በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ውስጥ ተረፈ ምርት ተገኘ!
የቦይንግ 737 ማክስ ጀትላይነር አውሮፕላኖች የነዳጅ ቱቦ ውስጥ አላስፈላጊ ተረፈ ምርት መገኘቱ ተገለጸ። ግኝቱ የአውሮፕላኖቹ አስተማማኝነት ላይ ጥያቄ አስነስቷል።የቦይንግ 737 ዋና ኃላፊ "ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ነው" ሲሉ ለሠራተኞቻቸው የተናገሩ ሲሆን፤ የቦይንግ ቃል አቀባይ በበኩላቸው የተረፈ ምርቱ መገኘት አውሮፕላኑን ከበረራ አያዘገየውም ብለዋል። 737 ማክስ በያዝነው ዓመት አጋማሽ ላይ ወደ ሥራ ይመለሳል መባሉ ይታወሳል።የተረፈ ምርቱ መገኘት ይፋ ከመደረጉ በፊት የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች በረራ እንዲያቋርጡ መወሰኑ ይታወሳል። ይህም በኢትዮጵያና በኢንዶኔዥያ አውሮፕላኖቹ ተከስክሰው የብዙዎች ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ የተላለፈ ውሳኔ ነበር።
ለአየር መንገዶች ያልተላለፉ ብዙ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ክንፍ ላይ በሚገኙ የነዳጅ ቱቦዎች ውስጥ አላስፈላጊ ተረፈ ምርቶች ተትተው መገኘታቸውን ድርጅቱ አሳውቋል።የቦይንግ ቃል አቀባይ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ ተረፈ ምርቶች (በእንግሊዘኛ Foreign Object Debris (FOD) የሚባሉት) የተገኙት መጋዘን ውስጥ የሚገኙ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ላይ የጥገና ፍተሻ ሲደረግ ነበር።"ተረፈ ምርቱ መገኘቱን ተከትሎ ምርመራ አድርገናል፤ ማስተካከያም አድርገናል" ብለዋል ቃል አቀባዩ።ፌደራል አቪየሽን አድሚንስትሬሽን (ኤፍኤኤ)፤ ቦይንግ ስለ ተረፈ ምርቶቹ ጥልቅ ምርመራ እያደረገ መሆኑን እንደሚያውቅ ለቢቢሲ ተናግሯል።ተረፈ ምርቶች ስንል አውሮፕላኑ በሚገጣጠምበት ወቅት ሠራተኞች የረሷቸው የብረት ቁርጥራጮች ወይም ሌላ አላስፈላጊ ቁሶችን የሚያካትት ሲሆን፤ በአንድ ወቅት በከፍተኛ ሁኔታ ይሸጥ የነበረው 737 ማክስ ባለፉት ጊዜያት የገጠሙት እክሎች ላይ የሚደመር መሰናክል ነው።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የቦይንግ 737 ማክስ ጀትላይነር አውሮፕላኖች የነዳጅ ቱቦ ውስጥ አላስፈላጊ ተረፈ ምርት መገኘቱ ተገለጸ። ግኝቱ የአውሮፕላኖቹ አስተማማኝነት ላይ ጥያቄ አስነስቷል።የቦይንግ 737 ዋና ኃላፊ "ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ነው" ሲሉ ለሠራተኞቻቸው የተናገሩ ሲሆን፤ የቦይንግ ቃል አቀባይ በበኩላቸው የተረፈ ምርቱ መገኘት አውሮፕላኑን ከበረራ አያዘገየውም ብለዋል። 737 ማክስ በያዝነው ዓመት አጋማሽ ላይ ወደ ሥራ ይመለሳል መባሉ ይታወሳል።የተረፈ ምርቱ መገኘት ይፋ ከመደረጉ በፊት የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች በረራ እንዲያቋርጡ መወሰኑ ይታወሳል። ይህም በኢትዮጵያና በኢንዶኔዥያ አውሮፕላኖቹ ተከስክሰው የብዙዎች ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ የተላለፈ ውሳኔ ነበር።
ለአየር መንገዶች ያልተላለፉ ብዙ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ክንፍ ላይ በሚገኙ የነዳጅ ቱቦዎች ውስጥ አላስፈላጊ ተረፈ ምርቶች ተትተው መገኘታቸውን ድርጅቱ አሳውቋል።የቦይንግ ቃል አቀባይ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ ተረፈ ምርቶች (በእንግሊዘኛ Foreign Object Debris (FOD) የሚባሉት) የተገኙት መጋዘን ውስጥ የሚገኙ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ላይ የጥገና ፍተሻ ሲደረግ ነበር።"ተረፈ ምርቱ መገኘቱን ተከትሎ ምርመራ አድርገናል፤ ማስተካከያም አድርገናል" ብለዋል ቃል አቀባዩ።ፌደራል አቪየሽን አድሚንስትሬሽን (ኤፍኤኤ)፤ ቦይንግ ስለ ተረፈ ምርቶቹ ጥልቅ ምርመራ እያደረገ መሆኑን እንደሚያውቅ ለቢቢሲ ተናግሯል።ተረፈ ምርቶች ስንል አውሮፕላኑ በሚገጣጠምበት ወቅት ሠራተኞች የረሷቸው የብረት ቁርጥራጮች ወይም ሌላ አላስፈላጊ ቁሶችን የሚያካትት ሲሆን፤ በአንድ ወቅት በከፍተኛ ሁኔታ ይሸጥ የነበረው 737 ማክስ ባለፉት ጊዜያት የገጠሙት እክሎች ላይ የሚደመር መሰናክል ነው።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
አንበሳ ጋራዥ በ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ወደ ዴፖ ሊቀየር ነው!
