YeneTube
117K subscribers
31.5K photos
485 videos
79 files
3.89K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
2020 so far:

- US killing of Qassem Soleimani

- Floods in Indonesia

- Ongoing Australian bushfire crisis

- Conflict in Libya

- Bomb attack in Burkina Faso

- Continued protests in India and Hong Kong

- Knife attack in Paris

- Interpol warrant for Carlos Ghosn
@YeneTube @Fikerassefa
"ኑ የታመሙትን እንጠይቅ ያለንን እንካፈል"

ሮትራክት(አርባ ምንጭ) ፣ አምዩ ቻሪቲ ፣ቀይ መስቀል ማህበር ፣ አርባ ምንጭ ወጣቶች ማህበር እንዲሁም ፒስ ሞዴል ኢቨንት ቤተሰቦች በገና በዓል ዕለት ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ አርባ ምንጭ ሆስፒታል በበዓሉ ዕለት የታመሙትን ይጠይቃሉ ለህፃናቶችም ስጦታን ይለግሳሉ

ከ6:00 ሰዓት ጀምሮ ከአቅም ከሌላቸው ጋር ምሳን ይቋደሳሉ የአልባስትም ድጋፍ ይደረጋል

"ኑ አብረን ወገኖቻችንን እንጠይቅ እርሶም በበዓሉ ዕለት የታመሙ ወገኖቻችንን እንጠይቅ"
በገላን የወንዶች አዳሪ ት/ቤት የ17 አመት ተማሪ ባልታወቀ ምክንያት ከፎቅ ላይ ወድቆ ሞተ ።

ሰዎች ገፍተረውት ወይን እራሱ ወድቆ ይሁን ባልታወቀ ምክያንት በገላን የወንዶች አዳሪ ት/ቤት ዩሀንስ አበራ የተባለ የ17 አመት ተማሪ ባለፈው ሀሙስ ታህሳስ 23 ከፎቅ ላይ ወድቆ የተገኘ ሲሆን በጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል ህክምና ቢደረገለትም ሒወቱ ማትረፍ ሳይቻል ቀርቷል።የቀብር ስነስርአቱም አርብ አዲስ አበባ ውስጥ ተፈፅሟል።
የተማሪው ቤተሰቦች በስልክ እንደነገሩኝ እስከ አሁን የሞቱን መንስኤ እንዳላወቁና ሟቹ ግን ከመሞቱ አንድ ቀን እስቀድሞ ስልክ ደውሎ ቀድሞ ከተማረበት ት/ቤት መሸኛ ስላልወሰደ ቅዳሜ ቤት እንደሚመጣና ጉዳዮን ጨርሶ ወደ ት/ቤት እንደሚመለስ ነግሮን ነበር ብለዋል።
ሟቹ የአስረኛ ከፍል ውጤቱ አራት ነጥብ ያመጣ ሲሆን 11 ክፍል ትምህርቱን በወንድይራድ ት/ቤት እየተከታተለ እያለ መንግስት በዚህ አመት በጀመረው በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በአንድ የትምህርት ማእከል በሚያስተምረው ፕሮግራም ለመማር ከሶስት ሳምንት በፊት ነበር ወደ ገላን ት/ቤት ገብቶ መማር የጀመረው።

Via:- tsefay Getinet
@YeneTube @Fikerassefa
ፖሊስ ለበዓሉ በቂ ዝግጅት ማድረጉን ገለፀ

የገና በዓል በሰላም እንዲከበር በቂ ዝግጅት ማድረጉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

በኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ሀላፊ ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ለጣቢያችን እንደተናገሩት፥ ፖሊስ ኮሚሽኑ ለበዓሉ በቂ ዝግጅት አድርጓል።

የፖሊስ አባላትም ሰዎች በሚበዙባቸው የግብይት ቦታዎች እና የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው አካባቢዎች ተሰማርተዋል ነው ያሉት።

በተለይም ስርቆት፣ ቅሚያ፣ ማታለል እና ባዕድ ነገር ከምግብ ጋር ቀላቅሎ መሸጥ በበዓል ግብይት ጊዜ ሊከሰቱ የሚችሉ ወንጀሎች በመሆናቸው ህብረተሰቡ ለግብይት ሲወጣ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስበዋል።

@YeneTube @Fikerassefa
እንኳን ደስ አለን❗️

ትናንት በቻይና በተደረገው የዢያሜን ዓለም አቀፍ ማራቶን ኢትዮጵያውያኑ አትሌት መዲና ደሜ እና አትሌት ብርሃን ነበበው አሸንፈዋል።

@YeneTube @Fikerassefa
የአርባምንጭ ቤተሰቦቻችን በዓሉን በበጎ ተግባር ያሳልፉ ዘንድ በክብር ተጠርታችኀል!

ሮትራክት(አርባ ምንጭ) ፣ አምዩ ቻሪቲ ፣ ቀይ-መስቀል ማህበር ፣ የአርባምንጭ ከተማ ወጣቶች ማህበር እና የኔቲዩብ እንዲሁም ፒስ ሞዴል ኢቨንት ቤተሰቦች በገና በዓል ዕለት ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ አርባ ምንጭ ሆስፒታል በበዓሉ ዕለት የታመሙትን ይጠይቃሉ ለህፃናቶችም ስጦታን ይለግሳሉ፡፡ ከ6:00 ሰዓት ጀምሮ ከአቅም ከሌላቸው ጋር ምሳን ይቋደሳሉ የአልባስትም ድጋፍ ይደረጋል

ምሳ ቦታ፦ሲቀላ ቀይ መስቀል ማህበር ግቢ ውስጥ

#share

@YeneTube @Fikerassefa
የእስር ጊዜያቸውን ቢጨርሱም 75 ኢትዮጵያዊያን በታንዛኒያ እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኙ ተገለጸ

በተለያዩ ወንጀሎች ተከሰው እና የዕስር ቅጣት ተጥሎባቸው በታንዛኒያ እስር ቤት የሚገኙ 75 ኢትዮጵያዊያን የዕስር ጊዜያቸውን ቢያጠናቅቁም ከእስር አለመፈታታቸው ታወቀ። በታንዛኒያ የማትዋራ ግዛት የቀጠናው ኮሚሽነር ጌላሲስ ባይካናዋ የዕስረኞችን ቅሬታ ባዳመጡበት ወቅት ኹለት ዓመታ ብቻ የዕስር ቅጣት ተጥሎባቸው የነበሩ 75 ኢትዮጵያዊያን የዕስር ጊዜያቸውን ቢያጠናቅቁም አሁንም በዕስር ላይ እንደሚገኙ እንደተገለፀ ጋርዲያን ኮሚሽሩን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

ከዚሁ በተጨማሪም በእስር ላይ የሚገኙት ታራሚዎች ከፈፀሙት ወንጀል በተለየ በሌላ እና ባለፈፀሙት ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው እንደታሰሩም ቅሬታቸውን ለቀጠናው ኮሚሽር ባቀረቡበት ወቅት ተናግረዋል። ቅሬታ አቅራቢዎች የእስር ጊዜያቸውን ማጠናቀቃቸውን ተናግረው የታንዛኒያ መንግስት ወደ አገራቸው እንዲሸኛቸው ጥያቄያቸውን ማቅረባቸውንም አስታውቀዋል።

Via:- Addis maleda
@YeneTube @Fikerassefa
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የአንድነት ፓርክን ጎበኙ።

ቀደም ባሉት ጊዜያት ፓርኩን ደጋግመው የጎበኙት ፕሬዚዳንቷ በዛሬው ጉብኝታቸው በየጊዜው አዳዲስ ነገሮች በፓርኩ እየተጨመሩ መምጣታቸውን መመልከታቸውን ተናግረዋል።

ፓርኩን "አንድ ጊዜ አይቸዋለሁ ተብሎ የሚቀርብበትና ታይቶ የሚጠገብም አይደለም" ያሉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ፥ በተለይ የኢትዮጵያውያንን ታሪክ ከማሳየትና ለትውልድ ከማስተላለፍ አኳያ ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

የአትዮጵያ ከተሞች ተመሳሳይ ዓይነት ታሪካዊ መዝናኛዎች እንደሚያስፈልጋቸው ጠቁመው፥ አንድነት ፓርክ የኢትዮጵያንም ሆነ የአዲስ አበባን መልካም ገፅታ ለዓለም በማስተዋወቅ ትልቅ ሚና እንዳለው ነው ያመለከቱት።

ከፓርኩ በተጨማሪ ታላቁን ብሄራዊ ቤተ መንግስት ጨምሮ የኢትዮጵያን ታሪክ ሊያሳዩ የሚችሉ ስራዎች በቀጣይ እንደሚከናወኑም በዚሁ ወቅት ተናግረዋል።

Via:- FBC
@YeneTube @FikerAssefa
አምባሳደር ፕ/ር አድማሱ ፀጋዬ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለካምቦዲያ ንጉስ አቀረበዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
በአርማጭሆ አካባቢ ሕጻናትን፣ ሾፌሮችን እና ግለሰቦችን በማገት ከቤተሰቦቻቸው ገንዘብ በመጠየቅ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ወደ 50 የሚደርሱ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ተመሥገን ጥሩነህ አስታውቀዋል፡፡

በተያያዘ ዜና በሞጣ ከተማ በሃይማኖት ተቋማት እና በንግድ ተቋማት ላይ በደረሰው ጥቃት እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩ ወደ 80 ያህል ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ተመስገን ጥሩነህ አስታወቁ።ከተጠርጣሪዎቹ መካከል 'ሕጋዊ የሆነውን መጅሊስ ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦች' እንዳሉበት እና በመስጂዶች ቃጠሎ መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡

Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
በኢሚግሬሽን ፣ የዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ የድቡብ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ተገቢውን አገልገሎት ባለመስጠቱ ለከፍተኛ እንግልት እየተዳረግን ነው ሲሉ ተገልጋዮች አማረሩ።

Via:- DW
@YeneTube @FikerAssefa
“ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እዚህ አገር ፍትህ እንዲመጣ ከፍተኛ መስዋእትነት የከፈሉ ሰው ናቸው፤ ከሁላችን የበለጠ እንጂ ያነሰ ቁርጠኝነት አላቸው ብዬ አላምንም”

~~~~~~ጀዋር መሐመድ~~~~~~
@Yenetube @Fikerassefa
YeneTube
“ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እዚህ አገር ፍትህ እንዲመጣ ከፍተኛ መስዋእትነት የከፈሉ ሰው ናቸው፤ ከሁላችን የበለጠ እንጂ ያነሰ ቁርጠኝነት አላቸው ብዬ አላምንም” ~~~~~~ጀዋር መሐመድ~~~~~~ @Yenetube @Fikerassefa
ዛሬ አቶ ጅዋር መሀመድ ከቢቢሲ አማርኛ ጋር አጠር ያለ ቆይታ ነበረው በዚህ ቃለ ምልልስ ፓስፓርት ስለ መመለሱ ጋር ለቀረበለት ጥያቄ #ፓስፖርቱን ለአሜሪካ መንግስት መመለሱን አስታውቋል እንዲሁም አሁን በኢትዮጵያ ፓለቲካ ላይ ለመሳተፍ ምንም #እንደማያግደው ተናግራል።

@YeneTube @Fikerassefa
ትናንት ምሽት በአማራ ክልል፣ አገው አዊ ዞን፣ አዮ ጓጉሳ ወረዳ እሁዲት ከተማ ቤተክርስቲያን ለማቃጠል ሙከራ አድርገዋል የተባሉ 3 ግለሰቦችን ለመያዝ የአካባቢው ማህበረሰብና የጸጥታ ሀይሎች ሙከራ ባደረጉበት ወቅት የአንዱ ህይወት አለፈ።

Via:- ElU
@YeneTube @Fikerassefa
አሜሪካዊቷ የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኛ ፒንክ
አውስትራልያ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመታደግ አምስት መቶ ሺ ዶላር ረዳች።

@YeneTube @FikerAssefa
መልካም ገና በዐል ይሁንላችሁ
ፎቶ:- @leykunadvertising
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የፊታችን ቅዳሜ ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊያቀኑ ነው።

እንደ ፕረስ ላቲና ዘገባ ከሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥር 2 ቀን 2012 ዓ.ም ወደ ደቡብ አፍሪካ ያቀናሉ።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዞ ዓላማም በኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ ቀጣይ ግንኙነት ዙሪያ ከፕሬዘዳንት ሲሪል ራማምፖሳ ጋር መምከር ነው።

በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የአገራቸውን ሁለንተናዊ እድገት እንዴት እንደሚደግፉም ከዳያስፖራዎቹ ጋር እንደሚመክሩ ተገልጿል።

በተጨማሪም የደቡብ አፍሪካ ግዙፍ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት መስኮች እንዲሰማሩ ማግባባት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጨማሪ የጉዞ ዓላማ ነው ተብሏል።

52 ሚሊዬን ህዝብ ያላትና ከአፍሪካ የበለጸገችዋ አገር ደቡብ አፍሪካ በአህጉሩ እና ዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ ኩባንያዎች ባለቤት ስትሆን ከኢትዮጵያ ጋር አንድ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረ ወዳጅነት አላት።

ኢትዮጵያ ደቡብ አፍሪካ ገጥሟት ከነበረው የእንግሊዝ አፓርታይድ ቅኝ ግዛት ነጻ እንድትወጣ ወታደራዊ ድጋፍ ከማድረግ አንስቶ በተለያዩ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማሲ ድጋፍ ማድረጓን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

Via :- Ethio FM
@Yebetube @FikerAssefa
💥ማስታወቂያ💥
School of American English

📌ቻይንኛ
📌ፈረንሳይኛ
📌ጀርመንኛ
📌ጣልያንኛ
📌አፋን ኦሮሞ
📌አረብኛ

አንቱታን ባተፈሩ መምህራን እናስተምራለን

አድራሻዎቻችን ⬇️
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ +251919913021
ፒያሳ ፒያሳ ገበያ ማዕከል +251919913023
22 ጎላጎል ህንፃ 6ተኛ ፎቅ +251919913022


💥💥💥10% Discount 💥💥💥💥

ቅናሹን ለመጠቀም
ይህንን ፓስት screenshot አድርገው መያዝና ስመጡ ማሣየት ይኖርብዎታል

T.me/SCHOOLOFAMERICAN
ኢ/ር ታከለ ኡማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በክረምት በጎፈቃድ መርሃ ግብር ቤታቸው የታደሰላቸው እናቶችን ጎበኙ!

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በክረምት በጎፈቃድ መርሃ ግብር ቤታቸው የታደሰላቸው እናቶች ቤት ቆይታ አድርገዋል። በጉብኝቱ ከምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ በተጨማሪ የተለያዩ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች መገኘታቸውን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።የከተማ አስተዳደሩ ባሳለፍነው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር በመዲናዋ ውስጥ ለሚገኙ 1ሺህ 573 ለሚሆኑ አረጋዊያን የመኖሪያ ቤት እድሳት ማከናወኑ ይታወሳል።

Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa