃላይ 59,648 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 21,789 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን የ933 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 19,449 የላቦራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 976 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
309 ሰዎች ሲያገግሙ 15 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።
እስካሁን በአጠቃላይ 59,648 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 21,789 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን የ933 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ትምህርት ሚኒስቴር የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የሚያስችሉ ሁኔታዎችን እያጤንኩ ነው አለ፡፡
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሚሊዮን ማቲዎስ የ2013 አ.ም.የትምህርት ሂደትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ከትምህርት ቤቶች አከፋፈት ጋር ተያይዞ ባሉ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ መከሰቱን ተከትሎ ከ42 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ይማሩ የነበሩ ከ26 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነዋል፡፡የ2013 ዓመት ትምህርትን ለመጀመር የሚስችሉ ሁኔታዎችን ለመቃኘት የጥናት ቡደን ተቋቁሞ ጥናት እያደረገ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡በጥናቱ መሰረት ትምህርት ቤቶች በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ለማስተማር የሚያስችል አቅም ስለመኖርና አለመኖራቸው ልየታ እየተካሄድ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የተማሪዎችን ርቀት ለማስጠበቅ በአንድ ወንበር አንድ ተማሪ እንዲቀመጥ የሚደረግ ሲሆን በፈረቃ ትምህርት መስጠት፣ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች መገንባት፣ የማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ለማስተማሪያነት መጠቀም እንደ አማራጭ ጥቅም ላይ እንደሚውሉ ተገልጧል፡፡ይህንን ታሳቢ በማድረግ አንዳንድ ክልሎች አስቀድመው ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን የገነቡ ቢሆንም ሁሉም ክልሎች በየትምህርት ቤቱ ተጨማሪ ክፍሎችን እንዲገነቡ እየተደረገ ነው።በትምህርት ቤቶች ውስጥ ውሃ እንዲኖር ማድረግ፣ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘርና ማስክ የማቅረብ ስራዎችም እንደሚሰሩ ተነስቷል፡፡የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ያለበት ሁኔታ እየተገመገመ ደረጃ በደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት የሚያስችሉ ሁኔታዎች እየተጤኑ ነው ያሉት ሚስትር ዴኤታው ሚሊዮን ማቲዎስ ለስኬቱ ወላጆችና ባለድርሻ አካላት ከመንግስት ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል፡፡
[MoE]
@YeneTube @FikerAssefa
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሚሊዮን ማቲዎስ የ2013 አ.ም.የትምህርት ሂደትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ከትምህርት ቤቶች አከፋፈት ጋር ተያይዞ ባሉ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ መከሰቱን ተከትሎ ከ42 ሺ በላይ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ይማሩ የነበሩ ከ26 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነዋል፡፡የ2013 ዓመት ትምህርትን ለመጀመር የሚስችሉ ሁኔታዎችን ለመቃኘት የጥናት ቡደን ተቋቁሞ ጥናት እያደረገ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡በጥናቱ መሰረት ትምህርት ቤቶች በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ለማስተማር የሚያስችል አቅም ስለመኖርና አለመኖራቸው ልየታ እየተካሄድ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የተማሪዎችን ርቀት ለማስጠበቅ በአንድ ወንበር አንድ ተማሪ እንዲቀመጥ የሚደረግ ሲሆን በፈረቃ ትምህርት መስጠት፣ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች መገንባት፣ የማህበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ለማስተማሪያነት መጠቀም እንደ አማራጭ ጥቅም ላይ እንደሚውሉ ተገልጧል፡፡ይህንን ታሳቢ በማድረግ አንዳንድ ክልሎች አስቀድመው ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን የገነቡ ቢሆንም ሁሉም ክልሎች በየትምህርት ቤቱ ተጨማሪ ክፍሎችን እንዲገነቡ እየተደረገ ነው።በትምህርት ቤቶች ውስጥ ውሃ እንዲኖር ማድረግ፣ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘርና ማስክ የማቅረብ ስራዎችም እንደሚሰሩ ተነስቷል፡፡የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ያለበት ሁኔታ እየተገመገመ ደረጃ በደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት የሚያስችሉ ሁኔታዎች እየተጤኑ ነው ያሉት ሚስትር ዴኤታው ሚሊዮን ማቲዎስ ለስኬቱ ወላጆችና ባለድርሻ አካላት ከመንግስት ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል፡፡
[MoE]
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from Teklu Tilahun - ተክሉ ጥላሁን
#ትንቢተ_ፍጻሜ
#3ኛ_ዕትም_በገበያ_ላይ
እያንዳንዷን ቀን በጥንቃቄ እና በብልሀት መኖርን መዘንጋት የለብንም፡፡ እኛ የመጨረሻዎቹ የሰው ልጅ ፍጥረቶች መሆናችንን ተገንዝበን ይህችን ዓለም ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እንደምንሰናበታት ባወቅን ጊዜ በእያንዳንዷ ቀናችን ጠንቃቃና ዝግጁ መሆን እንዳለብን መካሪ አያሻንም፡፡ ለሞት ከሚያበቁ በሽታዎች በርን ዘግቶ ማምለጥ፣ ከድንገተኛ መቅሰፍት እና ከወቅታዊ ወረርሽኝ ራስን በመሰወር የመጨረሻዋን ምድራዊ ሕይወት ኑሮ ጨርሶ ወደ ዘላለማዊ ቤታችን ጠቅልሎ ለመሄድ መጠንቀቅ የብልሆች ስራ ነው፡፡ ይህን እያሰባችሁ መኖር እንዳለባችሁ ለማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡
#ሲልቪያ_ብራውን
#END_of_DAYS መጽሐፍ
#ትንቢተ_ፍጻሜ በሚል በአማርኛ ተተርጉሞ በገበያ ላይ ውሏል፡፡
*
በክርስትና፣ በእስልምና፣ በጆሆቫ፣ በራስ ተፈሪያኖች… በሁሉም ኃይማኖቶች ስለዓለም ፍጻሜ የተነበየ መጽሐፍ፡፡
#ኢትዮጵያ_እና_የንጉሶች_ንጉስ_የሆኑት_አጼ_ኃይለስላሴም_በዚህ_መጽሐፍ_ውስጥ_ተጠቅሰዋል፡፡ ከትንቢተ ፍጻሜው ጋር ምን ያገናኛቸው ይሆን?
#እውን እንደሚባለው ዓለም ፍጻሜዋ አሁን ይሆን? #ወይስ_ስንት_ዘመን_ትቆይ_ይሆን?
