አቶ ጃዋር መሐመድና አቶ በቀለ ገርባ እንዲገናኙ ትዕዛዝ ተሰጠ!
ከኦሮሚኛ ሙዚቃ ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በተጠረጠሩበት የወንጀል ድርጊት በእሥር ላይ የሚገኙት አቶ ጃዋር መሐመድና አቶ በቀለ ገርባ ለየብቻቸው ታስረው የቆዩ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤት እንዲቀላቀሉ ወይም እንዲገናኙ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ ትዕዛዙን የሰጠው ነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ወንጀል ችሎት ሲሆን፣ አቶ በቀለ ገርባ ቀደም ብሎ በነበረው ችሎት ባቀረቡት አቤቱታ ምክንያት ነው፡፡
አቶ በቀለ በአቤቱታቸው ለፍርድ ቤቱ እንደገለጹት፣ እሳቸውና አቶ ጃዋር የታሰሩት ለየብቻቸው ነው፡፡አየርም ሆነ የፀሐይ ብርሃን እያገኙ አይደለም፡፡ በመሆኑም አብረው እንዲሆኑ፣ አየርና የፀሐይ ብርሃን እንዲያገኙ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ያቀረቡትን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ ተመልክቶ፣ እንዲቀላቀሉ ወይም እንዲገናኙ እንዲደረግ ለፌዴራል ፖሊስ ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
ከኦሮሚኛ ሙዚቃ ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በተጠረጠሩበት የወንጀል ድርጊት በእሥር ላይ የሚገኙት አቶ ጃዋር መሐመድና አቶ በቀለ ገርባ ለየብቻቸው ታስረው የቆዩ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤት እንዲቀላቀሉ ወይም እንዲገናኙ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ ትዕዛዙን የሰጠው ነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ወንጀል ችሎት ሲሆን፣ አቶ በቀለ ገርባ ቀደም ብሎ በነበረው ችሎት ባቀረቡት አቤቱታ ምክንያት ነው፡፡
አቶ በቀለ በአቤቱታቸው ለፍርድ ቤቱ እንደገለጹት፣ እሳቸውና አቶ ጃዋር የታሰሩት ለየብቻቸው ነው፡፡አየርም ሆነ የፀሐይ ብርሃን እያገኙ አይደለም፡፡ በመሆኑም አብረው እንዲሆኑ፣ አየርና የፀሐይ ብርሃን እንዲያገኙ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ያቀረቡትን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ ተመልክቶ፣ እንዲቀላቀሉ ወይም እንዲገናኙ እንዲደረግ ለፌዴራል ፖሊስ ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ኪት ማምረት ልትጀምር ነው፡- ጤና ሚኒስቴር
በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ኪት ከአንድ ወር በኋላ ማምረት እንደሚጀመር የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ለኢዜአ እንደተናገሩት ኮሮናቫይረስን የመመርመር አቅምን ከፍ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው።በአሁኑ ወቅትም ከአንድ ወር በኋላ ከቻይና መንግሥት ጋር በመተባበር የመመርመሪያ ኪት ለማምረት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።ለእዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ድጋፉን ከምታደርገው የቻይና መንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል።“የመመርመሪያ ኪቱን በአገር ውስጥ ማምረት ሲጀመር ከውጭ የሚገባውን ኪት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል” ያሉት ዶክተር ደረጀ፣ ምርቱ ለሌሎች የአፍሪካ አገራት እንደሚዳረስም ተናግረዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የመመርመር አቅም በእጅጉ ከፍ እንደሚያደርገው ጠቁመዋል።በሌላ በኩል በአሁኑ ወቅት የኢንፌክሽን መከላከያ ግብዓቶች በኢትዮጵያ በስፋት መመረት መጀመራቸውን ጠቁመው፣ የኮሮናቫይረስ መከላከያ ቁሶችን ወደ ውጭ አገራት መላክ መጀመሩንም ገልጸዋል።በሐዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ እነዚህን ቁሶች የሚያመርቱ ኩባንያዎች ቀዳሚ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል።በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 52 የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት የሚገኙ ሲሆን በእነዚህም በቀን ከ20 ሺህ በላይ ናሙናዎችን መመርመር ተችሏል።
[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ኪት ከአንድ ወር በኋላ ማምረት እንደሚጀመር የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ለኢዜአ እንደተናገሩት ኮሮናቫይረስን የመመርመር አቅምን ከፍ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው።በአሁኑ ወቅትም ከአንድ ወር በኋላ ከቻይና መንግሥት ጋር በመተባበር የመመርመሪያ ኪት ለማምረት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።ለእዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ድጋፉን ከምታደርገው የቻይና መንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል።“የመመርመሪያ ኪቱን በአገር ውስጥ ማምረት ሲጀመር ከውጭ የሚገባውን ኪት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል” ያሉት ዶክተር ደረጀ፣ ምርቱ ለሌሎች የአፍሪካ አገራት እንደሚዳረስም ተናግረዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የመመርመር አቅም በእጅጉ ከፍ እንደሚያደርገው ጠቁመዋል።በሌላ በኩል በአሁኑ ወቅት የኢንፌክሽን መከላከያ ግብዓቶች በኢትዮጵያ በስፋት መመረት መጀመራቸውን ጠቁመው፣ የኮሮናቫይረስ መከላከያ ቁሶችን ወደ ውጭ አገራት መላክ መጀመሩንም ገልጸዋል።በሐዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ እነዚህን ቁሶች የሚያመርቱ ኩባንያዎች ቀዳሚ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል።በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 52 የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት የሚገኙ ሲሆን በእነዚህም በቀን ከ20 ሺህ በላይ ናሙናዎችን መመርመር ተችሏል።
[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa
ጉዳት ለደረሰባቸው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ማቋቋሚያና ለቀጣይ ዕርዳታ የሦስት ቢሊዮን ብር ዕቅድ ይፋ ተደረገ!