ከሃምሳ ዓመት በላይ የአንበሳ አውቶቡስ ማቆሚያ እና የጥገና ቦታ ሆኖ ያገለገለው ዋናው መሥሪያ ቤት፣ በአንድ ጊዜ ከ850 በላይ አውቶቡሶችን ማስተናገድ እንችልና የተለያዩ አገልግሎቶችን እንዲሰጥ ‹‹የካ ዴፖ›› በሚል ግንባታ ሊከናወንለት ነው።በሦሰት ወራት ውስጥ የሚጀመረው ይህ ግንባታ፣ ኹለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር ወጪ ይጠይቃል። በተለምዶ ገርጂ መብራት ኃይል ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ በሚገኘው የአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት፣ በአስር ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ነው።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ከሃምሳ ዓመት በላይ የአንበሳ አውቶቡስ ማቆሚያ እና የጥገና ቦታ ሆኖ ያገለገለው ዋናው መሥሪያ ቤት፣ በአንድ ጊዜ ከ850 በላይ አውቶቡሶችን ማስተናገድ እንችልና የተለያዩ አገልግሎቶችን እንዲሰጥ ‹‹የካ ዴፖ›› በሚል ግንባታ ሊከናወንለት ነው።በሦሰት ወራት ውስጥ የሚጀመረው ይህ ግንባታ፣ ኹለት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር ወጪ ይጠይቃል። በተለምዶ ገርጂ መብራት ኃይል ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ በሚገኘው የአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት፣ በአስር ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ነው።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ስልጤ ዞን ወራቤ ገቡ!
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጤ ዞን ከተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ለመወያየት ነው ወራቤ የገቡት፡፡ከሁሉም የዞኑ ወረዳዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ውይይቱ ለማድረግ በቂ ዝግጅት ተደርጓል፡፡በውይይቱም የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ትኩረት ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጤ ዞን ከተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ለመወያየት ነው ወራቤ የገቡት፡፡ከሁሉም የዞኑ ወረዳዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ውይይቱ ለማድረግ በቂ ዝግጅት ተደርጓል፡፡በውይይቱም የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ትኩረት ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የአማዞን ባለቤት ጄፍ ቤዞስ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ትግል ለማገዝ 10 ቢሊየን ዶላር ለመስጠት ቃል ገቡ።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ህወሓት የተመሠረተበት 45ኛ ዓመት እየተከበረ ነው!
ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የተመሠረተበት 45ኛ ዓመት በመቀሌ ከተማ በመከበር ላይ ነው።በዓሉ የትግራይ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር)፣ የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ነባር ታጋዮች፣ የሰማዕታት ቤተሰቦች በተገኙበት በሰማዕታት ሐውልት የአበባ ጉንጉን በማስቀመጥ ተጀምሯል።በበዓሉ ላይ ከአክሱም ሥልጣኔ ጀምሮ ክልሉን አሁን እስካለበት ጊዜ የሚያሳዩ ልዩ፣ ልዩ ትርኢቶች ቀርበዋል።የክልሉ ልዩ ኃይል እና ፖሊስ ሠራዊት ያካተተ ወታደራዊ ሰልፍም ተካሒዷል።በዓሉን ለመታደም የሱዳን መንግሥት ተወካዮች፣ የፌዴራል ኃይሎች አባላት፣ ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ተወካዮች እየተሳተፉ ነው።
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የተመሠረተበት 45ኛ ዓመት በመቀሌ ከተማ በመከበር ላይ ነው።በዓሉ የትግራይ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር)፣ የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ነባር ታጋዮች፣ የሰማዕታት ቤተሰቦች በተገኙበት በሰማዕታት ሐውልት የአበባ ጉንጉን በማስቀመጥ ተጀምሯል።በበዓሉ ላይ ከአክሱም ሥልጣኔ ጀምሮ ክልሉን አሁን እስካለበት ጊዜ የሚያሳዩ ልዩ፣ ልዩ ትርኢቶች ቀርበዋል።የክልሉ ልዩ ኃይል እና ፖሊስ ሠራዊት ያካተተ ወታደራዊ ሰልፍም ተካሒዷል።በዓሉን ለመታደም የሱዳን መንግሥት ተወካዮች፣ የፌዴራል ኃይሎች አባላት፣ ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ተወካዮች እየተሳተፉ ነው።
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ኮድ ሁለት ዶልፊን መኪኖች እየተያዘ ነው!
በአብዛኛው (ዶልፊን ኮድ 2) መኪኖችን አዲስ አበባ ላይ እየተያዙ መሆኑን መረጃዎች እየደረሱን ይገኛሉ።
ለምን የሚለውን ጥያቄ ለመኪና ባለቤቶቹን ጠይቀን የተሰጠን ምላሽ
መልስ :- ኮድ 2 በቢኒባስ በህዝብ እንጂ ለቤት አገልግሎት አይውልም በሚል እንደታሰረባቸው ነው የነገሩን።
ነገር ግን የመኪኖቹ ሊብሬ ላይ የህዝብ እና የእቃ በሚል ነው የተሰጠቸው መኪኖቹ ከ5 ሰው ብላይ መጫን አይችልም እንዲሁም ከ6 ኩንታል በላይ መጫን እንደማይችሉ ይገልፃል።
@YeneTube @Fikerassefa
በአብዛኛው (ዶልፊን ኮድ 2) መኪኖችን አዲስ አበባ ላይ እየተያዙ መሆኑን መረጃዎች እየደረሱን ይገኛሉ።
ለምን የሚለውን ጥያቄ ለመኪና ባለቤቶቹን ጠይቀን የተሰጠን ምላሽ
መልስ :- ኮድ 2 በቢኒባስ በህዝብ እንጂ ለቤት አገልግሎት አይውልም በሚል እንደታሰረባቸው ነው የነገሩን።
ነገር ግን የመኪኖቹ ሊብሬ ላይ የህዝብ እና የእቃ በሚል ነው የተሰጠቸው መኪኖቹ ከ5 ሰው ብላይ መጫን አይችልም እንዲሁም ከ6 ኩንታል በላይ መጫን እንደማይችሉ ይገልፃል።
@YeneTube @Fikerassefa
የገንዘብ ሚንስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ሀርጌሳ ሱማሌ ላንድ ማቅናቱን ሰምተናል።
#Hargeisa #Somaliland
@YeneTube @Fikerassefa
#Hargeisa #Somaliland
@YeneTube @Fikerassefa
በደቡብ ኦሞ የኮሌራን ወረርሽኝ ለመቆጣጠር የኬሚካል እጥረት አጋጥሟል!
በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች ከታኅሳስ 15/2012 ጀምሮ የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ውሃን ለማከም የሚያገለግሉ ኬሚካሎችን ለማግኘት እና የትራንስፖርት አቅርቦት ላይ ችግር እንደገጠመው ዞኑ አስታወቀ።ወረርሽኙ በዞኑ ማሌ፣ ሀመር፣ ሰላማቦ እና ፀማይ በተሰኙ ወረዳዎች ላይ ከተከሰተ ከአንድ ወር 15 ቀን በላይ ሆኖታል። በበሽታው ከ 1ሺሕ 500 በላይ ሰዎች ተይዘው ሕክምና እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፣ የ20 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ከዞኑ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች ከታኅሳስ 15/2012 ጀምሮ የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ውሃን ለማከም የሚያገለግሉ ኬሚካሎችን ለማግኘት እና የትራንስፖርት አቅርቦት ላይ ችግር እንደገጠመው ዞኑ አስታወቀ።ወረርሽኙ በዞኑ ማሌ፣ ሀመር፣ ሰላማቦ እና ፀማይ በተሰኙ ወረዳዎች ላይ ከተከሰተ ከአንድ ወር 15 ቀን በላይ ሆኖታል። በበሽታው ከ 1ሺሕ 500 በላይ ሰዎች ተይዘው ሕክምና እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፣ የ20 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ከዞኑ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
መኪናችንን ያለ አግባብ መንግስት አስሮብናል ያሉ ግለሰቦች ለምክትል ከንቲባው ቅሬታቸውን አሰሙ
( Fidelpost.com)
በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች በመንገድ ላይ እንድንቆም እየተደረገ መኪናቹ በህገወጥ መልኩ በሌላ አገለግሎት ተሰማርቷል ተብለን አስከ 800,000 ብር ደረስ ቀረጥ ተጠይቀናል ያሉ ግለሰቦች ዛሬ ምክንትል ከንቲባ ታከለ በሚገኙበት የከተማው መስተዳደር ደጃፍ ዛሬ ጠዋት በመግኘት ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ቅሬታ አሰሚዎቹ ለፊደል ፓስት እንደተናገሩት 600 የሚጠጉ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በአዲሰ አበባ እና በደቡብ ክልል በ2 ቁጥር ታርጋ የተሰጣቸው D4D እና ዳማስ መኪኖቻቸው እንደታሰሩባቸው ገልፀዋል።
መኪናቸው ከተወሰደባቸው መሀል ሰዒድ ጠሀ እንዲህ በማለት ስለተፈጠረው ድርጊት ያስረዳል ” ከትናንት በስቲያ መሳርያ የያዙ ፓሊሶች መንገድ ላይ አስቆሙኝ ።ምን ተፈጠረ ስላቸው ትፈለጋለክ ብለው ወደ ጉሙሩክ ፅህፈት ቤት ወሰዱኝ። እዛም መኪናክ ለህዝብ አገልግሎት ወስደክ ለግልክ ስራ በማዋልክ 700, 000 ብር ቀረጥ ክፈል አሉኝ።
በጣም ግራ የገባኝ መኪናዬን በ2 ቁጥር ታርጋ ሳወጣ ፍቃድ የሰጠኝ የመንግስት አካል ነው።
ይሄ ስህተት ከሆነ መጠየቅ ያለበት እራሱ መንግስት እንጂ እኔ አይደለሁም” በማለት ቅሬታውን ገልፇል።
በጉምሩክ ኮሚሽን የአዲስ አበባ ቃሊቲ ጎሙሩክ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የበተነው ሰርኩርላር ደብዳቤ እንደሚያሳየው መኪኖቹ በህዝብ አገልግሎት ሰበብገብተው በግል አገልግሎት ሲሰሩ በመገኘታቸው ነው ለግል አገልግሎት በሚቀረጥ የቀረጥ ሂሳብ እንዲከፍሉ የተገደዱት ያሉት ብሏል።
ምንጭ:- Fidelpost.com
@Yenetube @Fikerassefa
( Fidelpost.com)
በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች በመንገድ ላይ እንድንቆም እየተደረገ መኪናቹ በህገወጥ መልኩ በሌላ አገለግሎት ተሰማርቷል ተብለን አስከ 800,000 ብር ደረስ ቀረጥ ተጠይቀናል ያሉ ግለሰቦች ዛሬ ምክንትል ከንቲባ ታከለ በሚገኙበት የከተማው መስተዳደር ደጃፍ ዛሬ ጠዋት በመግኘት ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ቅሬታ አሰሚዎቹ ለፊደል ፓስት እንደተናገሩት 600 የሚጠጉ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በአዲሰ አበባ እና በደቡብ ክልል በ2 ቁጥር ታርጋ የተሰጣቸው D4D እና ዳማስ መኪኖቻቸው እንደታሰሩባቸው ገልፀዋል።
መኪናቸው ከተወሰደባቸው መሀል ሰዒድ ጠሀ እንዲህ በማለት ስለተፈጠረው ድርጊት ያስረዳል ” ከትናንት በስቲያ መሳርያ የያዙ ፓሊሶች መንገድ ላይ አስቆሙኝ ።ምን ተፈጠረ ስላቸው ትፈለጋለክ ብለው ወደ ጉሙሩክ ፅህፈት ቤት ወሰዱኝ። እዛም መኪናክ ለህዝብ አገልግሎት ወስደክ ለግልክ ስራ በማዋልክ 700, 000 ብር ቀረጥ ክፈል አሉኝ።
በጣም ግራ የገባኝ መኪናዬን በ2 ቁጥር ታርጋ ሳወጣ ፍቃድ የሰጠኝ የመንግስት አካል ነው።
ይሄ ስህተት ከሆነ መጠየቅ ያለበት እራሱ መንግስት እንጂ እኔ አይደለሁም” በማለት ቅሬታውን ገልፇል።
በጉምሩክ ኮሚሽን የአዲስ አበባ ቃሊቲ ጎሙሩክ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የበተነው ሰርኩርላር ደብዳቤ እንደሚያሳየው መኪኖቹ በህዝብ አገልግሎት ሰበብገብተው በግል አገልግሎት ሲሰሩ በመገኘታቸው ነው ለግል አገልግሎት በሚቀረጥ የቀረጥ ሂሳብ እንዲከፍሉ የተገደዱት ያሉት ብሏል።
ምንጭ:- Fidelpost.com
@Yenetube @Fikerassefa
"ትግራይ ራስዋን የቻለች አገር ናት ብላችሁ አውጁ" ዶ/ር ደብረፅዮን
በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው ጣልቃ ገብነት እንዲሁም በትግራይ ላይ ያለው ጥላቻ የማይስተካከል ከሆነ "ትግራይ ራስዋን የቻለች አገር ናት ብላችሁ ልታውጁ ይገባል" ሲሉ ለተወካዮች ምክር ቤት ምክር ቤት አባላት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መልእክት አስተላልፈዋል።ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት ህወሓት የተመሰረተበትን 45ኛውን አመት አስመልክቶ በዛሬው እለት በመቀሌ ስታዲየም ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
የትግራይ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደብረፅዮን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባስተላለፉት መልእክት "የስልጣን ጊዜያችሁ እያለቀ ስለሚገኝ ከመበታተናችሁ በፊት ታሪክ ስሩ። በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ጣልቃ ገብነት በተለይም ትግራይን በተመለከተ በመሪዎች ደረጃ የተሰጡት የጥላቻና የፀረ ህዝብ ንግግሮች ችን በይፋ ኮንኑ" ብለዋል።አክለውም "ይህ የማይሆን ከሆነ ትግራይ ራሷን የቻለች አገር መሆኗን ወስኑ፤ አውጁ" ብለዋል።
"አገር በመበተን ሂደት ነበሩ ተብላችሁ በታሪክ እንዳትወቀሱ፤ ግዳጃችሁን ተወጡም" በማለት መልእክታቸውን ለተሰበሰበው ህዝብ አስተላልፈዋል።ዶ/ር ደብረፅዮን ከዚህም በተጨማሪ በትግራይና በኤርትራ መካከል ያለውን ታሪካዊ ዳራም እንዲሁም አሁንም ስላለው ግንኙነት ምክር አዘል መልእክት አስተላልፈዋል።
ህወሓት በትጥቅ ትግል በነበረበት ወቅት "የደርግን ስርዓት ለመጣል የትግራይ እና የኤርትራ ልጆች አንድ ጉድጓድ ላይ ተቀብረዋል" ያሉት ዶ/ር ደብረጽዮን ከኤርትራ ነጻነት በኋላም ቢሆን የትግራይ ህዝብ እና ህወሓት በኤርትራ ህዝብ የነጻነት ጥያቄ የማያወላዳ አቋም በመያዛቸው ብዙ ፖለቲካዊ ተቃውሞ ቢገጥመውም ከአቋሙ ውልፍት እንዳላለ ተናግረዋል።በሁለቱ ሃገራት ከተካሄደው ጦርነት በኋላ ሰላም ከመምጣቱ በፊትም የኤርትራ ተፈናቃዮችን "አቅፎ ጥላ" በመሆን ለኤርትራ ህዝብ ወዳጅ መሆኑን አስመሰክረዋል ብለዋል።
በየካቲት 11 በዓል ደግሞ የነበሩ ቅራኔዎችን ለመፍታት ዝግጁ መሆናቸውን የገለፁት ዶ/ር ደብረፅዮን የህዝብን ቀጣይነት አስምረውታል። "መንግሥታት ፈራሾች ናቸው እና ሰላማችንን ለማስቀጠል በህዝቦች መሀከል ውይይት እንዲጀመር እንፈልጋለን።" በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።በትግራይና ኤርትራ ህዝቦች መካከል ያለውን የቋንቋ እና ባህል ተመሳሳይነት፣ የጋራ ታሪክ እንዲሁም በደም የተሳሰሩ ከመሆናቸው አንፃር ለጦርነት የሚፈላለጉ ህዝቦች አለመሆናቸውን አፅንኦት በመስጠት ተናግረዋል።
ለዚህም የተለያዩ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትን በወነጀሉበት ንግግራቸው ህዝቡን የፖለቲካ አጀንዳ መደበቂያ አድርገውታልም ብለዋል።"የትግራይ እና ኤርትራ ህዝቦችን ወደ ጦርነት ሊማግዱት የሚያስቡ ኃይሎች አሉ፤ የተጀመረውን የሰላም ሂደት ተቋማዊ በሆነ መንገድ ከመፍታት ይልቅ ለፖለቲካ አጀንዳ መደበቅያ እያደረጉት ይገኛሉ" ብለዋል።የትግራይ ህዝብ እህትማማች ከሆነው የኤርትራ ህዝብ ጋር ግጭት የመግባት ምንም አይነት አላማ የለውም የሚሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ሁለቱን ሃገራት ወደ ጦርነት ለመክተት የሚደረጉ ሴራዎች እንዳሉም አልደበቁም።
ሁለቱን ሃገራት የሚያገናኙ መንገዶች መዘጋት እንዲሁም በኢትዮጵያ የሚገኙ የኤርትራውያን የስደተኞች መጠለያ እንዲዘጉ እና አዳዲስ ስደተኞች እንዳይቀበሉ የማድረግ ስራ "በኢትዮጵያና በኤርትራ መንግሥት የተደረገ ሴራ ነው" ብለዋል።አክለውም "የኤርትራ ህዝብ ችግር ችግራችን ስለሆነ ለእናንተ የሚዘጋ በር የለንም። ትግራይ አገራችሁ ነው፤ የኤርትራ ሠራዊት ትግራይ አገርህ ነው። እየታለመ ያለው የፖለቲካ ሴራ አብረን እናክሽፈው" በማለት ንግግራቸውን አድርገዋል።በአገሪትዋ የተለያዩ አከባቢዎች እየተካሄደ ስላለው የሠራዊት ስምሪት እና እሱን ተከትሎ ስለተከሰተው ጉዳት ተጠያቂ ሊኖር ይገባል ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን የትኛውን እንደሆነ ዝርዝር ከመስጠት ተቆጥበዋል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው ጣልቃ ገብነት እንዲሁም በትግራይ ላይ ያለው ጥላቻ የማይስተካከል ከሆነ "ትግራይ ራስዋን የቻለች አገር ናት ብላችሁ ልታውጁ ይገባል" ሲሉ ለተወካዮች ምክር ቤት ምክር ቤት አባላት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መልእክት አስተላልፈዋል።ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት ህወሓት የተመሰረተበትን 45ኛውን አመት አስመልክቶ በዛሬው እለት በመቀሌ ስታዲየም ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
የትግራይ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደብረፅዮን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባስተላለፉት መልእክት "የስልጣን ጊዜያችሁ እያለቀ ስለሚገኝ ከመበታተናችሁ በፊት ታሪክ ስሩ። በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ጣልቃ ገብነት በተለይም ትግራይን በተመለከተ በመሪዎች ደረጃ የተሰጡት የጥላቻና የፀረ ህዝብ ንግግሮች ችን በይፋ ኮንኑ" ብለዋል።አክለውም "ይህ የማይሆን ከሆነ ትግራይ ራሷን የቻለች አገር መሆኗን ወስኑ፤ አውጁ" ብለዋል።