ተርጓሚ ራሴላስ ጋሻነህ
የመጽሐፈ ሔኖክ ኢትዮጵያዊና የስኬት ፍልስፍና መጽሐፍት ተርጓሚ
👉 ይቀላቀሉን http://tttttt.me/teklutilahun
#3ኛ_ዕትም_በገበያ_ላይ
እያንዳንዷን ቀን በጥንቃቄ እና በብልሀት መኖርን መዘንጋት የለብንም፡፡ እኛ የመጨረሻዎቹ የሰው ልጅ ፍጥረቶች መሆናችንን ተገንዝበን ይህችን ዓለም ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እንደምንሰናበታት ባወቅን ጊዜ በእያንዳንዷ ቀናችን ጠንቃቃና ዝግጁ መሆን እንዳለብን መካሪ አያሻንም፡፡ ለሞት ከሚያበቁ በሽታዎች በርን ዘግቶ ማምለጥ፣ ከድንገተኛ መቅሰፍት እና ከወቅታዊ ወረርሽኝ ራስን በመሰወር የመጨረሻዋን ምድራዊ ሕይወት ኑሮ ጨርሶ ወደ ዘላለማዊ ቤታችን ጠቅልሎ ለመሄድ መጠንቀቅ የብልሆች ስራ ነው፡፡ ይህን እያሰባችሁ መኖር እንዳለባችሁ ለማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡
#ሲልቪያ_ብራውን
#END_of_DAYS መጽሐፍ
#ትንቢተ_ፍጻሜ በሚል በአማርኛ ተተርጉሞ በገበያ ላይ ውሏል፡፡
*
በክርስትና፣ በእስልምና፣ በጆሆቫ፣ በራስ ተፈሪያኖች… በሁሉም ኃይማኖቶች ስለዓለም ፍጻሜ የተነበየ መጽሐፍ፡፡
#ኢትዮጵያ_እና_የንጉሶች_ንጉስ_የሆኑት_አጼ_ኃይለስላሴም_በዚህ_መጽሐፍ_ውስጥ_ተጠቅሰዋል፡፡ ከትንቢተ ፍጻሜው ጋር ምን ያገናኛቸው ይሆን?
#እውን እንደሚባለው ዓለም ፍጻሜዋ አሁን ይሆን? #ወይስ_ስንት_ዘመን_ትቆይ_ይሆን?
ተርጓሚ ራሴላስ ጋሻነህ
የመጽሐፈ ሔኖክ ኢትዮጵያዊና የስኬት ፍልስፍና መጽሐፍት ተርጓሚ
👉 ይቀላቀሉን http://tttttt.me/teklutilahun
Forwarded from Teklu Tilahun - ተክሉ ጥላሁን
#መከረኞች
#እምዩ
ዘመን የማይሽራቸው መጽሐፍት በገበያ ላይ!!
#መከረኞች በአንድ ፊቱ የህብረተሰብ ታሪክ፣ በሌላ ፊቱ ፍልስፍና፣ በሶስተኛ መልኩ የጥበብ ስራ፣ ከዚህም ውጪ በብዙ አንጻር ሊተረጎም የሚችል ‹‹ዘላለማዊ›› ተብለው ከሚጠሩ ስነ-ፅሁፎች የሚመደብ፡፡
#እምዩ #የእናት_ፍቅርና_መስዋዕትነት ከባድ ፈተና ውስጥ የሚገባበት… እጅግ መሳጭ ታሪክ የያዘ ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር መጽሐፍ!!!
#የመጽሐፍ_ቅርስ_ካስፈለገዎት
#መከረኞችና_እምዩ_መጽሐፍት_አሉልዎት፡፡
በየመፅሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኟቸዋል፡፡
ይቀላቀሉን 👉 http://tttttt.me/teklutilahun
#እምዩ
ዘመን የማይሽራቸው መጽሐፍት በገበያ ላይ!!
#መከረኞች በአንድ ፊቱ የህብረተሰብ ታሪክ፣ በሌላ ፊቱ ፍልስፍና፣ በሶስተኛ መልኩ የጥበብ ስራ፣ ከዚህም ውጪ በብዙ አንጻር ሊተረጎም የሚችል ‹‹ዘላለማዊ›› ተብለው ከሚጠሩ ስነ-ፅሁፎች የሚመደብ፡፡
#እምዩ #የእናት_ፍቅርና_መስዋዕትነት ከባድ ፈተና ውስጥ የሚገባበት… እጅግ መሳጭ ታሪክ የያዘ ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር መጽሐፍ!!!
#የመጽሐፍ_ቅርስ_ካስፈለገዎት
#መከረኞችና_እምዩ_መጽሐፍት_አሉልዎት፡፡
በየመፅሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኟቸዋል፡፡
ይቀላቀሉን 👉 http://tttttt.me/teklutilahun
Forwarded from YeneTube
N A T C O M P U T E R S ®
ናት ኮ ም ፒ ው ተ ር ስ ®
HP Envy X-360 (convertable touch screen)
Intel®core i7 8TH GENERATION
🟢Storage : 1Tb
🟨ram : 16GB DDR4
🟥 status: New
⚫battery: 5hrs
🔘Inch : 15.6" FULL HD Slim CONVERTABLE TOUCH SCREEN
💵 price: 37500 ብር
አድራሻ : - ቦሌ መድሐኒያለም Morningstar Mall 1ኛ ፎቅ ከAngla Burger ፊት ለ ፊት
🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥
N AT C O M P U T E R S ®
ናት ኮ ም ፒ ው ተ ር ስ ®
ይደውሉ
☎️+251911522626 /+251953120011
📌join @natcomputers1
📩 @natyendex ለአጭር መልክት
ናት ኮ ም ፒ ው ተ ር ስ ®
HP Envy X-360 (convertable touch screen)
Intel®core i7 8TH GENERATION
🟢Storage : 1Tb
🟨ram : 16GB DDR4
🟥 status: New
⚫battery: 5hrs
🔘Inch : 15.6" FULL HD Slim CONVERTABLE TOUCH SCREEN
💵 price: 37500 ብር
አድራሻ : - ቦሌ መድሐኒያለም Morningstar Mall 1ኛ ፎቅ ከAngla Burger ፊት ለ ፊት
🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥 🖥
N AT C O M P U T E R S ®
ናት ኮ ም ፒ ው ተ ር ስ ®
ይደውሉ
☎️+251911522626 /+251953120011
📌join @natcomputers1
📩 @natyendex ለአጭር መልክት
YeneTube
ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋርን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ እስከ መስከረም 8 2013 ዓ.ም ክስ እንዲመሰርት ብይን ሰጠ! የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቶ ጃዋር መሃመድና በቀለ ገርባን ጨምሮ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ያሉ ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ እስከ መስከረም 8 2013 ዓ.ም ክስ እንዲመሰርት ብይን ሰጠ።ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋር መሃመድና…
በትናንትናው ችሎት ላይ አቶ ጃዋር ምስጋና ማቅረብ እንደሚፈልጉና ለመንግሥትም መልዕክት እንዳላቸው የተናገሩ ሲሆን፣ ለዳኞችና ለፖሊስ ምስጋና አቅርበዋል።
