እነ አቶ ልደቱ ምርጫ ቦርድን እንከሳለን አሉ!
ኢዴፓን በሃይል ተነጥቀናል ያሉት እነ አቶ ልደቱ አያሌው ምርጫ ቦርድ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ መፍትሔ እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ምላሽ የማይሰጣቸው ከሆነ ምርጫ ቦርድን በህግ ለመጠየቅ መዘጋጀቸውን አስታውቀዋል፡፡ከአንድ ወር በፊት የብሔራዊ ም/ቤት ስብሰባ አድርገው አዳዲስ አመራሮች መርጠው ምርጫ ቦርድ የፓርቲውን ህልውና እንዲያረጋግጥላቸው ጠይቀው የነበረ መሆኑን ለአዲስ አድማስ ያስረዱት ፕሬዚዳንቱ አቶ አዳነ ታደሠ ቦርዱ ምንም አይነት ምላሽ ሊሰጣቸው እንዳልቻለ ተናግረዋል፡፡በተደጋጋሚ በደብዳቤ ለምናቀርበው ጥያቄም ቦርዱም ዝምታን መርጧል ብለዋል፡፡“አሁንም ኢዴፓ በሀገሪቱ ፖለቲካ ላይ ጉልህ ሚና እንዳይጫወት ስውር ደባ እየፈፀመበት ነው የሚሉት አቶ አዳነ በፓርቲው ጉዳይ ቦርዱ ለመወሰን ለምን እንደተቸገረ አልገባንም ብለዋል፡፡
ችግሩ የተፈጠረው እንዴት ነው? ችግሩ ያለው ማን ጋር ነው? የሚሉትን ለይቶ ለማወቅ ሲባል አምስቱም የምርጫ ቦርድ አባላት በጋራ እንዲያነጋግሯቸው ህዳር 17/2012 በደብዳቤ መጠየቁንም አቶ አዳነ አስረድተዋል፡፡አምስቱም የቦርዱ አባላት ባሉበት ነው በኢዴፓ ጉዳይ ከእንግዲህ መወያየት የምንፈልገው ያሉት አቶ አዳነ ለዚህ ጥያቄያችን ምላሽ የማይሰጠን ከሆነ በቀጥታ ቦርዱ ላይ በፍ/ቤት ክስ እንመሠርታለን ብለዋል፡፡“በዋናነነት በኢዜማ የተወሰዱ ጽ/ቤቶቻችን እንዲመለሱ፣ ማህተማችን እንዲመለስ የቦርዱ ውሣኔ ወሳኝ ነው ያሉት አቶ አዳነ ቦርዱ በተደጋጋሚ ኢዴፓ አልፈረሰም የሚል መግለጫ መስጠቱንና ካልፈረሰ ለባለቤቶቹ መመለስ እንደሚገባው አስረድተዋል፡፡ይህን አቤቱታቸውንም በተመሳሳይ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በደብዳቤ ማቅረባቸውንም አቶ አዳነ ተናግረዋል፡፡
Via Addis Admas
@YeneTube @FikerAssefa
ኢዴፓን በሃይል ተነጥቀናል ያሉት እነ አቶ ልደቱ አያሌው ምርጫ ቦርድ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ መፍትሔ እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ምላሽ የማይሰጣቸው ከሆነ ምርጫ ቦርድን በህግ ለመጠየቅ መዘጋጀቸውን አስታውቀዋል፡፡ከአንድ ወር በፊት የብሔራዊ ም/ቤት ስብሰባ አድርገው አዳዲስ አመራሮች መርጠው ምርጫ ቦርድ የፓርቲውን ህልውና እንዲያረጋግጥላቸው ጠይቀው የነበረ መሆኑን ለአዲስ አድማስ ያስረዱት ፕሬዚዳንቱ አቶ አዳነ ታደሠ ቦርዱ ምንም አይነት ምላሽ ሊሰጣቸው እንዳልቻለ ተናግረዋል፡፡በተደጋጋሚ በደብዳቤ ለምናቀርበው ጥያቄም ቦርዱም ዝምታን መርጧል ብለዋል፡፡“አሁንም ኢዴፓ በሀገሪቱ ፖለቲካ ላይ ጉልህ ሚና እንዳይጫወት ስውር ደባ እየፈፀመበት ነው የሚሉት አቶ አዳነ በፓርቲው ጉዳይ ቦርዱ ለመወሰን ለምን እንደተቸገረ አልገባንም ብለዋል፡፡
ችግሩ የተፈጠረው እንዴት ነው? ችግሩ ያለው ማን ጋር ነው? የሚሉትን ለይቶ ለማወቅ ሲባል አምስቱም የምርጫ ቦርድ አባላት በጋራ እንዲያነጋግሯቸው ህዳር 17/2012 በደብዳቤ መጠየቁንም አቶ አዳነ አስረድተዋል፡፡አምስቱም የቦርዱ አባላት ባሉበት ነው በኢዴፓ ጉዳይ ከእንግዲህ መወያየት የምንፈልገው ያሉት አቶ አዳነ ለዚህ ጥያቄያችን ምላሽ የማይሰጠን ከሆነ በቀጥታ ቦርዱ ላይ በፍ/ቤት ክስ እንመሠርታለን ብለዋል፡፡“በዋናነነት በኢዜማ የተወሰዱ ጽ/ቤቶቻችን እንዲመለሱ፣ ማህተማችን እንዲመለስ የቦርዱ ውሣኔ ወሳኝ ነው ያሉት አቶ አዳነ ቦርዱ በተደጋጋሚ ኢዴፓ አልፈረሰም የሚል መግለጫ መስጠቱንና ካልፈረሰ ለባለቤቶቹ መመለስ እንደሚገባው አስረድተዋል፡፡ይህን አቤቱታቸውንም በተመሳሳይ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በደብዳቤ ማቅረባቸውንም አቶ አዳነ ተናግረዋል፡፡
Via Addis Admas
@YeneTube @FikerAssefa
ብራዚል ተዋናይ ሌዎናርዶ ዲካፓሪዮ አማዞን ጫካ እንዲቃጠል አድርጓል ስትል ከሳለች!
