የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጅቡቲ ቅርንጫፍ ከፈተ
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ጉሌህ በትላንትናው ዕለት የባንኩን ስራ መጀመር ይፋ አድርገዋል፡ ፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ባጫ ጊናና በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ አምባሳደር አብዱልአዚዝ ሙሐመድም በስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአገር ውጭ ቅርንጫፉ ከጅቡቲው ባሻገር በደቡብ ሱዳንም ከፍቶ በስራ ላይ ይገኛል፡፡
ምንጭ ፡- ጅቡቲ ፕሬስና ሶማሌላንድሰን
@YeneTube @Fikerassefa
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ጉሌህ በትላንትናው ዕለት የባንኩን ስራ መጀመር ይፋ አድርገዋል፡ ፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ባጫ ጊናና በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ አምባሳደር አብዱልአዚዝ ሙሐመድም በስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአገር ውጭ ቅርንጫፉ ከጅቡቲው ባሻገር በደቡብ ሱዳንም ከፍቶ በስራ ላይ ይገኛል፡፡
ምንጭ ፡- ጅቡቲ ፕሬስና ሶማሌላንድሰን
@YeneTube @Fikerassefa
ባለደራ
የባልደራስ ቃለጉባኤ ለምርጫ ቦርድ
ቦርዱ ያመጣችሁት ከበቂ በላይ ነው ብሏል።
ባልደራስ ለእዉነተኛ ዲሞክራሲ ትላንት ጥር 3/ 2012 ዓም በኢንተር ኮንትኔታል ሜዳ ላይ የተመሰረተበት ቃለጉባኤ እና የምስረታ አባላት ፊርማ የያዘ ፎርም ዛሬ ጥር 4/2012ዓም ለምርጫ ቦርድ አቅርቧል።
ምንጭ:- ስንታየሁ ቸኮል
@YeneTube @Fikerassefa
የባልደራስ ቃለጉባኤ ለምርጫ ቦርድ
ቦርዱ ያመጣችሁት ከበቂ በላይ ነው ብሏል።
ባልደራስ ለእዉነተኛ ዲሞክራሲ ትላንት ጥር 3/ 2012 ዓም በኢንተር ኮንትኔታል ሜዳ ላይ የተመሰረተበት ቃለጉባኤ እና የምስረታ አባላት ፊርማ የያዘ ፎርም ዛሬ ጥር 4/2012ዓም ለምርጫ ቦርድ አቅርቧል።
ምንጭ:- ስንታየሁ ቸኮል
@YeneTube @Fikerassefa
ብሔራዊ ሎተሪ ለስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች ለጊዜው ፍቃድ መስጠት ማቆሙን ገለፀ።
የብሔራዊ ሎተሪ የህግ ባለሙያ አቶ አመሀ ደሳለኝ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት ስፖርት ውርርድ ጥናትና የህግ ማዕቀፍ ላይ ተመስርቶ የተጀመረ መሆኑን ተናግረዋል።
ይሁንና ህብረተሰቡ ላይ እየተፈጠረ ያለውን ብዥታ ለመገምገምና ለማጥራት ለጊዜው አዲስ ፍቃድ ለሚጠይቁ አወራራጆች ፍቃድ መስጠት ማቆማቸውን ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ እስካሁን 21 የስፖርት ውርርድ ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች አሉ ተብሏል።
ለህዝቡ ግንዛቤ ለመስጠትና የተፈጠረውን ብዥታ ለማጥራት በብሄራዊ ሎተሪና ስፖርት ውርርድ ላይ በሚሰሩ ድርጅቶች አማካይነት በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል መግለጫ እየተሰጠ ነው።
የስፖርት ውርርድ ላይ ብሄራዊ ሎቶሪ ፍቃድ እንዲሰጥ በአዋጅ ቁጥር 535/1999 ቢፈቀድለተም በተግባር ፍቃድ መስጠት የጀመረው ግን ከ 2011 ዓ.ም ግማሽ በኋላ ነው።
ከዚያም በ2001 ሌላ የተሻሻለ አዋጅ እንደወጣለት ተነግሯል።
ምንጭ:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
የብሔራዊ ሎተሪ የህግ ባለሙያ አቶ አመሀ ደሳለኝ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት ስፖርት ውርርድ ጥናትና የህግ ማዕቀፍ ላይ ተመስርቶ የተጀመረ መሆኑን ተናግረዋል።
ይሁንና ህብረተሰቡ ላይ እየተፈጠረ ያለውን ብዥታ ለመገምገምና ለማጥራት ለጊዜው አዲስ ፍቃድ ለሚጠይቁ አወራራጆች ፍቃድ መስጠት ማቆማቸውን ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ እስካሁን 21 የስፖርት ውርርድ ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች አሉ ተብሏል።
ለህዝቡ ግንዛቤ ለመስጠትና የተፈጠረውን ብዥታ ለማጥራት በብሄራዊ ሎተሪና ስፖርት ውርርድ ላይ በሚሰሩ ድርጅቶች አማካይነት በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል መግለጫ እየተሰጠ ነው።
የስፖርት ውርርድ ላይ ብሄራዊ ሎቶሪ ፍቃድ እንዲሰጥ በአዋጅ ቁጥር 535/1999 ቢፈቀድለተም በተግባር ፍቃድ መስጠት የጀመረው ግን ከ 2011 ዓ.ም ግማሽ በኋላ ነው።
ከዚያም በ2001 ሌላ የተሻሻለ አዋጅ እንደወጣለት ተነግሯል።
ምንጭ:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
ካለፈው ሳምንት ወዲህ አሜሪካና ኢራን አንድ ሁለት ተባብለው ፍጥጫቸው አይሏል፡፡አሜሪካ በኢራን ላይ ተጨማሪ ማዕቀብም ጥላለች፡፡ 176 ንጹሀን የተቀጠፉበት አውሮፕላን ጉዳይም በኢራን ላይ ጫናዎች እንዲበረቱ አድርጓል፡፡
ምንጭ:- Al ain
@YeneTube @Fikerassefa
ምንጭ:- Al ain
@YeneTube @Fikerassefa
በህገ ወጥ መንገድ ወደ አዲስ አበባ ሊገባ የነበረ የጦር መሳሪያ ተያዘ
በህገ ወጥ መንገድ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ሊገባ የነበረ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ በሰበታ ከተማ ተያዘ።
የሰበታ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት መረጃ እንደሚያመለክተው፥ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያው የተያዘው ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ ነው።
የሰበታ ከተማ የፀጥታ አካላት ባደረጉት ክትትል በአይሱዙ የጭነት ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተጭኖ ከቦንጋ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ 52 ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያ መያዙንም ቢሮው አስታውቋል።
ተሽከርካሪው በረቀቀ መንገድ በድብቅ በተዘጋጀ ስፍራ መሳሪያዎችን ጭኖ ሲጓዝ እንደነበር የሰበታ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የከተማ አስተዳደሩ የፀጥታ አካላት ባደረጉት ፍተሻ የጦር መሳሪያዎቹ መያዛቸውን ጠቅሶ፥ አሁን ላይም በጉዳዩ ላይ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን አስረድቷል።
ፀረ ሰላም ሀይሎች የህዝቡን ሰላም ለማወክ ሌት ተቀን የሚሰሩትን ስራ ለመቆጣጠር የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ያለው ፖሊስ መምሪያው፤ ህብረተሰቡ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት እንዲያሳውቅም ጥሪውን አቅርቧል።
ምንጭ:- ኤፍ.ቢ.ሲ
@Yenetube @Fikerassefa
በህገ ወጥ መንገድ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ሊገባ የነበረ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ በሰበታ ከተማ ተያዘ።
የሰበታ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት መረጃ እንደሚያመለክተው፥ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያው የተያዘው ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ ነው።
የሰበታ ከተማ የፀጥታ አካላት ባደረጉት ክትትል በአይሱዙ የጭነት ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተጭኖ ከቦንጋ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ 52 ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያ መያዙንም ቢሮው አስታውቋል።
ተሽከርካሪው በረቀቀ መንገድ በድብቅ በተዘጋጀ ስፍራ መሳሪያዎችን ጭኖ ሲጓዝ እንደነበር የሰበታ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የከተማ አስተዳደሩ የፀጥታ አካላት ባደረጉት ፍተሻ የጦር መሳሪያዎቹ መያዛቸውን ጠቅሶ፥ አሁን ላይም በጉዳዩ ላይ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን አስረድቷል።
ፀረ ሰላም ሀይሎች የህዝቡን ሰላም ለማወክ ሌት ተቀን የሚሰሩትን ስራ ለመቆጣጠር የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ያለው ፖሊስ መምሪያው፤ ህብረተሰቡ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት እንዲያሳውቅም ጥሪውን አቅርቧል።
ምንጭ:- ኤፍ.ቢ.ሲ
@Yenetube @Fikerassefa
አዋሽ ባንክ ከወለድ ነፃ አገልግሎት የሚሰጥባቸውን ቅርንጫፎች በአዲስ አበባ ነገ ጥር 5/2012 ሊከፍት ነው
አዋሽ ባንክ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ አገልግሎት የሚሰጥባቸው ሦስት ቅርንጫፎችን ነገ ጥር 5/2012 በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚከፍት አስታወቀ።
ባንኩ ቅርንጫፎቹን በመርካቶ ኹለት ቅርንጫፍ እና በቦሌ ሚካኤል አንድ ቅርንጫፍ እንደሚከፍት አስታውቋል።
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
አዋሽ ባንክ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ አገልግሎት የሚሰጥባቸው ሦስት ቅርንጫፎችን ነገ ጥር 5/2012 በአዲስ አበባ ከተማ እንደሚከፍት አስታወቀ።
ባንኩ ቅርንጫፎቹን በመርካቶ ኹለት ቅርንጫፍ እና በቦሌ ሚካኤል አንድ ቅርንጫፍ እንደሚከፍት አስታውቋል።
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ ኃይለማርያም ደሣለኝ መጥሪያ ስላልደረሳቸው ፍርድ ቤት አልተገኙም
አቶ ኃይለማርም ደሣለኝ፣ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እና አቶ ደመቀ መኮንን ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ። የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በእነበረከት ስምኦን መዝገብ ላይ የመከላከያ ምስክር ለመስማት ነበር ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው።
የተከሳሽ ጠበቃ፤ መጥሪያ ለምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ለውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው መሰጠቱን ገልጸው የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለማርያም ደሣለኝን ማግኘት ባለመቻላቸው መጥሪያ መስጠት አለመቻላቸውን ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል።
በፋክስ በደረሰው መረጃ መሠረት አቶ ደመቀ እና አቶ ገዱ በሥራ ምክንያት መቅረብ አለመቻላቸውን መግለጻቸውን ፍርድ ቤቱ አስታውቋል። አንድ ሌላ ምስክርም በዛሬው ችሎት ላይ ሳይቀርቡ ቀርተዋል። ተከሳሾች የተሰከሳሽነት ቃላቸውን ለፍርድ ቤቱ በመስጠት ላይ ናቸው። የፍርድ ሂደቱ ከሰዓት በኋላም እንደሚቀጥል ቢቢሲ አስነብቧል በFacebook ገፁ።
Via:- BBC
@YeneTube @FikerAssefa
አቶ ኃይለማርም ደሣለኝ፣ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እና አቶ ደመቀ መኮንን ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ። የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በእነበረከት ስምኦን መዝገብ ላይ የመከላከያ ምስክር ለመስማት ነበር ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው።
የተከሳሽ ጠበቃ፤ መጥሪያ ለምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና ለውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው መሰጠቱን ገልጸው የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለማርያም ደሣለኝን ማግኘት ባለመቻላቸው መጥሪያ መስጠት አለመቻላቸውን ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል።
በፋክስ በደረሰው መረጃ መሠረት አቶ ደመቀ እና አቶ ገዱ በሥራ ምክንያት መቅረብ አለመቻላቸውን መግለጻቸውን ፍርድ ቤቱ አስታውቋል። አንድ ሌላ ምስክርም በዛሬው ችሎት ላይ ሳይቀርቡ ቀርተዋል። ተከሳሾች የተሰከሳሽነት ቃላቸውን ለፍርድ ቤቱ በመስጠት ላይ ናቸው። የፍርድ ሂደቱ ከሰዓት በኋላም እንደሚቀጥል ቢቢሲ አስነብቧል በFacebook ገፁ።
Via:- BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበበ ከተማ ፖሊስን ደመወዝ ከመክፈል ውጪ ከተማ አስተዳደሩ እንደማያስተዳረው ኢንጂነር ታከለ ኡማ ተናገሩ፡፡
ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና ካቢኔያቸው ከሕዝብ ተወካዩች ምክር ቤት አባላት ጋር ዛሬ ረፋድ ውይይት አካሂደዋል።
የምክር ቤቱ አባላት በከተማዋ የሚሰተዋለውን የተደራጀ ወንጀልና ዘረፋ ህብረተሰቡ ኑሮ ላይ ጫና እያሳደረ ነው ከተማዋ አስተዳድር ምን እየሰራ ነው የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸዋል።
ኢንጅነር ታከለ ለተነሳላቸው ጥያቄ የአዲስ አበባ ፖሊስ እኛ ደመወዝ ከመክፈል ውጪ ሌላ ሃላፊነት የለንም የከተማዋን ፖሊስ የሚመራው ፌደራል ፖሊስ ነው ብለዋል፡፡
የከተማዋን ፖሊስን መምራት ባንችልም የከተማው ጸጥታ ስለሚመለከተን ወጣትና ነዋሪውን የአካባቢውን ፀጥታ እንዲያስከብርና እንዲጠብቅ እንደገና እንዲደራጁ አድርገናል ብለዋል፡፡
የከተማዋን ፖሊስ ለማስተዳደር ሙሉ በሙሉ ሃላፊነት ባይሰጠን እንኳን የፌደራል ፖሊስን ውክልና ስጡን እና እንምራ ብለን ጥያቄ ብናቀርብም አልሰጡንም ችግሩን ለመፍታት የፓርላማውም ድጋፍ ያስፈልገናል ብለዋል ኢንጅነር ታከለ፡፡
Via:- ETHIO FM
@YeneTube @Fikerassefa
ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና ካቢኔያቸው ከሕዝብ ተወካዩች ምክር ቤት አባላት ጋር ዛሬ ረፋድ ውይይት አካሂደዋል።
የምክር ቤቱ አባላት በከተማዋ የሚሰተዋለውን የተደራጀ ወንጀልና ዘረፋ ህብረተሰቡ ኑሮ ላይ ጫና እያሳደረ ነው ከተማዋ አስተዳድር ምን እየሰራ ነው የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸዋል።
ኢንጅነር ታከለ ለተነሳላቸው ጥያቄ የአዲስ አበባ ፖሊስ እኛ ደመወዝ ከመክፈል ውጪ ሌላ ሃላፊነት የለንም የከተማዋን ፖሊስ የሚመራው ፌደራል ፖሊስ ነው ብለዋል፡፡
የከተማዋን ፖሊስን መምራት ባንችልም የከተማው ጸጥታ ስለሚመለከተን ወጣትና ነዋሪውን የአካባቢውን ፀጥታ እንዲያስከብርና እንዲጠብቅ እንደገና እንዲደራጁ አድርገናል ብለዋል፡፡
የከተማዋን ፖሊስ ለማስተዳደር ሙሉ በሙሉ ሃላፊነት ባይሰጠን እንኳን የፌደራል ፖሊስን ውክልና ስጡን እና እንምራ ብለን ጥያቄ ብናቀርብም አልሰጡንም ችግሩን ለመፍታት የፓርላማውም ድጋፍ ያስፈልገናል ብለዋል ኢንጅነር ታከለ፡፡
Via:- ETHIO FM
@YeneTube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የብድር አሰጣጥ እና አመላለስ ስርዓቱን በማስተካከል በ 2012 በጀት ዓመት አምስት ወራት ከ 3 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ የተበላሸ ብድር ማስመለስ መቻሉን አስታወቀ።
ልማት ባንኩ በ 2010 እና 2011 የሰጣቸው የተበላሹ ብድሮች መጠን ባንኩን ኪሳራ ውስጥ ከተውት የቆየ ሲሆን፣ በወቅቱም ከ 40 ቢሊዮን ብር በላይ ከሚሆን ገንዘብ ውስጥ እስከ 18 ቢሊዮን የሚደርሰው የተበላሸ እንደነበር ይታወሳል።
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ልማት ባንኩ በ 2010 እና 2011 የሰጣቸው የተበላሹ ብድሮች መጠን ባንኩን ኪሳራ ውስጥ ከተውት የቆየ ሲሆን፣ በወቅቱም ከ 40 ቢሊዮን ብር በላይ ከሚሆን ገንዘብ ውስጥ እስከ 18 ቢሊዮን የሚደርሰው የተበላሸ እንደነበር ይታወሳል።
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
በምዕ/ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ የመከላከያ ሰራዊት ልብስ በመልበስ ኬላ ዘርግተው ሲፈትሹ በነበሩ ታጣቂዎች፣ አንድ አሽከርካሪን ጨምሮ 6 ሰዎች ታግተው ተወስደዋል። ዕገታው የተፈጸመው ከ4 ቀን በፊት ሲሆን፣ አጋቾቹ በሰው ከ150ሺህ-250ሺህ ብር ጠይቀዋል።
Via Ethiopia Live Updates
@Yenetube @Fikerassefa
Via Ethiopia Live Updates
@Yenetube @Fikerassefa
በወለጋ ለበርካታ ቀናት ታግተው የቆዩ 13 ወንድ እና 8 ሴት ተማሪዎች እንደተለቀቁ መንግሥት ለመገናኛ ብዙኻን ቢያሳውቅም፣ ተማሪዎቹ አሁን ያሉበት ሁኔታ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ስለመገናኘታቸው ግን እስካሁን የጠራ መረጃ አልወጣም፡፡ ባጠቃላይ በአካባቢው ስንት ታጋች ተማሪዎች እንዳሉ እና ስለ አጋቾች ማንነትም የተብራራ መረጃ አልተሰጠም።