የመናገር መብታቸው እንደተጠበቀላቸውና ፖሊሶችም ጥሩ እንክብካቤ እያደረጉላቸው እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል።"ይኹን እንጂ ይህ እንክብካቤ ለታዋቂ ሰዎች ብቻ ሳይሆን፤ ለሁሉም ሰዎች መሆን እንዳለበት በማንሳት በሌሎች ስፍራዎች ደንብ ልብስ የለበሱት ፖሊሶች "ሰዎችን እየገደሉ ነው" በማለት ተናግረዋል።አክለውም " እኛ የፖለቲካ ታሳሪዎች ነን፤ ገድለን፣ ሰርቀን ወይንም ዘርፈን አይደለም እዚህ የተገኘነው፤ የታሰርነው ለኦሮሞ ሕዝብ ስለታገልን ነው" ያሉት አቶ ጃዋር፣ የፍትህ አካላትም፣ ፍትህ ከፖለቲካ ሥልጣንና ከፖለቲካ ድርጅት በላይ እንዲሆን እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል አቶ በቀለ ገርባ "በእስካሁኑ ቆይታ ለፍርድ ቤቱ፣ ለአቃቢያነ ሕግ እና ለፖሊሶች ክብር አለን" ብለዋል።"የፖለቲካ ሰዎች ተመርጠው የዋስ መብት የማያሰጥ አንቀጽ እየተፈለገባቸው እየተከሰሱ ነው" ያሉት አቶ በቀለ መንግሥት ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር መወያየት እንዳለበት ተናግረዋል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የመናገር መብታቸው እንደተጠበቀላቸውና ፖሊሶችም ጥሩ እንክብካቤ እያደረጉላቸው እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል።"ይኹን እንጂ ይህ እንክብካቤ ለታዋቂ ሰዎች ብቻ ሳይሆን፤ ለሁሉም ሰዎች መሆን እንዳለበት በማንሳት በሌሎች ስፍራዎች ደንብ ልብስ የለበሱት ፖሊሶች "ሰዎችን እየገደሉ ነው" በማለት ተናግረዋል።አክለውም " እኛ የፖለቲካ ታሳሪዎች ነን፤ ገድለን፣ ሰርቀን ወይንም ዘርፈን አይደለም እዚህ የተገኘነው፤ የታሰርነው ለኦሮሞ ሕዝብ ስለታገልን ነው" ያሉት አቶ ጃዋር፣ የፍትህ አካላትም፣ ፍትህ ከፖለቲካ ሥልጣንና ከፖለቲካ ድርጅት በላይ እንዲሆን እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል አቶ በቀለ ገርባ "በእስካሁኑ ቆይታ ለፍርድ ቤቱ፣ ለአቃቢያነ ሕግ እና ለፖሊሶች ክብር አለን" ብለዋል።"የፖለቲካ ሰዎች ተመርጠው የዋስ መብት የማያሰጥ አንቀጽ እየተፈለገባቸው እየተከሰሱ ነው" ያሉት አቶ በቀለ መንግሥት ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር መወያየት እንዳለበት ተናግረዋል።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
በክፍል ውስጥ የተማሪዎችን ቁጥር በመመጠንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ትምህርት ለማስጀመር ጥናት ተደርጓል - አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ
ለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ሊያጋልጥ በማይችልና ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ የመማር ማስተማር ሂደቱን በአዲሱ ዓመት ለማስጀመር ጥናት መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እንዳለው በአንድ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎችን ቁጥር በመመጠንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ትምህርት ማስጀመር በሚቻልበት መንገድ ላይ ጥናት ተደርጓል።የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ የ2013 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ መጀመሩን አመልክተዋል።
ኮሮናቫይረስ በፖለቲካ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፍ በሳደረው ጫና ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጭ እንዲሆኑ መደረጉንም አስታውሰዋል።
አቶ ሚሊዮን እንዳሉት ትምህርት መቋረጡ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመግታት አስተዋፅኦ ቢኖረውም በተማሪዎች በተለይም ከህጻናት እድገት አንጻር ከፍተኛ ጫና አሳድሯል።በተለይ ህጻናት ትምህርት ዝግ ሆኖ ቤት በመዋላቸው ለአስገድዶ መደፈርና ያለዕድሜ ጋብቻ መዳረጋቸውን ሚኒስቴር ዴኤታው ገልጸዋል።በኢትዮጵያ ባሉ ከ42 ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ከ700 ሺህ በላይ መምህራንና ከ26 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ይገኛሉ።
“ወቅቱ ኮሮናቫይረስ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ያለበት በመሆኑ ትምህርት ቤቶች መከፈታቸው ህብረተሰቡን እያነጋገረ ነው” ያሉት አቶ ሚሊዮን፣ ወረርሽኙ የሚቆምበት ጊዜ ባለመታወቁ ትምህርት እንደሚጀመርና ይህም የጤና ጥበቃ የሚያስቀምጠውን መስፈርት ተግባራዊ በማድረግ እንደሚከናወን ገልጸዋል።ባለፈው የመማር ማስተማር ሂደት በአማካይ ከ60 እስከ 80 ተማሪዎች በአንድ ክፍል ውስጥ ይማሩ የነበረበት ሁኔታ እንደነበር አቶ ሚሊዮን አስታውሰዋል።
በቀጣይ ትምህርት ሲከፈት በቅድመ መደበኛ 14 በመቶ የሚሆኑትን ትምህርት ቤቶች ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ብቻ በአንድ ክፍል እንዲያስተምሩና አንድ ተማሪ በአንድ ዴስክ ብቻ እንዲቀመጥ ለማድረግ መታቀዱን አስረድተዋል።አቶ ሚሊዮን እንዳሉት ቀሪዎቹ 80 በመቶ ተማሪዎች በፈረቃ እንዲማሩና 6 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርት ቤት በመገንባትና አማራጭ ማህበራዊ ተቋማትን በመጠቀም ለማስተማር ታቅዷል።
በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 24 በመቶ ወይም ከ20 እስከ 25 ተማሪዎች በአንድ ከፍል ውስጥ እንዲማሩ፣ 56 በመቶ በፈረቃ እንዲሁም 20 በመቶ ተጨማሪ ክፍል በመገንባት እንዲማሩ ተወስኗል።በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 19 በመቶ ተማሪዎች ወይም ከ20 እስከ 25 የሚሆኑት በአንድ ክፍል ውስጥ እንዲማሩ እንዲሁም 50 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ በፈረቃ የሚማሩ ይሆናል።
ሌሎች 31 በመቶ ተጨማሪ ክፍሎችን በመገንባትና አማራጭ ማህበራዊ ተቋማትን በመጠቀም ለማስተማር መታቀዱንም አመልክተዋል።በሽታን በመከላከል የትምህርት ተቋማትን ስራ ለማስጀመር ተቋማቱን ማስፋት እንደሚገባም አቶ ሚሊዮን ተናግረዋል።
ኦሮሚያ ክልል ሃብት በማሰባሰብ 30 ሺህ አዳዲስ ክፍሎችን መገንባቱን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ “አማራ ክልልም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ያለውን የክፍል እጥረት ችግር ለመቅረፍ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው” ብለዋል።
ተማሪዎች በተረጋጋ ሁኔታ እንዲማሩ የቀደመው የመማር ማስተማር ስልት በአዲስ መልክ እንደሚሆን ጠቁመው፣ ይህም የቡድን ስራን ጨምሮ የተማሪዎችን አካላዊ ንክኪን ሊያስቀር በሚችል መልኩ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።አቶ ሚሊዮን እንዳሉት የትምህርት ቤቶች አከፋፈት ጥናቱን መሰረት ያደረገ ይሆናል።ትምህርት ቤቶች በተመሳሳይ ወቀት አንድ ላይ ሊከፈቱ እንደማይችሉና ደረጃ በደረጃ የመክፈት ሂደት እንደሚኖር ገልጸው፣ አጀማመሩ ከክልል ክልልና ከዞን ዞን ሊለያይ እንደሚችል አመልክተዋል።
