YeneTube
119K subscribers
31.3K photos
484 videos
79 files
3.86K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
ምርጫ ቦርድም ኦፌኮ ጃዋርን በምን ህጋዊ ማስረጃ አባል አድርጎ እንደተቀበለ እንዲያብራራ ጠይቋል

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ በቅርቡ ፓርቲውን የተቀላቀለው ጃዋር መሀመድ ኢትዮጵያዊ ዜግነት እንዳለው የሚያረጋግጥ ማስረጃ እንዲያቀርብ ደብዳቤ እንደፃፈለት ዋዜማ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል።

የቀድሞው የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) ስራ አስኪያጅ ጃዋር መሀመድ የአሜሪካ ዜግነት ያለው ሲሆን የውጪ ዜግነቱን መልሶ የኢትዮጵያ ዜግነት ለመውስድ እየሞከረ እንደነበር ከወራት በፊት ገልጿል። ይሁንና የዜግነቱ ጉዳይ እልባት ሳያገኝ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲን ተቀላቅሎ መታወቂያም ወስዷል።

ጉዳዩን በተመለከት ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ለኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ድብዳቤ ፅፎ ማስረጃ የጠየቀ ሲሆን ፓርቲው በበኩሉ ጃዋር ማስረጃ እንዲያቀርብ በደብዳቤ አሳስቧል። የፓርቲው ሊቀመንበር መረራ ጉዲና ይህን መረጃ ለዋዜማ አረጋግጠዋል።
“የኛ አባል ሲሆን ለምን ይህ ጥያቄ እንደተነሳ ባይገባኝም እኛ ደብዳቤ ፅፈንለታል” ብለዋል ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና።

እንዴት ለዜግነቱ ማረጋገጫ ሳያቀርብ በህግ ባልተፈቀደ መልኩ ጃዋር መሀመድ ፓርቲውን እንዲቀላቀልና መታወቂያ እንዲወስድ እንደተፈቀደለት ከዋዜማ ላነሳንላቸው ጥያቄ መረራ ጉዲና ሲመልሱ ” እኛ የምናውቀው ኢትዮጵያዊ መሆኑን ነው፣ የሀገሩን ቋንቋ ይናገራል፣ ፊቱም ኢትዮጵያዊ ይመስላል፤ መንግስትም ይህን ያውቃል” ሲሉ ቀልድ አዘል ምላሽ ስጥተዋል።

በጃዋር ዜግነት ላይ ከመንግስት የሚነሳው ጥያቄ ፖለቲካዊ ፍላጎትንም ያካተተ ሊሆን ይችላል ያሉት መረራ ጉዲና ጃዋር በቅርብ ዜግነቱን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ይዞ እንደሚመጣ ተስፋ እንደሚያደርጉና ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድም በጊዜው ምላሽ እንደሚሰጡ ነግረውናል።

ፓርቲያቸው ከጃዋር መሀመድ ጋር የቆየ ግንኙነት እንዳለው ያመለከቱት መረራ ፓርቲውንም የተቀላቀለው ከዚህ ቀደም በነበራቸው ትብብርና መቀራረብ የተነሳ መሆኑን ይናገራሉ።

በኢትዮጵያ ህግ መሰረት ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ሰው በፖለቲካ ውስጥ የመሳተፍ መብት የለውም። ጃዋር መሀመድ ከሶስት ወራት በፊት በመጪው ምርጫ ለመወዳደር መዘጋጀቱን ግን ደግሞ ለየትኛው የስልጣን ወንበር እንደሚወዳደር እንዳልወሰነ ሲገልፅ ተደምጧል።

ጃዋር መንግስት ባደረገለት ከፍተኛ የአቀባበል ስነስርዓት ከአንድ አመት ተኩል በፊት ወደ ሀገር ቤት መግባቱ ይታወሳል። በወቅቱም በስልጣን ላይ ካለው መንግስት ጋር ተባብሮ ለመስራት እቅድ እንዳለው በማወጅ የድረ ገፅ ዘመቻ ሲያደርግበት የነበረውን ላፕቶፕ ኮምፒውተር የትግሉን መገባደድ ተምሳሌትነት እንዲሆን በማለት በወቅቱ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ለነበሩት ለማ መገርሳ በሚሊኒየም አዳራሽ በህዝብ ፊት ማስረከቡ አይዘነጋም።

Via:- ዋዜማ ራዲዮ
@YeneTube @Fikerassefa
በእስክንድር ነጋ የሚመራው ፓርቲ እውቅና አገኘ!

በቅርቡ የተመሰረተው እና ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ የተሰኘው አዲሱ ፓርቲ በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ የእውቅና ሰርተፍኬት አግኝቷል።

ምንጭ:- አሐዱ ሬዲዮ
@YeneTube @Fikerassefa
ቅ/ጳውሎስ ሆስፒታል ያወጣው ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ!

@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጥር 06 ጀምሮ አዳዲስ የሚኒስትርነት ሹመት የሰጡ ሲሆን በዚሁ መሠረት ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር፣ ኢ/ር) የትምህርት ሚኒስትር፣ አቶ መላኩ አለበል የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር እንዲሁም አብርሃም በላይ (ዶ/ር) የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው ከጥር 06 ቀን 2012 ጀምሮ መሾማቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።

Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጥር 06 ጀምሮ አዳዲስ የሚኒስትርነት ሹመት የሰጡ ሲሆን በዚሁ መሠረት ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር፣ ኢ/ር) የትምህርት ሚኒስትር፣ አቶ መላኩ አለበል የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር እንዲሁም አብርሃም በላይ (ዶ/ር) የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው ከጥር 06 ቀን 2012 ጀምሮ መሾማቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመልክቷል። Via ETV @YeneTube…
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የህወሓት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚዓብሔር ከጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ካቢኔ መሰናበታቸው ታውቋል። ከአንድ አመት በላይ የኢትዮጵያ ንግድና ኢንዱስትሪ ሚንስትር የነበሩት ፈትለወርቅ ገብረእግዚዓብሔር ተሽረዉ በአቶ መላኩ አለበል መተካታቸውን ኢቲቪ ዘግቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
አብን የዜግነት ፖለቲካ የሚከተሉ ፓርቲዎች ከአማራ ክልል ውጪ ባሉ ክልሎችም በስፋት እንዲንቀሳቀሱ ጥሪ አቀረበ።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የዜግነት ፖለቲካ የሚከተሉ አብዛኞቹ ፓርቲዎች ከአማራ ክልል ውጪ ተንቀሳቅሰው የሚሰሩ አይደሉም፤ ኢትዮጵያ ደግሞ አማራ ክልል ብቻ አይደለችም ብሏል፡፡የአብን ሊቀ መንበር ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት አማራው ኢትዮያዊ ነኝ ስላለ ብቻ ፤ እረኛ እንደሌለው ከብት ተበትኖ ሲፈናቀልና የሀገር ውስጥ ስደተኛ ሆኖ ነው የኖረው ብለዋል፡፡

አሁን አማራን ፤ የሚወዳትን ኢትዮጵያን እንደ ማታለያ በመጠቀም ድምፁን ማግኘት ሳይሆን የሚያስፈልገው ጉዳቱን ተረድቶ ጥቅሙን ማስከበር ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች ተንቀሳቅሰው ይሄን የተከፋፈለ ህዝብ አንድ የሚያደርግ የፖለቲካ ስራ ሰርተው ወደ አንድ ጠረጴዛ የሚያመጡ የዜግነት ፖለቲከኞች ጋር ችግር የለብንም ብለዋል አቶ ደሳለኝ፡፡

አሁን ባለው የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ የአማራን ጥቅም ተደራድሮ የሚያስከብር አደራጃጀት አማራጭ የለውም፡፡በአማራነት መደራጀት መተኪያ የሌለው መንገድ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ይሄ ደግሞ ኢህአዴግ ኢትዮጵያን ሲያስተዳድር የኢትዮጵያን መልክ የምናይበትን መነፅር ብሔር ብቻ ስላደረገው የተፈጠረ ፣ ያለ ሀቅ ስለሆነ ልናወግዘው አይገባም ብለዋል፡፡

ምንጭ:Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ ስም አውጪላቸው ለተባለችው ኮከብና ፕላኔት፣ “ቡና” እና “አቦል” የሚሉ ስሞች እንደሰጠቻቸው ተነገረ፡፡

ለኢትዮጵያ የተሰጠውን የህዋ አካል ስያሜን በተመለከተ ስሞችን እንዲመርጥ ሀላፊነት የተሰጠው ብሔራዊ የስም አሰያየም ኮሚቴ እንዳስታወቀው ከሆነ “ቡና” ለኮከቡ የተሰጠ ስያሜ ሲሆን፣ “አቦል” ደግሞ ፕላኔቱ የሚጠራበት ሆኗል፡፡ስያሜው የተሰጠው በሳይንሳዊ አጠራራቸው HD 16175 ለተባለችው ኮከብና ኮከቧ ለምትዞራት HD 16175-6 ለተባለች ፕላኔት ነው ተብሏል፡፡ከግንቦት 2011 ጀምሮ በፅሁፍ መልዕክት፣ በማህበራዊ ድረ ገፆችና በደብዳቤ ከ275 ሺ በላይ ስሞች ተሰብስበው እንደነበር ኮሚቴው ተናግሯል፡፡