Via Wazema
@YeneTube @Fikerassefa
Via Wazema
@YeneTube @Fikerassefa
Forwarded from YeneTube
💥ማስታወቂያ💥
School of American English
📌ቻይንኛ
📌ፈረንሳይኛ
📌ጀርመንኛ
📌ጣልያንኛ
📌አፋን ኦሮሞ
📌አረብኛ
አንቱታን ባተፈሩ መምህራን እናስተምራለን
አድራሻዎቻችን ⬇️
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ +251919913021
ፒያሳ ፒያሳ ገበያ ማዕከል +251919913023
22 ጎላጎል ህንፃ 6ተኛ ፎቅ +251919913022
💥💥💥10% Discount 💥💥💥💥
ቅናሹን ለመጠቀም
ይህንን ፓስት screenshot አድርገው መያዝና ስመጡ ማሣየት ይኖርብዎታል
T.me/SCHOOLOFAMERICAN
School of American English
📌ቻይንኛ
📌ፈረንሳይኛ
📌ጀርመንኛ
📌ጣልያንኛ
📌አፋን ኦሮሞ
📌አረብኛ
አንቱታን ባተፈሩ መምህራን እናስተምራለን
አድራሻዎቻችን ⬇️
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ +251919913021
ፒያሳ ፒያሳ ገበያ ማዕከል +251919913023
22 ጎላጎል ህንፃ 6ተኛ ፎቅ +251919913022
💥💥💥10% Discount 💥💥💥💥
ቅናሹን ለመጠቀም
ይህንን ፓስት screenshot አድርገው መያዝና ስመጡ ማሣየት ይኖርብዎታል
T.me/SCHOOLOFAMERICAN
Forwarded from YeneTube
✅SELL/BUY/ORDER/RENT EVERYTHING
✅SOFTWARE/WEB/GRAPHICS DESIGN
✅IT SUPPORT
✅STUDENT SCHOLARSHIPS/VISA's
✔ Work with us ✔ GET PAID ✔
📩 @CloudMultiTrading 📩
+1(617)580-0402 0944182119 +971586233799
📩 @CloudMultiTrading2 📩
Join our Channel⬇️
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEPkQuyukYp1DOpZEw
✅SOFTWARE/WEB/GRAPHICS DESIGN
✅IT SUPPORT
✅STUDENT SCHOLARSHIPS/VISA's
✔ Work with us ✔ GET PAID ✔
📩 @CloudMultiTrading 📩
+1(617)580-0402 0944182119 +971586233799
📩 @CloudMultiTrading2 📩
Join our Channel⬇️
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAEPkQuyukYp1DOpZEw
‹‹የሲዳማ ክልል የሚመራበት ህገ መንግስት በረቂቅ ደረጃ ተጠናቋል›› ሲሉ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለፁ።
ተቋማትን የመገንባት ስራ ከዚሁ ጎን ለጎን እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።ዋና አስተዳዳሪው አቶ ደስታ ሌዳሞ ሰሞኑን ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ በአሁኑ ወቅት አዲሱ የሲዳማ ክልል የሚመራበት የራሱ ህገ መንግስት በረቂቅ ደረጃ ተጠናቋል።
ህገ መንግስቱን የማርቀቅ ስራ ቀደም ሲል የተጀመረ ሲሆን፣ ከተረቀቀም አንድ ዓመት ያህል ሆኖታል።ረቂቅ ህገ መንግስቱ ላይ የሲዳማ ህዝብ አንድ ጊዜ እንዲወያይበት መደረጉን የተናገሩት አቶ ደስታ፤ በህዝቡ መተቸቱና ማስተቸቱ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
ተቋማትን የመገንባት ስራ ከዚሁ ጎን ለጎን እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።ዋና አስተዳዳሪው አቶ ደስታ ሌዳሞ ሰሞኑን ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ በአሁኑ ወቅት አዲሱ የሲዳማ ክልል የሚመራበት የራሱ ህገ መንግስት በረቂቅ ደረጃ ተጠናቋል።
ህገ መንግስቱን የማርቀቅ ስራ ቀደም ሲል የተጀመረ ሲሆን፣ ከተረቀቀም አንድ ዓመት ያህል ሆኖታል።ረቂቅ ህገ መንግስቱ ላይ የሲዳማ ህዝብ አንድ ጊዜ እንዲወያይበት መደረጉን የተናገሩት አቶ ደስታ፤ በህዝቡ መተቸቱና ማስተቸቱ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ክልል የምግብ ዋጋ ግሽበት 23 በመቶ ደረሰ!
የትግራይ ክልል የምግብ ዋጋ ግሽበት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፃር እስከ አስር በመቶ የሚደረስ ጭማሪ ማስመዝገቡን የብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ ዘገባ አመላከተ።ለምግብ ፍጆታ የሚውሉ ግብዓቶች ላይ በክልሉ የተስተዋለው የግሽበት መጠን በ2011 ከነበረበት የ 13 በመቶ የአስር በመቶ ጭማሪ በማድረግ አሁን 23 ከመቶ ላይ እንደሚገኝ የባንኩ ዓመታዊ ዘገባ ያስረዳል። አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ በትግራይ ክልል ባለፈው ዓመት 13.9 በመቶ ላይ የነበረ ሲሆን፣ አሁን 19.8 በመቶ ላይ ደርሶ ይገኛል።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ክልል የምግብ ዋጋ ግሽበት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፃር እስከ አስር በመቶ የሚደረስ ጭማሪ ማስመዝገቡን የብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ ዘገባ አመላከተ።ለምግብ ፍጆታ የሚውሉ ግብዓቶች ላይ በክልሉ የተስተዋለው የግሽበት መጠን በ2011 ከነበረበት የ 13 በመቶ የአስር በመቶ ጭማሪ በማድረግ አሁን 23 ከመቶ ላይ እንደሚገኝ የባንኩ ዓመታዊ ዘገባ ያስረዳል። አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ በትግራይ ክልል ባለፈው ዓመት 13.9 በመቶ ላይ የነበረ ሲሆን፣ አሁን 19.8 በመቶ ላይ ደርሶ ይገኛል።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ከትናንት ጀምሮ እየተወያዩ ነው።
ከዚህ ቀደም ሀገራቱ በደረሱት ስምምነት መሰረት ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ተገናኝተው በመወያየት ላይ የሚገኙት።በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ አተኩሮ እየተካሄደ ባለው ስብሰባ ላይ የሀገራቱ የውሃ ሚኒስትሮችም እየተካፈሉ ሲሆን፥ የአሜሪካ መንግስት እና የዓለም ባንክ ተወካዮችም በታዛቢነት ተገኝተዋል። ሚኒስትሮቹ በስብሰባቸው በውሃ ሚኒስትሮች ደረጃ በተለያዩ ዙሮች የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያደረጓቸውን ድርድሮች ውጤት ይመለከታሉ።ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በአዲስ አበባ ሲያካሂዱት የቆዩት አራተኛና የመጨረሻው የቴክኒክ ውይይት ያለስምምነት መጠናቀቁ ይታወሳል።
ውይይቱ ያለስምምነት የተጠናቀቀው ግብፅ የግድቡን የውሃ ሙሌት በተመለከተ አዲስ ሃሳብ ይዛ በመቅረቧ መሆኑንም የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ግብፅ ግድቡ ከ12 እስከ 21 ዓመት እንዲሞላ የሚል አዲስ ሀሳብ ማቅረቧ እና ኢትዮጵያ በበኩሏ ይህን ሃሳብ በማንኛውም መልኩ እንደማትቀበል መግለጿን ነው ሚኒስትሩ በወቅቱ የተናገሩት።ሶስቱ ሀገራት ከዚህ በፊት የህዳሴው ግድብ በ7 ዓመት ውስጥ እንዲሞላ ስምምነት ላይ ደረሰው የነበረ መሆኑ ይታወሳል።
ሶስቱ አገራት በዋሺንግተን ዲሲ በደረሱት ስምምነት አማካኝነት ስምምነት ላይ ካልደረሱ የህዳሴ ግድቡን አስመልክቶ በካርቱም የተፈረመው ስምምነት አንቀጽ 10 ተግባራዊ እንዲሆን ይደረጋል።የካርቱም ስምምነት አንቀጽ 10 “ሶስቱ አገራት በመርሆዎች ስምምነቱ አተረጓጎምና ተግባራዊነት የተነሱ አለመግባባቶችን በውይይት ወይም በድርድር ይፈታሉ፤ ይህንን ማድረግ ካልቻሉ ግን አደራዳሪ ሊጠይቁ ወይም ለአገራቸው መሪዎች ሊያሳውቁ ይችላሉ” ይላል።ይህንንም የሚያደርጉት የሶስቱም ሀገራት ስምምነት ሲኖር እንደሆነም አስቀምጧል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ከዚህ ቀደም ሀገራቱ በደረሱት ስምምነት መሰረት ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ተገናኝተው በመወያየት ላይ የሚገኙት።በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ አተኩሮ እየተካሄደ ባለው ስብሰባ ላይ የሀገራቱ የውሃ ሚኒስትሮችም እየተካፈሉ ሲሆን፥ የአሜሪካ መንግስት እና የዓለም ባንክ ተወካዮችም በታዛቢነት ተገኝተዋል። ሚኒስትሮቹ በስብሰባቸው በውሃ ሚኒስትሮች ደረጃ በተለያዩ ዙሮች የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያደረጓቸውን ድርድሮች ውጤት ይመለከታሉ።ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በአዲስ አበባ ሲያካሂዱት የቆዩት አራተኛና የመጨረሻው የቴክኒክ ውይይት ያለስምምነት መጠናቀቁ ይታወሳል።