ይህንን ተከትሎ አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ጭማሪ እየጠየቁ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን በሚያደርጉ ተቋማት ላይ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶችን እስከመዝጋት የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስድ አመልክተዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
ለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ሊያጋልጥ በማይችልና ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ የመማር ማስተማር ሂደቱን በአዲሱ ዓመት ለማስጀመር ጥናት መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እንዳለው በአንድ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎችን ቁጥር በመመጠንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ትምህርት ማስጀመር በሚቻልበት መንገድ ላይ ጥናት ተደርጓል።የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ የ2013 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ መጀመሩን አመልክተዋል።
ኮሮናቫይረስ በፖለቲካ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፍ በሳደረው ጫና ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጭ እንዲሆኑ መደረጉንም አስታውሰዋል።
አቶ ሚሊዮን እንዳሉት ትምህርት መቋረጡ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመግታት አስተዋፅኦ ቢኖረውም በተማሪዎች በተለይም ከህጻናት እድገት አንጻር ከፍተኛ ጫና አሳድሯል።በተለይ ህጻናት ትምህርት ዝግ ሆኖ ቤት በመዋላቸው ለአስገድዶ መደፈርና ያለዕድሜ ጋብቻ መዳረጋቸውን ሚኒስቴር ዴኤታው ገልጸዋል።በኢትዮጵያ ባሉ ከ42 ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ከ700 ሺህ በላይ መምህራንና ከ26 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ይገኛሉ።
“ወቅቱ ኮሮናቫይረስ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ያለበት በመሆኑ ትምህርት ቤቶች መከፈታቸው ህብረተሰቡን እያነጋገረ ነው” ያሉት አቶ ሚሊዮን፣ ወረርሽኙ የሚቆምበት ጊዜ ባለመታወቁ ትምህርት እንደሚጀመርና ይህም የጤና ጥበቃ የሚያስቀምጠውን መስፈርት ተግባራዊ በማድረግ እንደሚከናወን ገልጸዋል።ባለፈው የመማር ማስተማር ሂደት በአማካይ ከ60 እስከ 80 ተማሪዎች በአንድ ክፍል ውስጥ ይማሩ የነበረበት ሁኔታ እንደነበር አቶ ሚሊዮን አስታውሰዋል።
በቀጣይ ትምህርት ሲከፈት በቅድመ መደበኛ 14 በመቶ የሚሆኑትን ትምህርት ቤቶች ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ብቻ በአንድ ክፍል እንዲያስተምሩና አንድ ተማሪ በአንድ ዴስክ ብቻ እንዲቀመጥ ለማድረግ መታቀዱን አስረድተዋል።አቶ ሚሊዮን እንዳሉት ቀሪዎቹ 80 በመቶ ተማሪዎች በፈረቃ እንዲማሩና 6 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርት ቤት በመገንባትና አማራጭ ማህበራዊ ተቋማትን በመጠቀም ለማስተማር ታቅዷል።
በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 24 በመቶ ወይም ከ20 እስከ 25 ተማሪዎች በአንድ ከፍል ውስጥ እንዲማሩ፣ 56 በመቶ በፈረቃ እንዲሁም 20 በመቶ ተጨማሪ ክፍል በመገንባት እንዲማሩ ተወስኗል።በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 19 በመቶ ተማሪዎች ወይም ከ20 እስከ 25 የሚሆኑት በአንድ ክፍል ውስጥ እንዲማሩ እንዲሁም 50 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ በፈረቃ የሚማሩ ይሆናል።
ሌሎች 31 በመቶ ተጨማሪ ክፍሎችን በመገንባትና አማራጭ ማህበራዊ ተቋማትን በመጠቀም ለማስተማር መታቀዱንም አመልክተዋል።በሽታን በመከላከል የትምህርት ተቋማትን ስራ ለማስጀመር ተቋማቱን ማስፋት እንደሚገባም አቶ ሚሊዮን ተናግረዋል።
ኦሮሚያ ክልል ሃብት በማሰባሰብ 30 ሺህ አዳዲስ ክፍሎችን መገንባቱን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ “አማራ ክልልም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ያለውን የክፍል እጥረት ችግር ለመቅረፍ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው” ብለዋል።
ተማሪዎች በተረጋጋ ሁኔታ እንዲማሩ የቀደመው የመማር ማስተማር ስልት በአዲስ መልክ እንደሚሆን ጠቁመው፣ ይህም የቡድን ስራን ጨምሮ የተማሪዎችን አካላዊ ንክኪን ሊያስቀር በሚችል መልኩ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።አቶ ሚሊዮን እንዳሉት የትምህርት ቤቶች አከፋፈት ጥናቱን መሰረት ያደረገ ይሆናል።ትምህርት ቤቶች በተመሳሳይ ወቀት አንድ ላይ ሊከፈቱ እንደማይችሉና ደረጃ በደረጃ የመክፈት ሂደት እንደሚኖር ገልጸው፣ አጀማመሩ ከክልል ክልልና ከዞን ዞን ሊለያይ እንደሚችል አመልክተዋል።
ይህንን ተከትሎ አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ጭማሪ እየጠየቁ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን በሚያደርጉ ተቋማት ላይ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶችን እስከመዝጋት የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስድ አመልክተዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
በጠገዴ ወረዳ ሰው አግቶ ገንዘብ በተቀበለ ግለሠብ ላይ የሦሮቃ ንዑስ ወረዳ ፍ/ቤት የቅጣት ውሳኔ አስተላለፈ።
ግንቦት 19/2012 ዓ/ም ተጠርጣሪ ሙቀት አለማየሁ የማይ አጋም ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን በየነ ጥላሁን በሥራ ላይ እያለ 6 ሽህ ብር መክፈል አለብህ በማለት ለአራት ቀናት አግቶት ቆይቷል። የታገተው ግለሠብ ቤተሠቦችን ግንቦት 22/2012 ዓ/ም 6ሽህ ብር ከፍለው ከታገተበት አስለቅቀውታል። ተጠርጣሪው ገንዘቡን እንደተቀበለ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 አካባቢ ነዋሪነቱን አድርጓል። ፖሊስ ግለሠቡን በመከታተሉና ከማህበረሰቡ በደረሰ ጥቆማ በጎንደር ከተማ ነሀሴ 12/2012 ዓ/ም ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውላል።