ከጠቅላይ ቤተክህነትና የአገር ሽማግሌዎች ተውጣጥቶ የተቋቋመው ዓብይ ኮሚቴ በኦሮሚያ ክልል ጉዳት ለደረሰባቸው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ማቋቋሚያና ድንገተኛ ለሆኑ አደጋዎች የሚውል የሦስት ቢሊዮን ብር ገቢ ማሰባሰቢያ ዕቅድ ይፋ አደረገ፡፡የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በተገኙበትና የእሳቸውን ይሁንታ ያገኘው ዕቅድ ይፋ የተደረገው ነሐሴ 28 ቀን ሲሆን፣ በማግስቱ ከነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ሥራ መገባቱን፣ የዓብይ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሕግ ባለሙያው አቶ መኮንን ሰሙ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
የሦስት ቢሊዮን ብር ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ተግባራዊ የሚደረገው ወይም ለማግኘት የታቀደው፣ ከአብያተ ክርስቲያን፣ ከምዕመናን፣ ከቤተ ክርስቲያኒቷ አገልጋዮች ከዩኒቨርሲቲ ኮሌጆችና ከሁሉም ኢትዮጵያውያን ወገኖች መሆኑንና በእርግጠኝነት በአጭር ጊዜ ውስጥ ያሰቡትን እንደሚያሳኩ ሰብሳቢው ተናግረዋል፡፡የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም መነሻው በኦሮሚያ ክልል ከሰባት በላይ ዞኖችና ከ25 በላይ ወረዳዎች ላይ እምነታቸውን መሠረት ያደረገ ጥቃት ለደረሰባቸውና ቤታቸውን፣ ንብረታቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ላጡ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ማቋቋሚያ ቢሆንም፣ ሌሎች ያልታሰቡና ድንገተኛ ችግሮች ሲያጋጥሙ መርጃ የሚሆን ዘለቄታነት ያለው መተማመኛ የዕርዳታ ገንዘብ እንዲሆን ማድረግ መሆኑንም አክለዋል፡፡
በክልሉ ላይ የደረሰውን በተለይ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን በመለየት የደረሰባቸውን ግድያ፣ የአካል መጉደል፣ ንብረት መዝረፍና ማቃጠል፣ ከቤተ ክህነትና ከአገር ሽማግሌዎች የተውጣጣው ቡድን፣ የመገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም ወገኖች ሆነው በ25 ወረዳዎች ተዘዋውረው በመጎብኘትና በአካል በመገኘት የማጽናናትና የማረጋጋት ሥራ መሠራቱን የገለጹት አቶ መኮንን፣ በአካባቢው ባለው ሀገረ ስብከት አካውንት ተከፍቶ 42 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡
ይህ የተሰበሰበ ገንዘብ በማንም እጅ ሳይገባ በቀጥታ ተጎጂዎቹ በሚከፍቱት አካውንት ከአዲስ ዓመት በፊት ገቢ እንደሚደረግላቸው አስታውቀዋል፡፡ እጃቸውን ለዘረጉ በአገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉ ወገኖችንም አመስግነዋል፡፡ለተጎጂዎቹ የሚሰጠው ገንዘብ በሥፍራው ተገኝቶ የእያንዳንዱን ተጎጂ ወገን የጉዳት መጠን አጥንቶ የመጣ ቡድን ባቀረበው የጉዳት መጠን ላይ ተመሥርቶ መሆኑንም አቶ መኮንን ጠቁመዋል፡፡
በክልሉ ላይ በተለይ ሃይማኖትንና ማንነትን መሠረት በማድረግ በደረሰው ግፍ የተመላበት የጭካኔ ድርጊት፣ መላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችንና ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ቤተ ክርስቲያንን እንዳሳዘነ ጠቁመው፣ መንግሥት በድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ ሕግን የማስከበርና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ እየወሰደ ያለው ዕርምጃ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል፡፡ ነገር ግን አሁንም ቢሆን በቀጥታ በድርጊቱ ተሳትፎ የነበራቸው ግለሰቦችና በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ያሉ አመራሮች በመኖራቸው፣ የክልሉ መንግሥትና የፌዴራል መንግሥት በመተባበር በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡ ምንም ሳያጠፉ ታስረው እየተንገላቱ ያሉ ወገኖች በመኖራቸው እነሱም እንዲፈቱ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
ከጠቅላይ ቤተክህነትና የአገር ሽማግሌዎች ተውጣጥቶ የተቋቋመው ዓብይ ኮሚቴ በኦሮሚያ ክልል ጉዳት ለደረሰባቸው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ማቋቋሚያና ድንገተኛ ለሆኑ አደጋዎች የሚውል የሦስት ቢሊዮን ብር ገቢ ማሰባሰቢያ ዕቅድ ይፋ አደረገ፡፡የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በተገኙበትና የእሳቸውን ይሁንታ ያገኘው ዕቅድ ይፋ የተደረገው ነሐሴ 28 ቀን ሲሆን፣ በማግስቱ ከነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ሥራ መገባቱን፣ የዓብይ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሕግ ባለሙያው አቶ መኮንን ሰሙ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
የሦስት ቢሊዮን ብር ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ተግባራዊ የሚደረገው ወይም ለማግኘት የታቀደው፣ ከአብያተ ክርስቲያን፣ ከምዕመናን፣ ከቤተ ክርስቲያኒቷ አገልጋዮች ከዩኒቨርሲቲ ኮሌጆችና ከሁሉም ኢትዮጵያውያን ወገኖች መሆኑንና በእርግጠኝነት በአጭር ጊዜ ውስጥ ያሰቡትን እንደሚያሳኩ ሰብሳቢው ተናግረዋል፡፡የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም መነሻው በኦሮሚያ ክልል ከሰባት በላይ ዞኖችና ከ25 በላይ ወረዳዎች ላይ እምነታቸውን መሠረት ያደረገ ጥቃት ለደረሰባቸውና ቤታቸውን፣ ንብረታቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ላጡ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ማቋቋሚያ ቢሆንም፣ ሌሎች ያልታሰቡና ድንገተኛ ችግሮች ሲያጋጥሙ መርጃ የሚሆን ዘለቄታነት ያለው መተማመኛ የዕርዳታ ገንዘብ እንዲሆን ማድረግ መሆኑንም አክለዋል፡፡
በክልሉ ላይ የደረሰውን በተለይ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን በመለየት የደረሰባቸውን ግድያ፣ የአካል መጉደል፣ ንብረት መዝረፍና ማቃጠል፣ ከቤተ ክህነትና ከአገር ሽማግሌዎች የተውጣጣው ቡድን፣ የመገናኛ ብዙኃንና ሌሎችም ወገኖች ሆነው በ25 ወረዳዎች ተዘዋውረው በመጎብኘትና በአካል በመገኘት የማጽናናትና የማረጋጋት ሥራ መሠራቱን የገለጹት አቶ መኮንን፣ በአካባቢው ባለው ሀገረ ስብከት አካውንት ተከፍቶ 42 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡
ይህ የተሰበሰበ ገንዘብ በማንም እጅ ሳይገባ በቀጥታ ተጎጂዎቹ በሚከፍቱት አካውንት ከአዲስ ዓመት በፊት ገቢ እንደሚደረግላቸው አስታውቀዋል፡፡ እጃቸውን ለዘረጉ በአገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉ ወገኖችንም አመስግነዋል፡፡ለተጎጂዎቹ የሚሰጠው ገንዘብ በሥፍራው ተገኝቶ የእያንዳንዱን ተጎጂ ወገን የጉዳት መጠን አጥንቶ የመጣ ቡድን ባቀረበው የጉዳት መጠን ላይ ተመሥርቶ መሆኑንም አቶ መኮንን ጠቁመዋል፡፡
በክልሉ ላይ በተለይ ሃይማኖትንና ማንነትን መሠረት በማድረግ በደረሰው ግፍ የተመላበት የጭካኔ ድርጊት፣ መላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችንና ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ቤተ ክርስቲያንን እንዳሳዘነ ጠቁመው፣ መንግሥት በድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ ሕግን የማስከበርና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ እየወሰደ ያለው ዕርምጃ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል፡፡ ነገር ግን አሁንም ቢሆን በቀጥታ በድርጊቱ ተሳትፎ የነበራቸው ግለሰቦችና በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ያሉ አመራሮች በመኖራቸው፣ የክልሉ መንግሥትና የፌዴራል መንግሥት በመተባበር በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡ ምንም ሳያጠፉ ታስረው እየተንገላቱ ያሉ ወገኖች በመኖራቸው እነሱም እንዲፈቱ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa
መሐመድ አል አሩሲ ተሸለመ!