በባለሞያዎች ከተተቹ በኋላ ሶስት ስሞች ለዓለም አቀፉ አስትሮኖሚካል ህብረት የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥባቸው የቀረቡ ሲሆን ህብረቱ አስፈላጊውን ግምገማ በማድረግ “ቡና” እና “አቦል” የሚሉ ስሞችን አፅድቋል ተብሏል፡፡ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ህብረት ለኢትዮጵያ ይህንን ፕላኔትና ኮከብ የመሰየም እድል የሰጣት የአንድ መቶኛ ዓመት ምስረታውን አስመልክቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡

Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
#የመጨረሻ_የሆነው_ባይብል_ኮድ_3_በገበያ_ላይ_ዋለ!

#በአንድ_ምሽት_ሽያጭ_ብቻ_ሪከርድ_የያዘ_መጽሐፍ!!

ቁጥር 3 ባይብል ኮድ፡-

*ስለ አርማጌዶን መቅረብና ዓለምን ከጥፋት የማዳን ቁልፍ በኮድ ስለመቀመጡ…

* አሜሪካኖች የሚኮሩበትና አለም የሚያደንቀው ዝነኛው የስለላ ድርጅት ሲ.አይ.ኤ በቸልተኝነት በርካታ ከባባድ ስህተቶችን እንደሚሰራ…

*በዓለም ላይ ያሉ መሪዎች ስለሚገደሉበት ቦታ፣ ስለሚገድሏቸው ሰዎች ስም…

*ስለ እያንዳንዳችን ዕጣ ፈንታ እንዲሁም በኮድ ተፅፎ ስለሚገኘው ሚስጥራዊ ቁልፍና በአለም ላይ ስለተከናወኑና ወደፊት ስለሚከናወኑ ድርጊቶች ሁሉ በስም፣ በቀን፣ በቦታ ሳይቀር ከዛሬ ሶስት ሺ ዓመት በፊት…

#በመፅሐፍ_ቅዱስ_ውስጥ_በኮድ_ተቀምጧል!!

ቁጥር 3 ባይብል ኮድ ኮዶቹን እየፈታ ያስገርመናል፡፡

‹‹#ይህ_መፅሐፍ_እውነትነቱ_በዘመናዊ_ሳይንስ_የተረጋገጠለት_ተአምር_ነው››

በየመፅሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኙታል
Forwarded from YeneTube
 ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ
 በድረ ገፁ ላይ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ በማሟላት ዕቃዎቹን ወይም አገልግሎቱን መሸጥ ይችላል።
 ከ2700 በላይ ዕቃዎች
@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com
 0953707070
Forwarded from YeneTube
Samsung Galaxy A10s
2019 Model Phone
Brand New Packed &
Original with Full Accessories
6.2inch screen size
32GB Storage
13MP camera 1080HD
4000mAh battery capacity
Dual Sim Slot

📩 @CloudMultiTrading 📩
📞 0944182119 📞

@CloudTrading @CloudTrading
Forwarded from YeneTube
ሰርግዎን በቅርቡ ለመሰረግ አስበዋል?
እንግድያውስ የዲኮሩን ስራ በእኛ ላይ ይጣሉት

💥LEAD DECOR

በባህላዊ እና ዘመናዊ መልኩ ዝግጅትዎን እናስውባለን::
➡️ለሠርግ
➡️ለመልስ
➡️ለልደት
➡️ለስብሰባ አዳራሽ
እንዲሁም
ለልዩ ልዩ ዝግጅቶች

0912672317, 0920315163 ደውለው ያነጋግሩን

ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት ቻናላችንን ይቀላቀሉ⬇️
https://tttttt.me/LeadDecor
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሹም ሽር ሊያደርግ መሆኑን ሪፖርተር አስነብቧል፡፡ የትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊው ሰለሞን ኪዳኔ ከሃላፊነት ይነሳሉ፡፡ የመሬት አስተደዳር፣ የፕላን እና ልማት ኮሚሽን፣ የትምህርት፣ ቱሪዝም እና ፍትህ ቢሮ ሃላፊዎችም እንደሚነሱ ይጠበቃል፡፡ በተለይ የመሬት አስተዳደር ሹም ሽሩ እስከ ወረዳ ይወርዳል፡፡