የሶ/ን/ወረዳ ፖሊስ ተጠርጣሪውን ነሀሴ 25/2012 ዓ/ም ወንጀሉን ወደ ፈፀመበት ሶሮቃ ንዑስ ወረዳ በመውሰድ ምርመራውን ጀምሯል።ተከሳሹም ክዶ ተከራክሯል የሶ/ን/ወረዳ ዓ/ ህግ የተላለፈውን የኢፌድሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 586/1/ እና 590 ንዑስ ቁጥር "ሐ 2" በመጥቀስ በመተላለፍ የህግ ማስረጃወችን አሠምቷል።
ክሱን የተመለከተው የሶ/ን/ወረዳ/ፍ/ቤት ተከሳሹን ጥፋተኛ በማለት እሡንም ሆነ ሌሎችን ያስተምራል በማለት ናሀሴ 27/2012 ዓ/ ም በወለው የወንጀል ችሎት በ8 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ዓ/ህግ ተከሳሹ በጦር መሳሪያ ይዞ ወንጀሉን የፈፀመ በመሆኑ ቅጣቱን አንሷል ሲል ይግባኝ ጠይቋል ። መረጃውን ያደረሰን የሶሮቃ ንዑሥ ወረዳ ዓቃቢ ህግ ጽ/ቤትን ጠቅሶ የጠገዴ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ግንቦት 19/2012 ዓ/ም ተጠርጣሪ ሙቀት አለማየሁ የማይ አጋም ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን በየነ ጥላሁን በሥራ ላይ እያለ 6 ሽህ ብር መክፈል አለብህ በማለት ለአራት ቀናት አግቶት ቆይቷል። የታገተው ግለሠብ ቤተሠቦችን ግንቦት 22/2012 ዓ/ም 6ሽህ ብር ከፍለው ከታገተበት አስለቅቀውታል። ተጠርጣሪው ገንዘቡን እንደተቀበለ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 አካባቢ ነዋሪነቱን አድርጓል። ፖሊስ ግለሠቡን በመከታተሉና ከማህበረሰቡ በደረሰ ጥቆማ በጎንደር ከተማ ነሀሴ 12/2012 ዓ/ም ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ውላል።
የሶ/ን/ወረዳ ፖሊስ ተጠርጣሪውን ነሀሴ 25/2012 ዓ/ም ወንጀሉን ወደ ፈፀመበት ሶሮቃ ንዑስ ወረዳ በመውሰድ ምርመራውን ጀምሯል።ተከሳሹም ክዶ ተከራክሯል የሶ/ን/ወረዳ ዓ/ ህግ የተላለፈውን የኢፌድሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 586/1/ እና 590 ንዑስ ቁጥር "ሐ 2" በመጥቀስ በመተላለፍ የህግ ማስረጃወችን አሠምቷል።
ክሱን የተመለከተው የሶ/ን/ወረዳ/ፍ/ቤት ተከሳሹን ጥፋተኛ በማለት እሡንም ሆነ ሌሎችን ያስተምራል በማለት ናሀሴ 27/2012 ዓ/ ም በወለው የወንጀል ችሎት በ8 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ዓ/ህግ ተከሳሹ በጦር መሳሪያ ይዞ ወንጀሉን የፈፀመ በመሆኑ ቅጣቱን አንሷል ሲል ይግባኝ ጠይቋል ። መረጃውን ያደረሰን የሶሮቃ ንዑሥ ወረዳ ዓቃቢ ህግ ጽ/ቤትን ጠቅሶ የጠገዴ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
ዓለም ለሚቀጥለው ወረርሽኝ በአግባቡ መዘጋጀት አለባት- የአለም ጤና ድርጅት
የአለም ጤና ድርጅት ኃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በትናንትናው እለት ሀገራትን በህብረተሰብ ጤና ላይ አተኩረው እንዲሰሩ በጠየቁበት ወቅት፣ ዓለም ለሚቀጥለው ወረርሽኝ በሚገባ መዘጋጅት እንዳለባት ተናግረዋል፡፡እስካሁን ሮይተርስ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ በሽታ በፈረንጆቹ 2019 በቻይና ከተገኘበት ጊዜ ጀምሮ አዘጋጀሁት ባለው መረጃ መሰረት ከ27 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሲሆን 888 326 ሰዎችደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ዶክተር ቴድሮስ ይሄ የመጨረሻው ወረርሽኝ አይደለም ብለዋል፡፡ “ታሪክ እንደሚያስተምረን ወረርሽኞች የሚኖሩ ናቸው፤ስለሆነም ዓለም ከአሁን በላይ መዘጋጀት” እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
የአለም ጤና ድርጅት ኃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም በትናንትናው እለት ሀገራትን በህብረተሰብ ጤና ላይ አተኩረው እንዲሰሩ በጠየቁበት ወቅት፣ ዓለም ለሚቀጥለው ወረርሽኝ በሚገባ መዘጋጅት እንዳለባት ተናግረዋል፡፡እስካሁን ሮይተርስ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ በሽታ በፈረንጆቹ 2019 በቻይና ከተገኘበት ጊዜ ጀምሮ አዘጋጀሁት ባለው መረጃ መሰረት ከ27 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሲሆን 888 326 ሰዎችደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ዶክተር ቴድሮስ ይሄ የመጨረሻው ወረርሽኝ አይደለም ብለዋል፡፡ “ታሪክ እንደሚያስተምረን ወረርሽኞች የሚኖሩ ናቸው፤ስለሆነም ዓለም ከአሁን በላይ መዘጋጀት” እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮውን ወደ ትግራይ ክልል አዘዋወረ!
በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ባለቤትነት ስር የሚተዳደረውና በርካታ የልማት ድርጅቶችን አቅፎ በያዘው የትግራይ መልሶ ማቋቋም (ኤፈርት) ተብሎ በሚጠራው ድርጅቶች ውስጥ አንዱ የሆነው ሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮውን ወደ መቐለ ማዘዋወሩ ተገለፀ።
አዲስ ማለዳ ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው የኮንስትራክሽን ድርጅቱ ቦሌ ሸዋ ዳቦ አፍሪካ ጎዳና አካባቢ ባስገነባው የራሱ ህንፃ አገልግሎት ይሰጥ የነበረ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ወደ ትግራይ ክልል ማዘዋወሩ ተገልጿል።
በሱር ኮንስትራክሽን ውስጥ ከሚሰሩ ሰራተኞች መሃል ለአዲስ ማለዳ የተናገሩት እንዳሉት ኮቪድ 19 ከገባ ከጥቂት ቀናት በኋላ ዋና መስሪያ ቤቱ ወደ መቐለ መዛወሩን የተናገሩ ሲሆን በዚህም አዲስ አበባ የሚገኙ ሰራተኞች ፈቃድ እንደሰጠና ለዚህም ምክንያቱ ኮቪድ 19 ኢትዮጵያ መግባቱ መሆኑ እንደተገለፀላቸው ተናግረዋል።