ውይይቱ ያለስምምነት የተጠናቀቀው ግብፅ የግድቡን የውሃ ሙሌት በተመለከተ አዲስ ሃሳብ ይዛ በመቅረቧ መሆኑንም የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ግብፅ ግድቡ ከ12 እስከ 21 ዓመት እንዲሞላ የሚል አዲስ ሀሳብ ማቅረቧ እና ኢትዮጵያ በበኩሏ ይህን ሃሳብ በማንኛውም መልኩ እንደማትቀበል መግለጿን ነው ሚኒስትሩ በወቅቱ የተናገሩት።ሶስቱ ሀገራት ከዚህ በፊት የህዳሴው ግድብ በ7 ዓመት ውስጥ እንዲሞላ ስምምነት ላይ ደረሰው የነበረ መሆኑ ይታወሳል።
ሶስቱ አገራት በዋሺንግተን ዲሲ በደረሱት ስምምነት አማካኝነት ስምምነት ላይ ካልደረሱ የህዳሴ ግድቡን አስመልክቶ በካርቱም የተፈረመው ስምምነት አንቀጽ 10 ተግባራዊ እንዲሆን ይደረጋል።የካርቱም ስምምነት አንቀጽ 10 “ሶስቱ አገራት በመርሆዎች ስምምነቱ አተረጓጎምና ተግባራዊነት የተነሱ አለመግባባቶችን በውይይት ወይም በድርድር ይፈታሉ፤ ይህንን ማድረግ ካልቻሉ ግን አደራዳሪ ሊጠይቁ ወይም ለአገራቸው መሪዎች ሊያሳውቁ ይችላሉ” ይላል።ይህንንም የሚያደርጉት የሶስቱም ሀገራት ስምምነት ሲኖር እንደሆነም አስቀምጧል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ
በድረ ገፁ ላይ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ በማሟላት ዕቃዎቹን ወይም አገልግሎቱን መሸጥ ይችላል።
ከ2700 በላይ ዕቃዎችና አገልግሎቶች
@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com
0953707070
በድረ ገፁ ላይ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ በማሟላት ዕቃዎቹን ወይም አገልግሎቱን መሸጥ ይችላል።
ከ2700 በላይ ዕቃዎችና አገልግሎቶች
@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com
0953707070
የቲቦር ናዢ የኢትዮጵያ ጉብኝት
የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዢ ኢትዮጵያን ጨምሮ 5 የአፍሪካ አገራትን ሊጎበኙ ነው፡፡
ረዳት ሚንስትሩ ከጥር 6 እስከ 20/2012 በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሱዳን የሥራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ነው የተገለጸው፡፡
በሁለት ሳምንት ቆይታቸውም ከየአገራቱ ከፍተኛ አመራሮችና ዓለም ዐቀፍ የዋሽንግተን አጋር ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ይመክራሉ ተብሏል፡፡
ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ማጠናከር፣ አካባቢያዊ ፀጥታን ማጎልበት፣ ሙስናን መዋጋት እና የንግድና የመዋዕለ ነዋይ ፍሰትን ማበረታታት የታቦር ናዢ ጉብኝት ዓላማ መሆናቸውን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ገልጿል፡፡
ምንጭ:- አሀዱ ቴሌቪዥን
@YeneTube @Fikerassefa
የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዢ ኢትዮጵያን ጨምሮ 5 የአፍሪካ አገራትን ሊጎበኙ ነው፡፡
ረዳት ሚንስትሩ ከጥር 6 እስከ 20/2012 በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሱዳን የሥራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ነው የተገለጸው፡፡
በሁለት ሳምንት ቆይታቸውም ከየአገራቱ ከፍተኛ አመራሮችና ዓለም ዐቀፍ የዋሽንግተን አጋር ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ይመክራሉ ተብሏል፡፡
ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ማጠናከር፣ አካባቢያዊ ፀጥታን ማጎልበት፣ ሙስናን መዋጋት እና የንግድና የመዋዕለ ነዋይ ፍሰትን ማበረታታት የታቦር ናዢ ጉብኝት ዓላማ መሆናቸውን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ገልጿል፡፡
ምንጭ:- አሀዱ ቴሌቪዥን
@YeneTube @Fikerassefa
የትግራይ ቲቪ ጋዜጠኞች አሶሳ ላይ መታሰር እና የክልልሉ መልስ!
የትግራይ ቲቪ የአዲስ አበባ ቢሮ አስተባባሪ አቶ አክሊሉ ደባልቀው በስልክ ከነገረኝ:
"የትግራይ ቲቪ ጋዜጠኛ የሆነው ዳዊት ከበደ እና የካሜራ ባለሙያው በሀይሉ ውቤ ትናንት ምሽት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ሶስት ሰአት ገደማ ታስረዋል። ከቅዳሜ ጀምሮ የተለያዩ ቀረፃዎችን ሲያካሂዱ ቆይተው ትናንት እስካሁን ምክንያቱ ምን እንደሆነ ባልታወቀ ምክንያት ታስረዋል። እዛ ሆነው የሰሩት እና በቲቪ የተላለፈ ፕሮግራም እንኳን አልነበረም።"
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቃል አቀባይ አቶ መለሰ በየነ የሰጠኝ መልስ:
"እኔ ለስራ ሌላ ቦታ ነኝ ነገር ግን ስልክ በመደወል ለመረዳት እንደቻልኩት ጋዜጠኞቹ የነበረንን አሰራር ተከትለው አልመጡም። ይህ ማለት ወደ ክልሉ ለዘገባ እንደሚመጡ ለክልሉ ኮሚኒኬሽን አላሳወቁም። ምን መስራት እንደሚፈልጉ ነግረውን፣ እኛም ባለሙያ እና አስፈላጊም ከሆነ የፀጥታ አካላት መድበን መሆን ነበረበት። ለምሳሌ እኔ እንደ ክልሉ ኮሚኒኬሽን ሀላፊ ስለመምጣታቸው የማውቀው ነገር የለም። ታሰሩ ሲባል እንደሌላው ሰው ነው የሰማሁት። አሁን ግን የታሰሩበት ምክንያት ምን እንደሆነ በትክክል አጣርተን እናሳውቃለን።"
ምንጭ:- ኤልያስ መሰረት
@YeneTube @Fikeeassefa
የትግራይ ቲቪ የአዲስ አበባ ቢሮ አስተባባሪ አቶ አክሊሉ ደባልቀው በስልክ ከነገረኝ:
"የትግራይ ቲቪ ጋዜጠኛ የሆነው ዳዊት ከበደ እና የካሜራ ባለሙያው በሀይሉ ውቤ ትናንት ምሽት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ሶስት ሰአት ገደማ ታስረዋል። ከቅዳሜ ጀምሮ የተለያዩ ቀረፃዎችን ሲያካሂዱ ቆይተው ትናንት እስካሁን ምክንያቱ ምን እንደሆነ ባልታወቀ ምክንያት ታስረዋል። እዛ ሆነው የሰሩት እና በቲቪ የተላለፈ ፕሮግራም እንኳን አልነበረም።"
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቃል አቀባይ አቶ መለሰ በየነ የሰጠኝ መልስ:
"እኔ ለስራ ሌላ ቦታ ነኝ ነገር ግን ስልክ በመደወል ለመረዳት እንደቻልኩት ጋዜጠኞቹ የነበረንን አሰራር ተከትለው አልመጡም። ይህ ማለት ወደ ክልሉ ለዘገባ እንደሚመጡ ለክልሉ ኮሚኒኬሽን አላሳወቁም። ምን መስራት እንደሚፈልጉ ነግረውን፣ እኛም ባለሙያ እና አስፈላጊም ከሆነ የፀጥታ አካላት መድበን መሆን ነበረበት። ለምሳሌ እኔ እንደ ክልሉ ኮሚኒኬሽን ሀላፊ ስለመምጣታቸው የማውቀው ነገር የለም። ታሰሩ ሲባል እንደሌላው ሰው ነው የሰማሁት። አሁን ግን የታሰሩበት ምክንያት ምን እንደሆነ በትክክል አጣርተን እናሳውቃለን።"
ምንጭ:- ኤልያስ መሰረት
@YeneTube @Fikeeassefa