"አገር በመበተን ሂደት ነበሩ ተብላችሁ በታሪክ እንዳትወቀሱ፤ ግዳጃችሁን ተወጡም" በማለት መልእክታቸውን ለተሰበሰበው ህዝብ አስተላልፈዋል።ዶ/ር ደብረፅዮን ከዚህም በተጨማሪ በትግራይና በኤርትራ መካከል ያለውን ታሪካዊ ዳራም እንዲሁም አሁንም ስላለው ግንኙነት ምክር አዘል መልእክት አስተላልፈዋል።
ህወሓት በትጥቅ ትግል በነበረበት ወቅት "የደርግን ስርዓት ለመጣል የትግራይ እና የኤርትራ ልጆች አንድ ጉድጓድ ላይ ተቀብረዋል" ያሉት ዶ/ር ደብረጽዮን ከኤርትራ ነጻነት በኋላም ቢሆን የትግራይ ህዝብ እና ህወሓት በኤርትራ ህዝብ የነጻነት ጥያቄ የማያወላዳ አቋም በመያዛቸው ብዙ ፖለቲካዊ ተቃውሞ ቢገጥመውም ከአቋሙ ውልፍት እንዳላለ ተናግረዋል።በሁለቱ ሃገራት ከተካሄደው ጦርነት በኋላ ሰላም ከመምጣቱ በፊትም የኤርትራ ተፈናቃዮችን "አቅፎ ጥላ" በመሆን ለኤርትራ ህዝብ ወዳጅ መሆኑን አስመሰክረዋል ብለዋል።
በየካቲት 11 በዓል ደግሞ የነበሩ ቅራኔዎችን ለመፍታት ዝግጁ መሆናቸውን የገለፁት ዶ/ር ደብረፅዮን የህዝብን ቀጣይነት አስምረውታል። "መንግሥታት ፈራሾች ናቸው እና ሰላማችንን ለማስቀጠል በህዝቦች መሀከል ውይይት እንዲጀመር እንፈልጋለን።" በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።በትግራይና ኤርትራ ህዝቦች መካከል ያለውን የቋንቋ እና ባህል ተመሳሳይነት፣ የጋራ ታሪክ እንዲሁም በደም የተሳሰሩ ከመሆናቸው አንፃር ለጦርነት የሚፈላለጉ ህዝቦች አለመሆናቸውን አፅንኦት በመስጠት ተናግረዋል።
ለዚህም የተለያዩ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትን በወነጀሉበት ንግግራቸው ህዝቡን የፖለቲካ አጀንዳ መደበቂያ አድርገውታልም ብለዋል።"የትግራይ እና ኤርትራ ህዝቦችን ወደ ጦርነት ሊማግዱት የሚያስቡ ኃይሎች አሉ፤ የተጀመረውን የሰላም ሂደት ተቋማዊ በሆነ መንገድ ከመፍታት ይልቅ ለፖለቲካ አጀንዳ መደበቅያ እያደረጉት ይገኛሉ" ብለዋል።የትግራይ ህዝብ እህትማማች ከሆነው የኤርትራ ህዝብ ጋር ግጭት የመግባት ምንም አይነት አላማ የለውም የሚሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ሁለቱን ሃገራት ወደ ጦርነት ለመክተት የሚደረጉ ሴራዎች እንዳሉም አልደበቁም።
ሁለቱን ሃገራት የሚያገናኙ መንገዶች መዘጋት እንዲሁም በኢትዮጵያ የሚገኙ የኤርትራውያን የስደተኞች መጠለያ እንዲዘጉ እና አዳዲስ ስደተኞች እንዳይቀበሉ የማድረግ ስራ "በኢትዮጵያና በኤርትራ መንግሥት የተደረገ ሴራ ነው" ብለዋል።አክለውም "የኤርትራ ህዝብ ችግር ችግራችን ስለሆነ ለእናንተ የሚዘጋ በር የለንም። ትግራይ አገራችሁ ነው፤ የኤርትራ ሠራዊት ትግራይ አገርህ ነው። እየታለመ ያለው የፖለቲካ ሴራ አብረን እናክሽፈው" በማለት ንግግራቸውን አድርገዋል።በአገሪትዋ የተለያዩ አከባቢዎች እየተካሄደ ስላለው የሠራዊት ስምሪት እና እሱን ተከትሎ ስለተከሰተው ጉዳት ተጠያቂ ሊኖር ይገባል ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን የትኛውን እንደሆነ ዝርዝር ከመስጠት ተቆጥበዋል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ሳውድ አረቢያ ከሰሞኑ ሕጋዊ ሆነው በምድሯ እየኖሩ ያልተፈቀደላቸውን ሥራ የሚሠሩ የተለያዩ ሃገራት ዜጎች ማሠር መጀመሯ ተሰማ።
በሕጉ መሠረት አንድ የውጭ ዜጋ ወደሳውዲ ሲገባ እንዲሠራ በተፈረደለትን የሥራ መስክ የማይሠራ ከሆነ እንደ ሕገወጥ ይቆጠራል።
በዚሁም መሠረት ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ አንድ ሺህ ገደማ የሚሆኑ የሌሎች ሃገራት ዜጎች ሕጋዊ ሆነው ሳለ ፈቃድ ከተሰጣቸው የሥራ መስክ ውጭ በመሠማራታቸው በሁለት ሳምንት ውስጥ መታሠራቸውን ከጅዳ ነብዩ ሲራክ የላከልን ዜና ያመለክታል።
ይህን አስመልክቶም በጅዳ ቆንስል ጀነራል አቶ አብዱ ያሲን እንደገለጹት በዚህ የሳውዲ መንግሥት ርምጃ 11 ኢትዮጵያውያን ተይዘዋል።
Via:- የጀርመን ድምፅ ራዲዮ
@YeneTube @Fikerassefa
በሕጉ መሠረት አንድ የውጭ ዜጋ ወደሳውዲ ሲገባ እንዲሠራ በተፈረደለትን የሥራ መስክ የማይሠራ ከሆነ እንደ ሕገወጥ ይቆጠራል።
በዚሁም መሠረት ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ አንድ ሺህ ገደማ የሚሆኑ የሌሎች ሃገራት ዜጎች ሕጋዊ ሆነው ሳለ ፈቃድ ከተሰጣቸው የሥራ መስክ ውጭ በመሠማራታቸው በሁለት ሳምንት ውስጥ መታሠራቸውን ከጅዳ ነብዩ ሲራክ የላከልን ዜና ያመለክታል።
ይህን አስመልክቶም በጅዳ ቆንስል ጀነራል አቶ አብዱ ያሲን እንደገለጹት በዚህ የሳውዲ መንግሥት ርምጃ 11 ኢትዮጵያውያን ተይዘዋል።
Via:- የጀርመን ድምፅ ራዲዮ
@YeneTube @Fikerassefa
🇹🇷#Study_in_Turkey!🇹🇷
ያለምንም ፈተና ቱርክ ሀገር ሄደው መማር ይፈልጋሉ?
90% ስኮላርሺኘ አግኝተው መማርስ?
#Sky_Education_Consultancy ይህን መልካም አጋጣሚ አመቻቸሎት!
Deadline: 22 Feb 2020
👉 Medicine & Health sciences
👉 Engineering
👉 Psychology
👉 Pharmacy
👉 Law
👉 Business Administration
👉 Computer science and IT
👉 Architecture
👉 Finance & banking.. and more
#Education_visa_Guaranteed
#Guaranteed_acceptance_letter
#ዛሬውኑ_ያናግሩን!! LIMITED SEATS
#Sky_Education_Consultancy
0977202020
ያለምንም ፈተና ቱርክ ሀገር ሄደው መማር ይፈልጋሉ?
90% ስኮላርሺኘ አግኝተው መማርስ?
#Sky_Education_Consultancy ይህን መልካም አጋጣሚ አመቻቸሎት!
Deadline: 22 Feb 2020
👉 Medicine & Health sciences
👉 Engineering
👉 Psychology
👉 Pharmacy
👉 Law
👉 Business Administration
👉 Computer science and IT
👉 Architecture
👉 Finance & banking.. and more
#Education_visa_Guaranteed
#Guaranteed_acceptance_letter
#ዛሬውኑ_ያናግሩን!! LIMITED SEATS
#Sky_Education_Consultancy
0977202020
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳውድ አረቢያ መንግሥት ከሰሞኑ በመውሰድ ላይ ያለውን ርምጃ አስመልክቶ በጅዳ ቆንስል ጀነራል አቶ አብዱ ያሲን የሰጡን ማብራሪያ ያድምጡ።
ቪዲዮ ነቢዩ ሲራክ ከጄዳ (DW)
@YeneTube @Fikerassefa
ቪዲዮ ነቢዩ ሲራክ ከጄዳ (DW)
@YeneTube @Fikerassefa
ጠቅላይ ሚኒስትሩን ያበሳጨው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቀባበል
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማክሰኞ የካቲት 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) ጋር ለመገናኘት ወደ ጽሕፈት ቤታቸው ያመሩ ሲሆን፣ በዕለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን የጫነው ተሽከርካሪ ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት በር ላይ ሲደርስ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የእንኳን ደኅና መጡ አቀባበል ለማድረግ እየጠበቋቸው ነበር፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የፕሮቶኮል ኃላፊዎች የመኪናውን በር ከፍተው ሚኒስትሩ እንዲወጡ ሲጠየቁ የሚጠብቁት ሰው እንዳለ ይገልጻሉ፡፡ ከዚያም ወዲያው ይጠበቁ የነበሩት ግለሰብ የፖምፒዮ ፎቶግራፈር መሆናቸውን የተረዱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) በብስጭት ፊታቸውን አዙረው ወደ ጽሕፈት ቤታቸው ሲያቀኑ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከኋላ ተከትለው ሰላምታ ሲያቀርቡላቸው በምሥሉ ላይ ይታያሉ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ያደረጉትን ውይይት ከጨረሱ በኋላ ዓብይ (ዶ/ር) ከፖምፒዮ የፕሮቶኮል ኃላፊዎች ፈቃድ ውጪ መኪና እያሽከረከሩ ምሳ ወደሚበሉበት ቦታ ወስደዋቸዋል፡፡
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማክሰኞ የካቲት 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) ጋር ለመገናኘት ወደ ጽሕፈት ቤታቸው ያመሩ ሲሆን፣ በዕለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን የጫነው ተሽከርካሪ ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት በር ላይ ሲደርስ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የእንኳን ደኅና መጡ አቀባበል ለማድረግ እየጠበቋቸው ነበር፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የፕሮቶኮል ኃላፊዎች የመኪናውን በር ከፍተው ሚኒስትሩ እንዲወጡ ሲጠየቁ የሚጠብቁት ሰው እንዳለ ይገልጻሉ፡፡ ከዚያም ወዲያው ይጠበቁ የነበሩት ግለሰብ የፖምፒዮ ፎቶግራፈር መሆናቸውን የተረዱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) በብስጭት ፊታቸውን አዙረው ወደ ጽሕፈት ቤታቸው ሲያቀኑ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከኋላ ተከትለው ሰላምታ ሲያቀርቡላቸው በምሥሉ ላይ ይታያሉ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ያደረጉትን ውይይት ከጨረሱ በኋላ ዓብይ (ዶ/ር) ከፖምፒዮ የፕሮቶኮል ኃላፊዎች ፈቃድ ውጪ መኪና እያሽከረከሩ ምሳ ወደሚበሉበት ቦታ ወስደዋቸዋል፡፡
Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ።
ሹመቱ ጨፌ ኦሮሚያ እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ የጸደቀ ሲሆን፥ አቶ ሽመልስ አብዲሳም ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሆነው የተሾሙት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ሌሎች ሹመቶችን ለጨፌው እያቀረቡ ሲሆን፥ በዚህም ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒን ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርገው አቅርበዋል።በጉባኤው የህዝቡ አንድነት እንዲጠናከርና የህብረተሰቡ ችግር እንዲቀረፍ እየተሰራ መሆኑ ተነስቷል።አቶ ሽመልስ ባደረጉት ንግግርም ዜጎች ሀገር ወዳድ እንዲሆኑ የክልሉ መንግስትና በየደረጃው ያለው መዋቅር ይሰራል ብለዋል።አያይዘውም በክልሉ የዜጎች መፈናቅል እንዳይኖር ሲሰሩ መቆየታቸውንም ጠቅሰዋል።
በኢኮኖሚው ረገድ ህግና ደንቦች አርሶ እና አርብቶ አደሩን መሰረት አድርገው ይወጣሉም ነው ያሉት አቶ ሽመልስ። የህዝቦች መልካም ግንኙነት እንዲጠናከርና መቀራረብ እንዲኖር የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጨፌ ኦሮሚያ ሚያዚያ ወር 2011 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ እንደሾማቸው የሚታወስ ነው።ጨፌው እያካሄደ ባለው ጉባኤ በዛሬው እለት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የረቂቅ ሕግ አዘገጃጀት ሥርዓትን ለመወሰን የወጣ አዋጅን ማጽደቁ ይታወሳል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ሹመቱ ጨፌ ኦሮሚያ እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ የጸደቀ ሲሆን፥ አቶ ሽመልስ አብዲሳም ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሆነው የተሾሙት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ሌሎች ሹመቶችን ለጨፌው እያቀረቡ ሲሆን፥ በዚህም ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒን ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርገው አቅርበዋል።በጉባኤው የህዝቡ አንድነት እንዲጠናከርና የህብረተሰቡ ችግር እንዲቀረፍ እየተሰራ መሆኑ ተነስቷል።አቶ ሽመልስ ባደረጉት ንግግርም ዜጎች ሀገር ወዳድ እንዲሆኑ የክልሉ መንግስትና በየደረጃው ያለው መዋቅር ይሰራል ብለዋል።አያይዘውም በክልሉ የዜጎች መፈናቅል እንዳይኖር ሲሰሩ መቆየታቸውንም ጠቅሰዋል።
በኢኮኖሚው ረገድ ህግና ደንቦች አርሶ እና አርብቶ አደሩን መሰረት አድርገው ይወጣሉም ነው ያሉት አቶ ሽመልስ። የህዝቦች መልካም ግንኙነት እንዲጠናከርና መቀራረብ እንዲኖር የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጨፌ ኦሮሚያ ሚያዚያ ወር 2011 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ እንደሾማቸው የሚታወስ ነው።ጨፌው እያካሄደ ባለው ጉባኤ በዛሬው እለት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የረቂቅ ሕግ አዘገጃጀት ሥርዓትን ለመወሰን የወጣ አዋጅን ማጽደቁ ይታወሳል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
አቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ። ሹመቱ ጨፌ ኦሮሚያ እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ የጸደቀ ሲሆን፥ አቶ ሽመልስ አብዲሳም ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሆነው የተሾሙት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ሌሎች ሹመቶችን ለጨፌው እያቀረቡ ሲሆን፥ በዚህም ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒን ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርገው አቅርበዋል።በጉባኤው የህዝቡ አንድነት እንዲጠናከርና የህብረተሰቡ…
በመቀጠልም ጨፌ ኦሮሚያ የተለያዩ ሹመቶችን አፅድቋል፥ በዚህም መሠረት፦
1. ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ - የኦሮሞ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምክትል ፕሬዝዳንት፣
2. አቶ ፈቃዱ ተሰማ - የጨፌ ኦሮሚያ የመንግሥት ተጠሪ፣
3. አቶ አዲሱ አረጋ - በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ፣
4. አቶ ጀማል ከድር- የኦሮሚያ ከተሞች ልማት እና ቤቶች ቢሮ ኃላፊ
5. አቶ ጌታቸው ባልቻ - የኦሮሚያ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ
6. አቶ ጅቢሪል መሐመድ - የኦሮሚያ አስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ
7. አቶ ቦጋለ ፈለቀ - የኦሮሚያ የኢንተርፕራይ እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ
8. አቶ ካሳሁን ጎፌ - የኦሮሚያ ገቢዎች ባለሥልጣን ኃላፊ
9. አቶ ዳንኤል አሰፋ - የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ
10. አቶ ከበደ ዴሲሳ - የኦሮሚያ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ
11. አቶ ተሾመ ግርማ - የኦሮሚያ ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኃላፊ
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
1. ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ - የኦሮሞ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምክትል ፕሬዝዳንት፣
2. አቶ ፈቃዱ ተሰማ - የጨፌ ኦሮሚያ የመንግሥት ተጠሪ፣
3. አቶ አዲሱ አረጋ - በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ፣
4. አቶ ጀማል ከድር- የኦሮሚያ ከተሞች ልማት እና ቤቶች ቢሮ ኃላፊ
5. አቶ ጌታቸው ባልቻ - የኦሮሚያ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ
6. አቶ ጅቢሪል መሐመድ - የኦሮሚያ አስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ
7. አቶ ቦጋለ ፈለቀ - የኦሮሚያ የኢንተርፕራይ እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ
8. አቶ ካሳሁን ጎፌ - የኦሮሚያ ገቢዎች ባለሥልጣን ኃላፊ
9. አቶ ዳንኤል አሰፋ - የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ
10. አቶ ከበደ ዴሲሳ - የኦሮሚያ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ
11. አቶ ተሾመ ግርማ - የኦሮሚያ ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኃላፊ
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የኦሮሚያ ቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ አባላት ክህነታቸው ተይዟል ሲል ቀዱስ ሲኖዶሱ አወጀ።
የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ ከየካቲት 9 እስከ 11/2012 ዓ.ም ድረስ ያደረገውን አስቸኳይ ስብሰባ ተከትሎ ዛሬ ከሰዓት ላይ መግለጫ ሰጥቷል።
የሲኖዶሱን መግለጫ በጽሁፍ ያቀረቡት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሲሆኑ በሚከተሉት ላይ የቅዱስ ሲኖዶሱን አቋም አሳውቀዋል።
https://telegra.ph/detail-02-19
የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ ከየካቲት 9 እስከ 11/2012 ዓ.ም ድረስ ያደረገውን አስቸኳይ ስብሰባ ተከትሎ ዛሬ ከሰዓት ላይ መግለጫ ሰጥቷል።
የሲኖዶሱን መግለጫ በጽሁፍ ያቀረቡት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሲሆኑ በሚከተሉት ላይ የቅዱስ ሲኖዶሱን አቋም አሳውቀዋል።
https://telegra.ph/detail-02-19
OBS : OMN : LTV
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንግስት በሶስት መገናኛ ብዙሃን ላይ እርምጃ እንዲወስድ ጠየቀች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያኒቱና በምእመናን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል፡፡
ቤተክርስቲያኗ ለኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን በላከዉ መግለጫ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ኦኤም ኤን፣ ኤል ቲቪ እና ኦሮሚያ ብሮድካስት ሰርቪስ ወይም ኦቢኤስ የተሰኙ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ በጥንታዊትና ሐዋርያዊት በሆነችዋ እንዲሁም ለአገርና ለወገን ባለውለታና ባለታሪክ በሆነችው ቤተ ክርስቲያናችን የከፈቱት የስም ማጥፋት ዘመቻ እያካሄዱ ናቸው ብላለች።
መገናኛ ብዙሃኑ ታሪክን እያበላሹ የተሳሳተ መረጃ ለሕዝብ እያስተላፉ ይገኛሉም ብላለች ቤተክርስቲያኗ።
ከዚህም የተነሳ ከ60 ሚሊዮን ያላነሰ ተከታይ ያላትን ቤተ ክርስቲያን ክብሯንና ልዕልናዋን ዝቅ ባደረገ መልኩ የሚያስተላልፉት የተሳሳተ መረጃ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ብቻ ሳይሆን አገራዊ ቀውስ ለማምጣት እየተደረገ ያለ ጥረት በመሆኑ የሚመለከተው የመንግሥት አካል አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ የጣቢያዎቹ ኃላፊዎች ከብዙኃን መገናኛ ሕግ እና ደንብ አኳያ በሕግ እንዲጠየቁ ለወደፊቱም ከእንዲህ ዓይነት ሕገወጥ ድርጊት እንዲታቀቡ መንግሥትም በዚሁ ላይ አስፈላጊውን ውሳኔ እንዲያሳልፍልን ቅዱስ ሲኖዶስ ጠይቋል፡፡
Via:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንግስት በሶስት መገናኛ ብዙሃን ላይ እርምጃ እንዲወስድ ጠየቀች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያኒቱና በምእመናን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል፡፡
ቤተክርስቲያኗ ለኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን በላከዉ መግለጫ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ኦኤም ኤን፣ ኤል ቲቪ እና ኦሮሚያ ብሮድካስት ሰርቪስ ወይም ኦቢኤስ የተሰኙ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ በጥንታዊትና ሐዋርያዊት በሆነችዋ እንዲሁም ለአገርና ለወገን ባለውለታና ባለታሪክ በሆነችው ቤተ ክርስቲያናችን የከፈቱት የስም ማጥፋት ዘመቻ እያካሄዱ ናቸው ብላለች።
መገናኛ ብዙሃኑ ታሪክን እያበላሹ የተሳሳተ መረጃ ለሕዝብ እያስተላፉ ይገኛሉም ብላለች ቤተክርስቲያኗ።
ከዚህም የተነሳ ከ60 ሚሊዮን ያላነሰ ተከታይ ያላትን ቤተ ክርስቲያን ክብሯንና ልዕልናዋን ዝቅ ባደረገ መልኩ የሚያስተላልፉት የተሳሳተ መረጃ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ብቻ ሳይሆን አገራዊ ቀውስ ለማምጣት እየተደረገ ያለ ጥረት በመሆኑ የሚመለከተው የመንግሥት አካል አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ የጣቢያዎቹ ኃላፊዎች ከብዙኃን መገናኛ ሕግ እና ደንብ አኳያ በሕግ እንዲጠየቁ ለወደፊቱም ከእንዲህ ዓይነት ሕገወጥ ድርጊት እንዲታቀቡ መንግሥትም በዚሁ ላይ አስፈላጊውን ውሳኔ እንዲያሳልፍልን ቅዱስ ሲኖዶስ ጠይቋል፡፡
Via:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
👍1