YeneTube
የአማራ ክልል የሠላምና ደህንነት ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አገኘው ተሻገር ከኃላፊነታቸው ተነሱ! የክልሉ የሠላምና ደህንነት ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አገኛው ተሻገር ከኃላፊነታቸው ተነስተው በምትካቸውም ሲሣይ ዳምጤ የቢሮው ኃላፊ ሆነው ተሾሙ፡፡የአማራ ክልል ምክር ቤት ዛሬ የካቲት 10/2012 ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ላይ ሲሳይ ዳምጤ የቢሮው ኃላፊ እንዲሆኑ በአብለጫ ድምጽ፣ በአንድ ታቀውሞ እና በሦስት ድምጸ ተዓቅቦ…
#update
አቶ አገኘሁ ተሻገር የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሾሙ!
የአማራ ክልል የሠላምና የሕዝብ ደኅንነት ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ አገኘሁ ተሻገር በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ደረጃ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሆነው መሾማቸውን የሠላምና የሕዝብ ደኅንነት ቢሮው በማኅበራዊ ገጹ አስታውቋል፡፡የአማራ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ አቶ ሲሳይ ዳምጤን የክልሉ ሠላምና የሕዝብ ደኅንነት ቢሮ ኃላፊ አድርጎ መሾሙ ይታወሳል ሲል የዘገበው አብመድ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ አገኘሁ ተሻገር የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሾሙ!
የአማራ ክልል የሠላምና የሕዝብ ደኅንነት ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ አገኘሁ ተሻገር በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ደረጃ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሆነው መሾማቸውን የሠላምና የሕዝብ ደኅንነት ቢሮው በማኅበራዊ ገጹ አስታውቋል፡፡የአማራ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ አቶ ሲሳይ ዳምጤን የክልሉ ሠላምና የሕዝብ ደኅንነት ቢሮ ኃላፊ አድርጎ መሾሙ ይታወሳል ሲል የዘገበው አብመድ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ እስከ 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ምስል መለየት የሚያስችሉ የደህንነት ካሜራዎች ሊገጠሙ ነው፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ዋና መንገዶች የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ እስከ 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ምስል መለየት የሚያስችሉ የደህንነት ካሜራዎችን ለመግጠም እንቅስቃሴ ተጀምሯል።የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በዘርፉ ልምድ ካለው ድርጅት ጋር በአዲስ አበባ ከተማ ቴክኖሎጂውን መዘርጋት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ደኤታ አቶ ጀማል በከር የዜጎችን ደህንነት በቴክኖሎጂ ለማስጠበቅ ትኩረት እየተሰራ ሲሆን ቴክኖሎጂው ዜጎች ከደህንነት ስጋት ተላቀው የእለት ተእለት ተግባራቸውን እንዲከውኑ ያግዛል ብለዋል፡፡በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚገጠሙት የደህንነት ካሜራዎች ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከል የዜጎች ደህንነት ለማረጋገጥ የሚስችሉ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
ምንጭ:Addis Ababa city Admin press Secretariat
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ዋና መንገዶች የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ እስከ 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ምስል መለየት የሚያስችሉ የደህንነት ካሜራዎችን ለመግጠም እንቅስቃሴ ተጀምሯል።የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በዘርፉ ልምድ ካለው ድርጅት ጋር በአዲስ አበባ ከተማ ቴክኖሎጂውን መዘርጋት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ደኤታ አቶ ጀማል በከር የዜጎችን ደህንነት በቴክኖሎጂ ለማስጠበቅ ትኩረት እየተሰራ ሲሆን ቴክኖሎጂው ዜጎች ከደህንነት ስጋት ተላቀው የእለት ተእለት ተግባራቸውን እንዲከውኑ ያግዛል ብለዋል፡፡በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚገጠሙት የደህንነት ካሜራዎች ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከል የዜጎች ደህንነት ለማረጋገጥ የሚስችሉ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
ምንጭ:Addis Ababa city Admin press Secretariat
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሚከተሉት ስድስት ፓርቲዎች የምዝገባ እውቅና ሰጥቷል፡፡
1. ሕብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
2. መላው አማራ ህዝብ ፓርቲ
3. ነጻነትና ሰላም ለኢትዮጵያ ህብረት ፓርቲ
4. የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ( ኢዜማ)
5. አፋር ነጻ አውጪ ግንባር ፓርቲ ( አነግፓ)
6. የቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ
Via NEBE
@YeneTube @FikerAssefa
1. ሕብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
2. መላው አማራ ህዝብ ፓርቲ
3. ነጻነትና ሰላም ለኢትዮጵያ ህብረት ፓርቲ
4. የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ( ኢዜማ)
5. አፋር ነጻ አውጪ ግንባር ፓርቲ ( አነግፓ)
6. የቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ
Via NEBE
@YeneTube @FikerAssefa
ብልፅግና ፓርቲ በ40 ሚሊዮን ብር አዲስ ጽሕፈት ቤት ሊገነባ ነው!