ከኢትዮጵያዊ ቤተሰቦች በሳዑዲ አረቢያ የተወለደውና የሕዳሴ ጎድብን በሚመለከት ስለኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለማቀፍ መገናኛ ብዙኅን ሙግት ያደርጋል። ይህንንም በራሱ ተነሳሽትን ያደረገው ነው።አረብኛ ቋንቋ ተናጋሪ በመሆኑም የኢትዮጵያን ሐሳብና እውነት በዛው ቋንቋ ለሰሚው ሲያስረዳና ሲከራከር የቆየው አሕመድ አል አሩሲ የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
ከኢትዮጵያዊ ቤተሰቦች በሳዑዲ አረቢያ የተወለደውና የሕዳሴ ጎድብን በሚመለከት ስለኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለማቀፍ መገናኛ ብዙኅን ሙግት ያደርጋል። ይህንንም በራሱ ተነሳሽትን ያደረገው ነው።አረብኛ ቋንቋ ተናጋሪ በመሆኑም የኢትዮጵያን ሐሳብና እውነት በዛው ቋንቋ ለሰሚው ሲያስረዳና ሲከራከር የቆየው አሕመድ አል አሩሲ የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።
[Addis Maleda]
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት አምስት ወራት በኮቪድ 19 ኮሮና ቫይረስ ምክንያት የገዛ መኖሪያ ግቢያቸውን ሳይቀር በመስጠት፣ መጠለያ የሌላቸውን በመደገፍ የበጎ አድራጎት ሥራ የሠሩት ካሊድ ናስር በ8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ድርጅት ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል።
በሁለተኛም ልዩ ተሸላሚ የሆኑት ኪሮስ አስፋው ናቸው። እኚህ ግለሰብ ከህዳሴ ግድብ ግንባታ ጋር በተያያዘ ባደረጉት በጎ ሥራ የተሸለሙ ሲሆን፤ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ያለማቋረጥ መቶ ጊዜ ቦንድ የገዙ መሆናቸውም በመድረኩ ተጠቅሷል።
የንባብ ለሕይወት መሥራችና አዘጋጆች መካከል የሚገኘው ጋዜጠኛ ቢንያም ከበደ የ8 ኛው በጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።ይልቁንም በኮቪድ 19 ወቅት ልጆች በየቤታቸው ሲሆኑ የሚመለከቱት የሚመጥናቸውና በተለያየ ቋንቋ መሰናዶዎች የሚቀርብበት የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቭዥንን ከመክፈት ጀምሮ ያደረጉት አስተዋፅኦም የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚ አድርጓቸዋል።
[@AddisMaleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በሁለተኛም ልዩ ተሸላሚ የሆኑት ኪሮስ አስፋው ናቸው። እኚህ ግለሰብ ከህዳሴ ግድብ ግንባታ ጋር በተያያዘ ባደረጉት በጎ ሥራ የተሸለሙ ሲሆን፤ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ያለማቋረጥ መቶ ጊዜ ቦንድ የገዙ መሆናቸውም በመድረኩ ተጠቅሷል።
የንባብ ለሕይወት መሥራችና አዘጋጆች መካከል የሚገኘው ጋዜጠኛ ቢንያም ከበደ የ8 ኛው በጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።ይልቁንም በኮቪድ 19 ወቅት ልጆች በየቤታቸው ሲሆኑ የሚመለከቱት የሚመጥናቸውና በተለያየ ቋንቋ መሰናዶዎች የሚቀርብበት የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቭዥንን ከመክፈት ጀምሮ ያደረጉት አስተዋፅኦም የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚ አድርጓቸዋል።
[@AddisMaleda]
@YeneTube @FikerAssefa
በሁለተኛ ዙር የሽልማት መሰናዶ በአዲስ አበባ ዮኒቨርስቲ መምህርነትና ተመራማሪነትን ጨምሮ በተለያየ ኃላፊነት አገልግለዋል። አሁንም በኢትዮጵያ በተለያዩና በርካታ ኃላፊነቶች እያገለገሉ ነው። የውሃ ዲፕሎማሲ ባለሞያ ሲሆኑ ከህዳሴ ግድቡ ግንባታ ጀምሮ ገለፃ በመስጠት ይታወቃሉ። ድርድር ላይ ይሳተፋሉ፤ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ በሚነሳባቸው በመድረኮችም ይሳተፉሉ። በጉዳዩ በማማከርም ይጠቀሳሉ።በድርድሩ ሂደት በዓለም መገናኛ ብዙኅን ሳይቀር የኢትዮጵያ ድምፅ ሆነው የተሟገቱም ናቸው።አባይን በሚመለከት የፅፉትን መፅሐፍም በበይነ መረብ በነፃ አሰራጭተዋል። ዶክተር ያዕቆቦ አርሳኖ የ8 ኛው በጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል።
[አዲስ ማለዳ]
@YeneTube @FikerAssefa
[አዲስ ማለዳ]
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል በሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው በከፊል የመጫን ዕገዳ ተነሳ!
ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ በሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ላይ ተጥሎ የቆየው በግማሽ የመጫን ዕገዳ መነሳቱን የአማራ ክልል መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ውቤ አጥናፉ ለኢዜአ እንደገለጹት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ክስተት ተከትሎ ላላፉት አምስት ወራት አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተደንግጎ መቆየቱ ይታወሳል።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ የከተማ ታክሲዎች፣ ባለሦስት እግር ባጃጅ ታክሲዎች፣ ሀገር አቋራጭ አውቶብሶችና ሌሎች የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ከመደበኛ የመጫን አቅማቸው በግማሽ እንዲቀንሱ አስገዳጅ መመሪያ ወጥቶ ተግባራዊ ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰዋል።
ይሁንና የፌዴራል ትራንስፖርት ባለሥልጣን የአዋጁ ጊዜ መጠናቀቁን በማስመልከት ዕገዳው የተነሳ መሆኑን ዛሬ ለቢሮው በላከው ደብዳቤ በማሳወቁ ከዛሬ ጀምሮ በክልሉ ሁሉም ዞኖችና የከተማ አስተዳደሮች ዕገዳው መነሳቱን እንዲያውቁት ተደርጎ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩን አስታውቀዋል።ማንኛውም የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭ ተሽከርካሪዎች በከፊል የመጫን ዕገዳው በመነሳቱ በወንበራቸው ልክ በመጫን ተጠቃሚዎችን በመደበኛው ታሪፍ የሚያስከፍሉ ይሆናል” ብለዋል።አሽከርካሪዎች፣ ረዳቶችና ተገልጋዮች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አስገዳጅ መሆኑን በመገንዘብ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ በሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ላይ ተጥሎ የቆየው በግማሽ የመጫን ዕገዳ መነሳቱን የአማራ ክልል መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ውቤ አጥናፉ ለኢዜአ እንደገለጹት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ክስተት ተከትሎ ላላፉት አምስት ወራት አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተደንግጎ መቆየቱ ይታወሳል።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ የከተማ ታክሲዎች፣ ባለሦስት እግር ባጃጅ ታክሲዎች፣ ሀገር አቋራጭ አውቶብሶችና ሌሎች የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ከመደበኛ የመጫን አቅማቸው በግማሽ እንዲቀንሱ አስገዳጅ መመሪያ ወጥቶ ተግባራዊ ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰዋል።
ይሁንና የፌዴራል ትራንስፖርት ባለሥልጣን የአዋጁ ጊዜ መጠናቀቁን በማስመልከት ዕገዳው የተነሳ መሆኑን ዛሬ ለቢሮው በላከው ደብዳቤ በማሳወቁ ከዛሬ ጀምሮ በክልሉ ሁሉም ዞኖችና የከተማ አስተዳደሮች ዕገዳው መነሳቱን እንዲያውቁት ተደርጎ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩን አስታውቀዋል።ማንኛውም የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭ ተሽከርካሪዎች በከፊል የመጫን ዕገዳው በመነሳቱ በወንበራቸው ልክ በመጫን ተጠቃሚዎችን በመደበኛው ታሪፍ የሚያስከፍሉ ይሆናል” ብለዋል።አሽከርካሪዎች፣ ረዳቶችና ተገልጋዮች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አስገዳጅ መሆኑን በመገንዘብ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ዋልያ ቢራ በአዲስ አበባ በጎርፍ ለተጠቁ እና ሌሎች ወገኖች የበዓል ስጦታ አበረከተ
በአዲስ አበባ ቂሊንጦ አካባቢ በቅርቡ በጎርፍ ለተጠቁ ወገኖች እና ሌሎች በከተማው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ወገኖች ዋልያ ቢራ የበዓል ስጦታ አበረከተ፡፡ ስጦታው ለእያንዳንዱ ግለሰብ 1 በግ፣ 5 ኪሎ ዘይት፣ አምስት ኪሎ የስንዴ ዱቄት እና 5 ኪሎ ሽንኩርትን ያካተተ ነው፡፡
‹‹በጎ ሥራን በተግባር እንቀላቀል›› በሚል የተዘጋጀው እንቅስቃሴ አካል የሆነው የዋልያ የበአል ድጋፍ ተጠቃሚ የሚያደርገው በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ 150 ወገኖችን ነው፡፡ የተደረገው ድጋፍ አጠቃለይ ወጪው 1 ሚሊዮን ብር ይደርሳል፡፡
በጎርፍ ከተጠቁት ውጪ የበዓል ስጦታውን ያገኙት ወገኖች የተመረጡት እንዳልክ እና ማህደር በተሰኘው ሬዲዮ ፕሮግራም አማካኝነት በሕዝብ በተደረገ ጥቆማ ነው፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
በአዲስ አበባ ቂሊንጦ አካባቢ በቅርቡ በጎርፍ ለተጠቁ ወገኖች እና ሌሎች በከተማው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ወገኖች ዋልያ ቢራ የበዓል ስጦታ አበረከተ፡፡ ስጦታው ለእያንዳንዱ ግለሰብ 1 በግ፣ 5 ኪሎ ዘይት፣ አምስት ኪሎ የስንዴ ዱቄት እና 5 ኪሎ ሽንኩርትን ያካተተ ነው፡፡
‹‹በጎ ሥራን በተግባር እንቀላቀል›› በሚል የተዘጋጀው እንቅስቃሴ አካል የሆነው የዋልያ የበአል ድጋፍ ተጠቃሚ የሚያደርገው በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ 150 ወገኖችን ነው፡፡ የተደረገው ድጋፍ አጠቃለይ ወጪው 1 ሚሊዮን ብር ይደርሳል፡፡
በጎርፍ ከተጠቁት ውጪ የበዓል ስጦታውን ያገኙት ወገኖች የተመረጡት እንዳልክ እና ማህደር በተሰኘው ሬዲዮ ፕሮግራም አማካኝነት በሕዝብ በተደረገ ጥቆማ ነው፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 1,206 ሰዎች በኮሮና ሲያዙ የ 21 ሰዎች ህይወት አለፈ!