ድርጅቱ ይህን ይበል እንጂ ከቀናት በኋላ በአዲስ አበባ ለሚገኙ ሰራተኞች የተገለፀው ፈቃደኛ ሆነው ትግራይ ክልል መቀሌ ገብተው መስራት ከፈለጉ እንደሚችሉ እና ካልሆነ ግን በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን እንደለቀቁ እንደሚወሰድ እንደተነገራቸው አዲስ ማለዳ ከምንጮቿ አረጋግጣለች።ከዚህ ጉዳይ ጋር ጋዜጣው ያነጋገራቸው የሱር ኮንስትራክሽን ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ታደሰ የማነ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት ከሆነ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ተሰማርቶ ያለው ሱር ኮንትራክሽን ከዚህ ቀደም የነበረውን ዋናውን ቢሮ አለመልቀቁን እና ቅሬታውም ከእውነት የራቀ ነው በማለት ተናግረዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ እንደሚሉት ከዚህ ቀደም የሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮ የሚገኝበት ደምበል አካባቢ ከሜጋ ህንፃ ጎን እንደሆነ እና አሁንም እዛው እንዳለ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።ታደሰ ጨምረውም አሁን ደምበል አካባቢ የሚገኘው ቢሯቸው አገልግሎት እየሰጠ ያልሆነበት ምክንትን ሲጠቅሱ፤ በትግራይ ክልል ከ30 በላይ ፕሮጀክቶች በመጀመራቸው እና ሱር ኮንስትራክሽንም ለስራው ቅርብ መሆን ስላለበት አንዳንድ ዋና ዋና የስራ ኃላፊዎች ወደዛው መቅረብ ስላለባቸው መሆኑን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
ነገር ግን ይላሉ በፕሮጀክቱ ላይ ለመሳተፍ ምን ያህል ሰራተኞች እንደሄዱ በቁጥር እንደማያውቁ እና አዲስ አበባ ከሚገኘው ዋናው ቢሮም ምንም አይነት ሰራተኛ በእረፍት ላይ አይገኝም ሲሉ አስተባብለዋል።ሱር ኮንስትራክሽን በኤፈርት ስር ከሚገኙ ወደ 14 የሚጠጉ ድርጅቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከሦስት ሺሕ በላይ ቋሚ እና ከሰባት ሺሕ በላይ ደግሞ ቀን ሰራተኞችን በስሩ ሚያስተዳደር ግዙፍ ኩባንያ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
ከ20 ዓመታት በፊት በ108 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተመሰረተው ሱር ኮንስትራክሽን በሕወሓት ባለቤትነት በሚመራው ኤፈርት ኩባንያዎች አንዱ አካል እንደሆነም ይታወቃል።ሱር ኮንስትራክሽን በአገር ውስጥ ካሉ ኮንስትራክሽኖች ደረጃ አንድ ግንባታ ድርጅት ሲሆን፤ ሀይድሮፓወር ፕሮጀክቶች እና የመኖሪያ ቤት ግንነባታዎችም ላይ በስፋት እንደሚሳተፍም ይታወቃል።ከተሳተፈባቸው ፕሮጀክቶችም መካከል በከፍተኛ ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የዛሬማ ሜይዴይ ግድብ አንዱ ሲሆን በአገር በቀል ድርጅቶች ይህን የሚያክል ከፍተኛ በጀት ያላቸውን ፕሮጀክቶች በዋና ተቋራጭነት በመሳተፍ ሱር ቀዳሚው ድርጅት ነው።በተመሳሳይም በመቐለ ከተማ መኖሪያ መንደርም በመገንባት ስራ ላይም ተሰመራርቷል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ባለቤትነት ስር የሚተዳደረውና በርካታ የልማት ድርጅቶችን አቅፎ በያዘው የትግራይ መልሶ ማቋቋም (ኤፈርት) ተብሎ በሚጠራው ድርጅቶች ውስጥ አንዱ የሆነው ሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮውን ወደ መቐለ ማዘዋወሩ ተገለፀ።
አዲስ ማለዳ ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው የኮንስትራክሽን ድርጅቱ ቦሌ ሸዋ ዳቦ አፍሪካ ጎዳና አካባቢ ባስገነባው የራሱ ህንፃ አገልግሎት ይሰጥ የነበረ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ወደ ትግራይ ክልል ማዘዋወሩ ተገልጿል።
በሱር ኮንስትራክሽን ውስጥ ከሚሰሩ ሰራተኞች መሃል ለአዲስ ማለዳ የተናገሩት እንዳሉት ኮቪድ 19 ከገባ ከጥቂት ቀናት በኋላ ዋና መስሪያ ቤቱ ወደ መቐለ መዛወሩን የተናገሩ ሲሆን በዚህም አዲስ አበባ የሚገኙ ሰራተኞች ፈቃድ እንደሰጠና ለዚህም ምክንያቱ ኮቪድ 19 ኢትዮጵያ መግባቱ መሆኑ እንደተገለፀላቸው ተናግረዋል።
ድርጅቱ ይህን ይበል እንጂ ከቀናት በኋላ በአዲስ አበባ ለሚገኙ ሰራተኞች የተገለፀው ፈቃደኛ ሆነው ትግራይ ክልል መቀሌ ገብተው መስራት ከፈለጉ እንደሚችሉ እና ካልሆነ ግን በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን እንደለቀቁ እንደሚወሰድ እንደተነገራቸው አዲስ ማለዳ ከምንጮቿ አረጋግጣለች።ከዚህ ጉዳይ ጋር ጋዜጣው ያነጋገራቸው የሱር ኮንስትራክሽን ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ታደሰ የማነ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት ከሆነ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ተሰማርቶ ያለው ሱር ኮንትራክሽን ከዚህ ቀደም የነበረውን ዋናውን ቢሮ አለመልቀቁን እና ቅሬታውም ከእውነት የራቀ ነው በማለት ተናግረዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ እንደሚሉት ከዚህ ቀደም የሱር ኮንስትራክሽን ዋና ቢሮ የሚገኝበት ደምበል አካባቢ ከሜጋ ህንፃ ጎን እንደሆነ እና አሁንም እዛው እንዳለ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።ታደሰ ጨምረውም አሁን ደምበል አካባቢ የሚገኘው ቢሯቸው አገልግሎት እየሰጠ ያልሆነበት ምክንትን ሲጠቅሱ፤ በትግራይ ክልል ከ30 በላይ ፕሮጀክቶች በመጀመራቸው እና ሱር ኮንስትራክሽንም ለስራው ቅርብ መሆን ስላለበት አንዳንድ ዋና ዋና የስራ ኃላፊዎች ወደዛው መቅረብ ስላለባቸው መሆኑን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
ነገር ግን ይላሉ በፕሮጀክቱ ላይ ለመሳተፍ ምን ያህል ሰራተኞች እንደሄዱ በቁጥር እንደማያውቁ እና አዲስ አበባ ከሚገኘው ዋናው ቢሮም ምንም አይነት ሰራተኛ በእረፍት ላይ አይገኝም ሲሉ አስተባብለዋል።ሱር ኮንስትራክሽን በኤፈርት ስር ከሚገኙ ወደ 14 የሚጠጉ ድርጅቶች ውስጥ አንዱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከሦስት ሺሕ በላይ ቋሚ እና ከሰባት ሺሕ በላይ ደግሞ ቀን ሰራተኞችን በስሩ ሚያስተዳደር ግዙፍ ኩባንያ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
ከ20 ዓመታት በፊት በ108 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተመሰረተው ሱር ኮንስትራክሽን በሕወሓት ባለቤትነት በሚመራው ኤፈርት ኩባንያዎች አንዱ አካል እንደሆነም ይታወቃል።ሱር ኮንስትራክሽን በአገር ውስጥ ካሉ ኮንስትራክሽኖች ደረጃ አንድ ግንባታ ድርጅት ሲሆን፤ ሀይድሮፓወር ፕሮጀክቶች እና የመኖሪያ ቤት ግንነባታዎችም ላይ በስፋት እንደሚሳተፍም ይታወቃል።ከተሳተፈባቸው ፕሮጀክቶችም መካከል በከፍተኛ ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የዛሬማ ሜይዴይ ግድብ አንዱ ሲሆን በአገር በቀል ድርጅቶች ይህን የሚያክል ከፍተኛ በጀት ያላቸውን ፕሮጀክቶች በዋና ተቋራጭነት በመሳተፍ ሱር ቀዳሚው ድርጅት ነው።በተመሳሳይም በመቐለ ከተማ መኖሪያ መንደርም በመገንባት ስራ ላይም ተሰመራርቷል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
ኮሮና ቫይረስ በአውሮፓ በድጋሚ እያንሰራራ መሆኑ ተገለጸ!
ስፔን በምዕራብ አውሮፓ ግማሽ ሚሊዮን የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎችን በመመዝገብ የመጀመሪያዋ አገር ሆናለች፡፡በሀገሪቱ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ከ525 ሺ የበለጠ ሲሆን ይህም የሆነው ትምህርት ቤቶች እንደገና ከመከፈታቸው ጋር በተያያዘ ቫይረሱ ለሁለተኛ ጊዜ በማገርሸት ላይ በመሆኑ ነው፡፡
በሌሎች የአውሮፓ ሀገራትም በተመሳሳይ ቫይረሱ በድጋሚ በማንሰራራት ላይ ይገኛል፡፡ ፈረንሳይ በየቀኑ የተጠቂዎች ቁጥር “አሳሳቢ” በሆነ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን ያሳወቀች ሲሆን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እለት ተእለት በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በአማካይ ከ 5,000 በላይ መድረሱን ይፋ አድርጋለች፡፡
የተጠቂዎች ቁጥር እየጨመረባት ባለችው በሌላኛዋ አውሮፓዊት ሀገር ዩናይትድ ኪንግደም የአገር ውስጥ የቫይረሱ ስርጭት በአብዛኛው ከወጣቶች የተያያዘ ስለመሆኑ ዘ ናሺናል ዘግቧል፡፡በመላው ዓለም እስካሁን የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከ 27.4 ሚሊዮን በላይየደረሰ ሲሆን ከ 896,000 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸው አልፎ ከ 19 ሚሊዮን የሚበልጡት አገግመዋል፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ስፔን በምዕራብ አውሮፓ ግማሽ ሚሊዮን የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎችን በመመዝገብ የመጀመሪያዋ አገር ሆናለች፡፡በሀገሪቱ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ከ525 ሺ የበለጠ ሲሆን ይህም የሆነው ትምህርት ቤቶች እንደገና ከመከፈታቸው ጋር በተያያዘ ቫይረሱ ለሁለተኛ ጊዜ በማገርሸት ላይ በመሆኑ ነው፡፡
በሌሎች የአውሮፓ ሀገራትም በተመሳሳይ ቫይረሱ በድጋሚ በማንሰራራት ላይ ይገኛል፡፡ ፈረንሳይ በየቀኑ የተጠቂዎች ቁጥር “አሳሳቢ” በሆነ ደረጃ እየጨመረ መሆኑን ያሳወቀች ሲሆን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እለት ተእለት በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በአማካይ ከ 5,000 በላይ መድረሱን ይፋ አድርጋለች፡፡
የተጠቂዎች ቁጥር እየጨመረባት ባለችው በሌላኛዋ አውሮፓዊት ሀገር ዩናይትድ ኪንግደም የአገር ውስጥ የቫይረሱ ስርጭት በአብዛኛው ከወጣቶች የተያያዘ ስለመሆኑ ዘ ናሺናል ዘግቧል፡፡በመላው ዓለም እስካሁን የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከ 27.4 ሚሊዮን በላይየደረሰ ሲሆን ከ 896,000 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸው አልፎ ከ 19 ሚሊዮን የሚበልጡት አገግመዋል፡፡
[Al ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች በበዓሉ ዋዜማ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳይጠቀሙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳሰበ!
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2013 ዓ.ም ዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚኖረው የኃይል ፍልጎት ለማሟላት የቅድመ ጥንቃቄ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በበአሉ ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን የኃይል መዋዠቅንና መቆራረጥ ለመቀነስ የድንጋይና እህል ወፍጮ፣ የፕላስቲክ፣ የጨርቃ ጨርቅ፣ የብረታ ብረት፣ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ የኬሚካልና ሌሎች ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ከጳጉሜ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከንጋቱ 12፡00 ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 4፡00 ድረስ ከግሪድ የሚያገኙትን የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳይጠቀሙ የተለመደ ትብብራቸውን አንዲሰጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳስቧል።
በዋዜማና በበዓሉ ቀን የኤሌክትሪክ ኃይል ሳይቆራረጥና ሳይዋዥቅ ለማቅረብ እንዲሁም ችግሩ ከተከሰተም በተገቢው መንገድ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑንንም ነው ተቋሙ የገለፀው፡፡በተደጋጋሚ ጊዜ የኃይል መቆራረጥ የሚስተዋልባቸውን አካባቢዎች በመለየት በመካከለኛና በዝቅተኛ መስመሮች ላይ ጭነት የማመጣጠንና የቅድመ መከላከል ጥገና ስራዎች በመሰራት ላይ መሆኑንንም አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ በመሆን ከኃይል ማመንጫ ጀምሮ እስከ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና ትራንስፎርመሮች ብልሽቶች ሲያጋጥሙ በአፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውም ተገልጿል፡፡
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2013 ዓ.ም ዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚኖረው የኃይል ፍልጎት ለማሟላት የቅድመ ጥንቃቄ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በበአሉ ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን የኃይል መዋዠቅንና መቆራረጥ ለመቀነስ የድንጋይና እህል ወፍጮ፣ የፕላስቲክ፣ የጨርቃ ጨርቅ፣ የብረታ ብረት፣ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ የኬሚካልና ሌሎች ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ከጳጉሜ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ከንጋቱ 12፡00 ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 4፡00 ድረስ ከግሪድ የሚያገኙትን የኤሌክትሪክ ኃይል እንዳይጠቀሙ የተለመደ ትብብራቸውን አንዲሰጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳስቧል።
በዋዜማና በበዓሉ ቀን የኤሌክትሪክ ኃይል ሳይቆራረጥና ሳይዋዥቅ ለማቅረብ እንዲሁም ችግሩ ከተከሰተም በተገቢው መንገድ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑንንም ነው ተቋሙ የገለፀው፡፡በተደጋጋሚ ጊዜ የኃይል መቆራረጥ የሚስተዋልባቸውን አካባቢዎች በመለየት በመካከለኛና በዝቅተኛ መስመሮች ላይ ጭነት የማመጣጠንና የቅድመ መከላከል ጥገና ስራዎች በመሰራት ላይ መሆኑንንም አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ በመሆን ከኃይል ማመንጫ ጀምሮ እስከ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና ትራንስፎርመሮች ብልሽቶች ሲያጋጥሙ በአፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውም ተገልጿል፡፡
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአምስት ቋንቋዎች የተሰናዳ የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት መተግበሩን አስታወቀ!
