የአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ህንጻዎች ለመጠገን የ400 ሚሊየን ብር የፕሮጀክት ጥናት መጠናቀቁን የጎንደር የአለም አቀፍ ቅርሶች አስተዳዳሪ አስታወቁ፡፡
አስተዳዳሪው አቶ ጌታሁን ስዩም ለኢዜአ እንደገለፁት የፕሮጀክት ጥናቱ በቀጣዮቹ አምስት አመታት የጥገና ስራውን ደረጃ በደረጃ ለማካሄድ የሚያስችል ነው፡፡
በጥናቱ አማራ ክልልን ጨምሮ የፌደራል የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸውን አስተዳዳሪው ተናግረዋል፡፡
የጥገና በጀቱ በፌዴራል መንግስት ድጋፍ እንደሚሸፈንና አለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶችም ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከክልሉ መንግስት በተመደበ በጀትና ከጎብኝዎች ገቢ በ36 ሚሊየን ብር የቤተ-መንግስቱ ዙሪያ አጥር ጥገና መጀመሩን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
የፌዴራል የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው የአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ህንጻዎች ከተጋረጠባቸው አደጋ ለመታደግ ጥናቶች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል።
በ16ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸው የአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ህንፃ እንደ አውሮፓውያን የቀመር ዘመን በ1979 በዩኔስኮ በአለም የሰው ሰራሽ ቅርስነት የተመዘገበ መሆኑ ይታወቃል፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
አስተዳዳሪው አቶ ጌታሁን ስዩም ለኢዜአ እንደገለፁት የፕሮጀክት ጥናቱ በቀጣዮቹ አምስት አመታት የጥገና ስራውን ደረጃ በደረጃ ለማካሄድ የሚያስችል ነው፡፡
በጥናቱ አማራ ክልልን ጨምሮ የፌደራል የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸውን አስተዳዳሪው ተናግረዋል፡፡
የጥገና በጀቱ በፌዴራል መንግስት ድጋፍ እንደሚሸፈንና አለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶችም ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከክልሉ መንግስት በተመደበ በጀትና ከጎብኝዎች ገቢ በ36 ሚሊየን ብር የቤተ-መንግስቱ ዙሪያ አጥር ጥገና መጀመሩን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
የፌዴራል የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው የአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ህንጻዎች ከተጋረጠባቸው አደጋ ለመታደግ ጥናቶች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል።
በ16ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸው የአጼ ፋሲል ቤተ መንግስት ህንፃ እንደ አውሮፓውያን የቀመር ዘመን በ1979 በዩኔስኮ በአለም የሰው ሰራሽ ቅርስነት የተመዘገበ መሆኑ ይታወቃል፡፡
@YeneTube @Fikerassefa
የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 10 ዓመታት አቋርጦት የነበረውን ‹ኦሪጅናል› የትምህርት ማስረጃ መስጠት ዳግም መጀመሩ ተገለጸ፡፡
በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመረቁ ተማሪዎች ‹ኦሪጅናል› የትምህርት ማስረጃቸውን ላለፉት 10 ዓመታት ሳያገኙ መቆየታቸውን እና በቅርቡ ችግሩ መቀረፉን የዩኒቨርስቲው የሬጅስተራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክተር አቶ ዘውዱ ጸጋየ ተናግረዋል።
ከጥቅምት 17/2012 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪዎች ኦሪጅናል የትምህርት ማስረጃዎች ደረጃውን በጠበቀ ምሥጢራዊ ሕትመት ተዘጋጅቶ ባለጉዳይ በጠየቀ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መስጠት መቻሉንም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት።
ሕትመቶቹ በቀላሉ ለሀሰተኛ ማስረጃ አገልግሎት እንዳይዉሉ ምሥጢራዊ በሆነ መንገድ እየተሠሩ መሆናቸውን አብመድ ዘግቧል።
@Yenetube @Fikerassefa
በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመረቁ ተማሪዎች ‹ኦሪጅናል› የትምህርት ማስረጃቸውን ላለፉት 10 ዓመታት ሳያገኙ መቆየታቸውን እና በቅርቡ ችግሩ መቀረፉን የዩኒቨርስቲው የሬጅስተራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክተር አቶ ዘውዱ ጸጋየ ተናግረዋል።
ከጥቅምት 17/2012 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪዎች ኦሪጅናል የትምህርት ማስረጃዎች ደረጃውን በጠበቀ ምሥጢራዊ ሕትመት ተዘጋጅቶ ባለጉዳይ በጠየቀ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መስጠት መቻሉንም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት።
ሕትመቶቹ በቀላሉ ለሀሰተኛ ማስረጃ አገልግሎት እንዳይዉሉ ምሥጢራዊ በሆነ መንገድ እየተሠሩ መሆናቸውን አብመድ ዘግቧል።
@Yenetube @Fikerassefa
በጋምቤላ ክልል የጦር መሳሪያ ሲያዘዋውሩ የተገኙ ሰባት ግለሰቦች ቁጥጥር ስር ዋሉ!!
የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያዎችን ሲያዘዋውሩ ያገኛቸውን ሰባት ተጠርጣሪዎች ባለፉት ሁለት ቀናት በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ቱት ኮር ዛሬ ለኢዜአ እንደለጹት ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከ12 ህገ-ወጥ የጦር መሳሪዎችና ከ741 ጥይቶች ጋር ነው።
“ግለሰቦች የታያዙት ባለፉት ሁለት ቀናት በመንግስትና በግል ተሽከርካሪዎች የጦር መሳሪያዎችንና ጥይቶችን ጭነው ከኢታንግና ላሬ ወረዳዎች ወደ ጋምቤላ ከተማ ለማስገባት ሲሞክሩ ኢታንግ ኬላ ላይ በተደረገ ፍተሻ ነው” ብለዋል።