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 25,158 የላቦራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 1,206 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
531 ሰዎች ሲያገግሙ 21 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።
እስካሁን በአጠቃላይ 58 ሺ 672 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 21 ሺ 307 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን የ918 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 25,158 የላቦራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 1,206 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
531 ሰዎች ሲያገግሙ 21 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።
እስካሁን በአጠቃላይ 58 ሺ 672 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 21 ሺ 307 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን የ918 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
የኢዜማ ከፍተኛ አመራሮች የዓይን ብሌናቸውን ከህልፈታቸው በኋላ ለመለገስ ቃል ገቡ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፓርቲ (ኢዜማ) ከፍተኛ አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች በኢትዮጵያ የዓይን ባንክ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ከህልፈታቸው በኋላ የዓይን ብሌናቸውን ለመለገስ የዓይን ባንኩ የቃልኪዳን ሰነድ ላይ ፊርማቸውን አስቀምጠዋል።የኢትዮጵያ የዓይን ባንክ ዳይሬክተር ወ/ሮ ለምለም አየለ አባላቱ መጥተው ቃል በመግባታቸው ምስጋናቸውን አቅርበው ሌሎች የህብረተሰብ አካለትም ከህልፈታቸው በኋላ ብሌናቸውን ለመለገስ ቃል እንደገቡ ጥሪ አቅርበዋል::
የኢዜማ ስራ አስፈጻሚ አባል እና የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ በበኩላቸው ከስጦታወች ሁሉ የላቀውን የብርሃን ስጦታ ከህልፈታችን በኋላ ለመልገስ ቃል በመግባታችን ኩራት ይሰማናል በማለት በቀጣይም ሌሎች ማህበረስቦችን በማንቃት ቃል እንድገቡ ለማድረግ ጥረት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡የኢትዮጵያ የዓይን ባንክ እስካሁን ለ2 ሺህ 465 ወገኖች የብሌን ንቅለ ተከላ ተከናውኖላቸው ብርሃናቸው እንዲመለስ ማድረጉን ባንኩ አስታውቋል።
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፓርቲ (ኢዜማ) ከፍተኛ አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች በኢትዮጵያ የዓይን ባንክ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ከህልፈታቸው በኋላ የዓይን ብሌናቸውን ለመለገስ የዓይን ባንኩ የቃልኪዳን ሰነድ ላይ ፊርማቸውን አስቀምጠዋል።የኢትዮጵያ የዓይን ባንክ ዳይሬክተር ወ/ሮ ለምለም አየለ አባላቱ መጥተው ቃል በመግባታቸው ምስጋናቸውን አቅርበው ሌሎች የህብረተሰብ አካለትም ከህልፈታቸው በኋላ ብሌናቸውን ለመለገስ ቃል እንደገቡ ጥሪ አቅርበዋል::
የኢዜማ ስራ አስፈጻሚ አባል እና የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ በበኩላቸው ከስጦታወች ሁሉ የላቀውን የብርሃን ስጦታ ከህልፈታችን በኋላ ለመልገስ ቃል በመግባታችን ኩራት ይሰማናል በማለት በቀጣይም ሌሎች ማህበረስቦችን በማንቃት ቃል እንድገቡ ለማድረግ ጥረት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡የኢትዮጵያ የዓይን ባንክ እስካሁን ለ2 ሺህ 465 ወገኖች የብሌን ንቅለ ተከላ ተከናውኖላቸው ብርሃናቸው እንዲመለስ ማድረጉን ባንኩ አስታውቋል።
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ መንግስት ዝርዝር ነገር እስኪያወጣ ድረስ ታክሲዎች በግማሽ መጫናቸውን እንዲቀጥሉ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አሳሰበ።
በኮሮና ቫይረስ መስፋፋት ምክንያት የትራንስፖርት አገልግሎት በተለይም የታክሲ አገልግሎት በግማሽ እንዲጭኑ ተሳፋሪዎች በእጥፍ እንዲከፍሉ መደረጉ ይታወሳል።ለአምስት ወራት የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም ነሀሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም መጠናቀቁን ተከትሎ የተወሰኑ ክልሎች በግማሽ የመጫን አገልግሎቱ መነሳቱን አሳውቀዋል።ይሁንን በአዲስ አበባ ታክሲዎች የአስቸኳይ አዋጁ መጠናቀቁን ተከትሎ ለምን ወደ ቀድሞው የትራስፖርት አገልግሎት አይመለስም ተብሎ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮን ተጠይቋል።የቢሮው የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ አቶ አረጋዊ ማሩ እንዳሉት ጉዳዩን በተመለከተ በመግለጫ እስከምናሳውቅ ድረስ ታክሲዎች በግማሽ መጫናቸውን እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ቢሮው ከደቂቃዎች በኋላ መግለጫ የሚሰጥ በመሆኑ ዝርዝር ነገሮችን ይፋ እናደርጋለን ብሏል።
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሮና ቫይረስ መስፋፋት ምክንያት የትራንስፖርት አገልግሎት በተለይም የታክሲ አገልግሎት በግማሽ እንዲጭኑ ተሳፋሪዎች በእጥፍ እንዲከፍሉ መደረጉ ይታወሳል።ለአምስት ወራት የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም ነሀሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም መጠናቀቁን ተከትሎ የተወሰኑ ክልሎች በግማሽ የመጫን አገልግሎቱ መነሳቱን አሳውቀዋል።ይሁንን በአዲስ አበባ ታክሲዎች የአስቸኳይ አዋጁ መጠናቀቁን ተከትሎ ለምን ወደ ቀድሞው የትራስፖርት አገልግሎት አይመለስም ተብሎ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮን ተጠይቋል።የቢሮው የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ አቶ አረጋዊ ማሩ እንዳሉት ጉዳዩን በተመለከተ በመግለጫ እስከምናሳውቅ ድረስ ታክሲዎች በግማሽ መጫናቸውን እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ቢሮው ከደቂቃዎች በኋላ መግለጫ የሚሰጥ በመሆኑ ዝርዝር ነገሮችን ይፋ እናደርጋለን ብሏል።
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
ከአዲስ አበባ ወደ ሁሉም የአገሪቱ ክፍል የሚደረጉ አውቶቡሶች በወንበር ልክ መጫን መጀመራቸውን የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን አስታወቀ።