በኢትዮጵያውያን የተሠራና ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛል የተባለና ‹‹ጉዞ ጐ›› የተባለ በአምስት ቋንቋዎችና በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የተሠራ የኤሌክሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት መተግበሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ፡፡
ጉዞ ጐ የተሰኘው የበረራ ትኬት ሽያጭ ማከናወኛ ሶፍትዌር በአማርኛ፣ በኦሮሚኛ፣ በትግሪኛ፣ በሶማሊኛና እንግሊዝኛ ወይም እንዲተገበር ያደረገው ሶልጌት ትራቭል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው ስምምነት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ በረራ ካላቸው አሥር አየር መንገዶች ጋር የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ዘዴውን በመተግበር፣ በባንኩ በኩል የአየር ትኬት ሽያጭ በኦንላይን መጀመሩን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. የስምምነት ሰነድ በመፈጸም ትግበራውን ይፋ አድርገዋል፡፡
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ዮሐንስ ሚሊዮን፣ አዲስ የተተገበረውን የኦንላይን ኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ዘዴን በሚመለከት እንደገለጹት፣ የክፍያ ሥርዓትን ከማዘመን አንፃር ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡ ሶልጌት ትራቭል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያበለፀገው ጉዞ ጐ ዲጂታላይዝ የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መተግበሪያ፣ የአየር በረራ ትኬቶችን የመቁረጥና ለደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት የሚያገኙበት አሠራር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያውያን የተሠራና ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛል የተባለና ‹‹ጉዞ ጐ›› የተባለ በአምስት ቋንቋዎችና በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የተሠራ የኤሌክሮኒክስ ክፍያ ሥርዓት መተግበሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ፡፡
ጉዞ ጐ የተሰኘው የበረራ ትኬት ሽያጭ ማከናወኛ ሶፍትዌር በአማርኛ፣ በኦሮሚኛ፣ በትግሪኛ፣ በሶማሊኛና እንግሊዝኛ ወይም እንዲተገበር ያደረገው ሶልጌት ትራቭል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው ስምምነት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ በረራ ካላቸው አሥር አየር መንገዶች ጋር የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ዘዴውን በመተግበር፣ በባንኩ በኩል የአየር ትኬት ሽያጭ በኦንላይን መጀመሩን የሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. የስምምነት ሰነድ በመፈጸም ትግበራውን ይፋ አድርገዋል፡፡
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ዮሐንስ ሚሊዮን፣ አዲስ የተተገበረውን የኦንላይን ኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ዘዴን በሚመለከት እንደገለጹት፣ የክፍያ ሥርዓትን ከማዘመን አንፃር ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡ ሶልጌት ትራቭል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያበለፀገው ጉዞ ጐ ዲጂታላይዝ የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መተግበሪያ፣ የአየር በረራ ትኬቶችን የመቁረጥና ለደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት የሚያገኙበት አሠራር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ለ1 ሺህ 29 የአየር ኃይል መኮንኖች የማእረግ እድገት ሰጠ!
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ለ1 ሺህ 29 የአየር ኃይል መኮንኖች የማእረግ እድገት ሰጠ።
የማእረግ እድገቱኑን የሰጡት የአየር ኃይሉ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ይልማ መርዳሳ በስነ-ስርአቱ ላይ እንደተናገሩት የማእረግ እድገቱ ለተጨማሪ ኃላፊነት የሚጋብዝ በመሆኑ መኮንኖቹ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን ለስኬት ማብቃት እንዳለባቸው አሳስበዋል።በእለቱ የአየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮችን ሀብት ማስመዝገብ፣ የተቋሙ የድህረ ገፅ ምርቃት እና የአብራሪዎች ትጥቅ ትውውቅ ተደርጓል።በዝግጅቱ ላይ ሰራዊቱ “ለገበታ ለሀገር” ፕሮጀክቶችም የአንድ ወር ሙሉ ደሞዛቸውን እንደሚሰጡ ተገልጿል።
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ለ1 ሺህ 29 የአየር ኃይል መኮንኖች የማእረግ እድገት ሰጠ።
የማእረግ እድገቱኑን የሰጡት የአየር ኃይሉ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ይልማ መርዳሳ በስነ-ስርአቱ ላይ እንደተናገሩት የማእረግ እድገቱ ለተጨማሪ ኃላፊነት የሚጋብዝ በመሆኑ መኮንኖቹ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን ለስኬት ማብቃት እንዳለባቸው አሳስበዋል።በእለቱ የአየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮችን ሀብት ማስመዝገብ፣ የተቋሙ የድህረ ገፅ ምርቃት እና የአብራሪዎች ትጥቅ ትውውቅ ተደርጓል።በዝግጅቱ ላይ ሰራዊቱ “ለገበታ ለሀገር” ፕሮጀክቶችም የአንድ ወር ሙሉ ደሞዛቸውን እንደሚሰጡ ተገልጿል።
[EBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፖሊስ በአሥራት ጋዜጠኞች ላይ ያቀረበውን የይግባኝ ጥያቄ ውድቅ አደረገ።
የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ይግባኝ የወንጀል ችሎት ፖሊስ በአሥራት ጋዜጠኞች ላይ ያቀረበውን የይግባኝ ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።ፖሊስ የአሥራት ጋዜጠኞች በዋስትና ከእስር ቢፈቱ መረጃ ያጠፉብኛል ቢልም ፍርድ ቤቱ ይግባኙን አልተቀበለውም።ፖሊስ ከአራቱ የአሥራት ጋዜጠኞች መካከል በበላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብርና ምስጋናው ከፈለኝ ላይ ይግባኝ ጠይቆ የነበር ሲሆን በዋነኛነት ከኢመድኤ / INSA፣ ከሆስፒታል እና ከብሮድካስት ባለስልጣን መረጃ እንደሚያመጣ ጠቅሶ ከእስር ከወጡ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስለሆኑ መረጃ ያጠፉብኛል ብሏል ማለቱን አስራት ሚዲያ በፌስ ቡክ ገጹ ይፋ አደርጓል።
ይሁንና ፍርድ ቤቱ መረጃ ይመጣባቸዋል ከሚባሉት ተቋማት መረጃ ማጥፋት ሆነ ማዛባት እንደማይቻል ገልፆ የእስር ፍርድ ቤቱ በተደጋጋሚ ፖሊስ መረጃ እንዲታቀርብ ቀጠሮ ከሰጠ በኋላ ጋዜጠኞቹ በዋስትና እንዲለቀቁ ማድረጉ ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብሎታል።የአሥራት ጋዜጠኞች በአራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋስትና እንዲወጡ ከተወሰነላቸው በኋላ እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር የከፈሉ ሲሆን ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ በእስር እንዳቆያቸው ጠበቃቸው መግለፃቸው ይታወቃል።
[ኢትዮ ኤፍ ኤም]
@YeneTube @FikerAssefa
የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ይግባኝ የወንጀል ችሎት ፖሊስ በአሥራት ጋዜጠኞች ላይ ያቀረበውን የይግባኝ ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።ፖሊስ የአሥራት ጋዜጠኞች በዋስትና ከእስር ቢፈቱ መረጃ ያጠፉብኛል ቢልም ፍርድ ቤቱ ይግባኙን አልተቀበለውም።ፖሊስ ከአራቱ የአሥራት ጋዜጠኞች መካከል በበላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብርና ምስጋናው ከፈለኝ ላይ ይግባኝ ጠይቆ የነበር ሲሆን በዋነኛነት ከኢመድኤ / INSA፣ ከሆስፒታል እና ከብሮድካስት ባለስልጣን መረጃ እንደሚያመጣ ጠቅሶ ከእስር ከወጡ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስለሆኑ መረጃ ያጠፉብኛል ብሏል ማለቱን አስራት ሚዲያ በፌስ ቡክ ገጹ ይፋ አደርጓል።
ይሁንና ፍርድ ቤቱ መረጃ ይመጣባቸዋል ከሚባሉት ተቋማት መረጃ ማጥፋት ሆነ ማዛባት እንደማይቻል ገልፆ የእስር ፍርድ ቤቱ በተደጋጋሚ ፖሊስ መረጃ እንዲታቀርብ ቀጠሮ ከሰጠ በኋላ ጋዜጠኞቹ በዋስትና እንዲለቀቁ ማድረጉ ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብሎታል።የአሥራት ጋዜጠኞች በአራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋስትና እንዲወጡ ከተወሰነላቸው በኋላ እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር የከፈሉ ሲሆን ፖሊስ በሕገወጥ መንገድ በእስር እንዳቆያቸው ጠበቃቸው መግለፃቸው ይታወቃል።
[ኢትዮ ኤፍ ኤም]
@YeneTube @FikerAssefa