ብልፅግና ፓርቲ በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ ከ 40 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ባለሦስት ወለል የጽሕፈት ቤት ሕንፃ ለማስገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀመጠ።ግንባታው በያዝነው ዓመት ተጀምሮ በቀጣይ ኹለት ዓመታት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል የተባለ ሲሆን፣ የፓርቲው የዞን ኃላፊዎች እና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ቢሮዎች፣ ሦስት አዳራሾች እና መዝናኛ ክበቦች እንደሚኖሩት ታውቋል።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
ብልፅግና ፓርቲ በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ ከ 40 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ባለሦስት ወለል የጽሕፈት ቤት ሕንፃ ለማስገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀመጠ።ግንባታው በያዝነው ዓመት ተጀምሮ በቀጣይ ኹለት ዓመታት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል የተባለ ሲሆን፣ የፓርቲው የዞን ኃላፊዎች እና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ቢሮዎች፣ ሦስት አዳራሾች እና መዝናኛ ክበቦች እንደሚኖሩት ታውቋል።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ መንግሰት ላለፉት ሶስት አመታት ከኤርትራ ድንበር አቋርጠው ለሚመጡ #ኤርትራዊያን የቡድን እውቅናን መሰረት በማድረግ ጥገኝነት በመስጠት ስታስተናድ ብትቆይም ባለፉት ሁለት ሳምንታት ግን ይህንን ማቆሟን አስታወቀች፡፡
ይህም ከተለያዩ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ወቀሳ እያስነሳ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት የስተደተኞችን ስምምነት የጣሰ ነው ተብሏል፡፡
የወል ጥገኝነት ማለት የአንድ አገር መንግስት ወይም የተባበሩት መንግሰታት የስደተኞች ኮሚሽን ስደተኞች ከሚሰደዱበት አገር ባለ ሁኔታ፣ አገር አልባ ከሆኑ እና በሌሎች መሰል ምክንያቶች በግል ጥገኝነት ለመጠየቅ የሚያበቃ ምክንያት እንዳላቸው ሳይጠየቁ የዛ አገር ዜጋ ወይም የዛ ቡድን አባል ከሆኑ ብቻ የሚሰጥ የጥገኝነት አይነት ነው፡፡
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
ይህም ከተለያዩ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ወቀሳ እያስነሳ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት የስተደተኞችን ስምምነት የጣሰ ነው ተብሏል፡፡
የወል ጥገኝነት ማለት የአንድ አገር መንግስት ወይም የተባበሩት መንግሰታት የስደተኞች ኮሚሽን ስደተኞች ከሚሰደዱበት አገር ባለ ሁኔታ፣ አገር አልባ ከሆኑ እና በሌሎች መሰል ምክንያቶች በግል ጥገኝነት ለመጠየቅ የሚያበቃ ምክንያት እንዳላቸው ሳይጠየቁ የዛ አገር ዜጋ ወይም የዛ ቡድን አባል ከሆኑ ብቻ የሚሰጥ የጥገኝነት አይነት ነው፡፡
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ የሚመረቱ የሲጋራ ምርቶች ላይ ኻያ ፍሬ የሚይዝ አንድ ፓኬት ሲጋራ ከዚህ ቀደም ሲሸጥበት ከነበረው 25 ብር ዋጋ ወደ 40 ብር፣ የ15 ብር ጭማሪ አሳየ።
ምንም እንኳን የምርት ዋጋ ላይ ጭማሪ ባይኖርም፣ አከፋፋዮች በኤክሳይስ ታክስ ምክንያት በሚኖረው የዋጋ ጭማሪ ላይ የተሻለ ጥቅም ለማግኘት በሚል ምርት በመያዛቸው የተፈጠረ እንደሆነም አዲስ ማለዳ ከተለያዩ አካላት አረጋግጣለች።
@YeneTube @Fikerassefa
ምንም እንኳን የምርት ዋጋ ላይ ጭማሪ ባይኖርም፣ አከፋፋዮች በኤክሳይስ ታክስ ምክንያት በሚኖረው የዋጋ ጭማሪ ላይ የተሻለ ጥቅም ለማግኘት በሚል ምርት በመያዛቸው የተፈጠረ እንደሆነም አዲስ ማለዳ ከተለያዩ አካላት አረጋግጣለች።
@YeneTube @Fikerassefa
በደቡብ ክልል ጉራፋርዳ ወረዳ በትናንትናው ዕለት ከተከሰተው ሁከት እና ብጥብጥ ጋር በተያያዘ የወረዳው አስተዳዳሪን ጨምሮ የተለያዩ የስራ ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በአሁኑ ወቅት የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ ተከትሎ በክልሉ ህግን የማስከበር እና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ሥራ በልዩ ሁኔታ መጀመሩን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።በተለይም በህዝቡ ውስጥ የቆዩ ቅራኔዎችን በመፍታት መግባባት ላይ የተመሠረተች ሀገርና መንግስት ለመገንባት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግ መቆየቱ ተመላክቷል።በአንፃሩ በተለያዩ ዋልታ ረገጥ አስተሳሰቦች ሰለባ በሆኑ አካላት አንቀሳቃሽነት በተለያዩ አካባቢዎች የዜጎችን ሰላማዊ እንቅስቃሴ የሚያውኩ ተግባራት ሲፈጸሙ መቆየታቸው ነው የተገለጸው።
ክልሉ የመቻቻልና የአብሮነት ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል እና የተጀመረው ለውጥ እንዳይደናቀፍ የክልሉ መንግስት መሰል ችግሮችን ለማስወገድ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።አሁን ላይም ለህዝቡ ሰላማዊ ኑሮ አስጊ እና ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ መሪ ተዋናይ የነበሩ አካላት ላይ የክልሉ መንግስት ህጋዊ እርምጃ መውሰድ መጀመሩ ተመላክቷል።
በዚህ መሰረትም በጉራፋርዳ ወረዳ ትላንት በተከሰተው ሁከት እና ብጥብጥ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ የተለያዩ አመራሮችና ባለሙያዎች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ነው የተገለጸው።በቁጥጥር ስር የዋሉትም አቶ ኩንዲሳ ንጉሴ የወረዳው አስተዳዳሪ፣ አቶ ሃይሉ ይግለጡ የወረዳው ድርጅት ጽህፈት ቤት ሃላፊ፣ አቶ ቢሰጥ ወርቁ የአቃቤ ህግ ጽህፈት ቤት ሃላፊ፣አቶ ኦይሳ አለሙ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ፣ አቶ እንዳልክ ደምሴ ሰላምና ጽህፈት ቤት ሃላፊ፣ አቶ ማስቲ ፎልጂ የማዘጋጃ ቤት ሃላፊ፣ አቶ አጥናፉ ግዛው የአስተዳደር ጽህፈት ቤት ሃላፊ፣አቶ ታጋይ ሳሙኤል ኮጃ የማዘጋጃ ቤት ሃላፊ እና ሌሎች ባለሙያዎች መሆናቸው ተገልጿል።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
በአሁኑ ወቅት የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ ተከትሎ በክልሉ ህግን የማስከበር እና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ሥራ በልዩ ሁኔታ መጀመሩን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።በተለይም በህዝቡ ውስጥ የቆዩ ቅራኔዎችን በመፍታት መግባባት ላይ የተመሠረተች ሀገርና መንግስት ለመገንባት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግ መቆየቱ ተመላክቷል።በአንፃሩ በተለያዩ ዋልታ ረገጥ አስተሳሰቦች ሰለባ በሆኑ አካላት አንቀሳቃሽነት በተለያዩ አካባቢዎች የዜጎችን ሰላማዊ እንቅስቃሴ የሚያውኩ ተግባራት ሲፈጸሙ መቆየታቸው ነው የተገለጸው።
ክልሉ የመቻቻልና የአብሮነት ተምሳሌት ሆኖ እንዲቀጥል እና የተጀመረው ለውጥ እንዳይደናቀፍ የክልሉ መንግስት መሰል ችግሮችን ለማስወገድ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።አሁን ላይም ለህዝቡ ሰላማዊ ኑሮ አስጊ እና ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ መሪ ተዋናይ የነበሩ አካላት ላይ የክልሉ መንግስት ህጋዊ እርምጃ መውሰድ መጀመሩ ተመላክቷል።
በዚህ መሰረትም በጉራፋርዳ ወረዳ ትላንት በተከሰተው ሁከት እና ብጥብጥ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ የተለያዩ አመራሮችና ባለሙያዎች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ነው የተገለጸው።በቁጥጥር ስር የዋሉትም አቶ ኩንዲሳ ንጉሴ የወረዳው አስተዳዳሪ፣ አቶ ሃይሉ ይግለጡ የወረዳው ድርጅት ጽህፈት ቤት ሃላፊ፣ አቶ ቢሰጥ ወርቁ የአቃቤ ህግ ጽህፈት ቤት ሃላፊ፣አቶ ኦይሳ አለሙ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ፣ አቶ እንዳልክ ደምሴ ሰላምና ጽህፈት ቤት ሃላፊ፣ አቶ ማስቲ ፎልጂ የማዘጋጃ ቤት ሃላፊ፣ አቶ አጥናፉ ግዛው የአስተዳደር ጽህፈት ቤት ሃላፊ፣አቶ ታጋይ ሳሙኤል ኮጃ የማዘጋጃ ቤት ሃላፊ እና ሌሎች ባለሙያዎች መሆናቸው ተገልጿል።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግስት ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች የሞዴስ እና ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ላይ ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግስት ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች ሞዲስ እና ሌሎች የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በነጻ ለማቅረብ ከባለሃብቶች እና ከበጎ ፍቃደኛ ግለሰቦች የሰበሰባቸውን ቁሳቁሶች አሰራጭቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ የከንቲባ ጽህፈት ቤት ሓላፊ እና የተማሪዎች ምገባ ኤጀንሲ የቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ አለምጸሀይ ጳውሎስ እንዲሁም ሌሎች የከተማዋ የስራ ኃላፊዎች በዛሬው ዕለት በቦሌ ክፍለ ከተማ ቦሌ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች የሞዴስ እና ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶቹን አስረክበዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የተማሪዎች የምገባ ሂደት ምን እንደሚመስል እና በቀጣይ መስተካከል ባለባቸው ጉዳዮች ዙሪያ በትምህርት ቤቱ የመስክ ምልከታ አድርገዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ከትምህርት ቤቶች እድሳት ጀምሮ የተማሪዎች ምገባ፣ የደንብ ልብስ ፣የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች እና የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ በማቅረብ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ወ/ሮ አለምጸሀይ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ:- አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
@YeneTube @Fikerassefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግስት ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች ሞዲስ እና ሌሎች የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በነጻ ለማቅረብ ከባለሃብቶች እና ከበጎ ፍቃደኛ ግለሰቦች የሰበሰባቸውን ቁሳቁሶች አሰራጭቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ የከንቲባ ጽህፈት ቤት ሓላፊ እና የተማሪዎች ምገባ ኤጀንሲ የቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ አለምጸሀይ ጳውሎስ እንዲሁም ሌሎች የከተማዋ የስራ ኃላፊዎች በዛሬው ዕለት በቦሌ ክፍለ ከተማ ቦሌ ማህበረሰብ ትምህርት ቤት ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች የሞዴስ እና ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶቹን አስረክበዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የተማሪዎች የምገባ ሂደት ምን እንደሚመስል እና በቀጣይ መስተካከል ባለባቸው ጉዳዮች ዙሪያ በትምህርት ቤቱ የመስክ ምልከታ አድርገዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ከትምህርት ቤቶች እድሳት ጀምሮ የተማሪዎች ምገባ፣ የደንብ ልብስ ፣የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች እና የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ በማቅረብ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ወ/ሮ አለምጸሀይ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ:- አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
@YeneTube @Fikerassefa
ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያግዝ አዲስ መድኃኒት ለገበያ ሊቀርብ ነው ተባለ፡፡
የቻይና ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንደገለጸው መድኃኒቱን ለገበያ የሚያቀርበው ዠጂያንግ ሂሱን ፋርማሲዩቲካል የተሰኘው ግዙፍ የቻይና መድኃኒት አምራች ኩባንያ ነው ተብሏል።
የኮቪድ-19ን በሽታ የሚከላከለው አዲሱ መድኃኒት ፋቪፒራቪር የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፣ ለገበያ ለማቅረብ ከአገሪቱ ባለሥልጣናት ፈቃድ ማግኘቱ አስታውቋል።
በመረጃው መሠረት መድኃኒቱ ለገበያ ከቀረበ በኋላም፣ ኩባንያው በመድኃኒቱ ላይ የሚያደርገውን ክሊኒካዊ ፍተሻ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
የቻይና ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ፋቪፒቪር “በመጠኑም ቢሆን ውጤታማነት አለው” ካለ በኋላ፣ በክሊኒካዊ ፍተሻው ወቅት ቢያንስ 70 ሰዎች መሳተፋቸውን ይፋ አድርጓል።
የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር) ፣ ለኮቪድ-19 በሽታ ክትባት ለመሥራት ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ይወስዳል ብለው እንደነበር ኢቢሲ ሮይተርስ ጠቅሶ ዘግቧል።
Via:- Addis Ababa City Administration
@YeneTube @Fikerassefa
የቻይና ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንደገለጸው መድኃኒቱን ለገበያ የሚያቀርበው ዠጂያንግ ሂሱን ፋርማሲዩቲካል የተሰኘው ግዙፍ የቻይና መድኃኒት አምራች ኩባንያ ነው ተብሏል።
የኮቪድ-19ን በሽታ የሚከላከለው አዲሱ መድኃኒት ፋቪፒራቪር የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፣ ለገበያ ለማቅረብ ከአገሪቱ ባለሥልጣናት ፈቃድ ማግኘቱ አስታውቋል።
በመረጃው መሠረት መድኃኒቱ ለገበያ ከቀረበ በኋላም፣ ኩባንያው በመድኃኒቱ ላይ የሚያደርገውን ክሊኒካዊ ፍተሻ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
የቻይና ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ፋቪፒቪር “በመጠኑም ቢሆን ውጤታማነት አለው” ካለ በኋላ፣ በክሊኒካዊ ፍተሻው ወቅት ቢያንስ 70 ሰዎች መሳተፋቸውን ይፋ አድርጓል።
የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር) ፣ ለኮቪድ-19 በሽታ ክትባት ለመሥራት ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ይወስዳል ብለው እንደነበር ኢቢሲ ሮይተርስ ጠቅሶ ዘግቧል።
Via:- Addis Ababa City Administration
@YeneTube @Fikerassefa
የሱማሌላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ የፕሬዝዳንት ፎርማጆን ይቅርታ እንደተቀበሉ የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል፡፡ ፎርማጆ ይቅርታ የጠየቁት የቀድሞው አምባገነን ዚያድ ባሬ በሱማሌላንድ ሕዝብ ላይ ላደረሱት በደል ነበር፡፡ በተያያዘ፣ ፎርማጆ ሐርጌሳን መጎብኘት እንደሚፈልጉ ዛሬ በይፋ አስታውቀዋል፡፡ ቢሂ ግን ጥያቄውን አልተቀበሉም፡፡
Via:- Wazema
@YeneTube @Fikerassefa
Via:- Wazema
@YeneTube @Fikerassefa
የስልጤ ዞን ርዕሰ መዲና የሆነችው ወራቤ ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድን ለመቀበል ዝግጅቷን በማጠናቀቅ ላይ ትገኛለች።
በነገው እለት ማለትም የካቲት 11/2012 የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ከስልጤ ዞን ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለመወያየት ፕሮግራም መያዙ ይታወቃል።
በመሆኑም ይህን ፕሮግራም በተሟላ መልኩ ለማስኬድና እንግዶችንም በተገቢው ክብር ለመቀበል የዞኑ ርዕሰ መዲና ወራቤ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
ውይይቱ የሚደረግባቸው ቦታዎች ማለትም የስልጤ ባህል አደራሽና የወራቤ ስታድየም አስፈላጊው ዝግጅት በመጠናቀቅ ላይ ነው።
መላው የዞናችን ህዝብ ለጠቅላይ ሚኒስተሩና እሳቸውን ተከትለው ለሚመጡ እንግዶች የተለመደውን የእንግዳ አቀባበል እንዲያደርግና ለውይይቱ ውጤታማነትም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
ምንጭ:- ስ/ዞ/ህ/ግ/ጽ/ቤት
@YeneTube @Fikerassefa
በነገው እለት ማለትም የካቲት 11/2012 የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ከስልጤ ዞን ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለመወያየት ፕሮግራም መያዙ ይታወቃል።
በመሆኑም ይህን ፕሮግራም በተሟላ መልኩ ለማስኬድና እንግዶችንም በተገቢው ክብር ለመቀበል የዞኑ ርዕሰ መዲና ወራቤ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
ውይይቱ የሚደረግባቸው ቦታዎች ማለትም የስልጤ ባህል አደራሽና የወራቤ ስታድየም አስፈላጊው ዝግጅት በመጠናቀቅ ላይ ነው።
መላው የዞናችን ህዝብ ለጠቅላይ ሚኒስተሩና እሳቸውን ተከትለው ለሚመጡ እንግዶች የተለመደውን የእንግዳ አቀባበል እንዲያደርግና ለውይይቱ ውጤታማነትም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
ምንጭ:- ስ/ዞ/ህ/ግ/ጽ/ቤት
@YeneTube @Fikerassefa
ኮሮና ቫይረስ በተቀሰቀሰበት ዉሃን ከተማ የሚገኝ ሆስፒታል ዳይሬክተር በኮሮና ቫይረስ ተጠቅቶ መሞቱን የአከባቢው ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
#Coronavirus
@YeneTube @Fikerassefa
#Coronavirus
@YeneTube @Fikerassefa
የኬንያው ሳፋሪኮም ኩባንያ ከኢትዮጵያ ቴሌኮም ፍቃድ ለማግኘት ከሌሎች ኩባንያዎች ጋር ለመጣመር በመነጋገር ላይ እንደሆነ ዘ ኢስት አፍሪካን አስነብቧል፡፡ ቴሌኮሙ ለ2 የግል ቴሌኮም ኩባንያዎች ፍቃድ ለመስጠት በሚያዚያ ጨረታ ያወጣል፡፡ ሳፋሪኮም ከሌሎች ጋር የሚጣመረው ጨረታው ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ስለሚጠይቅ ነው፡፡
Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
Via Wazema
@YeneTube @FikerAssefa
ፖምፔዮ በግደቡ ዙሪያ የሚካሄደው ውይይት በቅርቡ መቋጫ እንደሚያገኝ ጠቆሙ!
የኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከአሜሪካው አቻቸው ማይክ ፖምፔዮ ጋር ዛሬ ከሰዓት በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ማይክ ፖምፔዮ፤ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ ግንኙነት በርካታ ዓመታትን አስቆጥሯል ያሉ ሲሆን፤ ከ1930ዎቹ ጀምሮ ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሲያካሂዱ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።በአሜሪካዋ ዋሽንግተን ዲ.ሲ በርካታ ቁጥር ያለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ መኖሩን የጠቆሙት ፖምፒዮ በዛሬው መግለጫቸው በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ እና በመጪው ምርጫ ላይ የአገራቸውን አቋም አንጸባርቀዋል።
የህዳሴው ግድብ ድርድር ትኩረቱን ስቶ የውሃ ድርሻ ክፍፍል ላይ ሆኗል ተባለ
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ
ፕሬዝደንት ትራምፕ ሦስቱንም አገራት ሊያስማማ የሚችል ስምምነት እንዲፈጠር ቅድሚያ የሰጡት ጉዳይ ነው ብለዋል ማይክ ፖምፔዮ።የግድቡ ግንባታ በአሜሪካ የገንዘብ ሚንስትር እና በዓለም ባንክ አደራዳሪነት ሲካሄድ መቆየቱን እና የየአገራቱ የውጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ልዩነቶቻቸውን ለመፍታት ወደ ዋሽንግተን በተደጋጋሚ መጓዛቸውን አስታውሰዋል።
ፖምፒዮ "የመግባቢያ ነጥቦች እየተጠናቀቁ ወደ ስምምነት ተቃርቧል። አሁንም ግን የሚቀር ሥራ አለ" ብለዋል። "የሦስቱ አገራት መሪዎችም ሆኑ አሜሪካ፤ የሁሉንም አገራት ፍላጎት ያማከል ስምምነት እንዲደረስ ነው ጥረት ሲደረግ የቆየው። ብዙ ሥራ ይቀረናል፤ በቀጣዩ ወር ግን እንደሚጠናቀቅ ተስፋ አደርጋለሁ" ብለዋል።
ምርጫ
"የአብይ አስተዳደር ተጠያቂ እና ሁሉን አሳታፊ በሆነ የዲሞክራሲ ሥርዓት ያምናል፤ አሜሪካም እንዲሁ" ያሉት የቀድሞ የሲአይኤ አለቃ ማይክ ፖምፔዮ፤ ስለቀጣዩ ምርጫ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር መወያየታቸውን ተናግረዋል።ቀጣዩ ምርጫ ነጻ እና ታዓማኒነት ያለው ሆኖ ሁሉንም እንደሚያሳትፍ ተወያይተናል ብለዋል።
አንበጣ መንጋን መከላከል
በአፍሪካ ቀንድ የተከሰተውን አንበጣ መንጋ ለመከላከል አሜሪካ ድጋፍ እንደምታደርግ አስታውቀዋል። በኬንያ፣ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የተከሰተውን የአንበጣ መንጋ ለመከላከል አሜሪካ የ8 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ እንደምታደረግ አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው ለውጥ
በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉት የለውጥ ሥራዎች ሕዝቡን በረዥም ጊዜ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው ያሉት ፖምፔዮ፤ "በእዚህ ላይ የእኛ አስተዋጽኦ በተቻለን መጠን መደገፍ ነው" ብለዋል።"እንዲህ ዓይነት ትልልቅ ለውጦች ሲካሄዱ ውጤቶች በፍጥነት ላይታዩ ይችላሉ" ያሉት ፖምፔዮ፤ በአፍሪካ መዲና ከሴት ርዕሰ ብሔር ጋር ተገናኝተው መወያየታቸው እንዳስደነቃቸው አልሸሸጉም።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከአሜሪካው አቻቸው ማይክ ፖምፔዮ ጋር ዛሬ ከሰዓት በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ማይክ ፖምፔዮ፤ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ ግንኙነት በርካታ ዓመታትን አስቆጥሯል ያሉ ሲሆን፤ ከ1930ዎቹ ጀምሮ ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሲያካሂዱ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።በአሜሪካዋ ዋሽንግተን ዲ.ሲ በርካታ ቁጥር ያለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ መኖሩን የጠቆሙት ፖምፒዮ በዛሬው መግለጫቸው በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ እና በመጪው ምርጫ ላይ የአገራቸውን አቋም አንጸባርቀዋል።
የህዳሴው ግድብ ድርድር ትኩረቱን ስቶ የውሃ ድርሻ ክፍፍል ላይ ሆኗል ተባለ
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ
ፕሬዝደንት ትራምፕ ሦስቱንም አገራት ሊያስማማ የሚችል ስምምነት እንዲፈጠር ቅድሚያ የሰጡት ጉዳይ ነው ብለዋል ማይክ ፖምፔዮ።የግድቡ ግንባታ በአሜሪካ የገንዘብ ሚንስትር እና በዓለም ባንክ አደራዳሪነት ሲካሄድ መቆየቱን እና የየአገራቱ የውጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ልዩነቶቻቸውን ለመፍታት ወደ ዋሽንግተን በተደጋጋሚ መጓዛቸውን አስታውሰዋል።
ፖምፒዮ "የመግባቢያ ነጥቦች እየተጠናቀቁ ወደ ስምምነት ተቃርቧል። አሁንም ግን የሚቀር ሥራ አለ" ብለዋል። "የሦስቱ አገራት መሪዎችም ሆኑ አሜሪካ፤ የሁሉንም አገራት ፍላጎት ያማከል ስምምነት እንዲደረስ ነው ጥረት ሲደረግ የቆየው። ብዙ ሥራ ይቀረናል፤ በቀጣዩ ወር ግን እንደሚጠናቀቅ ተስፋ አደርጋለሁ" ብለዋል።
ምርጫ
"የአብይ አስተዳደር ተጠያቂ እና ሁሉን አሳታፊ በሆነ የዲሞክራሲ ሥርዓት ያምናል፤ አሜሪካም እንዲሁ" ያሉት የቀድሞ የሲአይኤ አለቃ ማይክ ፖምፔዮ፤ ስለቀጣዩ ምርጫ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር መወያየታቸውን ተናግረዋል።ቀጣዩ ምርጫ ነጻ እና ታዓማኒነት ያለው ሆኖ ሁሉንም እንደሚያሳትፍ ተወያይተናል ብለዋል።
አንበጣ መንጋን መከላከል
በአፍሪካ ቀንድ የተከሰተውን አንበጣ መንጋ ለመከላከል አሜሪካ ድጋፍ እንደምታደርግ አስታውቀዋል። በኬንያ፣ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የተከሰተውን የአንበጣ መንጋ ለመከላከል አሜሪካ የ8 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ እንደምታደረግ አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው ለውጥ
በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉት የለውጥ ሥራዎች ሕዝቡን በረዥም ጊዜ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው ያሉት ፖምፔዮ፤ "በእዚህ ላይ የእኛ አስተዋጽኦ በተቻለን መጠን መደገፍ ነው" ብለዋል።"እንዲህ ዓይነት ትልልቅ ለውጦች ሲካሄዱ ውጤቶች በፍጥነት ላይታዩ ይችላሉ" ያሉት ፖምፔዮ፤ በአፍሪካ መዲና ከሴት ርዕሰ ብሔር ጋር ተገናኝተው መወያየታቸው እንዳስደነቃቸው አልሸሸጉም።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በምዕራብ ጉጂ ዞን ዱግዳ ዳዋ ወረዳ 59 ኩንታል ካናቢስ አደንዛዥ እጽ ተያዘ!
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን ዱግዳ ዳዋ ወረዳ 59 ኩንታል የካናቢስ አደንዛዥ እጽ ተያዘ።የጉጂ ዞን ፖሊስ መምሪያ ወንጀል መከላከል ሃላፊ ኮማንደር አዳሙ አባተ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፥ በዱግዳ ዳዋ ወረዳ 59 ኩንታል የካናቢስ አደንዛዥ እጽ በዛሬው ዕለት ተይዟል።አደንዛዥ እጹ በአንድ የጭነት ኤፍ ኤስ አር ተሽከርካሪ ተጭኖ ከሻሸመኔ ወደ ሞያሌ በመጓዝ ላይ እያለ ነው በህዝብ ጥቆማ የተያዘው።በወሩ ለሁለተኛ ጊዜ መሰል አደንዛዥ እጽ መያዙን የገለጹት ኮማንደር አዳሙ፥ በአካባቢው የሚስተዋለውን የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን ዱግዳ ዳዋ ወረዳ 59 ኩንታል የካናቢስ አደንዛዥ እጽ ተያዘ።የጉጂ ዞን ፖሊስ መምሪያ ወንጀል መከላከል ሃላፊ ኮማንደር አዳሙ አባተ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፥ በዱግዳ ዳዋ ወረዳ 59 ኩንታል የካናቢስ አደንዛዥ እጽ በዛሬው ዕለት ተይዟል።አደንዛዥ እጹ በአንድ የጭነት ኤፍ ኤስ አር ተሽከርካሪ ተጭኖ ከሻሸመኔ ወደ ሞያሌ በመጓዝ ላይ እያለ ነው በህዝብ ጥቆማ የተያዘው።በወሩ ለሁለተኛ ጊዜ መሰል አደንዛዥ እጽ መያዙን የገለጹት ኮማንደር አዳሙ፥ በአካባቢው የሚስተዋለውን የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ለሰዐታት ተቋርጦ የነበረው የሞባይል ዳታ ኢንተርኔት እና የጥሪ አገልግሎት ተመልሷል መስራት ጀምሯል።
የብሮድባንድ አገልግሎት እና የSMS አገልግሎት ብቻ ነበር ሲሰራ የነበረው።
ለምን ተቋረጠ ? የሚለውን አጥርተን እናቀርባለን።
@YeneTube @Fikerassefa
የብሮድባንድ አገልግሎት እና የSMS አገልግሎት ብቻ ነበር ሲሰራ የነበረው።
ለምን ተቋረጠ ? የሚለውን አጥርተን እናቀርባለን።
@YeneTube @Fikerassefa
አሜሪካ በአባይ ግድብ ዙሪያ ከታዛቢነት ወደ አደራዳሪነት ስለማደጓ የሱዳን መንግስት ቃል አቀባይ መናገራቸው ahramonline ዘግቧል።
@YeneTube @Fikerassefa
@YeneTube @Fikerassefa
የየካቲት 11ን 45ኛ አመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ የብልፅግና ፓርቲ የአባል አመራር ዶ/ር አብርሀም በላይ የሰጡት መግለጫ።
እጅግ የተከበርከውና ከባድ የህይወት መስዋእትነትን ጨምሮ ውድ ዋጋ በመክፈል እና መራራ ትግል በማካሄድ ለራስህ ብቻ ሳይሆን ለወገኖችህ የሚተርፍ ድል ያስመዘገበከው መላው የትግራይ ሕዝብ እንኳን ለ45ኛው የካቲት 11 በዓልህ በሰላም አደረስህ።ውድ የትግራይ ህዝብ እና የትግሉ ሰማእታት ቤተሰብ እና የትግሉ ሰለባዎች በሙሉ
ከ45 ዓመታት በፊት ይደርስብህ የነበረው የዘመናት ጭቆና...
ሙሉው መግለጫ👇👇👇
https://telegra.ph/anniversary-02-19
እጅግ የተከበርከውና ከባድ የህይወት መስዋእትነትን ጨምሮ ውድ ዋጋ በመክፈል እና መራራ ትግል በማካሄድ ለራስህ ብቻ ሳይሆን ለወገኖችህ የሚተርፍ ድል ያስመዘገበከው መላው የትግራይ ሕዝብ እንኳን ለ45ኛው የካቲት 11 በዓልህ በሰላም አደረስህ።ውድ የትግራይ ህዝብ እና የትግሉ ሰማእታት ቤተሰብ እና የትግሉ ሰለባዎች በሙሉ
ከ45 ዓመታት በፊት ይደርስብህ የነበረው የዘመናት ጭቆና...
ሙሉው መግለጫ👇👇👇
https://telegra.ph/anniversary-02-19