በኮሮና ቫይረስ መስፋፋት ምክንያት የትራንስፖርት አገልግሎት በተለይም የታክሲ አገልግሎት በግማሽ እንዲጭኑ ተሳፋሪዎች በእጥፍ እንዲከፍሉ መደረጉ ይታወሳል።ለአምስት ወራት የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም ነሀሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም መጠናቀቁን ተከትሎ ትራንስፖርቱ በተለይም ከመናሀሪያዎች የሚደረጉ የትራንስፖርት አገልግሎት ወደ ቀድሞ ይዘቱ መመለሱ ተገልጿል።
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት አውቶቡሶች ከጷግሜ 1 ቀን 2012 ዓ.ም አንስቶ በወንበር ልክ እና በታሪፉ መሰረት ተሳፋሪዎቻቸውን ማስተናገድ መጀመራቸውን የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል።
የአማራ ክልል ትራንስፖርት ቢሮ የአስቸኳይ አዋጁ መነሳቱን ተከትሎ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች በወንበር ልክ እና በተቀመጠላቸው ታሪፍ ተሳፋሪዎችን እንዲጭኑ ማድረጉ ይታወሳል።የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ በበኩሉ በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መግለጫ እስከምሰጥ ድረስ ታክሲዎች በግማሽ መጫናችሁን ቀጥሉ ብሏል።
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሮና ቫይረስ መስፋፋት ምክንያት የትራንስፖርት አገልግሎት በተለይም የታክሲ አገልግሎት በግማሽ እንዲጭኑ ተሳፋሪዎች በእጥፍ እንዲከፍሉ መደረጉ ይታወሳል።ለአምስት ወራት የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም ነሀሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም መጠናቀቁን ተከትሎ ትራንስፖርቱ በተለይም ከመናሀሪያዎች የሚደረጉ የትራንስፖርት አገልግሎት ወደ ቀድሞ ይዘቱ መመለሱ ተገልጿል።
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት አውቶቡሶች ከጷግሜ 1 ቀን 2012 ዓ.ም አንስቶ በወንበር ልክ እና በታሪፉ መሰረት ተሳፋሪዎቻቸውን ማስተናገድ መጀመራቸውን የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል።
የአማራ ክልል ትራንስፖርት ቢሮ የአስቸኳይ አዋጁ መነሳቱን ተከትሎ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች በወንበር ልክ እና በተቀመጠላቸው ታሪፍ ተሳፋሪዎችን እንዲጭኑ ማድረጉ ይታወሳል።የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ በበኩሉ በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መግለጫ እስከምሰጥ ድረስ ታክሲዎች በግማሽ መጫናችሁን ቀጥሉ ብሏል።
[Ethio FM]
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሮናቫይረስ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሞ የነበረው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በሚቀጥለው ዓመት በማንኛውም ሁኔታ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዝዳንት "ኮቪድ-19 ጠፋም አልጠፋ በሚቀጥለው ዓመት ኦሊምፒክ ይካሄዳል" ብለዋል።ጆን ኮትስ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንዳረጋገጡት በሚቀጥለው ዓመት ኦሊምፒክ የሚጀምረው በሐምሌ 23 ይሆናል።ኦሊምፒክ መካሄድ የነበረበት ዘንድሮ በሐምሌ ወር ነበር። ሆኖም የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ተከትሎ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሞ ነበር።
ሆኖም ውድድሩን ከፈረንጆቹ 2021 ወዲያ መግፋት ስሜት የሚሰጥ ነገር አይደለም ብለዋል።በሐምሌ ወር የቶክዮ 2020 ኦሊምፒክ ሊቀመንበር ቶሺሮ ሙቶ "ውድድሮቹን በዝግ ስታዲየም ማካሄድ ይቻል ነበር። ያንን ስላልፈለግን ነው ያዘገየነው" ብለው ነበር።
ምናልባት ከየአገሩ የሚመጡ ወኪሎችን ቁጥር በመቀነስ፣ በየውድድሩ የሚታደሙ ተመልካቾችን በማሳነስ፣ እንዲሁም የመክፈቻና መዝጊያ ሥነ ሥርዓቱን ቀለል በማድረግ የሚካሄድበት መንገድ ሊቀየስ ይችላል።ከመላው ዓለም 11 ሺህ አትሌቶች ከ200 አገራት እንደሚገኙ ይጠበቅ ነበር።
በሚቀጥለው ዓመት ሐምሌ ላይ ውድድሩ ሲታሰብ የጉዞ ገደቦችን በተመለከተ የተባለ ነገር የለም።ሚስተር ሙቶ የኦሊምፒክ ውድድሩን ለማድረግ የኮቪድ-19 ክትባትን መጠበቅ አይኖርብንም ብለዋል። የጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው በወረርሽኝ መሀል ክትባት ሳይኖር እንዲህ ዓይነት ውድድር ሊካሄድ አይችልም ይላሉ።
"ክትባት ከተገኘ መልካም፤ ካልተገኘ ግን እሱ እስኪገኝ ኦሊምፒክ አይቆምም" ብለዋል ሊቀመንበሩ።የውድድሩ አስተባባሪ ዮሺሮ ሞሪ በሚያዝያ ወር ኦሊምፒክ በ2021 ካልተደረገ እስከናካቴው መሰረዝ ነው ያለበት ብለው ነበር።ከዚህ ቀደም የኦሎምፒክ ውድድር በጦርነት ምክንያት ሳይካሄድ ቀርቶ ያውቃል እንጂ የሚካሄድበት ጊዜ ሲገፋ ይህ በታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ነው።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዝዳንት "ኮቪድ-19 ጠፋም አልጠፋ በሚቀጥለው ዓመት ኦሊምፒክ ይካሄዳል" ብለዋል።ጆን ኮትስ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንዳረጋገጡት በሚቀጥለው ዓመት ኦሊምፒክ የሚጀምረው በሐምሌ 23 ይሆናል።ኦሊምፒክ መካሄድ የነበረበት ዘንድሮ በሐምሌ ወር ነበር። ሆኖም የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ተከትሎ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሞ ነበር።
ሆኖም ውድድሩን ከፈረንጆቹ 2021 ወዲያ መግፋት ስሜት የሚሰጥ ነገር አይደለም ብለዋል።በሐምሌ ወር የቶክዮ 2020 ኦሊምፒክ ሊቀመንበር ቶሺሮ ሙቶ "ውድድሮቹን በዝግ ስታዲየም ማካሄድ ይቻል ነበር። ያንን ስላልፈለግን ነው ያዘገየነው" ብለው ነበር።
ምናልባት ከየአገሩ የሚመጡ ወኪሎችን ቁጥር በመቀነስ፣ በየውድድሩ የሚታደሙ ተመልካቾችን በማሳነስ፣ እንዲሁም የመክፈቻና መዝጊያ ሥነ ሥርዓቱን ቀለል በማድረግ የሚካሄድበት መንገድ ሊቀየስ ይችላል።ከመላው ዓለም 11 ሺህ አትሌቶች ከ200 አገራት እንደሚገኙ ይጠበቅ ነበር።
በሚቀጥለው ዓመት ሐምሌ ላይ ውድድሩ ሲታሰብ የጉዞ ገደቦችን በተመለከተ የተባለ ነገር የለም።ሚስተር ሙቶ የኦሊምፒክ ውድድሩን ለማድረግ የኮቪድ-19 ክትባትን መጠበቅ አይኖርብንም ብለዋል። የጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው በወረርሽኝ መሀል ክትባት ሳይኖር እንዲህ ዓይነት ውድድር ሊካሄድ አይችልም ይላሉ።
"ክትባት ከተገኘ መልካም፤ ካልተገኘ ግን እሱ እስኪገኝ ኦሊምፒክ አይቆምም" ብለዋል ሊቀመንበሩ።የውድድሩ አስተባባሪ ዮሺሮ ሞሪ በሚያዝያ ወር ኦሊምፒክ በ2021 ካልተደረገ እስከናካቴው መሰረዝ ነው ያለበት ብለው ነበር።ከዚህ ቀደም የኦሎምፒክ ውድድር በጦርነት ምክንያት ሳይካሄድ ቀርቶ ያውቃል እንጂ የሚካሄድበት ጊዜ ሲገፋ ይህ በታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ነው።
[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
ህንድ በኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ሁለተኛ ሆነች!