ተጠርጣሪዎቹ ታህሳስ 13/2012 ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት አካባቢና ትላንት ረፋድ ላይ በተለያዩ ሁለት ተሽከርካሪዎች በመደበቅ በድምሩ 12 ክላሽንኮቭ ጠመንጃና 741 የክላሽና የብሬን ጠመንጃ ጥይትችን ወደ ጋምቤላ ሊያስገቡ ሲሉ መያዛቸውን ተናግረዋል።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎቹ የምርመራ ሒደቱ እንደተጠናቀቀ ክስ እንደሚመሰረትባቸው የጠቆሙት ምክትል ኮሚሽነር ቱት ኮር መሰል የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል የህብረተሰቡ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
Via:- EPA
@Yenetube @Fikerassefa
የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያዎችን ሲያዘዋውሩ ያገኛቸውን ሰባት ተጠርጣሪዎች ባለፉት ሁለት ቀናት በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ቱት ኮር ዛሬ ለኢዜአ እንደለጹት ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከ12 ህገ-ወጥ የጦር መሳሪዎችና ከ741 ጥይቶች ጋር ነው።
“ግለሰቦች የታያዙት ባለፉት ሁለት ቀናት በመንግስትና በግል ተሽከርካሪዎች የጦር መሳሪያዎችንና ጥይቶችን ጭነው ከኢታንግና ላሬ ወረዳዎች ወደ ጋምቤላ ከተማ ለማስገባት ሲሞክሩ ኢታንግ ኬላ ላይ በተደረገ ፍተሻ ነው” ብለዋል።
ተጠርጣሪዎቹ ታህሳስ 13/2012 ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት አካባቢና ትላንት ረፋድ ላይ በተለያዩ ሁለት ተሽከርካሪዎች በመደበቅ በድምሩ 12 ክላሽንኮቭ ጠመንጃና 741 የክላሽና የብሬን ጠመንጃ ጥይትችን ወደ ጋምቤላ ሊያስገቡ ሲሉ መያዛቸውን ተናግረዋል።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎቹ የምርመራ ሒደቱ እንደተጠናቀቀ ክስ እንደሚመሰረትባቸው የጠቆሙት ምክትል ኮሚሽነር ቱት ኮር መሰል የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል የህብረተሰቡ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
Via:- EPA
@Yenetube @Fikerassefa
የንግድ ባንክ ጠቅላላ ተቀማጭ ከ7መቶ ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱ ተገለፀ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ የአብስራ ከበደ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፣ የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ብር ከ7መቶ 12 ቢልዮን ብር በላይ የደረሰ ሲሆን ከተመሰረተም 77 ዓመታትን አስቆጥሯል። ባንኩ ሲመሰረት የመነሻ ካፒታሉ አንድ ሚሊዮን የማርያ ትሬዛ የነበረ ሲሆን፣ አሁኑ ላይ ከ7መቶ 12 ቢልዮን ብር በላይ ሃብት ማከማቸት ችሏል።
እንደዳይሬክተሩ ባንኩ አሁን ላይ ከ40ሺ በላይ ሰራተኞች እና ከ22ሚልዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን በአገሪቱ ለተከናወኑ የልማት ስራዎች ባንኩ ዋንኛ የፋይናንስ ምንጭ በመሆን በማገልገል ላይ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ የአብስራ ከበደ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፣ የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ብር ከ7መቶ 12 ቢልዮን ብር በላይ የደረሰ ሲሆን ከተመሰረተም 77 ዓመታትን አስቆጥሯል። ባንኩ ሲመሰረት የመነሻ ካፒታሉ አንድ ሚሊዮን የማርያ ትሬዛ የነበረ ሲሆን፣ አሁኑ ላይ ከ7መቶ 12 ቢልዮን ብር በላይ ሃብት ማከማቸት ችሏል።
እንደዳይሬክተሩ ባንኩ አሁን ላይ ከ40ሺ በላይ ሰራተኞች እና ከ22ሚልዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን በአገሪቱ ለተከናወኑ የልማት ስራዎች ባንኩ ዋንኛ የፋይናንስ ምንጭ በመሆን በማገልገል ላይ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
ሀዋሳ ሰላሟ ተረጋግጧል - ጥራቱ በየነ
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓልን አስመልክቶ ከጋዜጤኞች ለቀረበ ጥያቄ መልስ ሰጡ፡፡
ከበዓላት ጋር ተያይዞ የሚደረግ የዋጋ ጭማሪ፣የቱሪስት ፍሰት እና የጸጥታ ሁኔታን አስመልክቶ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ም/ከንቲባው በከተማዋ ከሚስተናገዱ ታላላቅ መንፈሳዊ በዓል አንዱ የሆነውን የቅዱስ #ገብርኤል በዓል ስናስተናግድ ምንም አይነት #የዋጋ_ጭማሪ እንዳይኖር ከነጋዴው ማህበረሰብ ጋር ቅድመ ውይይት ተደርጓል ብለዋል፡፡
በተለይም በሀዋሳ ከተማ ከተካሄደው ሪፍረንደም በኃላ የከተማው ጸጥታ አስተማማኝ ደረጃ ላይ መድረሱን የገለጹት አቶ ጥራቱ በከተማዋ በርካታ ስብሰባዎች መካሄድ፣የከተማው ገቢ ማደግ እና የኢንቨስትመንት ፍላጎት ጥያቄ እየጨመረ መምጣት የሰላም መኖሩ አረጋጋጭ ነው ብለዋል፡፡
አቶ ጥራቱ አክለውም ከበዓሉ ዋዜማ ጀምሮ የከተማው ነዋሪ ሁሉ በዓሉ በሚከበርበት አካባቢ የጽዳት ዘመቻ እያደረጉ መሆኑን ሲገልጹ የበዓሉ ታዳሚዎች ያለምንም ስጋት ወደ ከተማዋ እንዲመጡ #በመጋበዝ_ጭምር ነው፡፡
Via:- ሀዋሳ ከተማ መንግስት ኮምንኬሽን
@Yenetube @Fikerassefa
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓልን አስመልክቶ ከጋዜጤኞች ለቀረበ ጥያቄ መልስ ሰጡ፡፡
ከበዓላት ጋር ተያይዞ የሚደረግ የዋጋ ጭማሪ፣የቱሪስት ፍሰት እና የጸጥታ ሁኔታን አስመልክቶ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ም/ከንቲባው በከተማዋ ከሚስተናገዱ ታላላቅ መንፈሳዊ በዓል አንዱ የሆነውን የቅዱስ #ገብርኤል በዓል ስናስተናግድ ምንም አይነት #የዋጋ_ጭማሪ እንዳይኖር ከነጋዴው ማህበረሰብ ጋር ቅድመ ውይይት ተደርጓል ብለዋል፡፡
በተለይም በሀዋሳ ከተማ ከተካሄደው ሪፍረንደም በኃላ የከተማው ጸጥታ አስተማማኝ ደረጃ ላይ መድረሱን የገለጹት አቶ ጥራቱ በከተማዋ በርካታ ስብሰባዎች መካሄድ፣የከተማው ገቢ ማደግ እና የኢንቨስትመንት ፍላጎት ጥያቄ እየጨመረ መምጣት የሰላም መኖሩ አረጋጋጭ ነው ብለዋል፡፡
አቶ ጥራቱ አክለውም ከበዓሉ ዋዜማ ጀምሮ የከተማው ነዋሪ ሁሉ በዓሉ በሚከበርበት አካባቢ የጽዳት ዘመቻ እያደረጉ መሆኑን ሲገልጹ የበዓሉ ታዳሚዎች ያለምንም ስጋት ወደ ከተማዋ እንዲመጡ #በመጋበዝ_ጭምር ነው፡፡
Via:- ሀዋሳ ከተማ መንግስት ኮምንኬሽን
@Yenetube @Fikerassefa
የአማራና የትግራይ ክልል ህዝቦችን ግንኙነት የሚያጠናክር ምክክር ነገ በአዲስ አበባ ይደረጋል
የአማራና የትግራይ ክልል ህዝቦችን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ነገ በአዲስ አበባ ምክክር እንደሚደረግ የሰላም ሚኒስቴር አስታውቋል።
የሰላም ሚኒስቴር ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሚያዘጋጁት የውይይት መድረክ ላይ ከሁለቱ ክልሎች የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ይገኛሉ ነው የተባለው።
@Yenetube @Fikerassefa
የአማራና የትግራይ ክልል ህዝቦችን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ነገ በአዲስ አበባ ምክክር እንደሚደረግ የሰላም ሚኒስቴር አስታውቋል።
የሰላም ሚኒስቴር ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሚያዘጋጁት የውይይት መድረክ ላይ ከሁለቱ ክልሎች የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ይገኛሉ ነው የተባለው።
@Yenetube @Fikerassefa
በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ በተሰማሩ አካላት እስከሞት ቅጣት የሚያደርስ ህግ እየረቀቀ መሆኑን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብት ኮሚሽን ዳይሬክተር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ በሰው የመነገድና ሕገ-ወጥ ድንበር የማሻገር ወንጀል ለመከላከል ረቂቅ ሕጉ አስፈላጊ ቢሆንም፤ የሞት ቅጣት መያዙ ግን ስህተት ነው፡፡ የሞት ፍርድ ጨካኝና ኢሰብዓዊ የሆነ ሊመለስ የማይችል ቅጣት በመሆኑ ተፈጻሚነቱ ሊታቀብና ለወደፊቱም ሊቀር ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
👎1
ምርጫ ቦርድ ለብልፅግና ፓርቲ የእውቅና ሰርተፊኬት ለመስጠት ወሰነ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእውቅና ጥያቄ እና፣ የፓርቲ መለያ ሰንደቅ አላማ የማጸደቅ ጥያቄን ያቀረቡ ፓርቲዎችን ጉዳይ አይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ በዚህም መሰረት
1.የኢህአዴግ አባል የነበሩ ሶስት ፓርቲዎች እና ሌሎች አምስት ፓርቲዎች በጋራ ራሳቸውን በማክሰም ብልጽግና ፓርቲን መመስረታቸውን በማሳወቅ የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጣቸው ህዳር 24 ቀን 2012 ዓ.ም በጽሁፍ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያቀረቡ ሲሆን ቦርዱም ጥያቄያቸውን በፓለቲካ ፓርቲዎችና ምርጫ አዋጅ 1162/2011 መሰረት መርምሮ ውሳኔውን ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት ቦርዱ የእውቅና ጥያቄ ከቀረበለት በኋላ በተጨማሪ መሟላት ያለባቸውን ሰነዶች በታህሳስ 01 ቀን 2012 ዓ.ም በመጠየቅ በጥያቄውም መሰረት ታህሳስ 06 ቀን 2012 ዓ.ም የጥያቄዎቹ ምላሾችና ማብራሪያዎች ተሟልተው መቅረባቸውን በማረጋገጡ ብልጽግና ፓርቲን ለመመስረት
1. የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ( ኦዴፓ)፣
2.የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች
ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን)፣
3.የሃረሪ ብሔራዊ ሊግ (ሐብሊ)፣
4.አማራ ዴሞክራያዊ ፓርቲ ( አዴፓ) ፣
5. የኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶህዴፓ)፣
6. የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ) ፣
7.የጋምቤላ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ (ጋህአዴን)
8.የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ( ቤጉህዴፓ)
በተናጠል በጠቅላላ ጉባኤያቸው ውሳኔ መሰረት አድርገው ውህደቱን ለመቀላቀልና ፓርቲያቸውን ለማክሰም የወሰኑት ውሳኔዎች እንዲሁም ውህደቱን ለመመስረት ያደረጉትን ስምምነት በሙሉ ህጉን ተከትሎ የተፈጸመ በመሆኑ ቦርዱ ፓርቲዎቹ ተሰርዘው ብልጽግና ፓርቲ የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጠው ወስኗል፡፡በዚህም መሰረት ውህዱ ፓርቲ በአዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 92/2 መሰረት በተመዘገበ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ውህደቱ ያስገኘውን ሃብትና ንብረት እና እዳ የሚያሳይ የሂሳብ ሪፓርት ለቦርዱ እንዲያቀርብ በውሳኔው ውስጥ ተካቷል፡፡
2.የኦሮሞ ብሔራዊ ፓርቲ በምዝገባ ወቅት ያቀረበው ሰንደቅ አላማ ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ጋር ይመሳሰላል በሚል በቦርዱ የቀረበለትን ጥያቄ እንደማይመሳሰል በመግለጽ ልዮነቱን አብራርቶ ቦርዱ እንዲቀበለው ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ቦርዱ በሁለቱ ሰንደቅ አላማዎች መካከል አለ የተባለውን ልዩነት መርምሮ የኦሮሞ ብሔራዊ ፓርቲ የጠቀሳቸው ልዮነቶች ለማስተዋል የሚያስቸግሩ በመሆናቸው እና ድምጽ ሰጭዎችን የሚያምታቱ ሆነው ስለሚገኙ ሰንደቅ አላማውን ቀይሮ በማቅረብ ምዝገባውን እንዲያጠናቅቅ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
3.እናት ፓርቲ በሚል አገር አቀፍ ፓርቲ ለማቋቋም በሂደት ላይ ያለ ፓርቲ በአዋጅ 1162/ 2011 መሰረት ጊዜያዊ የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጠው ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ በአዋጁ ላይ የተቀመጠውን ጊዜያዊ ሰርተፍኬት መውሰጃ መስፈርት በማሟላቱ እናት ፓርቲ የጊዜያዊ እውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጠው ቦርዱ ወስኗል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእውቅና ጥያቄ እና፣ የፓርቲ መለያ ሰንደቅ አላማ የማጸደቅ ጥያቄን ያቀረቡ ፓርቲዎችን ጉዳይ አይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ በዚህም መሰረት
1.የኢህአዴግ አባል የነበሩ ሶስት ፓርቲዎች እና ሌሎች አምስት ፓርቲዎች በጋራ ራሳቸውን በማክሰም ብልጽግና ፓርቲን መመስረታቸውን በማሳወቅ የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጣቸው ህዳር 24 ቀን 2012 ዓ.ም በጽሁፍ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያቀረቡ ሲሆን ቦርዱም ጥያቄያቸውን በፓለቲካ ፓርቲዎችና ምርጫ አዋጅ 1162/2011 መሰረት መርምሮ ውሳኔውን ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት ቦርዱ የእውቅና ጥያቄ ከቀረበለት በኋላ በተጨማሪ መሟላት ያለባቸውን ሰነዶች በታህሳስ 01 ቀን 2012 ዓ.ም በመጠየቅ በጥያቄውም መሰረት ታህሳስ 06 ቀን 2012 ዓ.ም የጥያቄዎቹ ምላሾችና ማብራሪያዎች ተሟልተው መቅረባቸውን በማረጋገጡ ብልጽግና ፓርቲን ለመመስረት
1. የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ( ኦዴፓ)፣
2.የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች
ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን)፣
3.የሃረሪ ብሔራዊ ሊግ (ሐብሊ)፣
4.አማራ ዴሞክራያዊ ፓርቲ ( አዴፓ) ፣
5. የኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶህዴፓ)፣
6. የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ) ፣
7.የጋምቤላ ህዝቦች አንድነት ፓርቲ (ጋህአዴን)
8.የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ( ቤጉህዴፓ)
በተናጠል በጠቅላላ ጉባኤያቸው ውሳኔ መሰረት አድርገው ውህደቱን ለመቀላቀልና ፓርቲያቸውን ለማክሰም የወሰኑት ውሳኔዎች እንዲሁም ውህደቱን ለመመስረት ያደረጉትን ስምምነት በሙሉ ህጉን ተከትሎ የተፈጸመ በመሆኑ ቦርዱ ፓርቲዎቹ ተሰርዘው ብልጽግና ፓርቲ የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጠው ወስኗል፡፡በዚህም መሰረት ውህዱ ፓርቲ በአዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 92/2 መሰረት በተመዘገበ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ውህደቱ ያስገኘውን ሃብትና ንብረት እና እዳ የሚያሳይ የሂሳብ ሪፓርት ለቦርዱ እንዲያቀርብ በውሳኔው ውስጥ ተካቷል፡፡
2.የኦሮሞ ብሔራዊ ፓርቲ በምዝገባ ወቅት ያቀረበው ሰንደቅ አላማ ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ጋር ይመሳሰላል በሚል በቦርዱ የቀረበለትን ጥያቄ እንደማይመሳሰል በመግለጽ ልዮነቱን አብራርቶ ቦርዱ እንዲቀበለው ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ቦርዱ በሁለቱ ሰንደቅ አላማዎች መካከል አለ የተባለውን ልዩነት መርምሮ የኦሮሞ ብሔራዊ ፓርቲ የጠቀሳቸው ልዮነቶች ለማስተዋል የሚያስቸግሩ በመሆናቸው እና ድምጽ ሰጭዎችን የሚያምታቱ ሆነው ስለሚገኙ ሰንደቅ አላማውን ቀይሮ በማቅረብ ምዝገባውን እንዲያጠናቅቅ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
3.እናት ፓርቲ በሚል አገር አቀፍ ፓርቲ ለማቋቋም በሂደት ላይ ያለ ፓርቲ በአዋጅ 1162/ 2011 መሰረት ጊዜያዊ የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጠው ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ በአዋጁ ላይ የተቀመጠውን ጊዜያዊ ሰርተፍኬት መውሰጃ መስፈርት በማሟላቱ እናት ፓርቲ የጊዜያዊ እውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጠው ቦርዱ ወስኗል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
@YeneTube @FikerAssefa
ነገ ሐሙስ ታህሳስ 16 ቀን 2012 ዓ.ም በመላው ኢትዮጵያ ከፊል የፀሀይ ግርዶሽ (ፓርሻል ሶላር ኢክሊፕስ) እንደሚታይ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ አስታወቀ፡፡
የፀሀይ ግርዶሹ ከጠዋቱ 12፡37 እስከ ጠዋቱ 1፡26 የሚቆይ እንደሆነ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ቤዛ ተስፋዬ አስታውቀዋል፡፡የፀሀይ ግርዶሹ ለኳታር፣ ህንድ፣ ፊሊፒንስ፣ ማሌዥያ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ እስከ 94 በመቶ ፀሀይ እንደምትሸፈን ታውቋል፡፡በዓለማችን የፀሀይ ግርዶሽ በየሁለት አመቱ ሊከሰት የሚችል ክስተት ሲሆን ሰው በትክክል ሊያይበት በሚችለው ቦታ የሚከሰተው በአራት መቶ አመት አንድ ጊዜ ነው፡፡ከፊል የፀሀይ ግርዶሹን ለመመልከት ወደ ፀሀይ ያለ መከላከያ ፊልተር እንዳይመለከቱ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ማሳሰቡን ያገኘነው መረጃ አመልክቷል፡፡
Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
የፀሀይ ግርዶሹ ከጠዋቱ 12፡37 እስከ ጠዋቱ 1፡26 የሚቆይ እንደሆነ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ቤዛ ተስፋዬ አስታውቀዋል፡፡የፀሀይ ግርዶሹ ለኳታር፣ ህንድ፣ ፊሊፒንስ፣ ማሌዥያ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ እስከ 94 በመቶ ፀሀይ እንደምትሸፈን ታውቋል፡፡በዓለማችን የፀሀይ ግርዶሽ በየሁለት አመቱ ሊከሰት የሚችል ክስተት ሲሆን ሰው በትክክል ሊያይበት በሚችለው ቦታ የሚከሰተው በአራት መቶ አመት አንድ ጊዜ ነው፡፡ከፊል የፀሀይ ግርዶሹን ለመመልከት ወደ ፀሀይ ያለ መከላከያ ፊልተር እንዳይመለከቱ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ማሳሰቡን ያገኘነው መረጃ አመልክቷል፡፡
Via Walta
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ወጣቶች ማህበር በሞጣ በታቀጠለው መስጊድ መልሶ ግንባታ እሳተፋለው ብሏል።
ማህበሩ ዛሬ ባህርዳር ባደረገው ስብሰባ በሞጣ በተቃጠለው መስጊድ ተቃውሞውን ገልፆ መስጆዶችን መልሶ ለመገንባት በሚደረገው ስራም እገዛ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።
Via Tesfaye Getinet
@YeneTube @FikerAssefa
ማህበሩ ዛሬ ባህርዳር ባደረገው ስብሰባ በሞጣ በተቃጠለው መስጊድ ተቃውሞውን ገልፆ መስጆዶችን መልሶ ለመገንባት በሚደረገው ስራም እገዛ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።
Via Tesfaye Getinet
@YeneTube @FikerAssefa
ለሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ማሰባሰቢያና ለሲ ኤን ኤን የዓመቱ ጀግና ፍሬወይኒ የአቀባበል መርሃ ግብር ሊካሄድ ነው!
በአዲስ አበባ ከተማ በመንግስት ትምህርት ቤት ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች ሞዲስ እና ሌሎች የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በነጻ ለማቅረብ የከተማ አስተዳደሩ ከተለያዩ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል። በዚሁ መሰረት የፊታችን ታህሳስ 28 ቀን 2012ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የቁሳቁስ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር መዘጋጀቱን አስተባባሪዎቹ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።በመርሃ ግብሩ 700 ሺህ ሞዴስ…
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ በመንግስት ትምህርት ቤት ለሚማሩ ሴት ተማሪዎች ሞዲስ እና ሌሎች የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በነጻ ለማቅረብ የከተማ አስተዳደሩ ከተለያዩ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል። በዚሁ መሰረት የፊታችን ታህሳስ 28 ቀን 2012ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የቁሳቁስ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር መዘጋጀቱን አስተባባሪዎቹ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።በመርሃ ግብሩ 700 ሺህ ሞዴስ…
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
👎1
"ድርጅታችን ብልፅግና ፓርቲ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የእውቅና ሰርተፊኬት በማግኘቱ የድርጅታችን አባላት እና ደጋፊዎች" እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን"
--- ብልፅግና ፓርቲ---
@Yenetube @Fikerassefa
--- ብልፅግና ፓርቲ---
@Yenetube @Fikerassefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በዓለም ተፅዕኖ ከፈጠሩ 50 ግለሰቦች አንዱ ሆኑ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ በፋይናንሺያል ታይምስ ጋዜጣ ከፈረንጆቹ 2010-2019 በነበሩት 10 ዓመታት በዓለም ላይ ለውጥ በማምጣት ከተጠቀሱት 50 ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ዝርዝር ተካትተዋል።
1ኛ) በፖለቲካው መስክ፦
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ቱኒዚያዊው ሞሃመድ ቡአዚዝ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜሪከል የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሳዑዲው አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሃመድ ቢን ሳልማን የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቻይናው መሪ ዢ ዥንፒንግ እና ሌሎችም ተካትተዋል።
2ኛ) በምጣኔ ሀብት፣ በቢዝነስና በቴክኖሎጂ፦
የአማዞን ኩባንያ ባለቤት ጄፍ ቤዞስ የአፕል ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቲም ኩክ ቢል እና ሚሊንዳ ጌትስ የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክ ፕሬዚዳንት ክርስቲን ላጋርድ ቻይናዊው ስራ ፈጣሪ ባለሃብት ጃክ ማ የፌስቡክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማርክ ዙከርበርግ እና ሌሎችም ተካትተዋል።
3ኛ) በባህል፣ በሚዲያ፣ በስፖርት እና በሳይንስ ዘርፍ፦
ሊዮኔል ሜሲ እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ
አሜሪካዊቷ ሙዚቀኛ ቴይለር ስዊፍት የሜዳ ቴኒስ ንግስቷ ሴሬና ዊሊያምስ እና ሌሎችም ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተካትተዋል።
ምንጭ፡-ኢፕድ
@Yenetube @Fikerassefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ በፋይናንሺያል ታይምስ ጋዜጣ ከፈረንጆቹ 2010-2019 በነበሩት 10 ዓመታት በዓለም ላይ ለውጥ በማምጣት ከተጠቀሱት 50 ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ዝርዝር ተካትተዋል።
1ኛ) በፖለቲካው መስክ፦
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ቱኒዚያዊው ሞሃመድ ቡአዚዝ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜሪከል የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሳዑዲው አልጋ ወራሽ ልዑል ሞሃመድ ቢን ሳልማን የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቻይናው መሪ ዢ ዥንፒንግ እና ሌሎችም ተካትተዋል።
2ኛ) በምጣኔ ሀብት፣ በቢዝነስና በቴክኖሎጂ፦
የአማዞን ኩባንያ ባለቤት ጄፍ ቤዞስ የአፕል ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቲም ኩክ ቢል እና ሚሊንዳ ጌትስ የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክ ፕሬዚዳንት ክርስቲን ላጋርድ ቻይናዊው ስራ ፈጣሪ ባለሃብት ጃክ ማ የፌስቡክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማርክ ዙከርበርግ እና ሌሎችም ተካትተዋል።
3ኛ) በባህል፣ በሚዲያ፣ በስፖርት እና በሳይንስ ዘርፍ፦
ሊዮኔል ሜሲ እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ
አሜሪካዊቷ ሙዚቀኛ ቴይለር ስዊፍት የሜዳ ቴኒስ ንግስቷ ሴሬና ዊሊያምስ እና ሌሎችም ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተካትተዋል።
ምንጭ፡-ኢፕድ
@Yenetube @Fikerassefa
የዶክተር አምባቸው ፋውንዴሽን ሊቋቋም ነው፡፡
በሰኔ 15 ጥቃት ሕይወታቸው ያለፉ የአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች 6ኛ ወር መታሰቢያ በአዲስ አበባ ማምሻውን ተካሂዷል፡፡ በመታሰቢያ መርሀ ግብሩም በቀድሞው የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አምባቸው መኮንን (ዶክተር) ሥም ፋውንዴሽን ለማቋቋም እንቅስቃሴ መጀመሩ ይፋ ተደርጓል፡፡በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የዶክተር አምባቸውን ራዕዮች እውን ለማድረግ ፋውንዴሽኑ መቋቋሙ አስፈላጊ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ‹‹በማንኛውም ሰዋዊ ተግባር መልካም የሠራን ማስታወስና ሥራውን መዘከር ተገቢ ነው፡፡ይህንንም ሐሳብ ለማሳካት ለፋውንዴሽኑ እውን መሆን የሚያስፈልጉ ድጋፎችን ማድረግ ይገባናል›› ብለዋል፡፡
ፍትሕንና እውነትን እስከ መጨረሻው የመፈለግ ጉዳይ፣ የዶክተር አምባቸው ራዕዮች እውን እንዲሆኑ የመደገፍና በሐዘኑ ወቅት ቃል እንደተገባው ቤተሰቦቻቸውን ለትልቅ ዓላማና ወግ ማዕረግ ማብቃት ከሁሉም እንደሚጠበቅም አቶ ደመቀ አስገንዝበዋል፡፡የዶክተር አምባቸው ልጅ መዓዛ አምባቸውም በመተሳቢያው ላይ መልዕክት አስተላልፋለች፡፡ ‹‹የአባቴን ዓላማ ለማሳካት ፋውንዴሽኑ ይቋቋማል፤ አባቴ ለተልዕኮና ዓላማ ተገዥ ነበር›› ያለችው መዓዛ ፋውንዴሽኑም ለመሠል ተልዕኮ እንደሚቋቋም አስታውቃለች፤ ለፋውንዴሽኑ እውን መሆን እየለፉ ያሉ አካላትንም አመሥግናለች፡፡ፋውንዴሽኑ እንደሚመሠረት በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል በተዘጋጀው የ6ኛ ወር መታሰቢያ ላይ ዛሬ ይፋ ይደረግ እንጅ ዝርዝር የፋውንዴሽኑ ተግባራትና ሌሎች ጉዳዮች በ1ኛ ዓመት መታሰቢያቸው ላይ እንደሚገለጹ ነው መዓዛ አምባቸው የተናገረችው፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
በሰኔ 15 ጥቃት ሕይወታቸው ያለፉ የአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች 6ኛ ወር መታሰቢያ በአዲስ አበባ ማምሻውን ተካሂዷል፡፡ በመታሰቢያ መርሀ ግብሩም በቀድሞው የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አምባቸው መኮንን (ዶክተር) ሥም ፋውንዴሽን ለማቋቋም እንቅስቃሴ መጀመሩ ይፋ ተደርጓል፡፡በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የዶክተር አምባቸውን ራዕዮች እውን ለማድረግ ፋውንዴሽኑ መቋቋሙ አስፈላጊ መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ‹‹በማንኛውም ሰዋዊ ተግባር መልካም የሠራን ማስታወስና ሥራውን መዘከር ተገቢ ነው፡፡ይህንንም ሐሳብ ለማሳካት ለፋውንዴሽኑ እውን መሆን የሚያስፈልጉ ድጋፎችን ማድረግ ይገባናል›› ብለዋል፡፡
ፍትሕንና እውነትን እስከ መጨረሻው የመፈለግ ጉዳይ፣ የዶክተር አምባቸው ራዕዮች እውን እንዲሆኑ የመደገፍና በሐዘኑ ወቅት ቃል እንደተገባው ቤተሰቦቻቸውን ለትልቅ ዓላማና ወግ ማዕረግ ማብቃት ከሁሉም እንደሚጠበቅም አቶ ደመቀ አስገንዝበዋል፡፡የዶክተር አምባቸው ልጅ መዓዛ አምባቸውም በመተሳቢያው ላይ መልዕክት አስተላልፋለች፡፡ ‹‹የአባቴን ዓላማ ለማሳካት ፋውንዴሽኑ ይቋቋማል፤ አባቴ ለተልዕኮና ዓላማ ተገዥ ነበር›› ያለችው መዓዛ ፋውንዴሽኑም ለመሠል ተልዕኮ እንደሚቋቋም አስታውቃለች፤ ለፋውንዴሽኑ እውን መሆን እየለፉ ያሉ አካላትንም አመሥግናለች፡፡ፋውንዴሽኑ እንደሚመሠረት በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል በተዘጋጀው የ6ኛ ወር መታሰቢያ ላይ ዛሬ ይፋ ይደረግ እንጅ ዝርዝር የፋውንዴሽኑ ተግባራትና ሌሎች ጉዳዮች በ1ኛ ዓመት መታሰቢያቸው ላይ እንደሚገለጹ ነው መዓዛ አምባቸው የተናገረችው፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
👍1
ዶክተር አሚር የኢትዮጵያን ህዝብ አመሰግነዋል። በቀጣይ ሀገሬን በአቅሜ እደግፋለው ሲሉ በፌስ ቡክ ገፃቸው አሳውቀዋል።
"በቅድሚያ ሀገሬንና ሕዝቤን በጤና ሚኒስትርነት እንዳገለግል ለሰጡኝ እድል፣ የተሰጠኝን ኃላፊነት ማሳካት እንድችል ላሳዩኝ ያላሰለሰ ድጋፍና ጽኑ ዕምነት እንዲሁም ያቀረብኩትን የሥራ መልቀቂያ ስለተቀበሉኝ ክቡር የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አሕመድን ከልብ አመሰግናለሁ።
በጤና ሚኒስቴር በተለያዩ ኃላፊነቶች በቆየሁባቸው ዘጠኝ አመታት፣ በተለይም ከሚያዝያ 2010 ዓ.ም ጀምሮ በሚኒስትርነት ባገለገልኩባቸው አንድ ዓመት ከስምንት ወር በፍጹም መከባበርና ለስራ ቅድሚያ በመስጠት በጋራ ስላከናወናቸው ተግባራት የስራ ባልደረቦቼን ፣ጓደኞቼንና የልማት አጋር ድርጅቶችን በሙሉ በእጅጉ ማመስገን እወዳለሁ:: በእነዚህ አመታት የተቀዳጀናቸው ስኬቶች ሁሉ የጋራ ጥረት ውጤቶች እንደመሆናቸው በእኩል ልንኮራባቸው ይገባል::ያላሟላናቸው ነገሮችን በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ወደ ስኬት እንደሚመጡ እርግጠኛ ነኝ::
ገና በወጣትነት እድሜ የህክምና ትምህርቴን ጨርሼ ስራ ከጀመርኩበት ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ፣ በሙያዬና በተለያዩ የመንግስት የሀላፊነት ዘርፎች ሳገለግል ያለኝን እውቀት፣ ጉልበትና የስራ ልምድ ያልሰስት ደስ ብሎኝ በስራ ላይ ለማዋል ጥሬያለሁ።
አሁን ወደ ኋላ ስመለከተው ግን በቆይታዬ ወቅት ከሰራሁት ይልቅ የተማርኩት፣ ከሰጠሁትም የተቀበልኩት እጅግ የላቀ እንደሆነ ተረድቻለሁ። "ተማሪ ካስተዋለ አስተማሪ ሁልጊዜም አለ" እንዲሉ ጥሩ ስሰራ በማበረታታት ሳጠፋም በማረም የዛሬ ማንነቴን በመቅረጽ በማንነቴ ላይ የማይጠፋ አሻራውን ላስቀመጠው የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንደበቴ ከማመስገን በተጨማሪ በቀጣይ የሥራ ዘመኔ ሁሉ አቅሜ በፈቀደ መጠን ሀገሬንና ያደኩበትን ቤቴን የጤና ሚኒስቴርን ለመድጋፍ ቃል እገባለሁ:: "
አመሰግናለሁ
አሚር አማን
@Yenetube @Fikerassefa
"በቅድሚያ ሀገሬንና ሕዝቤን በጤና ሚኒስትርነት እንዳገለግል ለሰጡኝ እድል፣ የተሰጠኝን ኃላፊነት ማሳካት እንድችል ላሳዩኝ ያላሰለሰ ድጋፍና ጽኑ ዕምነት እንዲሁም ያቀረብኩትን የሥራ መልቀቂያ ስለተቀበሉኝ ክቡር የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አሕመድን ከልብ አመሰግናለሁ።
በጤና ሚኒስቴር በተለያዩ ኃላፊነቶች በቆየሁባቸው ዘጠኝ አመታት፣ በተለይም ከሚያዝያ 2010 ዓ.ም ጀምሮ በሚኒስትርነት ባገለገልኩባቸው አንድ ዓመት ከስምንት ወር በፍጹም መከባበርና ለስራ ቅድሚያ በመስጠት በጋራ ስላከናወናቸው ተግባራት የስራ ባልደረቦቼን ፣ጓደኞቼንና የልማት አጋር ድርጅቶችን በሙሉ በእጅጉ ማመስገን እወዳለሁ:: በእነዚህ አመታት የተቀዳጀናቸው ስኬቶች ሁሉ የጋራ ጥረት ውጤቶች እንደመሆናቸው በእኩል ልንኮራባቸው ይገባል::ያላሟላናቸው ነገሮችን በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ወደ ስኬት እንደሚመጡ እርግጠኛ ነኝ::
ገና በወጣትነት እድሜ የህክምና ትምህርቴን ጨርሼ ስራ ከጀመርኩበት ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ፣ በሙያዬና በተለያዩ የመንግስት የሀላፊነት ዘርፎች ሳገለግል ያለኝን እውቀት፣ ጉልበትና የስራ ልምድ ያልሰስት ደስ ብሎኝ በስራ ላይ ለማዋል ጥሬያለሁ።
አሁን ወደ ኋላ ስመለከተው ግን በቆይታዬ ወቅት ከሰራሁት ይልቅ የተማርኩት፣ ከሰጠሁትም የተቀበልኩት እጅግ የላቀ እንደሆነ ተረድቻለሁ። "ተማሪ ካስተዋለ አስተማሪ ሁልጊዜም አለ" እንዲሉ ጥሩ ስሰራ በማበረታታት ሳጠፋም በማረም የዛሬ ማንነቴን በመቅረጽ በማንነቴ ላይ የማይጠፋ አሻራውን ላስቀመጠው የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንደበቴ ከማመስገን በተጨማሪ በቀጣይ የሥራ ዘመኔ ሁሉ አቅሜ በፈቀደ መጠን ሀገሬንና ያደኩበትን ቤቴን የጤና ሚኒስቴርን ለመድጋፍ ቃል እገባለሁ:: "
አመሰግናለሁ
አሚር አማን
@Yenetube @Fikerassefa
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ - EBC
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች በተገለፀው ክፍት የስራ መደብ ለይ ተፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ በኮርፖሮሽናችን ድህረ-ገፅና ፌስቡክ እንዲሁም የሬዲዮና የቴሌቪዥን ቻናሎች እና በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት የውጭ ሰሌዳ ቦርድ ላይ ከወጣበትና ከተገለፀበት ከታህሳስ 20 ቀን 2012 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት አምስት ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ሰው ሃይል ምልመላና መረጣ ቡድን ቢሮ ቁጥር 1020 በመቅረብ ወይም በተወካይ ተገቢውን የስራ ልምድና የትምህርት ዝግጅት ዋናውንና የማይመለስ ኮፒ በማቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የትምህርትደረጃ እና የስራ ልምድ
በአካውንቲንግ፤ማርኬቲንግ፤ፐርቸዚንግ ፕሮኪዩርመንት ወይም ቢዚነስ ማናጅመንት፤በሎጀስቲክ
የመጀመሪ ዲግሪ---------------- 4 ዓመት
ዲፕሎማ/10+3/ ወይም ደረጃ III- 6 ዓመት
ቴክኒክና ሙያ------------------- 8 ዓመት
በአካውንታንትነት፤በኦዲተርነት፤በግዢና ንብረት አስተዳደር ስራ፤በፐርቸዚንግነት፤በፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ የሰሩ፤በትራንዚትና በተመሳሳይ የስራ ዘርፍ የሰሩ ፤ስራ ማቀድ፤የመተንተን፤የማደራጀት የማስተባበር፤የመከታተልና የመደገፍ እንዲሁም ጊዜውን ለተቋሙ ስራ ለማዋል ቁርጠኛ የሆኑ፤የለውጥ አስተሳሰብና ተነሳሽነት ያላቸው፤በስራቸው መልካም ባህሪ ያላቸው፤ታማኝና በስራመስኩ የስራ ልምድ የሚየቀርቡ መሆን አለባቸው፡፡
ማሳሰቢያ፤
1. ከዚህ በላይ የተገለፀውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ከላይ በተገለፁ 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ እየቀረባችሁ ዘወትር በሥራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 1020 እየቀረባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
2. አመልካቾች ለምዝገባ ሲቀርቡ ከስራው ጋር አግባብነት ያለው የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃቸውን ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር ይዘው መቅረብ አለባቸው፡፡
3. ከደረጃ 3------5 የተጠቀሱት የትምህርት ማስረጃዎችለምዝገባ የሚያገለግሉት ለቀረበው ደረጃ ከሙያ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት (ሲኦሲ) ጋር ሲቀርብ ብቻ ነው፡፡
4. የከፍተኛ የትምህርት ተቋም ወጪ መጋራትየሚመለከታቸው አመልካቾች ለምዝገባ ሲቀርቡ ከተማሩበት ተቋም የተሰጣቸውን የእዳ መግለጫና ተቀጥረው ሰርተው ከሆነ የከፈሉትን መጠን የሚያሳይ ማስረጃ ይዘው መቅረብ የጠበቅባቸዋል፡፡
5. ከውጭ አገር የተገኙ የትምህርት ማስረጃዎች በአገር ውስጥ ከሚመለከተው አካል የአቻ ግመታ ያገኙና ማስረጃ የሚቀርብባቸው መሆን ይገባቸዋል፡፡
6. አመልካቾች ለምዝገባ ሲቀርቡ ዋናውን የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃቸውን ከማይመለስ አንድ ፎቶ ኮፒ ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡
7. አመልካቾች ምዝገባቸውን ለማካሄድ በአካል ቀርበው ወይም ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ማስረጃቸውን በተወካይ በመላክ የተዘግጀውን ፎርም መሙላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
8. ቀጥታ አግባብነት የለው የትምህርት ዝግጅት እና የስራ ልምድ ውጭ ለምዝገባ የሚቀርቡ ሌሎች ማስረጃዎች ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
9. ለምዝገባ በአመልካቾች የሚቀርቡ የስራ ልምድ ማስረጃዎች የስራ ልምዱ የተገኘበት የስራ መደብና ደመወዝ፤ ከመቼ እስከ መቼ እንደሰሩና የስራ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን መግለፅ አለባቸው፡፡
10. የፈተና ጊዜ በውስጥ ማስታወቂያ ውይም በሬዲዮና በቴሌቪዥን አማካኝነት የሚገለፅ ይሆናል፡፡
11. አመልካቾች ተጨማሪ መረጃ ማግኝት ከፈለጉ በቢሮ ቁጥር 0115172556 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
@Yenetube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች በተገለፀው ክፍት የስራ መደብ ለይ ተፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ በኮርፖሮሽናችን ድህረ-ገፅና ፌስቡክ እንዲሁም የሬዲዮና የቴሌቪዥን ቻናሎች እና በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት የውጭ ሰሌዳ ቦርድ ላይ ከወጣበትና ከተገለፀበት ከታህሳስ 20 ቀን 2012 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት አምስት ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ሰው ሃይል ምልመላና መረጣ ቡድን ቢሮ ቁጥር 1020 በመቅረብ ወይም በተወካይ ተገቢውን የስራ ልምድና የትምህርት ዝግጅት ዋናውንና የማይመለስ ኮፒ በማቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የትምህርትደረጃ እና የስራ ልምድ
በአካውንቲንግ፤ማርኬቲንግ፤ፐርቸዚንግ ፕሮኪዩርመንት ወይም ቢዚነስ ማናጅመንት፤በሎጀስቲክ
የመጀመሪ ዲግሪ---------------- 4 ዓመት
ዲፕሎማ/10+3/ ወይም ደረጃ III- 6 ዓመት
ቴክኒክና ሙያ------------------- 8 ዓመት
በአካውንታንትነት፤በኦዲተርነት፤በግዢና ንብረት አስተዳደር ስራ፤በፐርቸዚንግነት፤በፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ የሰሩ፤በትራንዚትና በተመሳሳይ የስራ ዘርፍ የሰሩ ፤ስራ ማቀድ፤የመተንተን፤የማደራጀት የማስተባበር፤የመከታተልና የመደገፍ እንዲሁም ጊዜውን ለተቋሙ ስራ ለማዋል ቁርጠኛ የሆኑ፤የለውጥ አስተሳሰብና ተነሳሽነት ያላቸው፤በስራቸው መልካም ባህሪ ያላቸው፤ታማኝና በስራመስኩ የስራ ልምድ የሚየቀርቡ መሆን አለባቸው፡፡
ማሳሰቢያ፤
1. ከዚህ በላይ የተገለፀውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ከላይ በተገለፁ 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ እየቀረባችሁ ዘወትር በሥራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 1020 እየቀረባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
2. አመልካቾች ለምዝገባ ሲቀርቡ ከስራው ጋር አግባብነት ያለው የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃቸውን ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር ይዘው መቅረብ አለባቸው፡፡
3. ከደረጃ 3------5 የተጠቀሱት የትምህርት ማስረጃዎችለምዝገባ የሚያገለግሉት ለቀረበው ደረጃ ከሙያ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት (ሲኦሲ) ጋር ሲቀርብ ብቻ ነው፡፡
4. የከፍተኛ የትምህርት ተቋም ወጪ መጋራትየሚመለከታቸው አመልካቾች ለምዝገባ ሲቀርቡ ከተማሩበት ተቋም የተሰጣቸውን የእዳ መግለጫና ተቀጥረው ሰርተው ከሆነ የከፈሉትን መጠን የሚያሳይ ማስረጃ ይዘው መቅረብ የጠበቅባቸዋል፡፡
5. ከውጭ አገር የተገኙ የትምህርት ማስረጃዎች በአገር ውስጥ ከሚመለከተው አካል የአቻ ግመታ ያገኙና ማስረጃ የሚቀርብባቸው መሆን ይገባቸዋል፡፡
6. አመልካቾች ለምዝገባ ሲቀርቡ ዋናውን የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃቸውን ከማይመለስ አንድ ፎቶ ኮፒ ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡
7. አመልካቾች ምዝገባቸውን ለማካሄድ በአካል ቀርበው ወይም ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ማስረጃቸውን በተወካይ በመላክ የተዘግጀውን ፎርም መሙላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
8. ቀጥታ አግባብነት የለው የትምህርት ዝግጅት እና የስራ ልምድ ውጭ ለምዝገባ የሚቀርቡ ሌሎች ማስረጃዎች ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
9. ለምዝገባ በአመልካቾች የሚቀርቡ የስራ ልምድ ማስረጃዎች የስራ ልምዱ የተገኘበት የስራ መደብና ደመወዝ፤ ከመቼ እስከ መቼ እንደሰሩና የስራ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን መግለፅ አለባቸው፡፡
10. የፈተና ጊዜ በውስጥ ማስታወቂያ ውይም በሬዲዮና በቴሌቪዥን አማካኝነት የሚገለፅ ይሆናል፡፡
11. አመልካቾች ተጨማሪ መረጃ ማግኝት ከፈለጉ በቢሮ ቁጥር 0115172556 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
@Yenetube @Fikerassefa
የጤና ሚንስትሩ ሥልጣን መልቀቅ
የኢትዮጵያ ጤና ሚንስትር የነበሩት ዶክተር አሚር አማን ከኃላፊነታቸው ለቀቁ።
ከወራት በፊት የሥራ መልቀቂያን አስገብተው የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)ን ምላሽ ሲጠባበቁ የከረሙት ዶክተር አሚር ጥያቄቸው ተቀባይነት ማግኘቱን ይፋ አድርገዋል።
በህክምና ሙያ ትምህርት የተመረቁት የቀድሞው ሚንስትር ከ2001 ጀምሮ ወደ ሥራው ዓለም የተቀላቀሉ ሲሆን ለዓመታት በጤና ጥበቃ ሚንስትር ዴኤታነትም አገልግለዋል።
ከሚያዚያ 2010 ጀምሮ ደግሞ የጤና ሚንስትር ሆነው እስከዛሬ ሰርተዋል።
በቀጣይ በዩናይትድ ስቴትስ በሚገኝ ዓለም ዓቀፍ የጤና ተቋም ሥራን ሊጀምሩ እንደሚችሉ እየተነገረላቸው የሚገኙት ዶክተር አሚር የኢትዮጵያን ሕዝብ በቻሉት ሁሉ እያለገሉ እንደሚኖሩ ቃል ገብተዋል።
@Yenetube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ጤና ሚንስትር የነበሩት ዶክተር አሚር አማን ከኃላፊነታቸው ለቀቁ።
ከወራት በፊት የሥራ መልቀቂያን አስገብተው የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)ን ምላሽ ሲጠባበቁ የከረሙት ዶክተር አሚር ጥያቄቸው ተቀባይነት ማግኘቱን ይፋ አድርገዋል።
በህክምና ሙያ ትምህርት የተመረቁት የቀድሞው ሚንስትር ከ2001 ጀምሮ ወደ ሥራው ዓለም የተቀላቀሉ ሲሆን ለዓመታት በጤና ጥበቃ ሚንስትር ዴኤታነትም አገልግለዋል።
ከሚያዚያ 2010 ጀምሮ ደግሞ የጤና ሚንስትር ሆነው እስከዛሬ ሰርተዋል።
በቀጣይ በዩናይትድ ስቴትስ በሚገኝ ዓለም ዓቀፍ የጤና ተቋም ሥራን ሊጀምሩ እንደሚችሉ እየተነገረላቸው የሚገኙት ዶክተር አሚር የኢትዮጵያን ሕዝብ በቻሉት ሁሉ እያለገሉ እንደሚኖሩ ቃል ገብተዋል።
@Yenetube @FikerAssefa
በጃፓን ኦሎምፒክ ወቅት የጠፋው የአበበ ቢቂላ ቀለበት ከ55 ዓመታት በኋላ ለቤተሰቦቹ ተመለሰ
እኤአ 1964 በተካሄደው በጃፓን ኦሎምፒክ ወቅት አበባ ቢቂላ የቶኪዮ ማራቶን ውድድርን ባሸነፈበት ውድድር ወቅት የጠፋው ቀለበት ለቤተሰቦቹ ተመለሰ፡፡
የጠፋው የአበበ ቀለበት በወቅቱ በፅዳት ስራ ላይ በነበረች ጃፓናዊት እጅ እንደነበረ እና ከ55 ዓመታት በልጇ አማካኝነት ለአበበ ቤተሰቦች መመለሱ ነው የተገለፀው፡፡
በወቅቱ አበበ ቢቂላ ቀለበቱን በእስታዲዮም መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ረስቶት መውጣቱ ስታዲየሙን በማጽዳት ስራ ላይ የነበሩት ባረክ እናት አግኝተውት ለአበበ ቢቂለ እንዲሰጠው ለልጃቸው እንዳስረከቡት ሚስተር ባረክ ተናግሯል፡፡
በወቅቱ የ19 ዓመት ልጅ የነበረው ሚስትር ባረክ ለግማሽ ክፍለ ዘመን የዘለለ አደራ ይዞ በዕድለኝነት ስሜት የአበበን ቤተሰብ ይቅርታ በመጠየቅ ቀለበቱን አስረክቧል፡፡
የአበበ ቤተሰብም ይቅርታውን በመቀበል ቀለበቱን ተቀብለዋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
እኤአ 1964 በተካሄደው በጃፓን ኦሎምፒክ ወቅት አበባ ቢቂላ የቶኪዮ ማራቶን ውድድርን ባሸነፈበት ውድድር ወቅት የጠፋው ቀለበት ለቤተሰቦቹ ተመለሰ፡፡
የጠፋው የአበበ ቀለበት በወቅቱ በፅዳት ስራ ላይ በነበረች ጃፓናዊት እጅ እንደነበረ እና ከ55 ዓመታት በልጇ አማካኝነት ለአበበ ቤተሰቦች መመለሱ ነው የተገለፀው፡፡
በወቅቱ አበበ ቢቂላ ቀለበቱን በእስታዲዮም መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ረስቶት መውጣቱ ስታዲየሙን በማጽዳት ስራ ላይ የነበሩት ባረክ እናት አግኝተውት ለአበበ ቢቂለ እንዲሰጠው ለልጃቸው እንዳስረከቡት ሚስተር ባረክ ተናግሯል፡፡
በወቅቱ የ19 ዓመት ልጅ የነበረው ሚስትር ባረክ ለግማሽ ክፍለ ዘመን የዘለለ አደራ ይዞ በዕድለኝነት ስሜት የአበበን ቤተሰብ ይቅርታ በመጠየቅ ቀለበቱን አስረክቧል፡፡
የአበበ ቤተሰብም ይቅርታውን በመቀበል ቀለበቱን ተቀብለዋል፡፡
@Yenetube @Fikerassefa
👍1