Via Wazema Radio
@YeneTube @FikerAssefa
የአውሮፓ ኅብረት የነሐሴውን ሀገር ዐቀፍ ምርጫ ለመታዘብ እችል እንደሆነ ሁኔታዎችን እያጠናሁ ነው ብሏል፡፡ የኅብረቱ ቡድን ለ2 ሳምንታት በክልሎች ተዘዋውሮ የጸጥታ እና ትራንስፖርቱን አመችነት ይገመግማል፡፡ ይህ የተገለጸው የኅብረቱ ተወካዮች ዛሬ ከፓርላማው አመራሮች ጋር ባደረጉት ውይይት እንደሆነ የዘገበው ፋናን ጠቅሶ ዋዜማ ራዲዮ ነው፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን በታላቁ የኅዳሴ ግድብ የውኃ አሞላል እና አስተዳደር የመጨረሻ የሥምምነት ረቂቅ ለማዘጋጀት በካርቱም ተሰበሰቡ። አሜሪካ እና የዓለም ባንክ በሚታዘቡት በዚህ ውይይት የሶስቱ አገራት የቴክኒክ እና የሕግ ባለሙያዎች "የሥምምነት ረቂቅ" እንደሚያዘጋጁ የግብፅ የመስኖ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ መሐመድ ኤል-ሴባዊ ተናግረዋል። የሚዘጋጀው የሥምምነት ረቂቅ በግድቡ የውኃ አሞላል እና አስተዳደር ላይ እንደሚያተኩር ቃል-አቀባዩ ጨምረው ገልጸዋል።በካርቱም የተጀመረው ስብሰባ እስከ ነገ ይዘልቃል።

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በብሔር ፌዴራሊዝም የተደራጁና የህዝቦችን የራስን መብት በራስ የመወሰን መብት እንዲከበር እንደሚታገሉ የሚገልፁ ፓርቲዎች በዛሬው ዕለት አብረው ለመስራት የሚያስላቸውን ፊርማ ተፈራርመዋል። የስምምነቱ አካል የሆኑት የኦጋዴን ነፃነት ግንባር (ኦብነግ)፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)፣ እንዲሁም ሞጂና አገውን የወከሉ ፓርቲዎች እንደተገኙ ከኦብነግ የትዊተር ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ።

@YeneTube @FikerAssefa
Audio
በአዲስ አበባ በ10ሩም ክፍለ ከተሞች ሲሰሩ የቆዩ የመሬት አስተዳደር እና ማኔጅመንት የስራ ኃላፊዎች ከወንበራቸው መነሳታቸው ተሰምቷል፡፡

የስራ ኃላፊዎቹ ከቦታቸው የተነሱት ከንቅዘት እና ከሌብነት ጋር በተያያዘ እንደሆነ ሰምቻለው ይለናል ሸገር ራዲዮ፡፡ከ10ሩ ክፍለ ከተሞች አንዱ በሆነው ቦሌ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ባለሙያዎች የተጭበረበረ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እስከማዘጋጀት የደረሰ የማጭበርበር ስራ ውስጥ ተዘፍቀው ነበር፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ያዳምጡ⬆️⬆️
Via Sheger FM
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በምርጥ የአፍሪካ ወጣት አትሌት ዘርፍ አሸናፊ ሆኑ!

የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን (CAA) በትናንትናው እለት የ2019 ወንድና ሴት ምርጥ አትሌቶችን እንዲሁም አሰልጣኞችን ስም ዝርዝር አሳውቋል፡፡በምርጥ የአፍሪካ ወጣት ሴት አትሌት ዘርፍ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ በ1500ሜ. ምድብ (3፡54፡38) በምርጥ የአፍሪካ ወጣት ወንድ አትሌት ዘርፍ አትሌት ለሜቻ ግርማ በ3000ሜ. መሰናክል ምድብ (8፡01፡36) የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ሲል ኮማንደር ሁሴን ሺቦን መርጧል፡፡

ምንጭ: ኢፕድ
@YeneTube @FikerAssefa
1
የመንግሥታት ግንኙነት ሥርዓት ረቂቅ አዋጅ ዳግም እንዲፈተሽ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ የፍትህና የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጠየቀ።

 ቋሚ ኮሚቴው የመንግሥታት ግንኙነት ሥርዓት ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ ትናንት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል።በውይይቱ ላይ ረቂቅ አዋጁ የክልል መንግሥታት ያሏቸውን ሥልጣንና ተግባራት በማይጋፋ መልኩ እንዲቀራረቡና የጋራ ዕቅድ ነድፈው እንዲንቀሳቀሱ ያስችላል ተብሏል።
በየእርከኑ በመግሥታትና አቻ ተቋማት መካከል በመርህ ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የትብብር ሥርዓት ለመፍጠር ያግዛልም ነው የተባለው።

በረቂቁ ላይ የአዲስ አበባና የድሬዳዋ መስተዳድሮች እንደ ክልል መጠቀሳቸው ግን አግባብ አለመሆኑን ተወያዮቹ ገልጸዋል።ይህም ረቂቁ ለክልል መንግሥታት የጎንዮሽ ግንኙነት እና የክልልና የፌደራል መንግሥት የተዋረድ ግንኙነትን እንደሚመለከት ከሚለው ጋር ይጣረሳል ብለዋል።ረቂቁ ክልልና የፌደራል መንግሥትን በእኩል አተያይ የማቅረብ አዝማሚያው ግልጽነት እንደሚጎድለው ያነሱት ተወያዮቹ፥ በረቂቁ ላይ ደንብ የሚያወጣው አካል ተለይቶ አለመቀመጡም የረቂቁን ምልዑነት እንደሚያጎድለው አስረድተዋል።

ረቂቁ ሕገ መንግሥቱ ማሻሻያ ከተደረገበት በኋላ ይፅደቅ የሚል ሃሳብ ተነስቶ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፥ ረቂቅ ሕጉ ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ጋር ሲነጻጸር ኢትዮጵያ ይህን ህግ በማርቀቅ ረገድ መዘግየቷ ተጠቁሞ ውሳኔ እንዲሰጥበት ተጠይቋል።በረቂቁ መንግሥታት በሚመሰርቷቸው የመድረክ ውሳኔዎች በ3/4 ድምፅ ይጽደቅ በሚለው ላይ፥ በማይገኙ የመድረኩ አባላት ላይ ተፈጻሚነትን በተመለከተ የተቀመጠው ሃሳብ ግልጽነት ይጎድለዋል ተብሏል።ከዚህ ባለፈም ረቂቁ አስገዳጅ መሆን አለመሆኑን በተመለከተ ጥያቄዎች ተነስተው ውይይት የተደረገ ሲሆን፥ ረቂቁ ተሻሽሎ እንዲቀርብ ለዳግም እንዲታይ መወሰኑን ከኢዜአና ፋና ዘግበዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ በትናንትናው ዕለት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጓል።ብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚው በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ አቋም እንደሚወስድ እና ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ታውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
#የመጨረሻ_የሆነው_ባይብል_ኮድ_3_በገበያ_ላይ_ዋለ!

#በአንድ_ምሽት_ሽያጭ_ብቻ_ሪከርድ_የያዘ_መጽሐፍ!!

ቁጥር 3 ባይብል ኮድ፡-

*ስለ አርማጌዶን መቅረብና ዓለምን ከጥፋት የማዳን ቁልፍ በኮድ ስለመቀመጡ…

* አሜሪካኖች የሚኮሩበትና አለም የሚያደንቀው ዝነኛው የስለላ ድርጅት ሲ.አይ.ኤ በቸልተኝነት በርካታ ከባባድ ስህተቶችን እንደሚሰራ…

*በዓለም ላይ ያሉ መሪዎች ስለሚገደሉበት ቦታ፣ ስለሚገድሏቸው ሰዎች ስም…

*ስለ እያንዳንዳችን ዕጣ ፈንታ እንዲሁም በኮድ ተፅፎ ስለሚገኘው ሚስጥራዊ ቁልፍና በአለም ላይ ስለተከናወኑና ወደፊት ስለሚከናወኑ ድርጊቶች ሁሉ በስም፣ በቀን፣ በቦታ ሳይቀር ከዛሬ ሶስት ሺ ዓመት በፊት…

#በመፅሐፍ_ቅዱስ_ውስጥ_በኮድ_ተቀምጧል!!

ቁጥር 3 ባይብል ኮድ ኮዶቹን እየፈታ ያስገርመናል፡፡

‹‹#ይህ_መፅሐፍ_እውነትነቱ_በዘመናዊ_ሳይንስ_የተረጋገጠለት_ተአምር_ነው››

በየመፅሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ያገኙታል