ህንድ በትናንትናው ዕለት በ24 ሰዓታት ዉስጥ ብቻ ከ90 ሺ በላይ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎችን ያገኘች ሲሆን ይህም ቫይረሱ ከተከሰተ ወዲህ በአንድ ሀገር የተከሰተ ከፍተኛው የተጠቂዎች ቁጥር ነው፡፡በሀገሪቱ እስካሁን ከ 4.2 ሚሊዮን በላይ የቫይረሱ ተጠቂዎች ተገኝተዋል፡፡ በዚህም ብራዚልን በመብለጥ ህንድ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ በእስካሁኑ ምርመራ ህንድ በቫይረሱ ታማሚዎች ቁጥር ከብራዚል በ 70 ሺ ያህል ብልጫ አሳይታለች ሲል ዘ ናሺናል ዘግቧል፡፡በተጠቂዎች ቁጥር ከአንደኛ እስከሶስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት አሜሪካ ፣ ህንድ እና ብራዚል በመላው ዓለም በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ቁጥር 53 በመቶ የሚሆኑት ይገኙባቸዋል፡፡በዓለማችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ27 ሚሊዮን ሲበልጥ ከነዚህም ከ19 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ማገገማቸውን እና ከ887 ሺ በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን ዎርልዶ ሜትርስ አስነብቧል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
ህንድ በትናንትናው ዕለት በ24 ሰዓታት ዉስጥ ብቻ ከ90 ሺ በላይ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎችን ያገኘች ሲሆን ይህም ቫይረሱ ከተከሰተ ወዲህ በአንድ ሀገር የተከሰተ ከፍተኛው የተጠቂዎች ቁጥር ነው፡፡በሀገሪቱ እስካሁን ከ 4.2 ሚሊዮን በላይ የቫይረሱ ተጠቂዎች ተገኝተዋል፡፡ በዚህም ብራዚልን በመብለጥ ህንድ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ በእስካሁኑ ምርመራ ህንድ በቫይረሱ ታማሚዎች ቁጥር ከብራዚል በ 70 ሺ ያህል ብልጫ አሳይታለች ሲል ዘ ናሺናል ዘግቧል፡፡በተጠቂዎች ቁጥር ከአንደኛ እስከሶስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት አሜሪካ ፣ ህንድ እና ብራዚል በመላው ዓለም በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ቁጥር 53 በመቶ የሚሆኑት ይገኙባቸዋል፡፡በዓለማችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ27 ሚሊዮን ሲበልጥ ከነዚህም ከ19 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ማገገማቸውን እና ከ887 ሺ በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን ዎርልዶ ሜትርስ አስነብቧል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ለሰላም መስፈን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጠ!
በአማራ ክልል ለሰላም መስፈን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና የመስጠት ስነስርአት በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።በስነስርአቱ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተገኝተዋል።መድረኩ ሁሉም አካል ለሰላም መስፈንና ለህግ የበላይነት መረጋገጥ ቅድሚያ ሰጥቶ እንዲሰራ ለማሳሰብ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa
በአማራ ክልል ለሰላም መስፈን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና የመስጠት ስነስርአት በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።በስነስርአቱ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተገኝተዋል።መድረኩ ሁሉም አካል ለሰላም መስፈንና ለህግ የበላይነት መረጋገጥ ቅድሚያ ሰጥቶ እንዲሰራ ለማሳሰብ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
[ETV]
@YeneTube @FikerAssefa
የአሥራት ጋዜጠኞች በዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ወሰነ!
አራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአሥራት ጋዜጠኞች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔ ማስተላለፉን አስራት ሚዲያ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል።ፖሊስ በተደጋጋሚ መረጃ አቀርባለሁ በሚል ቀጠሮ እንዲሰጠው ቢጠይቅም በተሰጠው ቆጠሮ አለኝ ያለውን መረጃ ማቅረብ አልቻለም።በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብር፣ ምስጋናው ከፈለኝ እና ዮናታን ሙሉጌታ በእያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል።
@YeneTube @FikerAssefa
አራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአሥራት ጋዜጠኞች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔ ማስተላለፉን አስራት ሚዲያ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል።ፖሊስ በተደጋጋሚ መረጃ አቀርባለሁ በሚል ቀጠሮ እንዲሰጠው ቢጠይቅም በተሰጠው ቆጠሮ አለኝ ያለውን መረጃ ማቅረብ አልቻለም።በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብር፣ ምስጋናው ከፈለኝ እና ዮናታን ሙሉጌታ በእያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል።
@YeneTube @FikerAssefa
አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ!
በእንቦጭ አረም በመዘጋቱ አገልግሎት ለጊዜው አቋርጦ የነበረው የአዋሽ II የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡የእንቦጭ አረሙ የውሃ መቀየሻ ግድብ ላይ በመተኛቱ የተነሳ የውሃ መቀበያው (water intake) አገልግሎቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡አረሙን ከወንጂ ስኳር ፋብሪካ በተገኘ ኤክስካቫተር የማንሳት ሥራ ሲከናወን ቆይቶ የውሃ መቀበያው በመከፈቱ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከአርብ ነሐሴ 29 ጀምሮ ዳግም ኃይል ማምረት ጀምሯል፡፡32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ1966 ዓ.ም ነበር፡፡
[EEPCo]
@YeneTube @FikerAssefa
በእንቦጭ አረም በመዘጋቱ አገልግሎት ለጊዜው አቋርጦ የነበረው የአዋሽ II የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡የእንቦጭ አረሙ የውሃ መቀየሻ ግድብ ላይ በመተኛቱ የተነሳ የውሃ መቀበያው (water intake) አገልግሎቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡አረሙን ከወንጂ ስኳር ፋብሪካ በተገኘ ኤክስካቫተር የማንሳት ሥራ ሲከናወን ቆይቶ የውሃ መቀበያው በመከፈቱ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከአርብ ነሐሴ 29 ጀምሮ ዳግም ኃይል ማምረት ጀምሯል፡፡32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ1966 ዓ.ም ነበር፡፡
[EEPCo]
@YeneTube @FikerAssefa
የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ለአንድ ቀን ይፋዊ ስራ ጉብኝት ዛሬ ረፋድ አስመራ መግባታቸውን የኤርትራ የመረጃ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል አስታውቀዋል፡፡
አል ቡርሃን እና ልዑካቸው አስመራ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የኤርትራ ባለስልጣናት አቀባበል እንዳደረጉላቸውም ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት፡፡
መሪዎቹ በሁለትዮሽ እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩም ገልጸዋል፡፡ባሳለፍነው ወርሃ ሃምሌ ከፍተኛ የኤርትራ የመከላከያ ኃላፊዎች ወደ ካርቱም አቅንተው ከምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሃምዳን ደገሎ (ሄሜቲ) ጋር መምከራቸው ይታወሳል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