የብራዚሉ ፕሬዝደንት ጃይር ቦልሶናሮ ተዋናይ ሌዎናርዶ ዲካፕሪዮ የአማዞን ጫካ እሣት እንዲለብስ የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል ሲሉ ወቀሱ።ፕሬዝደንቱ ተዋናይ ይህንን ስለማድረጉ ምንም ዓይነት ማስረጃ ባይሰጡም አማዞን ጫካ ላይ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ሲወቅሱ የመጀመሪያቸው አይደለም።ሰደድ እሣቱን ያስነሱት የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት የፈለጉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ናቸው ያለው የብራዚል መንግሥት የጠረጠራቸውን በርካታ ሰዎች አሥሯል።ለአማዞን ጫካ መልሶ መቋቋም 5 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ቃል የገባው ሌዎናርዶ የፕሬዝደንቱን ወቀሳ አስተባብሏል።
አራት በጎ ፈቃደኛ የሰደድ እሣት ተከላካዮች በብራዚል መንግሥት መታሠራቸውን ተከትሎ በርካታ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የቦልሶናሮ መንግሥትን እየወረፉ ይገኛሉ።ኢ-መንግሥታዊ ድርጅቶች እና የመብት ተሟጋቾች የብራዚል መንግሥት ድርጊት ፖለቲካዊና ተፈጥሮ ላይ የሚሠሩ ድርጅቶችን ለመፈታተን ያሰበ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን ያሰማሉ።ባለፈው ነሐሴ የሰደድ እሣት ሰለባ የሆነው የብራዚሉ አማዞን ጫካ ጉዳይ ብዙዎችን ያስጨነቀ ሆኗል።
ፕሬዝደንቱ ባለፈው አርብ በመኖሪያ ቤታቸው ሳሉ ነው ወቀሳቸውን የሰነዘሩት። «ሌዎናርዶ ዲካፕሪዮ የሚሉት ሰውዬ ጥሩ ይመስላል አይደል? ገንዘብ ሰጥቶ አማዞንን የሚያነድ።» «እነዚህ ኤንጂኦ ተብየዎች ምንድነው የሚሠሩት? ጫካውን ያቃጥላሉ ከዚያ ፎቶ ያነሳሉ፤ ቪድዮ ይቀርፃሉ። ዎርልድ ዋይልድላይፍ ፈንድ [WWF] ለምሳሌ ከዲካፕሪዮ ጋር ነው የሚሠራው፤ እሱም 500 ሸህ ዶላር እርዳታ አድርጓል።በተፈጥሮ ጥበቃ ለተሰማሩ ድርጅቶች ድጋፍ በማድረግ የሚታወቀው ዲካፕሪዮ፤ ምንም እንኳ አማዞን ጫካ ውስጥ የሚሠሩ ድርጅቶች እርዳታ ቢሹም እኔ እርዳታ አላደረግኩም ሲል ወቀሳውን አስተባብሏል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
የብራዚሉ ፕሬዝደንት ጃይር ቦልሶናሮ ተዋናይ ሌዎናርዶ ዲካፕሪዮ የአማዞን ጫካ እሣት እንዲለብስ የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል ሲሉ ወቀሱ።ፕሬዝደንቱ ተዋናይ ይህንን ስለማድረጉ ምንም ዓይነት ማስረጃ ባይሰጡም አማዞን ጫካ ላይ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ሲወቅሱ የመጀመሪያቸው አይደለም።ሰደድ እሣቱን ያስነሱት የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት የፈለጉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ናቸው ያለው የብራዚል መንግሥት የጠረጠራቸውን በርካታ ሰዎች አሥሯል።ለአማዞን ጫካ መልሶ መቋቋም 5 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ቃል የገባው ሌዎናርዶ የፕሬዝደንቱን ወቀሳ አስተባብሏል።
አራት በጎ ፈቃደኛ የሰደድ እሣት ተከላካዮች በብራዚል መንግሥት መታሠራቸውን ተከትሎ በርካታ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የቦልሶናሮ መንግሥትን እየወረፉ ይገኛሉ።ኢ-መንግሥታዊ ድርጅቶች እና የመብት ተሟጋቾች የብራዚል መንግሥት ድርጊት ፖለቲካዊና ተፈጥሮ ላይ የሚሠሩ ድርጅቶችን ለመፈታተን ያሰበ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን ያሰማሉ።ባለፈው ነሐሴ የሰደድ እሣት ሰለባ የሆነው የብራዚሉ አማዞን ጫካ ጉዳይ ብዙዎችን ያስጨነቀ ሆኗል።
ፕሬዝደንቱ ባለፈው አርብ በመኖሪያ ቤታቸው ሳሉ ነው ወቀሳቸውን የሰነዘሩት። «ሌዎናርዶ ዲካፕሪዮ የሚሉት ሰውዬ ጥሩ ይመስላል አይደል? ገንዘብ ሰጥቶ አማዞንን የሚያነድ።» «እነዚህ ኤንጂኦ ተብየዎች ምንድነው የሚሠሩት? ጫካውን ያቃጥላሉ ከዚያ ፎቶ ያነሳሉ፤ ቪድዮ ይቀርፃሉ። ዎርልድ ዋይልድላይፍ ፈንድ [WWF] ለምሳሌ ከዲካፕሪዮ ጋር ነው የሚሠራው፤ እሱም 500 ሸህ ዶላር እርዳታ አድርጓል።በተፈጥሮ ጥበቃ ለተሰማሩ ድርጅቶች ድጋፍ በማድረግ የሚታወቀው ዲካፕሪዮ፤ ምንም እንኳ አማዞን ጫካ ውስጥ የሚሠሩ ድርጅቶች እርዳታ ቢሹም እኔ እርዳታ አላደረግኩም ሲል ወቀሳውን አስተባብሏል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ፣ ግብፅና ሱዳን መካከል እንደ አዲስ የተጀመረው ድርድር ነገ ካይሮ ይካሄዳል።በድርድሩም የሶስቱ ሀገራት የውሃና መስኖ ልማት ሚንስትሮች እንደሚገኙ AAWSA የተባለው የግብፅ ሚዲያ ዘግቧል።ባለፈው ወር አሜሪካ ተገናኝተው ከመከሩ በኋላ በአራት ዙር ድርድር ለማድረግ መስማማታቸው ይታወሳል። የመጀመሪያው ዙር አዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን ይህ ሁለተኛው የድርድሩ አካል ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ከወላይታ የሀገር ሽማግሌዎች እና የዞኑ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር በጽ/ቤታቸው ውይይት አድርገዋል።ጠ/ሚው በማህበራዊ ሚድያ ገፃቸው ውይይቱ ፍሬያማ ነበር ሲሉ ገልጸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
ሃጌ ጌኢንጎብ ማሸነፋቸው ተሰማ!!
የናሚቢያው ፕሬዚዳንት ሃጌ ጌኢንጎብ ረቡዕ ዕለት በተካሄደው ምርጫ በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ መመረጣቸውን የሀገሪቱ የምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
ፕሬዚዳንቱ ምርጫውን ያሸነፉት 56.3 በመቶ ድምፅ በማግኘት ሲሆን የቅርብ ተፎካካሪያቸው ፓንዱሌኒ ኢቱላ 29.4 በመቶ ድምፅ ማግኘታቸው ተነግሯል።
@Yenetube @Fikerassefa
የናሚቢያው ፕሬዚዳንት ሃጌ ጌኢንጎብ ረቡዕ ዕለት በተካሄደው ምርጫ በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ መመረጣቸውን የሀገሪቱ የምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
ፕሬዚዳንቱ ምርጫውን ያሸነፉት 56.3 በመቶ ድምፅ በማግኘት ሲሆን የቅርብ ተፎካካሪያቸው ፓንዱሌኒ ኢቱላ 29.4 በመቶ ድምፅ ማግኘታቸው ተነግሯል።
@Yenetube @Fikerassefa
የኢህአዴግ ውህደት የፊርማ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ነው!
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢህአዴግ እና ኦዲፒ ሊቀመንበር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የስምንቱ ፖርቲዎች ሊቀመናብርት ተገኝተዋል። ሚንስትሮችም በእንግድነት ታድመዋል።
Via:-EBC
@Yenetube @Fikerassefa
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢህአዴግ እና ኦዲፒ ሊቀመንበር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የስምንቱ ፖርቲዎች ሊቀመናብርት ተገኝተዋል። ሚንስትሮችም በእንግድነት ታድመዋል።
Via:-EBC
@Yenetube @Fikerassefa
😍ለጫማ አድናቂዎች😍
ለወንድም ለሴትም ሚሆኑ አዳዲስ ጫማዎችን እነሆ ብለናል::
💥ማስታወሻ:ተደራሽነታችን በአዲስ አበባ እንዲሁም ሁሉንም የክልል ከተምችን ያካትታል
🎯አድራሻ:-ገርጂ መብራት ሀይል ዊዝደም ህንፃ ፊት
ስልክ:-0900628132
0116296465
በቴሌግራም ለማግኘት ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉን👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAE3CCBtJE8NBy8ZShA
ለወንድም ለሴትም ሚሆኑ አዳዲስ ጫማዎችን እነሆ ብለናል::
💥ማስታወሻ:ተደራሽነታችን በአዲስ አበባ እንዲሁም ሁሉንም የክልል ከተምችን ያካትታል
🎯አድራሻ:-ገርጂ መብራት ሀይል ዊዝደም ህንፃ ፊት
ስልክ:-0900628132
0116296465
በቴሌግራም ለማግኘት ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉን👇👇
https://tttttt.me/joinchat/AAAAAE3CCBtJE8NBy8ZShA
#አስደሳች ዜና ለሞባይል መለዋወጫ ሱቆች
በስክሪን ኘሮቴክተር መሰቃየት ቀረ
አንዴ ገዝተው እስከ ሁል ጊዜ ከጥሩ ትርፍ ጋር ለሁሉም አይነት ስልክ የሚያገለግል።
በ 12000 ብር ብቻ
አሁኑኑ በ 0911522626
0953120011
ይደውሉ። ወይም በ @natyendex መልእክት ያስቀምጡ።
For more @natcomputers
በስክሪን ኘሮቴክተር መሰቃየት ቀረ
አንዴ ገዝተው እስከ ሁል ጊዜ ከጥሩ ትርፍ ጋር ለሁሉም አይነት ስልክ የሚያገለግል።
በ 12000 ብር ብቻ
አሁኑኑ በ 0911522626
0953120011
ይደውሉ። ወይም በ @natyendex መልእክት ያስቀምጡ።
For more @natcomputers
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
💥ማስታወቂያ💥
School of American English
📌ቻይንኛ
📌ፈረንሳይኛ
📌ጀርመንኛ
📌ጣልያንኛ
📌አፋን ኦሮሞ
📌አረብኛ
አንቱታን ባተፈሩ መምህራን እናስተምራለን
አድራሻዎቻችን ⬇️
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ +251919913021
ፒያሳ ፒያሳ ገበያ ማዕከል +251919913023
22 ጎላጎል ህንፃ 6ተኛ ፎቅ +251919913022
💥💥💥10% Discount 💥💥💥💥
ቅናሹን ለመጠቀም
ይህንን ፓስት screenshot አድርገው መያዝና ስመጡ ማሣየት ይኖርብዎታል
T.me/SCHOOLOFAMERICAN
School of American English
📌ቻይንኛ
📌ፈረንሳይኛ
📌ጀርመንኛ
📌ጣልያንኛ
📌አፋን ኦሮሞ
📌አረብኛ
አንቱታን ባተፈሩ መምህራን እናስተምራለን
አድራሻዎቻችን ⬇️
ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ +251919913021
ፒያሳ ፒያሳ ገበያ ማዕከል +251919913023
22 ጎላጎል ህንፃ 6ተኛ ፎቅ +251919913022
💥💥💥10% Discount 💥💥💥💥
ቅናሹን ለመጠቀም
ይህንን ፓስት screenshot አድርገው መያዝና ስመጡ ማሣየት ይኖርብዎታል
T.me/SCHOOLOFAMERICAN
የብልፅግና ፓርቲን የተቀላቀሉ ድርጅቶች የስምምነት የፊርማ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል፡፡
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢህአዴግ እና ኦዲፒ ሊቀመንበር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የስምንቱ ፖርቲዎች ሊቀመናብርት ተገኝተዋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ስነ-ስርዓቱ ላይ ባረጉት ንግግር ብልጽግና በእውነት እና በእውቀት ላይ ተመስርቶ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ያሻግራታል ብለዋል።
@Yenetube @FikerAssefa
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢህአዴግ እና ኦዲፒ ሊቀመንበር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የስምንቱ ፖርቲዎች ሊቀመናብርት ተገኝተዋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ስነ-ስርዓቱ ላይ ባረጉት ንግግር ብልጽግና በእውነት እና በእውቀት ላይ ተመስርቶ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ያሻግራታል ብለዋል።
@Yenetube @FikerAssefa
ለኦሮሞ መብት ተሟጋቹ #ጃዋር_መሀመድ ድጋፋቸውን እና #ተቃውሟቸውን ለመግለፅ ዛሬ በርካታ ኢትዮጵያውያን በጀርመን ኑርንበርግ ከተማ አደባባይ ወጥተዋል።
ለኦሮሞ መብት ተሟጋቹ ጃዋር መሀመድ ድጋፋቸውን እና ተቃውሟቸውን ለመግለፅ ዛሬ በርካታ ኢትዮጵያውያን በጀርመን ኑርንበርግ ከተማ አደባባይ ወጥተዋል። ጃዋር መሀመድ በዩናይትድ ስቴትስ ከተሞች እና በአውሮፓ ሀገራት እየተዟዟረ ከደጋፊዎቹ ጋር የሚያደርገውን ውይይት ቀጥሏል። ዛሬ በኑርንበርግ ከተማ ድጋፋቸውን ለመግለፅ አደባባይ የወጡት ኢትዮጵያውያን የኦነግን ጨምሮ የሌሎች ክልሎችን ባንዲራዎችም ይዘው ተስተውሏል።
ተቃውሟቸውን ለማሰማት የከተማዋ ባቡር ጣቢያ አካባቢ የወጡት ደግሞ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ያለውን ባንዲራ ይዘው ነበር። ተቃዋሚዎች በቅርቡ ጃዋር መሀመድ መንግሥት ጠባቂዎቼን ሊያነሳብኝ ነው የሚል መልዕክት ለደጋፊዎቹ ማስተላለፉን ተከትሎ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ለሞቱ 86 ሰዎችም የሻማ ማብራት ስነ ስርዓት አድርገዋል። ጃዋርም ለፍርድ ይቅረብ የሚል ጥሪ አስተላልፈዋል።
Via:- DW
@Yenetube @Fikerassefa
ለኦሮሞ መብት ተሟጋቹ ጃዋር መሀመድ ድጋፋቸውን እና ተቃውሟቸውን ለመግለፅ ዛሬ በርካታ ኢትዮጵያውያን በጀርመን ኑርንበርግ ከተማ አደባባይ ወጥተዋል። ጃዋር መሀመድ በዩናይትድ ስቴትስ ከተሞች እና በአውሮፓ ሀገራት እየተዟዟረ ከደጋፊዎቹ ጋር የሚያደርገውን ውይይት ቀጥሏል። ዛሬ በኑርንበርግ ከተማ ድጋፋቸውን ለመግለፅ አደባባይ የወጡት ኢትዮጵያውያን የኦነግን ጨምሮ የሌሎች ክልሎችን ባንዲራዎችም ይዘው ተስተውሏል።
ተቃውሟቸውን ለማሰማት የከተማዋ ባቡር ጣቢያ አካባቢ የወጡት ደግሞ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ያለውን ባንዲራ ይዘው ነበር። ተቃዋሚዎች በቅርቡ ጃዋር መሀመድ መንግሥት ጠባቂዎቼን ሊያነሳብኝ ነው የሚል መልዕክት ለደጋፊዎቹ ማስተላለፉን ተከትሎ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ለሞቱ 86 ሰዎችም የሻማ ማብራት ስነ ስርዓት አድርገዋል። ጃዋርም ለፍርድ ይቅረብ የሚል ጥሪ አስተላልፈዋል።
Via:- DW
@Yenetube @Fikerassefa
ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ክልል የመሆን ጥያቄ ካቀረበው የዎላይታ ዞን ባለሥልጣናት እና የማህበረሰቡ ተወካዮች ጋር ተወያዩ።
በውይይቱ የዎላይታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቢ፤ የሰላም ምኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል፤ የደቡብ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው እና የሐይማኖት መሪዎች ጭምር ተገኝተዋል። ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትዊተር «ፍሬያማ ውይይት አድርገናል» ብለዋል።
በውይይቱ የተሳተፈው እና የላጋ የተባለው የዎላይታ ወጣቶች ማኅበራዊ ንቅናቄ መሥራቾች አንዱ የሆነ አሸናፊ ከበደ «ዎላይታ ራሱን ችሎ ክልል ከመሆን ሌሎች አማራጮች ይኖራሉ አይኖሩም? የሚሉ ጉዳዮች እና ሌሎች ተያያዥ አማራጭ የሆኑ ጉዳዮች ምንድናቸው? እዚያ ላይ እንወያይ» ማለታቸውን ለዶይቼ ቬለ ተናግሯል።
ተሳታፊዎች «የአስራ አምስት ሚሊዮን የዎላይታ ሕዝብ አቋም እና ፍላጎት ህገ መንግሥቱ በሚፈቅደው መሠረት የዎላይታ ሕዝብ ራሱን ችሎ በራሱ ክልል የመሆን አማራጭ ተወዳዳሪ እና አቻ የለውም» የሚል ምላሽ ለጠቅላይ ምኒስትሩ እንደሰጡ አሸናፊለዶይቼ ቬለ አስረድቷል።
የዎላይታ ዞን ክልል ለመሆን ያቀረበው ጥያቄ በመጪው ታኅሳስ አስር ቀን አንድ አመት ይሞላዋል። ለጥያቄው መልስ ለማግኘት ከታኅሳስ አስር በፊት የሕዝበ ውሳኔ የሚካሔድበት ቀን እንዲታወቅ እንደሚፈልጉ አሸናፊ ለዶይቼ ቬለ ተናግሯል።
የዎላይታ ዞን የዴሞክራሲ ተቋማት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የኮምዩንኬሽን ኃላፊ አቶ አለማየሁ አፈወርቅ እንደሚሉት ከዚህ ቀደም በይፋ ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ ለማግኘት አሁንም ግፊት እየተደረገ ነው።
የደቡብ ክልል ምክር ቤቱ የዎላይታ ዞን ያቀረበውን ጥያቄ ለመመለስ «መወሰን የማይችል ከሆነ አመት ከሞላ በኋላ ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ሔዶ አንዳንድ ሥራዎችን ለመስራት በዞኑ ምክር ቤት እንደ ይግባኝ የተዋቀረ ኮሚቴ አለ።
ከዚያ በዘለለ ማሟላት ያለበትን አሟልቶ ነው የሔደው። አሁን ደግሞ ደኢሕዴን ወደ ብልፅግና ፓርቲ ተቀላቅለናል። በጠቅላላ ጉባኤ ተወስኗል። ብልፅግና እንደ ሀገር አንድን ብሔረሰብ መወከል የሚችል፤ ማሳተፍ የሚችል ነው ብለን እናምናለን።
የዎላይታም ጥያቄ በብልፅግና የማይመለስበት ምክንያት የለም ብለን እናምናለን» ሲሉ አቶ አለማየሁ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።
Via:- DW
@Yenetube @Fikerassefa
በውይይቱ የዎላይታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቢ፤ የሰላም ምኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል፤ የደቡብ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው እና የሐይማኖት መሪዎች ጭምር ተገኝተዋል። ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትዊተር «ፍሬያማ ውይይት አድርገናል» ብለዋል።
በውይይቱ የተሳተፈው እና የላጋ የተባለው የዎላይታ ወጣቶች ማኅበራዊ ንቅናቄ መሥራቾች አንዱ የሆነ አሸናፊ ከበደ «ዎላይታ ራሱን ችሎ ክልል ከመሆን ሌሎች አማራጮች ይኖራሉ አይኖሩም? የሚሉ ጉዳዮች እና ሌሎች ተያያዥ አማራጭ የሆኑ ጉዳዮች ምንድናቸው? እዚያ ላይ እንወያይ» ማለታቸውን ለዶይቼ ቬለ ተናግሯል።
ተሳታፊዎች «የአስራ አምስት ሚሊዮን የዎላይታ ሕዝብ አቋም እና ፍላጎት ህገ መንግሥቱ በሚፈቅደው መሠረት የዎላይታ ሕዝብ ራሱን ችሎ በራሱ ክልል የመሆን አማራጭ ተወዳዳሪ እና አቻ የለውም» የሚል ምላሽ ለጠቅላይ ምኒስትሩ እንደሰጡ አሸናፊለዶይቼ ቬለ አስረድቷል።
የዎላይታ ዞን ክልል ለመሆን ያቀረበው ጥያቄ በመጪው ታኅሳስ አስር ቀን አንድ አመት ይሞላዋል። ለጥያቄው መልስ ለማግኘት ከታኅሳስ አስር በፊት የሕዝበ ውሳኔ የሚካሔድበት ቀን እንዲታወቅ እንደሚፈልጉ አሸናፊ ለዶይቼ ቬለ ተናግሯል።
የዎላይታ ዞን የዴሞክራሲ ተቋማት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የኮምዩንኬሽን ኃላፊ አቶ አለማየሁ አፈወርቅ እንደሚሉት ከዚህ ቀደም በይፋ ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ ለማግኘት አሁንም ግፊት እየተደረገ ነው።
የደቡብ ክልል ምክር ቤቱ የዎላይታ ዞን ያቀረበውን ጥያቄ ለመመለስ «መወሰን የማይችል ከሆነ አመት ከሞላ በኋላ ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ሔዶ አንዳንድ ሥራዎችን ለመስራት በዞኑ ምክር ቤት እንደ ይግባኝ የተዋቀረ ኮሚቴ አለ።
ከዚያ በዘለለ ማሟላት ያለበትን አሟልቶ ነው የሔደው። አሁን ደግሞ ደኢሕዴን ወደ ብልፅግና ፓርቲ ተቀላቅለናል። በጠቅላላ ጉባኤ ተወስኗል። ብልፅግና እንደ ሀገር አንድን ብሔረሰብ መወከል የሚችል፤ ማሳተፍ የሚችል ነው ብለን እናምናለን።
የዎላይታም ጥያቄ በብልፅግና የማይመለስበት ምክንያት የለም ብለን እናምናለን» ሲሉ አቶ አለማየሁ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።
Via:- DW
@Yenetube @Fikerassefa
የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ ፎን ደር ላይን በመጪው ሳምንት ወደ አዲስ አበባ ያቀናሉ። ከርዕሰ-ብሔር ሣህለ ወርቅ ዘውዴ፣ ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋሳቂ ማኅማት ይገናኛሉ።
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
ኤችአይቪ በኢትዮጵያ ከሦስት ክልሎች ውጪ በወረርሽኝ ደረጃ ነው ያለው!
በኢትዮጵያ ከሦስት ክልሎች ውጪ ኤችአይቪ በወረርሽኝ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የፌደራል ኤች አይቪ መከላከልና መቆጣጠሪያ ጽሕፈት ቤት ገለፀ።ጋምቤላ፣ አዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ አፋር፣ ትግራይ፣ አማራና ቤንሻንጎል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ በኤችአይቪ ወረርሽኝ ውስጥ መሆናቸውን የጽህፈት ቤቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኑኬሽን ዳይሮክተሬት ዳይሬክተሩ አቶ ዳንኤል በትረ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
https://telegra.ph/AIDS-12-02
በኢትዮጵያ ከሦስት ክልሎች ውጪ ኤችአይቪ በወረርሽኝ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የፌደራል ኤች አይቪ መከላከልና መቆጣጠሪያ ጽሕፈት ቤት ገለፀ።ጋምቤላ፣ አዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ አፋር፣ ትግራይ፣ አማራና ቤንሻንጎል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ በኤችአይቪ ወረርሽኝ ውስጥ መሆናቸውን የጽህፈት ቤቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኑኬሽን ዳይሮክተሬት ዳይሬክተሩ አቶ ዳንኤል በትረ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
https://telegra.ph/AIDS-12-02
በሲዳማ ክልል የፓርቲው ቅርንጫፍ እንደሚከፈት አስታወቁ የዞኑ አስተዳዳሪ ገለፁ።
የብልጽግና ፓርቲ እየተበራከቱ የመጡ የህዝብ ፍላጎቶችን መመለስ በሚያስፈልግበት ወቅት የተወለደ ፓርቲ መሆኑን የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ገለጹ፡፡ የሲዳማ የክልልነት ሂደት ሲጠናቀቅም በክልሉ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት እንደሚከፈት አስታውቀዋል፡፡ዋና አስተዳዳሪው አቶ ደስታ ሌዳሞ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት በርካታ የህዝብ ፍላጎቶች ታይተዋል፤ ጥያቄዎችም ተነስተዋል፡፡ ይህን ሊመልስ የሚችል ቁመና ያለው ፓርቲ አስፈላጊ እንደመሆኑም የብልጽግና ፓርቲ ወቅቱ የፈጠረው ፓርቲ መሆኑ እሙን ነው፡፡የብልጽግና ፓርቲን በመመስረት ሂደትም የሲዳማ ተወላጅ የደኢህዴን አባላት ተሳታፊና የውሳኔው አካል እንደመሆናቸው የሲዳማ የክልልነት ሂደት ሲጠናቀቅ በፓርቲው ሕገ ደንብ መሰረት የፓርቲው ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በክልሉ ይኖራል፡፡
ምንጭ: ኢፕድ
@YeneTube @FikerAssefa
የብልጽግና ፓርቲ እየተበራከቱ የመጡ የህዝብ ፍላጎቶችን መመለስ በሚያስፈልግበት ወቅት የተወለደ ፓርቲ መሆኑን የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ገለጹ፡፡ የሲዳማ የክልልነት ሂደት ሲጠናቀቅም በክልሉ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት እንደሚከፈት አስታውቀዋል፡፡ዋና አስተዳዳሪው አቶ ደስታ ሌዳሞ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት በርካታ የህዝብ ፍላጎቶች ታይተዋል፤ ጥያቄዎችም ተነስተዋል፡፡ ይህን ሊመልስ የሚችል ቁመና ያለው ፓርቲ አስፈላጊ እንደመሆኑም የብልጽግና ፓርቲ ወቅቱ የፈጠረው ፓርቲ መሆኑ እሙን ነው፡፡የብልጽግና ፓርቲን በመመስረት ሂደትም የሲዳማ ተወላጅ የደኢህዴን አባላት ተሳታፊና የውሳኔው አካል እንደመሆናቸው የሲዳማ የክልልነት ሂደት ሲጠናቀቅ በፓርቲው ሕገ ደንብ መሰረት የፓርቲው ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በክልሉ ይኖራል፡፡
ምንጭ: ኢፕድ
@YeneTube @FikerAssefa
Center for Advancement of Rights and Democracy(CARD) አሳሳቢ የጥላቻ ገለጻዎች በአሜሪካ በሚገኙ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበረሰብ አባላት በቅርቡ ጀዋር መሃመድ በዩናይትድ ስቴትስ ከደጋፊዎቹ ጋር ውይይት ሊያደርግ ባቀናባቸው ከተሞች መንፀባረቁን ታዝቦ ይህንን መግለጫ (መልዕክት) አስተላልፏል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
የጀርመን መንግስት ለኢትዮጵያ የ352 ነጥብ 5 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ ማድረጉ ተገለፀ።
ከገንዘብ ድጋፉም 110 ሚሊየን ዩሮ በቀጥታ ለመንግስት በጀት ድጋፍ የሚውል መሆኑም ታውቋል።የጀርመን የኢኮኖሚ እና ልማት ትብብር ሚኒስትር ገርድ ሙለር የተመራ ልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ የአራት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት እያደረገ ነው።ልኡኩ በዛሬው እለትም ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር ተገናኝቶ ተወያይቷል።በውይይቱ ወቅትም የጀርመን መንግስት ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለውን የሪፎርም ስራዎች ለመደገፍ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።ከዚህ ባለፈም የጀርመን መንግስት የግብርና ስራን ለመደገፍ ከ100 በላይ የግብርና መሳሪያዎች ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
ከገንዘብ ድጋፉም 110 ሚሊየን ዩሮ በቀጥታ ለመንግስት በጀት ድጋፍ የሚውል መሆኑም ታውቋል።የጀርመን የኢኮኖሚ እና ልማት ትብብር ሚኒስትር ገርድ ሙለር የተመራ ልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ የአራት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት እያደረገ ነው።ልኡኩ በዛሬው እለትም ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር ተገናኝቶ ተወያይቷል።በውይይቱ ወቅትም የጀርመን መንግስት ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለውን የሪፎርም ስራዎች ለመደገፍ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።ከዚህ ባለፈም የጀርመን መንግስት የግብርና ስራን ለመደገፍ ከ100 በላይ የግብርና መሳሪያዎች ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል።
Via Fana
@YeneTube @FikerAssefa
ለ30 ሺሕ ሰዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት ሊሰጥ ነው!
ከኅዳር 22 እስከ 24 በሚሊኒየም አዳራሽ በሚከናወነው ዓለም አቀፍ የጤና ኤግዚቢሽን እና ኮንፍረንስ ከ 30 ሺሕ ለሚበልጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገለፀ።የአዲስ አበባ የግል የጤና ተቋማት አሠሪዎች ማኅበር ባዘጋጀው በዚህ ኤግዚቢሽን ላይ፣ የልብ እና የደም ግፊት ምርመራ፣ የስኳር፣ የዐይን እና የጥርስ ህክመና እንዲሁም የኤ.ች አይ. ቪ ምርመራ ከአገር ውስጥ የግል የጤና ተቋማት እና ከተለያዩ የውጪ አገራት በመጡ ባለሙያዎች እንደሚሰጥ ተገልጿል።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa
ከኅዳር 22 እስከ 24 በሚሊኒየም አዳራሽ በሚከናወነው ዓለም አቀፍ የጤና ኤግዚቢሽን እና ኮንፍረንስ ከ 30 ሺሕ ለሚበልጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገለፀ።የአዲስ አበባ የግል የጤና ተቋማት አሠሪዎች ማኅበር ባዘጋጀው በዚህ ኤግዚቢሽን ላይ፣ የልብ እና የደም ግፊት ምርመራ፣ የስኳር፣ የዐይን እና የጥርስ ህክመና እንዲሁም የኤ.ች አይ. ቪ ምርመራ ከአገር ውስጥ የግል የጤና ተቋማት እና ከተለያዩ የውጪ አገራት በመጡ ባለሙያዎች እንደሚሰጥ ተገልጿል።
ምንጭ: አዲስ ማለዳ
@YeneTube @FikerAssefa