አል ቡርሃን እና ልዑካቸው አስመራ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የኤርትራ ባለስልጣናት አቀባበል እንዳደረጉላቸውም ነው ሚኒስትሩ ያስታወቁት፡፡
መሪዎቹ በሁለትዮሽ እና በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩም ገልጸዋል፡፡ባሳለፍነው ወርሃ ሃምሌ ከፍተኛ የኤርትራ የመከላከያ ኃላፊዎች ወደ ካርቱም አቅንተው ከምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሃምዳን ደገሎ (ሄሜቲ) ጋር መምከራቸው ይታወሳል፡፡
[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ የኮሮና ቫይረስ መከሰትን ተከትሎ በወጣው የትራንስፖርት አገልግሎት ታሪፍና የመጫን አቅም መመሪያ ላይ ማሻሻያ ተደረገ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ባለስልጣን ማሻሻያውን አስመልክቶ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቷል።በመግለጫውም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሚኒባስ፣ የአንበሳ አውቶብስ፣ ሸገር እና ሀይገር ባሶች በወንበራቸው ልክ እንዲጭኑ ተወስኗል።የሚኒባስ ታክሲዎች ከኋላ ባለው መቀመጫ ከ2 ሰው በላይ መጫን አይችሉም ብሏል ቢሮው በመግለጫው።
እንዲሁም ባለ ሶስት እና ባለ አራት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪዎች እስከ ሹፌሩ 3 ሰው መጫን እንደሚችሉም ነው የተገለፀው።
ቀላል ባቡር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መመሪያ በ25 በመቶ የመጫን አቅም ብቻ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው አሁን ላይ ወደ 75 በመቶ ክፍ እንዲል መደረጉንም አስታውቋል።
ከታሪፍ ጋር በተያያዘም በእጥፍ ሲከፈል የነበረው ቀርቶ መጠነኛ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ባለስልጣኑ አስታውቋል።
በዚህም መሰረት የሚኒባስ ታክሲ ታሪፍ እንደሚከተለው ማስተካከያ ተደርጎበታል።
👉እስከ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 1 ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን ላይ 2 ብር
👉ከ2 ነጥብ 6 እስከ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 3 ብር የነበረው አሁን 4 ብር
👉ከ5 ነጥብ 1 እስከ 7 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 4 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 6 ብር
👉ከ7 ነጥብ 6 እስከ 10 ኪሎ ሜትር በፊት 6 ብር የበረው አሁን 8 ብር
👉ከ10 ነጥብ 1 እስከ 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር 7 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 10 ብር
👉ከ12 ነጥብ 6 እስከ 15 ኪሎ ሜትር በፊት 9 ብር የነበረው አሁን 12 ብር
👉ከ15 ነጥብ 1 እስከ 17 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 10 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 13 ብር
👉ከ17 ነጥብ 6 እስከ 20 ኪሎ ሜትር በፊት 12 ብር የነበረው አሁን 15 ብር
👉ከ20 ነጥብ 1 እስከ 22 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 13 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 17 ብር
👉ከ22 ነጥብ 6 እስከ 25 ኪሎ ሜትር በፊት 15 ብር የነበረው አሁን 19 ብር
👉ከ25 ነጥብ 1 እስከ እስከ 27 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 16 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 20 ብር
👉ከ27 ነጥብ 6 እስከ 30 ኪሎ ሜትር በፊት 18 የነበረው አሁን 22 ብር ሆኖ ማሻሻያ መደረጉንም የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ባለስልጣን በመግለጫው አመላክቷል።
ከተፈቀደው ሰው በላይ መጫን ከ1 ሺህ ብር ጀምሮ ከታሪፍ በላይ ማስከፈል 1 ሺህ 500 ብር ጀምሮ እንደሚያስቀጣም ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ይህንን ለመቆጣጠር ከትራፊክ ፖሊስ በዘለለ የፖሊስና የፀጥታ አካላት መሰማራታቸው የተገለፀ ሲሆን፥ ህብረተሰቡ ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ እና ትርፍ የሚጭኑትን ለመጠቆም የሚጠቁምበት የስክል ቁጥር በቅርቡ ይፋ ይሆናል ብሏል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ባለስልጣን ማሻሻያውን አስመልክቶ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቷል።በመግለጫውም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሚኒባስ፣ የአንበሳ አውቶብስ፣ ሸገር እና ሀይገር ባሶች በወንበራቸው ልክ እንዲጭኑ ተወስኗል።የሚኒባስ ታክሲዎች ከኋላ ባለው መቀመጫ ከ2 ሰው በላይ መጫን አይችሉም ብሏል ቢሮው በመግለጫው።
እንዲሁም ባለ ሶስት እና ባለ አራት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪዎች እስከ ሹፌሩ 3 ሰው መጫን እንደሚችሉም ነው የተገለፀው።
ቀላል ባቡር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መመሪያ በ25 በመቶ የመጫን አቅም ብቻ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው አሁን ላይ ወደ 75 በመቶ ክፍ እንዲል መደረጉንም አስታውቋል።
ከታሪፍ ጋር በተያያዘም በእጥፍ ሲከፈል የነበረው ቀርቶ መጠነኛ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ባለስልጣኑ አስታውቋል።
በዚህም መሰረት የሚኒባስ ታክሲ ታሪፍ እንደሚከተለው ማስተካከያ ተደርጎበታል።
👉እስከ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 1 ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን ላይ 2 ብር
👉ከ2 ነጥብ 6 እስከ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 3 ብር የነበረው አሁን 4 ብር
👉ከ5 ነጥብ 1 እስከ 7 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 4 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 6 ብር
👉ከ7 ነጥብ 6 እስከ 10 ኪሎ ሜትር በፊት 6 ብር የበረው አሁን 8 ብር
👉ከ10 ነጥብ 1 እስከ 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር 7 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 10 ብር
👉ከ12 ነጥብ 6 እስከ 15 ኪሎ ሜትር በፊት 9 ብር የነበረው አሁን 12 ብር
👉ከ15 ነጥብ 1 እስከ 17 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 10 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 13 ብር
👉ከ17 ነጥብ 6 እስከ 20 ኪሎ ሜትር በፊት 12 ብር የነበረው አሁን 15 ብር
👉ከ20 ነጥብ 1 እስከ 22 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 13 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 17 ብር
👉ከ22 ነጥብ 6 እስከ 25 ኪሎ ሜትር በፊት 15 ብር የነበረው አሁን 19 ብር
👉ከ25 ነጥብ 1 እስከ እስከ 27 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በፊት 16 ብር ከ50 ሳንቲም የነበረው አሁን 20 ብር
👉ከ27 ነጥብ 6 እስከ 30 ኪሎ ሜትር በፊት 18 የነበረው አሁን 22 ብር ሆኖ ማሻሻያ መደረጉንም የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ባለስልጣን በመግለጫው አመላክቷል።
ከተፈቀደው ሰው በላይ መጫን ከ1 ሺህ ብር ጀምሮ ከታሪፍ በላይ ማስከፈል 1 ሺህ 500 ብር ጀምሮ እንደሚያስቀጣም ባለስልጣኑ አስታውቋል።
ይህንን ለመቆጣጠር ከትራፊክ ፖሊስ በዘለለ የፖሊስና የፀጥታ አካላት መሰማራታቸው የተገለፀ ሲሆን፥ ህብረተሰቡ ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ እና ትርፍ የሚጭኑትን ለመጠቆም የሚጠቁምበት የስክል ቁጥር በቅርቡ ይፋ ይሆናል ብሏል።
[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa